Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Open in Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Chat us! Buy ads: https://telega.io/c/consite
Show more3 599
Subscribers
-124 hours
-87 days
+430 days
Posts Archive
የስራማስታወቂያ!📢
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (ERA)
በሰርቬይንግ 🚩 በድራፍቲንግ 🚩 በሲቪል 🚩COTM
የስራ ቦታ
አዲስ አበባ
የምዝገባ ጊዜ
ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት::
የምዝገባ ቦታ
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዓለምገና የመንገድ ጥገና ዲስትሪክት::
ስልክ ቁጥር -0113-871250
👉የቅድመ ክፍያ እና በኮንትራክተሩ ሚሰጥ ማስያዥያ
💫ቅድመ ክፍያ ማለት ምን ማለት ነው?
⏺አንድ ተቋራጭ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ዉል ከገባ በዉሉ ሰነድ ላይ በተቀመጠው መሰረት ቅድመ ክፍያ ይከፈለዋል ያው ወለድ የሌለው ብድር አሰሪው ለ ሥራ ተቋራጩ ይሰጠዋል ማለት ነው።
⏺ይህ ቅድመ ክፍያ የሚከፈለው ተቋራጩ ስራዉን ለመጀመር እንዲረዳው ነው።
⏺ስቶር ለመስራት ማሽነሪ እና የሰው ሃይል ሞቢላይዝ ለማድረግ ለግንባታ ስራ የሚረዱ አስፈላጊ የሆኑ ማቴርያል እንዲገዛ እና ወዘተ ለሆኑ እንቅስቃሴዎች ተቋራጩ ቅድመ ክፍያ ይከፈለዋል።
🏷በአብዛኛው የ ሃገራችን የዉል ሰነድ ላይ የምንመለከተው ቅድመ ክፍያ የዉሉን ዋጋ 20 ወይንም 30% ነው።
📜 ለ ምሳሌ ፕሮጀክቱ 100,000,000 ከሆነ
⚡️እንዴት አሰሪው 20,000,000 ብር አምኖ ለተቋራጩ ዉል ስለገቡ ብቻ ይሰጠዋል።
❇️እንግዲህ የኮንስትራክሽን ዉሎች መሰረት ተደርገው የሚዘጋጁት የሃገሪቱን ህግ መሰረት በማድረግ ነው የሃገሪቱ ህግ ደግሞ አለማችን ላይ በሰፊው ከምንጠቀመው የኮንስትራክሽን ህግ የወጣ ነው።
⏺አንዳንዴ ቀጥታም ልንጠቀመው እንችላለን። ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ scc & gcc የሚባሉ ህጎች ዉላችን ላይ አሉ።
- So ተቋራጩ ለሚወስደው ቅድመ ክፍያ እኩል የሆነ ማስያዥያ ለ አሰሪው ማቅረብ ይኖርበታል።
- FIDIC RED book 2017( GCC )የምንለው ከዚህ የተቀዳ ነው። በአንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ስለ ቅድመ ክፍያ ማስያዝያ እንዲህ ይላል።
- ስራ ተቋራጩ ለሚወስደው የቅድመ ክፍያ በወሰደው መጠን ልክ ማስያዝያ ለ አሰሪው ማቅረብ ዪጠበቅበታል ኮፒ ደግሞ ለ እንጂነሩ/ ሳይተ ሱፐርቪሶሩ መስጠት ግዴታ አለበት
