en
Feedback
የሸህ ሆጀሌ ሰፈር መስጂድ ወርሃዊ ሙሃደራ ፕሮግራም ቻናል

የሸህ ሆጀሌ ሰፈር መስጂድ ወርሃዊ ሙሃደራ ፕሮግራም ቻናል

Open in Telegram

በዚህ ቻናል ውስጥ ወርሃዊ ሙሃደራ ፕሮግራሞች እና የጁምዓ ኹጥባዎች እና አስተማሪ የሆኑ ሀዲሶች ያገኛሉ ። ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር ያድርጉ

Show more
593
Subscribers
No data24 hours
-27 days
+730 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '24
September '24
+6
in 0 channels
August '24
+14
in 0 channels
Get PRO
July '24
+9
in 0 channels
Get PRO
June '24
+8
in 0 channels
Get PRO
May '24
+29
in 1 channels
Get PRO
April '24
+3
in 0 channels
Get PRO
March '24
+11
in 1 channels
Get PRO
February '24
+6
in 0 channels
Get PRO
January '24
+34
in 1 channels
Get PRO
December '23
+26
in 0 channels
Get PRO
November '23
+108
in 2 channels
Get PRO
October '23
+178
in 1 channels
Get PRO
September '23
+7
in 0 channels
Get PRO
August '23
+4
in 0 channels
Get PRO
July '23
+16
in 0 channels
Get PRO
June '23
+24
in 0 channels
Get PRO
May '23
+8
in 0 channels
Get PRO
April '23
+22
in 0 channels
Get PRO
March '23
+52
in 0 channels
Get PRO
February '23
+21
in 0 channels
Get PRO
January '23
+35
in 0 channels
Get PRO
December '22
+30
in 0 channels
Get PRO
November '22
+209
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
20 September0
19 September0
18 September0
17 September0
16 September0
15 September+1
14 September0
13 September0
12 September0
11 September0
10 September0
09 September0
08 September0
07 September0
06 September0
05 September0
04 September0
03 September+1
02 September0
01 September+4
Channel Posts
«اللَّهمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ».

2
https://www.tiktok.com/@shehhnnt0ig?_t=8oJK43RmLiv&_r=1 ቲክቶክ አካውንታቸንን ፎሎው ያድርጉ
366
3
https://youtu.be/jVIQFXocYfo?si=6bWjwadWPzsY7yC0
582
4
https://youtu.be/Hzf4V4ghxqQ?si=nVwQstiUC2nRm5va
531
5
https://youtu.be/OcHKYsPWE9c?si=w_1iJbzn60uAXy30
474
6
አሰላሙ አለይኩም ውድ የፔጃችን ተከታታዮች የዩቱዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ እንዲሁም በሸህ ሙሀመድ ሀሚዲን መፍሁሙል ኢባዳ ( የኢባዳ ፅንስ ሀሳብ በእስልምና) የሚለው ሙሃደራ ተለቋል እና ገብተው ይመልከቱ። https://youtu.be/MkS1hVM83jc?si=oE7tS_185I42l2LF
533
7
የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ ዙህድ ማለት ምን ማለት ነው?
1
8
ዙህድ_ምን_ማለት_ነው_ሸህ_ያዕቁብ_ኹጥባ.m4a
331
9
የአሹራ ቀን ፆም! ለመልካም ስራ አስተዋሽ እንሁን ከኢብኑ አባስ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ
የአሹራ ቀን ፆም! ለመልካም ስራ አስተዋሽ እንሁን ከኢብኑ አባስ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ اللَّهُ - صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ﴾ “የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፍቃድ የአሹራን ቀን ፆም ዘጠነኛውን ጨምሬ እፆማለሁ።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1134 ከአቢ ቀታዳ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿صيامُ يومِ عاشوراءَ، إنِّي أحتَسِبُ على اللَّهِ أن يُكَفِّرَ السَّنةَ الَّتي قبلَهُ﴾ “የአሹራ ቀን ፆም ያለፈውን አመት ኃጢአት እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162
