ስናስብ *አለ አይደል....*
Open in Telegram
ሀሳብ..... የፈለቀኝን እንኩ... ጥሩ... መጥፎ... @hustler4injera @hilyet
Show moreThe country is not specifiedPsychology27 531
487
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from N/a
በልጅነት ጠጠር በልጅነት ሽታ
ስንኞች እናውድ ቤቶችን እንምታ
ከሰገነት ጥሎ ከማዕረግ ቢያጎድፈን
ልጅነት የማንክድ የሜዳ ልጆች ነን!!!
ምን አልባት ወራት አመታት ሊጠብቁህ ከሚችሉ ውስጥ ልሆን እችላለው። የምትመጣ ከሆነ ለመጠበቅ አልሰንፍም። ልክ ፊልም ላይ እንዳሉት ወይም ደሞ እንደሚያስመስሉት ዘመናትም እጠብቅሀለው አልልህም። ግን እንደራሴ አንደምወድህ ሴት የመምጣት ሀሳብ ካለህ እኔም የመጠበቅ ሀሳብ አለኝ ምንልባት ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ወዲያ ወዲያ.....ሰሜቶቼ እውነት መሆናቸውን ለማረጋገጥ ብቻ.....ምናልባትም እድል ከቀናኝ አብሬህ ላረጅ
ልትሸሸኝ ልትርቀኝ ስትል ይታወቀኛል። ቀስ በቀስ አለመኖርህን ልታስለምደኝ ስትሞክር ልቤን ታደክመዋለህ። እኔ እንደማልቀየር እያወኩ ...... አንተም መሞከርህን እንደማታቆም....ለምን እኔም አንተም እንድከም? ለምን የማይሆነውን ለማረግ እንጣር? .......ከአምተ መራቅ ለኔ ቢጠቅመኝ ኖሮ እመነኝ እራሴው አደርገው ነበር ግን እራሴን ከአንተ ጋር ስሆን ይበልጥ እወደዋለው....
ህፃን እያለው ለወንድ የሚያለቅሱ ሴቶች ባየው ቁጥር ብሽቅ እላለው ደካማ ነች ብዬ አስባለው። አሁን ላይ እነዛን ደካሞች እንደምሆን ምንም ታህል አልጠረጠርኩም ነበር። አሁን ላይ ግን ፍቅር ካለስለቀሰ ወዲያው መልሶ በሳቅ ካላፍነከመከ ፍቅር ነው እላለው?
የምትመጣ ከሆነ ለመጠበቅ ጭራሽ አልሰንፍም። ተስፋ....ተስፋ ነው ቀለቤ። ሸኝቼ መጠበቅ ጥንትም የእኔ ነው። በር በሩን ማየት ልማዴ ነው። ይመጣ ይሆን ማለት አዲሴም አይደለም። ስጠብቅ ስጠብቅ የኖረኩ ሰው ነኝ። ታዲያ ምን መሰለህ የጠበኩት ነገር ከቶ መቶ አያውቅም።ከመንገድ ይቅር ጭራሽ መንገድ አልጀመረ ይሆን አለውቅም። እኔ የማውቀው መጠበቄን ብቻ ነው....እኔ የማውቀው በር በሩን ማየት ብቻ ነው.....የታደልኩት ለመጠበቅ ነው
ቀረብሽኝ። ማንም አሳይቶኝ ማያቀውን ፍቅር ፣ ክብር ፣ እንክብካቤ አሳየሽኝ። እና አሁን አፈቅርሻለሁ ማለቴ የቱ ጋ ነው ሀፅያቱ?
ጌታን ጠይቅ
ምን ብዬ
ወደ ወይን የለወጥከውን ውሀ ለምን ከለከልክ? ከውሀው እዳኖን ወይን አረከው፤ እንዳንጠጣው ሀፅያት....
@snasb_hasab
አይገርምም?
እኔው ይሁዳ እኔው እየሱስ መሆኔ
እራሴን ስሜ ስሸጥ
እራሴን ስወጋ ፣እራሴን ሳስለቅስ ፣እራሴኑ ሳብስ
እራሴን ሰቅዬ ስገል
ደሞ ትንሳኤዬ ሲደርስ ስነሳ
በሌላውማ አላሳብብም
ለክቴም ለቡትቱዬም .. ይሁዳውም እየሱሱም እኔው ነኝ።
@snasb_hasab
የአለምን መዞር ብዙ አስተምረውኛል።
እኔን ጥላ እንደሚሆን ግን አልገመትኩም ነበር።
እንደዘገየው ይታወቀኛል። መዘግየቴን ግን አልጠላሁትም። በዝግመቴ መስመር ላይ ብዙ የቀዳሚዎቼን ሬሳ አልፌያለሁ።
ቀባሪና ወሬ ነጋሪ አለመሆን ቢያሳዝንም ሟች ከመሆን ግን አይወዳደርም።
"አለም በዞረች ቁጥር ከዞርክ የአለምን ውበት ቆም ብለህ አትረዳም"
Nawa
@snasb_hasab
ማሬ ማሬ ሲሉሽ አንዳች ነገር አይዋጥልኝም።
እንደ ማር መጣፈጥሽን አልክድም። እንደ ማር ተጣብቆ መቆየትሽን ግን ጥያቄ ምልክት አሸርጠዋለሁ።
ምናልባት የቆየሽ እንደሆነ መምሩን ፈርተሽ ይሆን አቀማምሰሽ ምትሰወሪው?