- ይህ የቅድመ ክፍያ ማስያዝያ የሚቀርበው ሃገር ውስጥ ህጋዊ ሰዉነት ካለው የፋይናንስ ተቋም ሲሆን እና አሰሪው የተስማማበት መሆን ይጠበቅበታል። ይህ የፋይናንስ ተቋም ዋስትናውን የሚሰጠው የዉሉ ወይንም የጨረታ ሰነዱ ላይ በተዘጋጀው ናሙና ቅጽ መሰረት ዪሆናል አንዳንዴም ባንኩ በራሱ ቅጽ አቅርቦ አሰሪው የተስማማበት ከሆነ its okay።
- ስራ ተቋራጩ የቅድሚያ ክፍያ ዋስትናው ቅድመ ክፍያውን ከፍሎ እስኪያጠናቅቅ ድረስ ተቀባይነት እና ተፈፃሚ ያለው መሆኑን ያረጋግጣል ነገር ግን ያስያዘውን የገንዘብ መጠን ተቋራጩ በከፈለው መጠን ደረጃ በደረጃ ሊቀንስ ይችላል።
የከፈለው መጠን እና የሚቀረው መጠን በክፍያ የምስክር ወረቀት ላይ ይገለጻል።
- የቅድመ ክፍያ ዋስትናው የሚያበቃበት ጊዜ ተጠቅሶ ከሆነ እና ተቋራጩ የወሰደውን ቅድመ ክፍያ ዋስትናው ከመጠናቀቁ 28 ቀን በፊት አጠናቆ ሳይከፍል የሚቀር ከሆነ
1. ተቋራጩ ቅድመ ክፍያው እስኪከፈል ድረስ የዚህን ዋስትና ትክክለኛነት ያራዝማል ቀኑን ያራዝመዋል ማለት ነው።
2. ተቋራጩ ይህንን የማራዘምያ ማስረጃ ወዲያውኑ ለአሠሪው ያቀርባል ለኢንጅነሩ ወይንም ሱፐርቫይሰሩ ግልባጭ ይዞ
3. አሠሪው ይህንን ማስረጃ ዋስትና ከማለቁ ከ7 ቀናት በፊት ካልተቀበለ፣ አሠሪው ያልተከፈለውን የቅድሚያ ክፍያ መጠን በዋስትናው መሠረት የመጠየቅ መብት አለው።
- ተቋራጩ የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና በሚቀርብበት ጊዜ ማመልከቻ ወይንም በደብዳቤ መልክ ለወሰደው ቅድመ ክፍያ ማስያዣ እንዳቀረበ መግለጽ ይጠበቅበታል።
@etconp
Repost from Ethio Construction Engineering
👉የቅድመ ክፍያ እና በኮንትራክተሩ ሚሰጥ ማስያዥያ
💫ቅድመ ክፍያ ማለት ምን ማለት ነው?
⏺አንድ ተቋራጭ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ዉል ከገባ በዉሉ ሰነድ ላይ በተቀመጠው መሰረት ቅድመ ክፍያ ይከፈለዋል ያው ወለድ የሌለው ብድር አሰሪው ለ ሥራ ተቋራጩ ይሰጠዋል ማለት ነው።
⏺ይህ ቅድመ ክፍያ የሚከፈለው ተቋራጩ ስራዉን ለመጀመር እንዲረዳው ነው።
⏺ስቶር ለመስራት ማሽነሪ እና የሰው ሃይል ሞቢላይዝ ለማድረግ ለግንባታ ስራ የሚረዱ አስፈላጊ የሆኑ ማቴርያል እንዲገዛ እና ወዘተ ለሆኑ እንቅስቃሴዎች ተቋራጩ ቅድመ ክፍያ ይከፈለዋል።
🏷በአብዛኛው የ ሃገራችን የዉል ሰነድ ላይ የምንመለከተው ቅድመ ክፍያ የዉሉን ዋጋ 20 ወይንም 30% ነው።
📜 ለ ምሳሌ ፕሮጀክቱ 100,000,000 ከሆነ
⚡️እንዴት አሰሪው 20,000,000 ብር አምኖ ለተቋራጩ ዉል ስለገቡ ብቻ ይሰጠዋል።
❇️እንግዲህ የኮንስትራክሽን ዉሎች መሰረት ተደርገው የሚዘጋጁት የሃገሪቱን ህግ መሰረት በማድረግ ነው የሃገሪቱ ህግ ደግሞ አለማችን ላይ በሰፊው ከምንጠቀመው የኮንስትራክሽን ህግ የወጣ ነው።
⏺አንዳንዴ ቀጥታም ልንጠቀመው እንችላለን። ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ scc & gcc የሚባሉ ህጎች ዉላችን ላይ አሉ።
- So ተቋራጩ ለሚወስደው ቅድመ ክፍያ እኩል የሆነ ማስያዥያ ለ አሰሪው ማቅረብ ይኖርበታል።