542
10
የጁምዓ_ኹጥባ_ሪሽዋ_ጉቦ_ሸህ_ሙሀመድ_አሚን.m4a
388
11
ሀ) ሰላት፦ ለሙስሊሞች በ24 ሰዓት ዉስጥ አምስት ጊዜ ሰላት መስገድ ግዴታ ነው። ሰላት የሚሰገድበት ጊዜ ከፊሎቹ የሰላት ጊዜ ከፀሐይ እንቅስቃሴ ጋር ይያዛሉ።ለምሳሌ፦ሱብሂ ሰላት ፀሐይ ከመውጣቷ በፊት ንጋት ላይ፥ የዙሁር ሰላት ደግሞ ልክ እኩለ ቀን ጥቂት እንዳለፈ ፀሐይ ከመሃል አናት ተንሽ ዘንበል ስትል ጀምሮ፥የአስር ሰላት ደግሞ ከሰዓት በሚባለው ጊዜ በፀሐይ አማካኝነት የሚፈጠረው የአንድ ነገር ጥላ(shadow) የነገሩን ቁመት እኩል ወይም እጥፍ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ(በአብዛኛው 10 ሰዓት ገደማ) ፥የመግሪብ ሰላት ደግሞ ልክ ፀሐይ ከጠለቀች ጀምሮ ይሰገዳል። የኢሻ ሰላት ደግሞ በፀሐይ መጥለቅን ተከትሎ በሰማይ ላይ የሚታየው ቀይ ድንግዝግዝ ያለ ብርሃን ሙሉ ለሙሉ ከጠፋበት ጊዜ አንስቶ ናቸው። ለ) ረመዳን፡- የረመዳን ወር መግባት የሚረጋገጠው የአዲስ ጨረቃን መወለድ መታየት አልያም የወሩ ቀናት 30ኛ ቀን መሙላቱን በማረጋገጥ ሲሆን የእለቱን ጾም ደግሞ ንጋት ላይ ፀሐይ ሊወጣ-ሊነጋ ሲቃረብ ይያዝና ምሽት ፀሐይ ስትጠልቅ ይፈታል። ሐ) ሐጅ፦የሐጅ ጊዜው/የዙልሂጃ ወር/ መግባት ከጨረቃ አቆጣጠር መሠረት በማድረግ የጨረቃ ዑደት 30 ቀን ሲሞላ ወይም በ29ኛ ቀን ላይ አዲስ ጨረቃ ስትታይ ወሩ መግባቱ ይረጋገጣል። ሐጅ ከተጀመረ በኋላ ከፊሎቹ ተግበራት በፀሐይ ሁኔታ ጋር ይያዛሉ።ለምሳሌ የዐረፋ ቀን ተግባራት፥ በሚና የሚሰገደው ሰላት ጊዜ፥ ወደ ሙዝደሊፋ ጉዞ ጊዜ፥ ወደ አረፋ ጉዞ ወዘተ ከፀሐይ እንቅስቃሴ ጋር ይያዛሉ። መ) ዘካ፦ ዘካ ሲወጣ አንድ ገንዘብ ዘካ ለማውጣት መጠኑ መድረስና ገንዘቡ በግለሰቡ እጅ አንድ ዓመት መቆየቱ ይታያል። በዚህ ጊዜ ዓመት የሚሰላው በጨረቃ አቆጣጠር አንድ ዓመት(354/355 ቀናት) እንጂ በፀሐይ አቆጣር አንድ ዓመት(365 ቀናት) አይደለም። ሠ) የበዓል ቀናት፦ ኢድ-አልፊጥር እና ኢድ አል-አደሃ እለት ከአዲስ(ለጋ) ጨረቃ(ሂላል) ጋር ይያዛል። ለዚያም ነው «ጨረቃ ከታየ” የሚባለው። ረ) የሱና ጾሞች፦የአረፋ ቀን ጾም(ዙልሂጃ 9ኛ ቀን)፥የአሹራ ቀን ጾም(የሙሀረም 10ኛ ቀን ጾም) እና የአያመል ቢድ ጾም በጨረቃ አቆጣጠር ባለው በየወሩ ባሉት በ13፥14፥ እና 15ኛ ቀናት የሚጾም የሱና ጾም በጨረቃ አቆጣጠር መሠረት ነው። ሸ) ፍቺ የፈጸመች ሴት ሌላ ከማግባቷ በፊት ከቀደመው ጋብቻ በማህጸኗ እርግዝና መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሦስት ወራት መጠበቅ እንዳለባት(አል-በቀራህ፡228) ላይ የተጠቀሰው ከጨረቃ ዑደት ጋር በተያያዘው ወር ነው። ቀ) በላቸው የሞተባቸው ሴቶች ደግሞ አራት ወራት ከአስር ቀናት መጠበቅ እንዳለባቸው(አል-በቀራህ፡234) የተጠቀሰው ከጨረቃ ዑደት(አቆጣጠር) ጋር በተያያዘው ወር ነው። በ) የአንድ ልጅ የእርግዝናና ከጡት መለያ ጊዜው ድምር በጠቅላላው ሠላሳ ወራት መሆኑ(አል-አህቃፍ፡15) በቁርኣን የተጠቀሰው ከጨረቃ ዑደት አቆጣጠር ጋር በተያያዘው ወር ነው። በቀጣይ ክፍል ደግሞ አላህ ካለ የሂጅራ ዘመን አቆጣጠር እንዴት እንደተጀመረ እንመለከታለን። እስከዚያው ቸር እንሰንብት። ይቀጥላል..
489
12
لَا ٱلشَّمْسُ يَنۢبَغِى لَهَآ أَن تُدْرِكَ ٱلْقَمَرَ وَلَا ٱلَّيْلُ سَابِقُ ٱلنَّهَارِ وَكُلٌّ فِىفَلَكٍ يَسْبَحُونَ «ፀሐይ ጨረቃን ልትደርስባት አይገባትም።ሌሊትም ቀንን (ያለጊዜው) ቀዳሚ አይሆንም። ሁሉም በመዞሪያቸው ዉስጥ ይዋኛሉ።»(ያሲን፡40) ይህንኑ የተቀመጠላቸውን የፍጥነት ልክ ጠብቀው መጓዛቸውን በሌላ ምዕራፍ እንዲህ በማለትም ገልጿል፦ ٱلشَّمْسُ وَٱلْقَمَرُ بِحُسْبَانٍ «ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ(ይሄዳሉ)።»(አል-ራህማን፡5) ሀ) አንድ ቀን(የቀንና ሌሊት መፈጠር) ❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄ አንድ ቀን ማለት ከመሬት አንጻር ፀሐይ እየተንቀሳቀሰች በሰማይ ላይ በተመሳሳይ ስፍራ ላይ ለመመለስ የሚወስድባት ጊዜ ወይም ፀሐይ አንድን የመሬት ክፍል (ስፍራ) በብርሃኗ በድጋሚ የምታገኝበት ጊዜ ሲሆን ይህ ጊዜ በዉስጡ የቀንና የሌሊት ጊዜ አለው። ይህም ለእያንዳንዱ የመሬት ክፍል ፀሐይ የሚያገኝበትና የማያገኝበት ጊዜን ይፈጥራል።የፀሐይ ብርሃን የሚያገኝበት ጊዜ ቀን ሲባል ፀሐይ የማያገኝበት ጊዜ ደግሞ ሌሊት ይሰኛል። በዚህ ዑደት ቀናቶች እየተፈጠሩ ይሄዳሉ።