ኦርቶዶክስ ተዋህዶ💒❤️🩹
Open in Telegram
"ለነፍሴነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና እንዳልጠፋ አምናለው ያንቺ ልጅ ነኝና">>>> ✅ኦርቶዶክሳዊ ምስሎች ✅መዝሙሮች እንዲሁም ግጥምና መልዕክቶችን ✅እናስተላልፍበታለን... ✅የቅዱሳን ታሪኮች ✅መንፈሳዊ መፀሀፍቶች ወዘተ... መሳደብ ፣ የማይሆን ቃል መናገርና መልቀቅ ❌ፈፅሞ የተከለከለ ነው።
Show more1 631
Subscribers
+624 hours
+47 days
+1730 days
Posts Archive
1 631
Repost from Dn Eyuel Habtamu
አቤቱ ፈዋሹ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ፤ ድሮ እንደ ሕፃን ልጅ በጠበልህ አምኜ በቅንነት እቀርብ እንደነበርኸው ሁሉ፣ ዛሬ ግን በኃጢአትና በዓለም እድፍ ልቤ ጎድፎና ቆሽሾ በፊትህ ቆሜያለሁ።
ጥላሸት ያበላሸውን የነፍሴንና የሥጋዬን ቆሻሻ በምህረትህ ጠበል እጠበው
ናዛዚ
1 631
❝ወደ ተቀደሰችው የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ስፍራ ይገቡ ዘንድ አሕዛብን ዝም አላላቸውም፡፡ በሕንፃዋ ላይ ቢሆን በሠራዊቱ ላይም ቢሆን ጻድቅና የዋህ በሆነ በንጉሥ አኖሬዎስ ሕዝብ ላይም ምንም ምን ክፉ ነገር ሳያደርጉ መለሳቸው እንጂ❞እንዳለ ድርሳነ ሩፋኤል ዘታኅሣሥ፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል የተጨነቁትን ከጭንቀት የሚያድን መልአክ ነው፡፡ በነሐሴ የሚነበበው የድርሳነ ሩፋኤል ተአምር ላይ ቴዎፍሎስ ለሚባል ሊቀ ጳጳስ ከጭንቀቱ እንደደረስለት ያስረዳናል፦ ይህ ቴዎፍሎስ የሚባል ደግ ጳጳስ እውነትን ስላስተማረ በሮም ሀገር የንጉሡ የወታደር አለቃ ጕድጓድ ቆፈረና በዕንጨት ሳጥን አድርጎ ከጕድጓዱ ውስጥ ጣለው፡፡ ጳጳሱም ምንም ሳይሆን ከሦስት ቀን በኋላ በአራተኛ ቀኑ ቅዱስ ሩፋኤል በአደረገለት ተአምር ከተጣለበት ጕድጓድ በሰላም ወጥቷል፡፡
❝አስተርእየኒ ሩፋኤል መልአከ ጥዒና ወፈውስ በራብዕት ዕለት ለአሕይዎ እምአመ ኀተሞ ንጉሥ በንፍቀ ዚአሁ አስተርአይኮ ለብእሲ ቀሲስ — ንጉሥ በራሱ ሳጥን ቆልፎ ከጣለው በኋላ በአራተኛ ቀኑ ልታድነው ለቀሲሱ የተገለጥክለት ፈጣን የማዳንና የሕይወት መልአክ ሩፋኤል ሆይ ለኔም ተገለጥልኝ❞እንዳለ ደራሲ። የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ የበዓሉ መታሰቢያ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ የመታሰቢያው ዕለት ጳጕሜን ሦስት ቀንና ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ቀን ነው ፤ ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ቀን አንደኛ በዓለ ሢመቱ ነው:: ሁለተኛ በቴዎዶስዮስ ልጅ በንጉሥ አኖሬዎስ ትእዛዝ ንጉሡ አኖሬዎስ ራሱም ከሠራተኞች ጋር አብሮ እየሠራ በቊስጥንጥንያ ሀገር ቤተ ክርስቲያኗን ከፈጸመ በኋላ ቅዳሴ ቤቱ ታኅሣሥ ፲፫ ቀን ተከብሯል። ስለ ሁለቱም የመታሰቢያው በዓላት የጥር ድርሳነ ሩፋኤል እንዲህ ይላል፡-