- FIDIC RED book 2017( GCC )የምንለው ከዚህ የተቀዳ ነው። በአንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ስለ ቅድመ ክፍያ ማስያዝያ እንዲህ ይላል።
- ስራ ተቋራጩ ለሚወስደው የቅድመ ክፍያ በወሰደው መጠን ልክ ማስያዝያ ለ አሰሪው ማቅረብ ዪጠበቅበታል ኮፒ ደግሞ ለ እንጂነሩ/ ሳይተ ሱፐርቪሶሩ መስጠት ግዴታ አለበት
- ይህ የቅድመ ክፍያ ማስያዝያ የሚቀርበው ሃገር ውስጥ ህጋዊ ሰዉነት ካለው የፋይናንስ ተቋም ሲሆን እና አሰሪው የተስማማበት መሆን ይጠበቅበታል። ይህ የፋይናንስ ተቋም ዋስትናውን የሚሰጠው የዉሉ ወይንም የጨረታ ሰነዱ ላይ በተዘጋጀው ናሙና ቅጽ መሰረት ዪሆናል አንዳንዴም ባንኩ በራሱ ቅጽ አቅርቦ አሰሪው የተስማማበት ከሆነ its okay።
- ስራ ተቋራጩ የቅድሚያ ክፍያ ዋስትናው ቅድመ ክፍያውን ከፍሎ እስኪያጠናቅቅ ድረስ ተቀባይነት እና ተፈፃሚ ያለው መሆኑን ያረጋግጣል ነገር ግን ያስያዘውን የገንዘብ መጠን ተቋራጩ በከፈለው መጠን ደረጃ በደረጃ ሊቀንስ ይችላል።
የከፈለው መጠን እና የሚቀረው መጠን በክፍያ የምስክር ወረቀት ላይ ይገለጻል።
- የቅድመ ክፍያ ዋስትናው የሚያበቃበት ጊዜ ተጠቅሶ ከሆነ እና ተቋራጩ የወሰደውን ቅድመ ክፍያ ዋስትናው ከመጠናቀቁ 28 ቀን በፊት አጠናቆ ሳይከፍል የሚቀር ከሆነ
1. ተቋራጩ ቅድመ ክፍያው እስኪከፈል ድረስ የዚህን ዋስትና ትክክለኛነት ያራዝማል ቀኑን ያራዝመዋል ማለት ነው።
2. ተቋራጩ ይህንን የማራዘምያ ማስረጃ ወዲያውኑ ለአሠሪው ያቀርባል ለኢንጅነሩ ወይንም ሱፐርቫይሰሩ ግልባጭ ይዞ
3. አሠሪው ይህንን ማስረጃ ዋስትና ከማለቁ ከ7 ቀናት በፊት ካልተቀበለ፣ አሠሪው ያልተከፈለውን የቅድሚያ ክፍያ መጠን በዋስትናው መሠረት የመጠየቅ መብት አለው።
- ተቋራጩ የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና በሚቀርብበት ጊዜ ማመልከቻ ወይንም በደብዳቤ መልክ ለወሰደው ቅድመ ክፍያ ማስያዣ እንዳቀረበ መግለጽ ይጠበቅበታል።
@etconp
👉 INTERCON Construction Chemicals
● Concrete Admixtures
● Bonding Agents
● Waterproofings
● Wall Putty, Prime Coat
● Concrete Repair Mortar
● Floor hardener, Epoxy
● Grout, Self-level mortar
● Quartz paint, Contextra
● Tile Adhesive & Tile Joint Fillers
● Geotextiles and other construction chemicals and materials
Tel: 0961955555
Address: Signal, around signal mall
ደሊና ዩፒቪሲ እና አልሙኒየም ስራ
በተለያዩ ዲዛይኖች እንደፍላጎትዎ ለቤት፣ ለቢሮ እና ለንግድ ቤትዎ ውበትና ጥንካሬ ያላቸው የUPVC ተካፋች እና ተንሸራታች መስኮቶች የUPVC በሮች እና ፓርቲሽኖች በፈለጉት ብዛት በተለያየ ቀለም እና ዲዛይን ጋዜቦ አደባባይ በሚገኘው ሱቃችን ያገኛሉ!