በጨረቃ አቆጣጠር(Lunar calander) አዲስ ቀን የሚገባው ጨረቃ ከምትወጣበት ምሸት ጀምሮ ነው።ለዚህም የአዲስ ወር መግባት ጨረቃ በምትታይበት ምሽት የሚታወቀው።ከዚህ የተነሳም ነው ነገ ለምንጾመው የረመዳን ጾም ማታውኑ የረመዳን ወር መግባቱን አውቀን የተራዊህ ሰላት የምንሰግደው። ለ) የወር መፈጠር ❇❇❇❇❇❇ ደመናማ ባልሆነ ሌሊት ወደ ሰማይ በትኩረት የተመለከተ ሰው የጨረቃን የተለያዩ የሚለዋወጡ ገጽታዎቿን ያስተውላል። አንዳንዴ ጨረቃ ሙሉ ሆና እንደ ኳስ ቅርጽ ኖራት ትታያለች። ሌላ ጊዜ የሙዝ ቅርጽ፥ ሌላ ጊዜ ደግሞ ግማሽ ክብ ቅርጽ እየያዘች ትታየናለች። መሬት ሆነን ጨረቃን ከርቀት ስንመለከት በትንሹ ትታየናች። ቀጥሎም የሚታየን መጠኗ እያደገ ይሄድና ሙሉ የጨረቃ ቅርጽ ይታየናል።ቀጥሎ መጠኗ እያነሰ ይሄድና ሙሉ ለሙሉ ትሰወርብናለች። ቀጥሎ ደግሞ የሚታየን መጠኗ ትንሽ ሆና መታየት ትጀምርና እያደገች በተመሳሳይ መልኩ ዑደቷን ትቀጥላላች። ይህ የሆነው በሚከተለው ምክንያት ነው። ጨረቃ በመሬት ዙሪያ ስትዞር፥ መሬት ደግሞ በፀሐይ ዙሪያ ትዞራለች።ጨረቃ ከፀሐይ ከምታገኘው ብርሃን በስተቀር የራሷን የብርሃን ምንጭ የላትም። ጨረቃ በመሬት ዙሪያ ለመዞር 29 ቀናት ተኩል ይፈጅባታል። ጨረቃ በመሬትና በፀሐይ መካከል ስትሆን ጨረቃ ከፀሐይ የምታገኘውና የምታንጸባርቀው ብርሃንን ራሷ በአንድ ጎኗ ከኛ ስለምትጋርድ መሬት ላይ በተቃራኒ አቅጣጫ ላለነው ጨረቃ አትታየንም።ይህን ጊዜ የአዲስ ጨረቃ ዑደት ጅማሮ ተብሎ ይወሰዳል።ከዚህ ጊዜ በኋላ ጨረቃ በምህዋሯ ላይ በትንሹ በተጓዘች መጠን ከፀሐይ ተነስቶ በርሷ ላይ ደርሶ የሚንጸባረቀው ብርሃን ምክንያት ከፊል የጨረቃ ክፍል መሬት ላለነው ይታየናል።ያኔ ለኛ የምትታየንን ያክል አኳላን እያየን ሌላው አካሏ ደግሞ ስለታገረደ የምናየውን የጨረቃ ክፍል ብቻ ቅርጽን እናስተውላላን። በየእለቱ ጨረቃ በተንቀሳቀሰች ቁጥር የሚታየን የጨረቃ ክፍል እያደገ ይሄድና በ15ኛው ቀን ሙሉ ለሙሉ ጨረቃን እንመለከታለን።ቀጥሎም ደግሞ ሌላኛው የአካሏ ከፍል በመጠኑ እየተጋረደ መሄድ ይጀምርና በ14 ወይም በ15ኛ ቀኑ ጨረቃ ሙሉ ለሙሉ በመጋረድ ከእይታችን ትሰወራላች።ይህ ሙሉ ጨረቃ ከመታየቷ በፊትና በኋላ ያለው ጊዜ በአንድነት አንድ የጨረቃ ዑደት ይሰኛል።በዚህ መልኩ አንድ ዑደት 29 ወይም 30 ቀን ሲወስድ የጨረቃ የሚለዋወጠው ገጽታዋ በ29 ወይም 30 ቀናት ዉስጥ ራሱን ይደግማል። ይህንን የጨረቃን አንድ ዑደት አንድ ወር ተብሎ ይቆጠራል። ሐ) አንድ ዓመት ❄❄❄❄❄ ጨረቃ አስራ ሁለት ተደጋጋሚ ዑደቶችን ስታሳይ 12 ወራት ወይም አንድ ዓመት ሞላ ይባላል።የጨረቃ አቆጣጠር በዓመት 354 ወይም 355 ቀናት አሉት።መሬት በፀሐይ ዙሪያ ለመዞር 365 ቀናትን ወይም አንድ ዓመት ሲለሚፈጅባት ፀሐይን መሠረት ያደረገ የዘመን አቆጣጠር አንድ ዓመት ሦስት መቶ ሥልሳ አምስት ቀናት አሉ።የጨረቃ አቆጣጠር ከፀሐይ አቆጣጠር በ11 ቀናት ገደማ ያንሳል።ይህ በመሆኑ ከፀሐይ አቆጣጠር አንጻር የጨረቃ አቆጣርን ካየነው በየዓመቱ 11 ቀናት ከስፍራው እየተለዋወጠ ይሄዳል። ለዚህም ነው በየዓመቱ የረመዳን መያዣ፥የኢድ ቀናት የፀሐይ ዘመን አቆጣጠርን ከሚጠቀመው «የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር» አንጻር በተመሳሳይ ቀን የማይዉለው። ጨረቃን መሠረት ያደረገ የዘመን አቆጣጠር ቀደም ብለን በጠቀሰነው መልኩ ጨረቃ በየጊዜው እየተሰወረች ዳግም ለጋ ጨረቃ ሆና ብቅ እያለች በመታየት በየቀኑ እያደገች ትሄዳለች።ቀጥሎም በሚታየው መጠኗ እየቀነሰች መልሳ መሰወር ትጀምራለች።ይህን የጨረቃን ቅርጽና እይታ ላይ መለዋወጥን ስናስተዉል ነገሩ አስገራሚና ለማወቅ የሚያጓጓ ነገር ነው። ለዚህ ነበር ቀደምት ሙስሊሞች ስለዚህ ጉዳይ የነቢዩ ሙሐመድን(ሰ.ዐ.ወ) ጠየቁ።በዚህን ጊዜ አላህ(ሰ. ዉ) ይህ የጨረቃ መለዋወጥ የተደረገበት ምክንያት የሰው ልጆች የጊዜ (ዘመን) አቆጣጠርንና የሐጅ ጊዜን ማወቂያ መሆኑን ጠቀሶ ቁርኣን አወረደ። እንዲህ በማለት፦ يَسْـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلْأَهِلَّةِ قُلْ هِىَ مَوَٰقِيتُ لِلنَّاسِ وَٱلْحَجِّ «(ሙሐመድ ሆይ!) ከለጋ ጨረቃዎች (መለዋወጥ) ይጠይቁሃል። እነርሱ ለሰዎች ጥቅም ለሐጅም(ማወቂያ) ጊዜያቶች (ምልክቶች) ናቸው በላቸው።»(አል-በቀራህ፡189) በዚህ የቁርኣን አገላለጽ ሙስሊሞች የጊዜ፥ቀንና ዓመታት አቆጣጠርን የጨረቃን አስገራሚን እንቅስቃሴንና ገጽታ ለውጥን መሠረት አድርጎ መሆን እንዳለበትም አመላካች ነው።ከዚህ በተጨማሪም የአላህ መልዕክተኛ(ሰ.ዐ.ወ) ሙስሊሞች የቀን አቆጣጠራቸው ጨረቃን መሠረት ያደረገ እንዲሆን በተለያዩ ሀዲሶች አስተምረዋል። ለአብነትም የረመዳን ጾም ወር መግባትንና መጠናቀቅን ማወቂያ ምልከቱ አዲስ(ለጋ ጨረቃ/ሂላልን) በማየት መሆን እንዳለበትም አስተምረዋል።