❝ታላቅ በዓሉንም በወርኃ ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ቀን አክብሩ!❞በዚች ዕለት የሰውንና የእንስሳቱን ማኅፀን በመፍታት ይጠብቅ ዘንድ ተሹሟል። በዚህ ታላቅ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነፀች ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤቷም በዚሁ ዕለት ነው፡፡
❝ዛቲ ዕለት ቅዳሴ ቤትከ ነያ፣ ዘኒ ዘኮነ በብሔረ ፅርዕ ወሮምያ ሩፋኤል መልአኩ ለአምላከ ሰማይ ኬንያ: ቀድስ ሕዝበከ ዘተጋብኡ በአርአያ ከዊን ኒቅያ: በዐውደ ምሕረትከ እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ — የፈጣሪ የሰማይ አምላክ አገልጋይ መልአክ ሩፋኤል ሆይ! ይች ዕለት በስምህ የታነፀች ቤተክርስቲያንህ የከበረችበት ነው፤ ይኸም የተደረገ በሮምና በፅር አገርነው፤ ምሕረትህ በሚነገርበት አደባባይ ሃሌ ሉያ እያሉ የተሰበሰቡ ሕዝብህንም ባርክ❞— እንዳለ አርኬ፡፡ ይልቁንም በወርኃ ጳጕሜን ሦስት ቀን በፍጹም ደስታ ታላቅ በዓል አድርጉ፡፡ ይች ዕለት ሊቀ-መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል የቤተ ክርስቲያን መሠረትን በዓሣ ዐንበሪው ላይ ያፀናባት:: ብፁዕ አባ ቴዎፍሎስንም ከእሥር ያዳነባት፤ ዳግመኛም ሰማያት ተከፍተው የቅዱሳንን ጸሎት ሁሉ ወደ አምላኩ እግዚአብሔር በእጁ የሚሳርግበት ዕለት ናትና፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ በቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በጳጉሜን ሦስት ሰማያት የሚከፈቱበት (ርኅዎተ ሰማይ) በመሆኑ በዚህች በተከበረችው ዕለት ምእመናን ጸሎታቸው ያርግላቸው ዘንድ ከምን ጊዜውም በበለጠ ተግተው ይጸልያሉ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን የእኛንም ጸሎታችንን በምልጃቸው የሚያሳርጉልን ቅዱሳን መላእክትም መሥዋዕቱን የሚያሳርጉበትና የአምላካችንን ምሕረት ቸርነት ለሰው ልጆች የሚያወርዱበት ዕለት ነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል አማላጅነት ሁላችንንም ይጠብቀን። እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን ምእመናን። የቅዱስ ሩፋኤል ቀን ጸሎታችሁን ስታደርሱ ስለ ቅዱስ ሩፋኤል ብላችሁ አንድ አቡነ ዘበሰማያት ❝ኃጥእ ባርያህን ኃይለራጉኤልንም አስበው❞ ብላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ፤ አደራ! ዲ/ን ኃይለራጉኤል
1 631
"ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ኀበ ሕንጻ ሕይወት ዘተሐደሰ፤
እምቅድመ ዝኒ ኀቤሁ ሥጋ ወልድኪ ፈለሰ፤
ቤዛዊተ ዓለም ማርያም አስተበቁዓኪ አንሰ፤
ትቤዝዊ በኪዳንኪ ዘዚዓየ ነፍሰ፤
እስመ በሥራያ ይዕቲ ቀብዓተኒ ፈውሰ።"
እንኳን ለእመቤታች ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ፍልሰተ ሥጋ (ትንሣኤና ዕርገት) አደረሳቹ!!!
መልካም በዓል!!!