ይደውሉልን፡0930099145 /46
Delina uPVC & Aluminum Works
Quality you can rely on, designs you’ll love Durable, modern, and built to perform Transforming your spaces with style and strength
📞 Call us at [0930099145/46]
📍 Gazebo square,near Mulmul Bakery
+3
ማስታወቂያ:-NAYHAf Construction Metal Trading- አቅራቢ🏗 ጥራትና ታማኝነትን የተላበሰ አገልግሎት" ከደንበኞች አብዛኛሆቻችሁ ታውቁታላችሁ
መገኛ አድራሻው ቦታ:-📍- ተክለሃይማኖት በርበሬ በረንዳ
ስልክ ቁጥር:-🔺📞+251- 944454610 🔺📞+251- 952730999 #LTZ 28 #LTZ 38 #LTZ 48 #CHS ከ ባለ 12mm ጀምሮ .... #RHS #I BEAM #U CHANNEL #H BEAM #Mesh Wire #የ ኣጥር ሽቦ #Galvanized Pipe #Angle #Aluminium Sheet #D ብረት#8 ቁጥር #ፌርሞችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ! ስትፈልጉ በቀጥታ ይደውሉ.. .
ዜና፡ የውጭ ሀገር ዜጎች በትንሹ 150 ሺህ ዶላር በመውጣት የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት እንዲሆኑ የሚፈቅደው አዋጅ ፀደቀ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ሀገር ዜጎች የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የመሆን መብት አዋጅን አጸደቀ። ከአዲስ አበባ ውጪ መስራት ቢፈልጉ በወጣው መመሪያ መሰረት ክልሎች ተፈፃሚ እንደሚያደርጉም ተገልጿል።
የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ #ኢትዮጵያ ገብተው በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ነው ተብሏል።
“አንድ የውጭ ሀገር ዜጋ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ መኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይንም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም” ተብሏል።
150 ሺህ ዶላር ሁኖ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ እንደሚሄድም ተመላክቷል።
"ማንኛው የውጭ ዜጋ በማናቸውም ጊዜ፣ በአንድ ግዜ የሚኖረው የመኖሪያ ቤት ቁጥር አንድ ብቻ" መሆኑ የተቆመ ሲሆን ሚኒስቴሩ "ከአገር ጥቅም አንጻር አስፈላጊ ሁኖ ሲያገኘው ይህን ቁጥር በመመሪያ ማሻሻል ይችላል" ተብሏል።
የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሆነ የውጭ ሀገር ዜጋ “ለግለሰብ ወይም ለቤተሰብ የማከራየት መብቱ እንደተጠበቀ ሁኖ መኖሪያ ቤቱን ለንግድ አላማ ማዋል የተከለከለ መሆኑ” በአዋጁ ተቀምጧል።
ይህ የተገለጸው በምክር ቤቱ የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአዋጁ ዙሪያ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡለት ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው።
መሬት የመንግስት እና የህዝብ እንደመሆኑ ለኢንቨስትመንት የሚመጡ ዜጎች መሬቱን የመሸጥ እና የመለወጥ መብት የላቸውም ተብሏል።
አዲስ ስታንዳንድ
የጨረታ ማስታወቂያ
FHC/NCB/PW/22/10/2017
1. የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለአስፋልት ኮንክሪት እና የፋዎንቴን ስራ ግዥ በጨረታ መለያ ቁጥር FHC/NCB/ PW/22/10/2017 ደረጃ 4 እና ከዛ በላይ የሆኑ የመንገድ ስራ ተቋራጭ እና ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ (RC-4, GC-4 & Above) ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
2. ኮርፖሬሽኑ ለአስፋልት ኮንከሪት እና የፋዎንቴን ስራ ግንባታ ግዥ ላይ የሚወዳደሩ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ቴከኒካል ሰነዳቸውንና ዋጋቸውን በተለያዩ በታሸጉ ኤንቨሎፖች ማቅረብ አለባቸው።
3. ጨረታው የሚከናወነው በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ-ሥርዓትና ይኼንኑ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞከራሲያዊ ሪፐብሊክ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የግዥ መመሪያ መሠረት ሲሆን ደረጃ 4 እና ከዛ በላይ የሆኑ የመንገድ ስራ ተቋራጭ እና ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ 2017 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን ይኖርበታል።