ኢማም ቡካሪና ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ የአላህ ምልዕክተኛ(ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል፦ «ጨረቃ ስታዩ ጹሙ።ጨረቃን ስታዩ ጾምን ፍቱ።»(ቡካሪና ሙስሊም)። በዚህ መልኩ ሙስሊሞች የረመዳን ወር መግባትን ማብሰሪያ ጨረቃ ስትታይ ጾም እንይዛለን። የሸዋል ወር ጨረቃም ስትታይ የረመዳን ወር ማብቃትን ማብሰሪያ በመሆኗ የጾም ፍች(ኢድ) ይሆናል።ለዚህም ነው «ጨረቃ ከታየ» እየተባለ በሚዲያም የሚሰማው። የጨረቃና የፀሐይን ስሌትን መሠረት ያደረጉ አምልኮዎች ⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕ ቀደም ባለው ርዕስ ሙስሊሞች የሚጠቀሙት የወርና የዓመት አቆጣጠሩ የጨረቃ አካሄድን መሠረት ያደረገ ሆኖ መመላከቱን ተመልክተናል።ቀጥለን ደግሞ በተወሰኑ የኢስላማዊ ድንጋጌዎች እንዴት የጨረቃንና የፀሐይን እንቅስቃሴን በተናጠልና በጣምራ መሠረት ያደረጉ ግንጋጌዎች በኢስላም እንዳሉ ደግሞ አብነተቶችን በቀጣይነት እንመለከታለን።
251
13
ጨረቃን ታመልካላችሁ እንዴ? ❌❌❌❌❌❌❌❌❌ ክፍል ሁለት፥ በአሕመዲን ጀበል ቀደም ባለው ክፍል አላህ(ሰወ) በቁርኣኑ ሙስሊሞች የጊዜ፥ዘመንና አቅጣጫን እና የሒሳብ ስሌት ማወቅ እንደሚገባቸው አብራርተናል።በተጨማሪም ሙስሊሞች ጨረቃን ጨምሮ ከአለህ ዉጭ ማንንም እንደማያመልኩና ለማንም እንደማይሰግዱ ከ1445ኛ ዓመተ ሒጅራ ዘመን መጠናቀቅ ዋዜማን ምክንያት በማድረግ ስለዘመን አቆጣጠርም በጨረፍታ ተመልክተናል። ቀጣዩን ክፍል ደግሞ እነሆ። የቀድሞ የዐረቦች የዘመን አቆጣጠር 🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵 ከነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) በነቢይነት መላክ በፊት ዐረቦች ዘንድ የተለየ የሚታወቅ የዘመን መቁጠሪያ አልነበረም።ሰባት የሳምንት ቀናት እና አስራ ሁለት ወራት በጥቅም ላይ ቢዉሉም ዓመቱን አስመልክቶ በተከታታይነት የሚቇጠር አልነበረም። ሆኖም ዓመትን ከሌላው ለመለየት የሆነ ጉልህ ክስተት የተፈጠረበትን እንደማጣቀሻ በመዉሰድ «የእንትን ዓመት» እየተባለ ይጠቀስ ነበር። ለምሳሌ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የተወለዱበትን ዓመት ብንወስድ በተለምዶ እንደምናውቀው የተወለዱት በዝሆን ዓመት ነው።ማለትም ከኢትዮጵያ ወደ የመን ያቀናው አብረሃ የተባለው አስተዳዳሪ ወደ መካ በማቅናት ካዕባን ለማፍረስ በዝሆን ጭምር የታጀበ ጦር ይዞ የዘመተበት ዓመትን ለመጥቀስ ነው «የዝሆን ዓመት» የተባለው።ዓመቱን ከሌላው ለመለየት የተጠቀሰው በዚያ ዓመት የተፈጸመውን ጉልህ ክስተትን መሠረት በማድረግ «የዝሆን ዓመት» ተብሎ ይታወሳል። ቀጥሎም ሌላ ጉልህ ክስተት ሲመጣ እንደገና አዲሱን ክስተት በማጣስ «የእንትን ዓመት» ተብሎ ይጠራ ነበር። የሚታወስና ትክረት የሚስብ ጉልህ ክስተት ካልተፈጠረ ግን ከቀደመው ክስተት በፊት፥ በኋላ እየተባለ ይጠቀስ ነበር።ልክ እኛ ሀገር የገጠር ሰዎች እድሜያቸውን ሲጠየቁ «በእንትን ዓመት ተወለድኩ»፥ ከክስተቱ አንድ ዓመት በፊት፥ በኋላ ተወለድኩ እንደሚሉት ማለት ነው። በዐረቦች ዘንድ ዓመቱ አሥራ ሁለት ወራት ያሉት መሆኑና የወራቱ ስያሜ ቀድሞውኑ የነበረ ነው።ከነቢዩ ኢብራሂም(ዐሰ) ጀምሮ በነርሱ ዘንድ በቀረ ቅሪት እውቀት፥እምነትና ልማድ መሠረት ከአስራ ሁለቱ ወራት መካከል አራቱ ወራት የተከበሩ መሆናቸውን ይረዳሉ።እነርሱም ዙልቂዕዳ፥ዙልሂጃ፥ሙሐረም እና ረጀብ የተሰኙት ወራት ናቸው።እነኝህ ወራት ዉስጥ ዉግያ ማድረግ ክልክል ነው። ሆኖም የጎሳ መሪዎች ለነርሱ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያ ጥቅም ሲሉ በተለያየ ጊዜ የተከበሩ ወራቶች ሲገቡ በስምምነት የዚያን ወር ስያሜ በመለወጥ ወይም ዓመቱን አዲስ እንደጀመረ በመስማማት ያንን የተለያዩ ክልከላዎችን በዉስጡ የያዘውን የተከበረውን ወር ገብቶ ሳለ በስምምነት ብቻ ገና እንዳልገባ በዘዴ ለማዘግየት ይሞክሩ ነበር።በዚህ ዘዴያቸው በተከበረው ወር ገብቶ እያለ በስምምነት ሌላ ወር ነው ብለው በመወሰናቸው ብቻ የዚያ የተከበረውን ወር ክብር ይዳፈራሉ። በተከበረው ወር ዉስጥ እርም የተደረገን ነገር (ለምሳሌ ዉግያ) በዚህ ዘዴያቸው የተፈቀደ እንደሆነ አድርገው ይቆጥራሉ። የተከበረ ያልነበረውን ሌላኛውንም ወርም በተራው የተከበረው ወር እርሱ ነው ብለው የስያሜ ለውጥ ያደርጉ ነበር።በቀጣይ ዓመት ደግሞ ወራቱን በመለዋወጥ ዉስጥ የነርሱ ጥቅም ከሌለበት የወራቱ ሁኔታ በነበረው መልኩ እንዲቆጠር ይተዉ ነበር።