Bibliophagos
Open in Telegram
ይህ Channel የተከፋተው መፅሐፍ ቅዱስን ለሚወዱ ሠዋች ነው።በዚ channel ውስጥ የተለያዪ መጸሀፍ ቅዱስ ላይ የተመሰረቱ ጥያቄዋች ይቀርባሉ ፣ መንፈሳዊ ሀሳቦች ይነሳሉ ፣ ትምህርቶች እናማማራለን ። መፅሐፍትን ከፍትን መፅሐፍት ያወሩለትን ኢየሱስ እንፈልጋለን ። በመፅሐፍ ቅዱስ በኩል ኢየሱስን የበለጠ ለማወቅ እና ለመውደድ እናጠናለን እናወራለን
Show more419
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-130 days
Posts Archive
419
"አምላኬ ሆይ
በገሃነም መቃጠልን ፈርቼ አንተን እያመለክሁ ብገኝ በገሃነም አቃጥለኝ ፤ በገነት ምኞት ተጠምጄ አንተን ያመለክሁ ቢመስለኝ ከደጃፉ አታድርሰኝ ፤ ነገር ግን አንተን በመፈለግ ብቻ እያመለኩህ ብገኝ ዘላለማዊውን ውበትህን አየው እርዳኝ ። "
የአንዲት ሴት ፀሎት
419
ለጠፉ በጎች ያለን ርህራሄ እና ፍቅር ወተን እነሱን የምንፈልግበት እና የምንጠራበት ሀይል ምንጭ ነው። የወንጌል ተልዕኮ ለሀጢያተኞች ካልን ፍቅር እንዲሁም ከሀጢአታቸው የተነሳ ለተዳረገባቸው የጥፋት ፍርድ ርህራሄ እና አዘኔታን ይጠይቃል። ለሀጢዕ ያልን ፍቅር ፣ ሀዜንታ እና ርህራሄ የእግዚአብሔር ክብር በምድር ሞልቶ የማየት ርሃብ ፣ በጉ ከምድር ነገዶች እና ከህዝቦች ሁሉ አምልኮ ሲቀበል የማየት ጥማት ክርስቲያንን ለወንጌል ተልዕኮ ያዘጋጀዋል ።
419
Repost from በክርስቶስ ( in christ)
(ምን ነካን ግን ?)
ከ10 አመቱ ታናሽ ወንድሜ ጋር ረዘም ያለ የእግር ጉዞ እያደረግን ። ለምን አንፀልይም ተባባልና ለመፀለይ ተስማማን ። ግን ትንሹ ወንድሜ" አንተ ልጅ እያለ የምትፀልየው ፀሎት ምን እያልክ ነው ?" ብሎ ጠየቀኝ ። የተወሰነ ሰከንዶች ለመመለስ አሰብ አረኩናል ። እኛማ እንደ አንተ ህፃን እያለ የምንፀልየው ፀሎት እንዲህ እያለን ነበር
" መፀሀፍ ቅዱስ በእጃችን ይዘን ጌታ ሆይ ቃል አስተምረን እና እንወቅህ እናም ጓደኞቻችን ኢየሱስን እንዲያውቁ እርዳቸው" እያልን እንፀልይ ነበር ።
ይሔን ፀሎት ለመፀለይ ከወንድሜ ተስማማንና መፀለይ ያዝን ። ጌታ ሆይ ቃልህን አስተምረኝ አንተን እንወቅህ እያልን ለየብቻችን ፀለይን ። መሃል ላይ በህፃንነት እድሜዬ ለጌታ የነበረን ርሃብ ፣ ጌታ ለማወቅ የነበረ ጉጉት ፣ ቃሉን ለማንበብ የነበረ ፍላጎት ፣ በመዳናችን መደሰት ፣ ፀሎት መውደድና በንፁህ ልብ ጌታን ጌታን ማለት ትዝ አለኝና አሁን ላይ ባለኝ ልብ ደነገጥኩ ። ርሃብ የጣለ እድገት እድገት አይደለም ፣ የቃሉን ፍላጎት የቀነሰ እውቀት እውቀት አይሆንም ፣ የፀሎት አምሮትን የቀነሰ ወግ ወንዝ የሚያሻግር ልማድ አይሆንም ፣ ለጌታ ፍቅር የሚኖረንን መንሰፍሰፍን ያጠፋ ብስለት እሱ ብስለት ሳይሆን ብክነት ነው የሚሆነን ። መንፈሳዊ ርሃብ ህይወት የሚያጣፍጥ ማጣፈጫ ነው።