4. የተሟላ የጨረታ ሰነድ ማንኛውም ፍላጎት ያለው ተጫራች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመከፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ለገሀር በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 201 ለዚሁ ታሽጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው በመጀመሪያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ወይም ሀምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ስዓት ድረስ እንዲያቀርቡ ሆኖ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 (ሀምሳ ሺ ብር) ሲፒኦ በፌዴራል ቤቶች ኮፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋርአያይዘው ማቅረብ አለባቸው። ዘግይቶ የቀረበ የጨረታ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፤ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሀምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት የኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬከተር 2ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
6. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በስልክ ቁጥር 011-855-30-35 ወይም
011-553-95-35 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን
Repost from Tender ጨረታ
የጨረታ ማስታወቂያ
FHC/NCB/PW/22/10/2017
1. የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለአስፋልት ኮንክሪት እና የፋዎንቴን ስራ ግዥ በጨረታ መለያ ቁጥር FHC/NCB/ PW/22/10/2017 ደረጃ 4 እና ከዛ በላይ የሆኑ የመንገድ ስራ ተቋራጭ እና ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ (RC-4, GC-4 & Above) ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
2. ኮርፖሬሽኑ ለአስፋልት ኮንከሪት እና የፋዎንቴን ስራ ግንባታ ግዥ ላይ የሚወዳደሩ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ቴከኒካል ሰነዳቸውንና ዋጋቸውን በተለያዩ በታሸጉ ኤንቨሎፖች ማቅረብ አለባቸው።
3. ጨረታው የሚከናወነው በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ-ሥርዓትና ይኼንኑ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞከራሲያዊ ሪፐብሊክ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የግዥ መመሪያ መሠረት ሲሆን ደረጃ 4 እና ከዛ በላይ የሆኑ የመንገድ ስራ ተቋራጭ እና ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ 2017 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን ይኖርበታል።
4. የተሟላ የጨረታ ሰነድ ማንኛውም ፍላጎት ያለው ተጫራች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመከፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ለገሀር በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 201 ለዚሁ ታሽጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው በመጀመሪያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ወይም ሀምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ስዓት ድረስ እንዲያቀርቡ ሆኖ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 (ሀምሳ ሺ ብር) ሲፒኦ በፌዴራል ቤቶች ኮፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋርአያይዘው ማቅረብ አለባቸው። ዘግይቶ የቀረበ የጨረታ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፤ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሀምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት የኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬከተር 2ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
6. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በስልክ ቁጥር 011-855-30-35 ወይም
011-553-95-35 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን
🧱New Point Bricks factory 新点砖厂🧱 Red brick:- This is the classic brick color that you see Quality with affordable price 🧱ጥራት ያላቸውን እና ለተለያዩ ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የቀይ ሸክላ ጡቦችን እናመርታለን።
🧱 ለሙሉ የቤት ግንባታ፣
🧱ለባንክ ቤት ካዝና፣
🧱 ለግቢ አጥር ማጠሪያ፣
🧱 ለመንገድ ዳር ጠርዞች፣
🧱 ለሆቴሎች፣ሬስቶራንት፣እና ካፌዎች ማሳመሪያ ፣
🧱 ለx-ray ክፍሎች፣
🧱 ለፍሳሽ ማንዋሎች፣
🧱 ለኪችን ሲንክ ማስቀመጫ ፣
🧱 ለሻወር ገንዳ ማሰቀመጫ፣
🧱 የPBC ፍሳሽ ማስወገጃ ለመሸፈን፣
🧱 ለአበባ መትከያ
🧱 ለብረት ማቅለጫ ፈርኒስ፣
🧱 ለፒዛ ኦቭን፣
🧱 ለምድጃ፣
🧱 ለቆሻሻ ማቃጠያ፣
NEW POINT BRICK FACTORY
*We produced best quality clay bricks for various construction purposes.