ይህንን አስመልክቶ አላህ(ሱወ) በቁርኣን እንዲህ በማለት ይተቻቸዋል፦ إِنَّمَا ٱلنَّسِىٓءُ زِيَادَةٌ فِى ٱلْكُفْرِ يُضَلُّ بِهِ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ يُحِلُّونَهُۥ عَامًاوَيُحَرِّمُونَهُۥ عَامًا لِّيُوَاطِـُٔوا۟ عِدَّةَ مَا حَرَّمَ ٱللَّهُ فَيُحِلُّوا۟ مَا حَرَّمَ ٱللَّهُ زُيِّنَلَهُمْ سُوٓءُ أَعْمَـٰلِهِمْ وَٱللَّهُ لَا يَهْدِى ٱلْقَوْمَ ٱلْكَـٰفِرِينَ «የአንዱን ወር ክብር ወደ ሌላው ማዘግየት በክህደት ላይ (ክህደት) መጨመር ብቻ ነው። በእነርሱ እነዚያ የካዱት ሰዎች ይሳሳቱበታል። በአንድ ዓመት የተፈቀደ ያደርጉታል።በሌላው ዓመትም ያወግዙታል።(ይህ) አላህ ያከበራቸውን ወሮች ቁጥር ሊያስተካካሉ፤ አላህም እርም ያደረገውን የተፈቀደ ሊያደርጉ ነው። የሥራዎቻቸው መጥፎው ለእነርሱ ተዋበላቸው።አላህም ከሓዲያን ሕዝቦችን አይመራም።»(አል-ተውባህ፡37) የወራት ብዛት ስንት ነው? ⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕ የተለያዩ የዘመን መቁጠሪያዎች በዓመት ዉስጥ የተለያዩ ብዛት ያላቸው ወራት አላቸው።አብዛኛዎቹ አስራ ሁለት ወራት ሲኖራቸው ከፊሎች ደግሞ ከአስራ ሁለት ወራት በላይ አሏቸው።ለምሳሌ አሁን በኢትዮጵያ በሥራ ላይ ያለው የዓመተ ምህረት(ዓ.ም) እያለ ከክርስቶስ ስቅለት ጋር ምህረት ተገኘ ብሎ የሚቆጥረው የክርስትና የዘመን አቆጣጠር(ጳጉሜን እንደ 13ኛ ወርነት ይቆጥራል)።የሂብሩና የቻይና የዘመን መቁጠሪያም በየተወሰነ ዓመታት 13ኛ ወር በዓመቱ ላይ ይጨምራሉ። የበሃኢ እምነት ተከታዮች የዘመን አቆጣጠር (Bahá'í Calendar) ደግሞ 19 ወራት ሲኖሩት በናይጄሪያ ያለው የኢግቦ የዘመን መቁጠሪያ(Igbo Calendar) አስራ ሦስት ወራት አሉት።ሌሎች ደግሞ ከአስራ ሁለት ወራት ያነሰ ወራት ያሏቸው አሉ። ከዚህ ረገድ ኢስላማዊ ካላንደር በዓመት ዉስጥ ምን ያክል ወራት ይኑረው? የሚለው ጥያቄን አላህ(ሱወ) በምርጫነት ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)፥ ለሰሃቦች ስምምነት(ረዐ) ወይም ሙስሊሞች እንዲወስኑበት ምርጫ አልሰጣቸውም። በቀጥታ ራሱ በቁርኣን ላይ ሰማይና ምድር ከተፈጠሩ እለት አንስቶ አላህ ዘንድ ተቀባይነት ያለው የወራቱ ብዛት አስራ ሁለት መሆናቸውን ግልጽ አደረገ። ከአስራ ሁለቱ መካከልም አራቱ የተከበሩ መሆናቸውንም ጠቀሰ። እንዲህ በማለት፦ إِنَّ عِدَّةَ ٱلشُّهُورِ عِندَ ٱللَّهِ ٱثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِى كِتَـٰبِ ٱللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ ٱلسَّمَـٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ مِنْهَآ أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ذَٰلِكَ ٱلدِّينُ ٱلْقَيِّمُ «የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ዉስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው። ከእነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው።ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው።»(አል-ተውባህ፡36) የቀን፥ ወርና ዓመት አፈጣጠር ❓❓❓❓❓❓❓❓❓ አላህ የፈጠራቸው ፀሐይና ጨረቃን ጨምሮ የተለያዩ አካላት መስመራቸውን ጠብቀው በፍጠረተ ዓለሙ ዉስጥ ይጓዛሉ። አላህ(ከማይገባው ገለጻ ጥራት ይገባውና) በቁርኣን ሌሊትና ቀን ፀሐይና ጨረቃ ሁሉም እርሱ ባስቀመጠላቸው የየራሳቸው ምህዋርን(ፈለክን) ይዘው እንደሚጓዙ እንዲህ በማለት ይገልጽልናል፦ وَهُوَ ٱلَّذِى خَلَقَ ٱلَّيْلَ وَٱلنَّهَارَ وَٱلشَّمْسَ وَٱلْقَمَرَ كُلٌّ فِى فَلَكٍ يَسْبَحُونَ «እርሱም ሌሊትንና ቀንን፥ ፀሐይንና ጨረቃንም የፈጠረ ነው። ሁሉም በፈለካቸው ዉስጥ ይዋኛሉ።»(አል-አንቢያእ፡33) ፀሐይና ጨረቃ ቀንና ሌሊት የተቀመጠላቸው የሚጓዙበትን መስመር ስተው አይጋጩም።አንዱም ከተቀመጠለት መስመርና ፍጥነት ወጥቶ ሌላኛውን አይቀድምም።ሁሉም እንዲዞሩበት አላህ የሰጣቸውን ምህዋራቸው ዉስጥ ይዞራሉ።ይህንኑ አላህ (ሱወ) እንዲህ በማለት ይገልጽልናል፦
167
14