በድነቴ ጠዋት በገባኸኝ ማግስት
ጨዋታ ወሬዬ መወደዴን ማድነቅ
ዘምሬህ አልጠግብ አውርቼህ አረካ
ይህች ትንሽ ልቤ ለፍቅርህ ሸፍታ
አልደግ አንተ ላይ ራሴን አልቻል
አጓጉል ነው ሁሉ ያለንተ መች ያምራል
@cgfsd
419
ጫማ ሠፊው ወንጌል ሰባኪ
ዊልያም ኬሪ የዘመናዊው ተልዕኮ አባት ( The Father Of Modern Mission ) በመባል ይታወቃል ። ጫማ ሠፊ እና በቤተክርስቲያን ውስጥ በመጋቢነት ያገለግል የነበረው ዊልያም ኬሪ የታልቁ ተልዕኮ ረሃብ ልቡ ላይ ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ ይቀጣጠል ነበር ። ወንጌል ፍጥረት ጋር ደርሶ የክርስቶስ ብርሃን ካሉበት ጨለማ ሲያወጣቸው ማየት የዊልያም ኬሪ የሁልጊዜም ፀሎቱ ነው ። የወንጌል እውነትን ላለመኑት የማድረስ ጥልቅ ናፍቆቱን ከግብ ለማድረስ ከቤተሰቡ ጋር ወደ ህንድ ሀገር ለተልዕኮ ያመራል ።
ፅኑ ተጋድሎ ግን አስደናቂ ፅናት ፣ ብርቱ ፈተና ግን ማይበገር እምነት ፣ ለወንጌል የተከፈለ መስዋዕትነት ፣ እንደ መጥምቁ ዪሐንስ ቀልጦ የሚያበራ ሻማ ፣ ለፍጥረት ያለ ድንቅ ርህራሄ ፣ ለወንጌል ያለ ፍቅር ፣ ከራስ ይልቅ ለጌታ መኖር የተያበት ግሩም ህይወት ። ዊልያም ኬሪ ጫማ ሠፊው ወንጌል ሠባኪ !
419
ይህ ፅሁፍ በወንጌል አገልግሎት በትጋት አገልግሎ ስላለፈው የተወደደው ወንጌላዊ ሬንሀርድ ቦንኬ የመቃብር ሀውልት ተፅፎ የሚገኝ ነው ። ህይወት ሁላችንም ሞት ወደተባለ ባቡር ያሳፍረናል ። ህይወት ነጭ ወረቀት እንደመሆኗ ሠው በዘመኑ ያሻውን ይፅፍበታል ። በእስትንፉሱ እያለ የፃፈው በሞቱ ላይ ይነበባል። በህይወት እያሉ የኖሩት ለሞት ቀን ለዝክር ይነበባል ። በህይወት እያለ በሞቱ ቀን ስለሚነበበው ዝክር እርግጠኛ የነበረው ጳውሎስ እንዲህ ይለናል
በመሥዋዕት እንደሚደረግ፥ የእኔ ሕይወት ይሠዋልና፥ የምሄድበትም ጊዜ ደርሶአል። መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፥ ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፥ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም ጳውሎስ በህይወት እያለ በተሠጠው ነጭ ወረቀት ላይ የፃፈበት መልካሙን ገድል መጋደል ፤ የተሠጠውን ሩጫ መጨረስ ፤ ለጽድቅ አክሊል የሚመጥን ስራ መስራት ነበር ። እኛስ ለተሰጠን የህይወት ነጭ ወረቀት ምን ፅፈንበት ይሆን ? ጳውሎስ ይህ የጽድቅ አክሊል ለሱ ብቻ እንዳይደለ ነግሮናል መገለጡን ለሚነፈፈቅ ጭምር እንጂ ። ህይወታችን ለጌታ ለጥቅም ሳይሆን እንዳንሞት መገለጡን እንውደድ። በቦንኬ መቃብር ሀውልት ላይ የሠፈረውን አየን በእኛስ የመቃብር ሀውልት ምን በመባል ይፃፍ ይሆን ?