🧱 For building construction,
🧱 For bank vaults,
🧱 Fence for the yard,
🧱 For road edges,
🧱 For Hotels,Restaurants,and Cafes decoration,
🧱 For x-ray rooms,
🧱 For manuals,
🧱 For kitchen,
🧱 For shower tray
🧱 To cover PBC drains,
🧱 For garden,
🧱 Furnace For steel factory,
🧱 For pizza oven,
🧱 For waste incinerator, 🧱 For more information join our telegram channel 🧱Order now 📲0912854327,0902378888 🧱"Quality is our first priority 🧱Thank you 谢谢
በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጁ አዳዲስ መደበኛ የጨረታ ሰነዶች (Standard Bidding Documents)
📌 በግዥና ንብረት ባለስልጣን በኩል ከአዲሱ የግዥ መመሪያ አንፃር የተዘጋጁ ሶስት ለእቃ (Goods)፣ ግንባታ (Works) እና ለማዕቀፍ (Framework) ግዥዎች የሚያገለግሉ መደበኛ የጨረታ ሰነዶች (Standard Bidding Document) በአማርኛ ቋንቋ ተዘጋጅተው በድህረ ገጻቸው ይፋ ተደርገዋል። ሰነዶቹ ከላይ አያይዘንላችኋል👆👇
📌 በቀጣይ በእንግሊዘኛ ቋንቋም ሰነዶቹ ተዘጋጅተው እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
+4
High quality yalachew china shawer wall and floor import argenal
0911798889
+1
በቅርቡ ለጨረታ ቀርበው የነበሩና በ4 ኪሎ እና በሳርቤት ፕላዛዎች እንዲሁም በየካ 2 ፓርኪንግ ውስጥ የሚገኙ የንግድ ቤቶች ኪራይ ጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር።
👉የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ እና የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ
ሰኔ 26/2017 ዓ/ም
ስለሪቴንሽን ገንዘብ መያዣ እና የጥገና የብልሽት አላፊነት መያዣ!🏗
(Retention Money/Bond) የሪቴንሽን ገንዘብ/መያዣ የሚባለው በኮንስትራክሽን ውል አስተዳደር ወቅት ሥራ ተቋራጩ ሥራውን ፈጽሞ ክፍያ በሚጠይቅበት ወቅት የፕሮጀክቱ ባለቤት ከግንባታው አማካሪ መሀንዲስ ጋር በመሆን ስለሥራው ጥራት ደረጃ በሚል ሊይዘው የሚችለው ዋስትና ነው፡፡