አምልኮን በጊዜ መፈጸም ግዴታ ከሆነ ስለጊዜ በሚገባ መረዳት ግድ ይላል ማለት ነው።ለዚህ እንዲያግዘን አላህ(ሱ.ወ) ቀናችንን በቀንና በምሽት ከፍሏል።ፀሐይንና ጨረቃን ደግሞ የጊዜ አቆጣጠርን አንድንረዳ አድርጎልናል። እንዲህ ይለናል፦ فَالِقُ ٱلْإِصْبَاحِ وَجَعَلَ ٱلَّيْلَ سَكَنًا وَٱلشَّمْسَ وَٱلْقَمَرَ حُسْبَانًا ذَٰلِكَتَقْدِيرُ ٱلْعَزِيزِ ٱلْعَلِيمِ «እርሱ ጎህን(ከሌሊት ጨለማ) ፈልቃቂ ሌሊትንም ማረፊያ ፀሐይንና ጨረቃንም (ለጊዜ) መቁጠሪያ አድራጊ ነው።ይህ የአሸናፊው የዐዋቂው(አላህ) ችሎታ ነው።»(አል-አንዓም፡96) ሐ) አቅጣጫን መረዳት ⇶⇶⇶⇶⇶⇶⇶⇶⇶ ሙስሊሞች በተለያዩ ስፍራና ሀገር ቢኖሩም በአንድ ነብይና ቁርኣን የሚመሩ ዓለም ዓቀፍ አንድ ሕዝብ ናቸው። በየእለቱ ሰላትን ሲሰግዱ የፊታቸውን አቅጣጫ በአቅራቢያቸው ወይም ሰፈራቸው ወዳለ መስጂድ አያዞሩም።ይህ ቢሆን ሁሉም ወደ ሰፈሩና መንደሩ ወዳሉ መስጂዶች አቅጣጫ ዞሮ ስለሚሰግድ የአቅጣጫ፥ የመስመርና የአካሄድ ልዩነት ሊከሰት ይችል ነበር። ኢስላም የአንድነት ሃይማኖት በመሆኑ ሙስሊሞች በጋራም ሆኑ በተናጥል ሰላትን ሲሰግዱ ወደ ተመሳሳይ አቅጣጫ ዞረው መስገድ እንዳለባቸው ደንግጓል። ይህ የአቅጣጫ አንድነት በሕይወት ካሉት ጋር ብቻ ሳይሆን ወደ ቀጣዩ ዓለም ከተሻገሩ የነቢዩ ሙሐመድ(ሰ. ዐ .ወ) ተከታይ ሙስሊሞቸም ጋር ተመሳሳይ ነው። እነርሱም በሕይወት ሳሉ በዚያው አቅጣጫ ሲሰግዱ ነበር።እስከ እለተ ትንሳኤም በየተራ በየዘመናቱ የሚኖሩ ሙስሊሞች በዚያው አቅጣጫ ገና ይሰግዳሉ። መስጂዶችም ሲሰሩ ይህንኑ የሰላት የቂብላ አቅጣጫን ጠብቀው ነው።በመስጂዶች ዉስጥ ሲሰገድም መስጊዱ የትም ይሁን የት የሚሰገድባቸው ወደ ተመሳሳይ የሰላት አቅጣጫ ተኩኖ ነው።ነቢዩ ሙሐመድ(ሰላምና ሰላት በርሳቸው ላይ ይሁንና) ነቢዩ ኢብራሂም ወደ ሰሩት መስጂድ (ካዕባ) ሙስሊሞች ዞረው እንዲሰግዱ መደረጉን ይወዱ ይወዱና ይመኙ ነበር።እየሰገዱም ይህንን ከአላህ ይከጅሉ ነበር።ይህ አላህ(ሱ.ወ) እንዲህ በማለት ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) እና ተከታዮቻቸውን በቁርኣን ያዘዘው ነው፦ قَدْ نَرَىٰ تَقَلُّبَ وَجْهِكَ فِى ٱلسَّمَآءِ فَلَنُوَلِّيَنَّكَ قِبْلَةً تَرْضَىٰهَا فَوَلِّ وَجْهَكَشَطْرَ ٱلْمَسْجِدِ ٱلْحَرَامِ وَحَيْثُ مَا كُنتُمْ فَوَلُّوا۟ وُجُوهَكُمْ شَطْرَهُۥ «የፊትህን ወደ ሰማይ መገላበጥ በእርግጥ እናያለን።ወደ ምትወዳትም ቂብላ እናዞርሃለን።ስለዚህ ፊትህን ወደ ተከበረው መስጊድ(ወደ ካዕባ) አቅጣጫ አዙር።የትም ስፍራ ብትሆኑም(ስትሰግዱ) ፊቶቻችሁን ወደርሱ አቅጣጫ አዙሩ።»(አል-በቀራህ፡144) ሙስሊሞች በመስጊድ ብቻ ሳይሆን የትም ስፍራ በየትኛውም ሰዓት ለጉዞ በወጡበትም ጭምር ሰላት ሲሰግዱ ሁሉም ወደ አንድ አቅጣጫ ዞረው እንዲሰግዱ ነው የታዘዙት።ያም አቅጣጫ ነቢዩ ኢብራሂም(ዐሰ) የገነቡት በመካ የሚገኘው የተከበረውና ወደተከለለው መሰጂድ (መስጂደል ሀራም) ወይም የካዕባ አቅጣጫ ነው። እንዲህ በማለትም ሙሰሊሞችን አዟል፦ وَمِنْ حَيْثُ خَرَجْتَ فَوَلِّ وَجْهَكَ شَطْرَ ٱلْمَسْجِدِ ٱلْحَرَامِ وَحَيْثُ مَا كُنتُمْفَوَلُّوا۟ وُجُوهَكُمْ شَطْرَهُۥ «ከየትም ከወጣህበት ስፍራ ፊትህን ወደ ተከለለው መስጊድ አቅጣጫ አዙር።»(አል-በቀራህ፡150) ሰላትን ለመስገድ ብቻ ሳይሆን በየትም ስፍራና ሁኔታ ስንጓዝ የጉዟችን አቅጣጫን ማወቅ እጅግ ወሳኝ ነው።በተለይ በዚህ ዘመን ኮመፓስ፥ ጂፒኤስና ሌሎች አቅጣጫ ጠቋሚ መሣሪያዎች ባልነበሩበት ጊዜ ሁሉም ሙስሊም በያለበት በቀላሉ የተለያዩ አቅጣጫዎችን የሚያውቅበትን መንገድ መኖሩ እጅግ አስፈላጊ ነው።አላህ(ሱ.ወ) በቀንም ሆነ በጨለማ ዉስጥ፥ በየብስም ሆነ በባህር ጉዞ ላይ ሳለን የምንፈልገውን አቅጣጫ እንድናውቅ ከዋክብትን እንዳገራልን እንዲህ በማለት ይገልጽልናል፦ وَهُوَ ٱلَّذِى جَعَلَ لَكُمُ ٱلنُّجُومَ لِتَهْتَدُوا۟ بِهَا فِى ظُلُمَـٰتِ ٱلْبَرِّ وَٱلْبَحْرِ قَدْفَصَّلْنَا ٱلْـَٔايَـٰتِ لِقَوْمٍ يَعْلَمُونَ «እርሱም ያ ከዋክብትን በየብስና በባሕር ጨለማዎች ዉስጥ በእርሷ ትመሩ ዘንድ ለእናንተ ያደረገ ነው።»(አል-አንዓም፡97) በሌላ ምዕራፍ ላይም በከዋክብት ስለሚመሩ ሰዎች እንዲህ ብሏል፦ وَعَلَـٰمَـٰتٍ وَبِٱلنَّجْمِ هُمْ يَهْتَدُونَ «ምልክቶችንም(አደረገ)።በከዋክብትም እነሱ ይምመራሉ።»(አል-ነሕል፡16) በጥቅሉ ፀሐይ፥ጨረቃና ከዋክብት ጊዜንና አቅጣጫን ከማወቅ ባሻገር ለሰው ልጆች የተለያዩ ጥቅሞች እንዲሰጡ አድርጎ አላህ ለሰው ልጆች አግርቷቸዋል።ስለፀሐይ፥ጨረቃና ከዋክብት እውቀት ያካበተ ሰው የፈጣሪያችንን የአላህን ተዓምራቶችን መረዳት አያዳግተውም። አላህ(ሰዉ) እንዲህ በማለት ይህንኑ ሀሳብ ይጠቅሳል፦ وَسَخَّرَ لَكُمُ ٱلَّيْلَ وَٱلنَّهَارَ وَٱلشَّمْسَ وَٱلْقَمَرَ وَٱلنُّجُومُ مُسَخَّرَٰتٌۢبِأَمْرِهِۦٓ إِنَّ فِى ذَٰلِكَ لَـَٔايَـٰتٍ لِّقَوْمٍ يَعْقِلُونَ «ለእናንተም ሌሊትንና ቀንን፥ ፀሐይንና ጨረቃን፥ ገራላችሁ።