419
ዕብራውያን 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።
¹⁵ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።
¹⁶ እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።
በኢዮብ መኳንንት
419
በአቂላ እና ጵርስቅላ መቃናት ያለባቸው ብዙ አጵሎሶች በቤተክርስቲያን ምስባክ ላይ ሞልተዋል። አጵሎሶችን የሚያሳድጉ አቂላ እና ጵርስቂላ እንዲበዙ መልሰን መላልሰን መፀለይ ከመቼውም በላይ አስፈላጊ ሆኖ ይታየኛል። አጵሎሶች ለቤተክርስቲያን ያስፈልጉናልና ፤ አጵሎሶችን ለቤተክርስቲያን ጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ አቂላ እና ጵርስቂላ ደግሞ አብዝተው ያስፈልጋሉ ።
በአገልጋይ አለማደግ እና አለመብቃት የሚጠቋቆሙ ሳይሆን ለማቅናት እና ለማስተማር ልብ ያላቸው የኔ ልድመቅ ጩኸት ሳይሆን የእግዚአብሔር መንግሰት አብሮ ሠራተኝነት ረሃብ ያላቸው አቂላ እና ጵርስቅላ ለዘመናችን ቤተክርስቲያን እጅጉን ያስፈልጉናል ። አጵሎሶች ሞልተናል እና አቂላ ሆይ የት ነህ ? ጵርስቂላስ ከወዴት ነሽ ?
419
እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንኩት እሷንም አጥብቄ እሻለው ከተገለጥብኝ ፀለቶቼ ይልቅ የተገለጥልኝ ፀሎቶቼን እንዲመልስ ። ተገለጥብኝ ከማለት ይልቅ ተገለጥልኝ እጅጉን ይበልጣልና ።
419
በጎልጎታ ድግስ ተደገሰ
ኢየሱስ ለአለም ስጋውን ቆረሰ
እየሱስ ደቀቀ እጅ እና እግሩ ደማ
በመሰቀል ላይ ሆኖ ጩኸትን አሰማ
ፍቅር ተሰበከ ደም እየፈሰሰ
ዕርቃኑን ተሰቅሎ ዓለም አለበሰ
ስጋው ተተልትሎ አጥንቱ ደቀቀ
ማይገፈፍ ልብስን ገራፊው ለበሰ
ኢየሱስ ተጠማ ደም እያለቀሰ
ከህይወት ውሃ ምንጭ ፍጥረት ረሰረሰ
የድግስ ባለቤት ድግሱ ላይ ሞቶ
ተጋባዥ ጠገበ የደገሰን በልቶ ።
419
እግዚአብሔር ለሠው ልጆች ያለው ፍቅር
የተረጋገጠው በኢየሱስ ነው ። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ፍቅር የተገለጠበት የእግዚአብሔር የፍቅር ማብራሪያ እንዲሁም የእግዚአብሔር ፍቅር ማረጋገጫ ነው ።
እግዚአብሔር እኛን እንደሚወደን ትልቁ ማረጋገጫ ኢየሱስን ስጦታ አርጎ መላኩ ነው ። ዉዱን ልጁን ስለሠጠን በዚያ ለኛ ያለውን መውደድ አረጋግጧል ።
ኢየሱስ የእግዚአብሔር የፍቅር ሰብከት ሰለሆነ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ፍቅር ማረጋገጫ ነው ።