የሪቴንሽን ገንዘብ/መያዣ (retention) ዓላማ የግንባታውን ጥራት ለማስጠበቅ ሲባል ሥራ ተቋራጮች ለአሰሪዎች የሚገቡት ዋስትና ነው፡፡የግዥ መመሪያውም በአንቀጽ 28.5(ለ) ላይ በግልጽ እንደሚደነግገው በእያንዳንዱ የክፍያ ሰርተፍኬት ላይ 5(አምስት) ፐርሰንት የክፍያው ገንዘብ የሚያዝ ይሆናል፡፡ በዋናነት ከተያዘው ገንዘብ ውስጥ 50(ሃምሳ) ፐርሰንት የሚሆነው ገንዘብ ሥራው እንደ ተጠናቀቀ እና ጊዚያዊ የርክክብ ምስክር ወረቀት (provisional acceptance certificate) ከተሰጠ በኋላ ለሥራ ተቋራጩ ይመለስለታል፡፡ የቀረው ገንዘብ ደግሞ እስከ አንድ አመት ድረስ ዋቢ ሆኖ ይቆያል፡፡ ነገር ግን የተቀረው የመያዣ ገንዘብን አስቀድሞ ሥራ ተቋራጩ ለአንድ አመት የሚጸና ዋስትና ማቅረብ ከቻለ የተያዘበትን ቀሪ ገንዘብ ማስለቀቅ ይችላል፡፡
በተመሳሳይ መልኩም የሲቪል ሥራዎችን በተመለከተም እኤአ በ1994 ዓ.ም የወጣው የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ወጥ ውልም ስለ የዋና ገንዘብ መያዣ ዋስትና በአንቀጽ 59(5) እና 60 ላይ ተቀራራቢ ድንጋጌዎችን ያስቀምጣል፡፡ ግን የሪቴንሽን ገንዘብ (retention) የፕሮጀክቱ ግንባታ ተጠናቆ የጊዜያዊ እና የመጨረሻ ርክክብ ከተፈጸመ በኋላ የተያዘው 5(አምስት) ፐርሰንት ገንዘብ አብዛኛውን ጊዜ ተመላሽ አይሆንም፡፡ በዚህ ሳቢያም ሥራ ተቋራጮች ለሌላ ወጪ የሚዳረጉበት ሁኔታ አለ፡፡
////The law stipulates that the retention bond shall be paid to contractor after provisional acceptance or final acceptance but its applicability is denied by government side most of the time. So, dear contractors, please ask before you bankrupt///
#የጥገና ወይም የብልሽት አላፊነት መያዣ (Maintenance or Defect Liability Bond) የጥገና ዋስትና የተበላሹ የግንባታ ግብዓቶችንና የሥራ አሰራር ግድፈቶችን ለመከላከል በሚል ሥራ ተቋራጩ ለፕሮጀክት ባለቤቱ የሚገባው ዋስትና ነው፡፡ በተለይም ከላይ ስለ ሪቴንሽን ገንዘብ/መያዣ (retention) ቆይታ እንደተመለከተው ለአንድ ዓመት ጊዜ የሚያዝበት ምክንያት ከጥራት ጉድለት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን ለመጠገን ነው፡፡ በሚለቀቅበትም ጊዜ ያለ ቅድመ ለመጠገን ነው፡፡
በሚለቀቅበትም ጊዜ ያለ ቅድመ ሁኔታ ዋስትና ሥራ ተቋራጩ እንዲያቀርብ የሚደረግበት ምክንያት በህንጻው ግንባታ ላይ የሚታዩ ግድፈቶችን ለመጠገን በሚል ነው፡፡
የጥገና እና ብልሽት አላፊነት መያዣ በዋናነት የዋና ገንዘብ መያዣ ቆይታ እንዳበቃ የሚጀምር ነው፡፡ በርግጥ ሥራ ተቋራጩ ለባለቤቱ ለተወሰኑ ዓመታት ዋቢ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ፡- በሲቪል የግንባታ ሥራዎች በተለይም በፍ/ህ/ቁ 3039 እንዲህ የሚል ይነበባል፡-''ሥራ ተቋራጩ ሥራውን ካስረከበበት ጊዜ ጀምሮ ስለመልካም አሰራር፣ ስለ ሥራው እና ስለጠንካራነቱ ለ10 (አስር) አመት መድን (guarantee/ warranty) ۱۵۰:: ০১ ২৪ ৫৯৫ በሥራው ጉድለት ወይም በተሰራበት መሬት ዓይነት ምክንያት በተሰራው ሥራ ላይ ለሚደርሰው መጥፋት ወይም መበላሸት አላፊ ነው፡፡"