ከዋክብትም በፈቃዱ የተገሩ ናቸው።በዚህ ዉስጥ ለሚያውቁ ሕዝቦች በእርግጥ ተዓምራቶች አልሉ።»(አል-ነህል፡12) ቁርኣን ለጊዜ፥ዘመን አቆጣጠር፥ ሒሳብና አቅጣጫን ለማወቅ ሙስሊሞችን ማነሳሳቱ በተለይ ከፀሐይ፥ከጨረቃና ከከዋክበት ጋር አጣምሮ መጥቀሱ ሙስሊሞች ከጊዜ፥ ከዋክብትና ጠፈር ጋር ልዩ ምርምር እንዲያደርጉ ገፊ ምክንያት መሆን ችሏል። ይህም በኢስላማዊ ስልጣኔ ዘመናት ሙስሊሞች ከሌሎች በላቀ ሁኔታ ስለ ስነ-ፈለክ፥ ስለመልከዓ ምድር፥ አቅጣጫዎች፥ ካርታዎች፥ ስለ ፍጠረተ ዓለም፥ ስለ-ሒሳብና ሌሎች በርካታ የሳይንስ ዘርፎች ገንነው መታወቅ ችለዋል።የሰላት ሰዓትን ለሁሉም ሙስሊም ለማሳወቅ የተደረገ ጥረት የጊዜ መቁጠሪያ ሰዓትን ሙስሊሞች እንዲፈጥሩም አድርጓቸዋል።ለአሁኑ በዚሁ ላብቃ። በቀጣይ ክፍል ደግሞ አላህ ካገራልን ስለኢስላማዊ የዘመን አቆጣጠር(የሒጅራ ዘመን አቆጣጠር) አብረን አንመለከታለን።
212
15
«ጨረቃን ታመልካላችሁ እንዴ?» 🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋 በአሕመዲን ጀበል፥ክፍል አንድ ስለኢስላም ያላቸው ግንዛቤ አናሳ የሆኑ አልያም ጥቂትም ቢሆን ለማወቅ ያልሞከሩ አካላት ዘንድ የተለያዩ ብዥታዎች አሉ።ከነኚህ መካከል በፌስቡክ ኮመንት ላይ ከዚህ ቀደም ያነበብኩት «ሙስሊሞች ግን ሁሌ በረመዳን <ጨረቃ ከታየች ረመዳን ነገ ይያዛል።/ረመዳን ከታየች በዓል ነው> የምትሉት ጨረቃን ታመልካላችሁ እንዴ?» የሚለው ተጠቃሽ ነው። ይህን መሰል ብዥታ ለመፈጠሩ አንዱ ምክንያት በአጠቃላይ ስለዘመን መቁጠሪያዎች በተለይም ደግሞ ስለየሙስሊሞች የቀን መቁጠሪያ ግንዛቤ እጦት የሚመነጭ ነው።ሊጠናቀቅ አንድ ቀን ብቻ በቀረው የ1445 ዓመተ ሂጅራ ፍጻሚ ወይም የ1446 ዓመተ ሂጅራ ዋዜማ ላይ ሆኜ ስለዚህ ርዕሰ ጉዳዩ ከሃይማኖቱ ባህሪ ጋር በማያያዝ ጥቂት ማለትን ወደድኩ። ኢስላም ከአላህ ዉጭ ለየትኛውም አካል ሙስሊሞች እንዲሰግዱ ወይም በማንኛውም መልኩ እንዲያመልኩ አይፈቅድም። ፀሐይ፥ጨረቃ፥ ከዋክብት፥ ነቢያት፥ ጻድቃን፥ቅዱሳን፥ አውሊያ፥ ባለአውሊያ፥ ሼህ፥ የአላህ መልዕክተኞች፥ መላዕክት(ገብርኤል፥ሚካኤል፥ወዘተ) ወይም ከአላህ ዉጭ ያለ የትኛውም አካልን ማምለክ በኢስላም ከተግባሩ በጸጸት እስካልተመለሰ ድረስ ግለሰቡ ምህረት የለሽ ከባድ ኃጢአትን በመፈጸሙ ለገሃነም ይዳረጋል። የትኛውም ዓይነት አምልኮ ጨረቃንም ሆነ ፀሐይን እንዲሁም ሌሎች ፍጥረታትን በሙሉ ለፈጠረው አንድ ፈጣሪ አላህ ብቻ የሚገባው። የሚሰገውም ለእርሱ ብቻ ነው። ይህም በበርካታ የቁርኣን ምዕራፍ ተጠቅሷል። ለአብነትም አላህ(ጥራት ይገባውና) እንዲህ ይላል፦ وَمِنْ ءَايَـٰتِهِ ٱلَّيْلُ وَٱلنَّهَارُ وَٱلشَّمْسُ وَٱلْقَمَرُ لَا تَسْجُدُوا۟ لِلشَّمْسِ وَلَالِلْقَمَرِ وَٱسْجُدُوا۟ لِلَّهِ ٱلَّذِى خَلَقَهُنَّ إِن كُنتُمْ إِيَّاهُ تَعْبُدُونَ «ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው። ለፀሐይና ለጨረቃ አትስገዱ።እነርሱን ለፈጠራቸው አላህ ስገዱ። እርሱን ብቻ የምትግገዙ እንደኾናችሁ(ለሌላ አትስገዱ)።»(ፉሲለት፡37) ስሌትና ኢስላም 🎯🎯🎯🎯🎯 ኢስላም በአምስት መሥረቶች ላይ የተገነባ ሃይማኖት ነው። እነርሱም ከአላህ ዉጭ በእውነት የሚመለክ አለመኖሩንና ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ. ዐ .ወ) የአላህ መልዕክተኛ መሆናቸውን መመስከር፥ በቀንና በሌሊት ዉስጥ አምስት ጊዜ ሰላትን መስገድ፥ የረመዳንን ወር መጾም፥መጠኑን ከሞላ ሀብት ላይ ዘካ(ምጽዋት) መስጠት እና በእድሜ ዘመን አንድ ጊዜ ሐጅ ማድረግ የሚሉ ናቸው። ከእነዚህ መካከል የአራቱ አተገባበር የጊዜ፥የዘመን አቆጣጠርን፥የመጠንና የሁኔታዎች ስሌትን የሚጠይቁ ናቸው። ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ በተናጠል እንመልከታቸው። ሀ) ሰላት፦ ሙስሊሞች በ24 ሰዓት ዉስጥ አምስት ጊዜ ወቅቱን ጠብቀው መስገድ ይገባቸዋል።