በተመሳሳይ መልኩ የመንግስት የግንባታ ውሎችንም በተመለከተ የፍትሐብሔር ሕጉ ከአንቀጽ 3277-3282 ላይ የ10 (አስር) አመት የብልሽት መድን ጊዜ ያስቀምጣል፡፡
የፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት በቅጽ 18 በሰ/መ/ቁ 101378 በአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን እና ናሰው ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ ማህበር መካከል በነበረው ክርክር የጥገና ዋስትና (maintenance bond) ሊኖርእንደሚችል ካተተ በኋላ አንድ ሥራ ተቋራጭ በሠራው ህንጻ ላይ የተከሠተ እርግጠኛ የአሰራር ጉድለት በሌለበት ሁኔታ ወደፊት የሚታይና የሚከሰት የአሰራር ጉድለት ሊኖር ይችላል በሚል ምክንያት ሥራ ተቋራጮች ለሰሩት ሥራ የመጨረሻ ክፍያ የማግኘት መብት መከልከል አግባብነት የሌለው መሆኑን እሰገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡
@consite🏗
👉ደረጃ 1 እና 2 የሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች አጠቃላይ የስራ ልምድ ከ ሁለት ወደ አምስት አመት ከፍ ሲደረግ የተርንኦቨር ስሌት ቀመር ላይ ደግሞ ማስተካከያ ተደርጓል።
🏷አዲሱ የፌደራል የግዥ መመሪያ 1073/2017 ስለ ግንባታ ስራ ግዥ አፈጻጸም አዳዲስ ዝርዝር ሁኔታዎችን አካቷል።
📜ከነዚህም መካከል:-
✅ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ባለስልጣን በሚሰጠው ደረጃ መሠረት ከደረጃ 6 እስከ 1ዐ ካሉት በስተቀር ሌሎች የሀገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች በስራ ተቋራጭ፣ በሽርክና ማህበር (Joint Venture) ወይም በንዑስ ስራ ተቋራጭነት በየዘርፉ ለደረጃ 1 እና 2 የአምስት ዓመት ልምድ፣ለደረጃ 3 የሦስት ዓመት ልምድ፣ ለደረጃ 4 እና 5 የሁለት ዓመት ልምድ ሊኖራቸው ይገባል፡፡
✅ የውጪ ሀገር ስራ ተቋራጮች ደግሞ በስራ ተቋራጭ፣ በሽርክና ማህበር ወይም በንዑስ ስራ ተቋራጭ ደረጃ በዘርፉ ቢያንስ የ8 ዓመት ልምድ ሊኖራቸው ይገባል፡፡
✅ በሌላ በኩል የሀገር ውስጥ ስራ ተቋራጭ ዓመታዊ የግብይት መጠን (ተርንኦቨር) የሚያዘው ባለፉት አምስት ዓመት ውስጥ ካስመዘገበው የግንባታ ስራ ዓመታዊ ተርንኦቨር የተሻለውን በመምረጥ ሆኖ፣ስራ ተቋራጮች እንዲያሟሉ የሚጠየቁት የተርንኦቨር መጠን የሚሰላው ሊሰራ የታሰበው የግንባታ ሥራ ግምታዊ ዋጋን ግንባታው ይጠናቀቃል ተብሎ ለሚገመተው ወር በማካፈል እና ውጤቱን በ12 እና 0.6 በማባዛት ይሆናል። ለምሳሌ፡ ከዚህ በፊት 12 ወራት ለሚወስድ እና የዋጋ ግምቱ 100 ሚሊየን ለሆነ ፕሮጀክት የሚጠየቀው ተርንኦቨር መጠን ከ80 ሚሊየን ወደ 60 ሚሊየን ዝቅ የሚያደርገው ይሆናል።
@etconp