ከሰላት አሰጋገድ ባሻገር በትክክለኛ ሰዓት ለመስገድ የጊዜ አቆጣጠርና በመካ የሚገኘውን መስጂደል ሀራም(ካዕባ) አቅጣጫን(ቂብላን) ማወቅ ይጠበቅባቸዋል። ለ) የረመዳን ጾም፦ የረመዳንን ወር ለመጾ የረመዳን ወር መድረሱን፥ መግባቱንና መች እንደሆነ(ጾም መያዣ ቀን)፥ ወሩ የሚጠናቀቀው በ30 ወይም በ29 ቀናት መሆኑን(የጾም ፍቺ ቀንን) እንዲሁም በየእለቱ የጾም ሰዓታትን ማለትም ጸም መጀመሪያ(ሱህር ማብቂያ/ንጋት) እና ማፍጠሪያ (የፀሐይ መጥለቂያ) ጊዜን ማወቅ ይጠበቃል። ሐ) ዘካ(የግዴታ ምጽዋት)፦ ከምን ዓይነት ንብረቶች ምን ያክል ዘካ እንደሚሰጥ መጠንን፥ ለነማን እንደሚሰጥ(የተቀባዮችን ዓይነትን)፥ መች አንደሚሰጥ ጊዜውን ማወቅና ማስላትን ይጠይቃል። መ) ሐጅ፦ የሐጅ ወር(ዙልሂጃ) ስንተኛው ወር፥ መች እንደሆነና ወሩ መግባቱን ማወቅ፥ የሐጅ ስነ ስርዓት የሚጀመርበትን ቀንና የሚጠናቀቅበትን እለት፥ በየእለቱ ምን ምን ተግባራት በምን ሰዓት እንደሚከናወኑ ማወቅን ይጠይቃል። እነዚህ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች በርካታ ኢስላማዊ የአምልኮ ሂደቶች የጊዜንና የዘመንን፥ የሁኔታንና የስፍራን፥ የመጠንና የደረጃ ሁኔታን ከግምት ማስገባትን የሚጠይቁ አሉ።ይህ በመሆኑ ሙስሊሞች እነዚህን በትክክል ለመረዳትና ለመተግበር የግድ የጊዜ፥የዘመን፥ የአቅጣጫና ሌሎች ስሌቶችን ማወቅ ይጠበቅባቸዋል። ለዚህም ነው አላህ(ሱ.ወ) ትኩረት ሰጥቶ በቁርኣን የጠቀሳቸው። ቀጥለን እነኚሁኑ አብረን እንመልከት። ሀ) ዘመን መቁጠሪያ እና የሒሳብ ስሌት 📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣 ሰከንዶች ተጠራቅመው ደቂቃ፥ ደቂቃዎች ሰዓት፥ ሰዓታት ቀን፥ ቀናት ሳምንታትና ወራት፥ ወራት ዓመት፥ ዓመታት የሰው የሕይወት ዘመን(እድሜ) እና ክፍለ ዘመናት እየሆኑ ጊዜን ይቆጠርባቸዋል።በዚህ መልኩ የሰው ልጅ የዘመን ክፍልፋዮች ወይም ጊዜ ድምር በመሆኑ ለዘመን የተለየ ትኩረት ሊሰጥ ግድ ይለዋል።ምክንያቱን ጊዜን በትክክል መረዳት፥ መለካትና ማስላት ለዚህ ዓለምም ሆነ ለቀጣይ ዓለም ስኬት እጅግ ወሳኝ ነው።ለዚህም ነው አላህ(ሱ.ወ) ስለዘመናት እና ሒሳብ እንድናውቅ የሚፈልገው።ለዚህም ነው በቀን ፀሐይን በምሽት(ሌሊት) ደግሞ ጨረቃን በመለኪያ(መስፈሪያነት) ምልክት እንዳደረገልን የነገረን። እንዲህም ይለናል፦ هُوَ ٱلَّذِى جَعَلَ ٱلشَّمْسَ ضِيَآءً وَٱلْقَمَرَ نُورًا وَقَدَّرَهُۥ مَنَازِلَ لِتَعْلَمُوا۟ عَدَدَٱلسِّنِينَ وَٱلْحِسَابَ «እርሱ ያ ፀሐይን አንጸባራቂ ጨረቃንም አብሪ ያደረገ ነው። የዓመታትን ቁጥርና ሒሳብን ታውቁ ዘንድም ለእርሱ መስፈሪያዎችን የለካ ነው።»(ዩኑስ፡5) በሌላ የቁርኣን ምዕራፍ ላይ ይህንኑ ሀሳብ እንዲህ በማለት ይደግመዋል፦ وَجَعَلْنَا ٱلَّيْلَ وَٱلنَّهَارَ ءَايَتَيْنِ فَمَحَوْنَآ ءَايَةَ ٱلَّيْلِ وَجَعَلْنَآ ءَايَةَ ٱلنَّهَارِمُبْصِرَةً لِّتَبْتَغُوا۟ فَضْلًا مِّن رَّبِّكُمْ وَلِتَعْلَمُوا۟ عَدَدَ ٱلسِّنِينَ وَٱلْحِسَابَ «ሌሊትንና ቀንንም (ለችሎታችን) ምልክቶች አደረግን። የሌሊትንም ምልክትም አበስን። የቀንንም ምልክትም የምታሳይ አደረግን።(ይህም የኾነበት) ከጌታችሁ ትርፍን ልትፈልጉ የዓመታትንም ቁጥርና ሒሳብንም ታውቁ ዘንድ ነው።»(አል-ኢስራእ፡12) ለ) ጊዜን መረዳትና መለካት 🔊🔊🔊🔊🔊🔊🔊🔊 የሰው ሕይወት(እድሜ) ራሱ የጊዜ ድምር በመሆኑ ስኬታማ እንዲሆን ከፈለገ እንቅስቃሴዎቹን በሞላ ከጊዜ ጋር አቆራኝቶና አስማምቶ መጓዝ ግድ ይለዋል።ለዚህም ይመስላል አላህ(ሱ.ወ) ሰላትን በአንድ ጊዜ ላይ ሰብሰብ አድርገን እንድንሰግድ ከማዘዝ ይልቅ በቀን ዉስጥ በተለያዩ አምስት ጊዜያት ከፋፍሎ ጊዜውንም ጠብቀን አንድንሰግድ ግዳጅ ያደረገብን።እያንዳንዱ ሳላት በወቅት የተወሰነ የመስገጃ ጊዜ አለው።አማኞችም ይህንን ተረድተው መተግበር ግዴታ ተደርጎባቸዋል። አላህ(ሱ.ወ) እንዲህ በማለት ይነግረናል፦ إِنَّ ٱلصَّلَوٰةَ كَانَتْ عَلَى ٱلْمُؤْمِنِينَ كِتَـٰبًا مَّوْقُوتًا «ሰላት በምእመናን ላይ በጊዜያት የተወሰነች ግዴታ ናትና።»(አል-ኒሳእ፡103)
304
16
«اللَّهمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ». متفق عليه.
313
17
ነገን በሸህ ሆጀሌ ሰፈር መስጂድ እየተማሩ እየተዝናኑ እየተሸለሙ ያሳልፉ ከልጅ እስከ ትልቅ ወሳኝ የሆነ ፕሮግራም ነው
ነገን በሸህ ሆጀሌ ሰፈር መስጂድ እየተማሩ እየተዝናኑ እየተሸለሙ ያሳልፉ ከልጅ እስከ ትልቅ ወሳኝ የሆነ ፕሮግራም ነው
747
18
በመልካም_ነገር_ከፍታ_ሸህ_ያዕቁብ_ኹጥባ.m4a
435
19
የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ ከሸህ ሆጀሌ ሰፈር መስጂድ
417
20
እነሆ ወሩን ጠብቆ መጣልዎ ተናፋቂው ተወዳጁ ፕሮግራም በተዎዳጁ በአንደበተ ርቱ ኡስታዝ ሙሀመድ ሙስጦፋ እሁድ ሰኔ 23 ቀጠሮዎን ከ4:30 ጀምሮ በሸህ ሆጀሌ ሰፈር መስጂድ ያድርጉ። እየተማሩ እየተሸለ+1
እነሆ ወሩን ጠብቆ መጣልዎ ተናፋቂው ተወዳጁ ፕሮግራም በተዎዳጁ በአንደበተ ርቱ ኡስታዝ ሙሀመድ ሙስጦፋ እሁድ ሰኔ 23 ቀጠሮዎን ከ4:30 ጀምሮ በሸህ ሆጀሌ ሰፈር መስጂድ ያድርጉ። እየተማሩ እየተሸለሙ እውቀትን ይገብዩ ይለዎታል።
705