ማርም እኮ ሲበዛ ይመራል ሲሉ ሰምተሽ...
@snasb_hasab
Repost from N/a
This saying moved me to my core
የለም
አንዳንዴ ከሰዎች የምንለምደው ነገር አለን
ወሬያቸው ፣ ፍቅራቸው ብዙ ብዙ ነገራቸው
What we don't realize በጊዜ ሂደት ለልምዶቹ እስረኛ እንደምንሆን ነው
በፈለጉ ሰአት የሰጡንን ምግብ በመንፈግ ሊያስርቡን የሚችሉበትን ስልጣን እየሰጠናቸው እንዳለን ነው
አንውደድ አላልኩም!
አንላመድ አልወጣኝም!
ግን የገዛ ቀለባችንን እናዘጋጅ የለም ስንቃችን አይለየን አይነት....... ያኔ ምግባቸው ሲኖር ድሎት ሲቀር ደሞ dissert እንጂ main dish አይጎለንም😉
ምን ቃል አለ ሚደረደር
ለአዲስ አመት የሚነገር
የሚቦ'ካ የሚጋገር
እነደው አንድ ብርቅ ነገር
ያልታቀደ ለዘመናት
ያልተፀለየ ለአፅዋማት
ያልተደሰኮረ ለአፅናፋት
ምን ብስራት አለ? ምንስ መዓት
እንዳልተቀበሉት ስመው
አንደማይሸኙት ረግመው
አዲስ ብለው ሸላለሙት
ገርፈው ገፈው ሊያረጉት ሙት
01/01/2015
Nawa
@Snasb_hasab
እኔ
እንቁ ጣጣ ወስዶ እንቁ ጣጣ መላሽ
አመቱ ሲጀመር ዩሀንስ አስነጋሽ
ሳድ'ፍ ኖሬ ኖሬ ጷግሜን የምጠመቅ
ከርችቶቹ እኩል ላሎርድ የምሰበቅ
የተስፋ ድርሳናት የማገለባብጥ
ትላንቴን ከነገ የማገለማምጥ
አሃዱን ለማያልፍ ህልም ለባሽ ቅዠት
ብሩህ ብቻ የማይ አደይ አደይ ምሸት
ይሄ ነው የኔ እውነት
05/13/14
Nawa
@snasb_hasab
የአመት ፌርማታ ዋርካ የቆመባት
ሁሉም ከራሱጋ እንዲወያይባት
ትንፋሽ አሰባስቦ ጉዞን ለመጀመር
ኋላን አመስግኖ ነገን ለመቀመር
መድረሻም እንዲሆነን እንዲሁም መነሻ
ለፀፀት ለቁጭት ጥርስንም መንከሻ
ጣጣን ከእንቁ እያስተባበረ
እንደቀድሞው ሁሉ
ከችቦዎች ቀድሞ አመትን ደመረ
05/13/14
Nawa
@snasb_hasab
Repost from HOME || ቤት 🏚
[አንድ አልቃሻ-ሟች-ጻድቅ ሰውዬ የገጠመው ግጥም]
...
ከዚህ ሲዖል ኑሮ ሞቴ መነጠቀኝ
ጀሊል በእዝነቱ ተጀነት ወፈቀኝ
መኮነኔ ቀርቶ ተቀመጥኩ ተ'ግዜር ቀኝ
[እኔ ግን]
ያልለመድኩት ሲሳይ ደበተኝ ጨነቀኝ
ገነት መሀል ቆሜ ሲዖል ተናፈቀኝ!
...
ከአብርሃም ጉያ ፤ ከእቅፈ-ማርያም
ካማልክቱ እልፍኝ ፤ ከጽርሐ-አርያም
ለሰርክ ዝማሬ መለኮት ፊት መቅረብ
ማሰማት አኰቴት ፤ ተግ የማይል ወረብ
ይሰለቻል እንዴ ልክ እንደ አልቦ ረብ?
ሀሴት ሲበዛበት ልቤ ስለሰጋ
በቃ ሲዖል ልውረድ እምባዬን ፍለጋ!
...
ልብረቅ እንደመብረቅ
ቁልቁል ልወርወረው
አንድ ሌጣ ሆኜ
አለምን ልውረረው
ፅድቄ ይቅርና
ኃጢአቴ ይሰፈር
ልወርወር ከኢዮር
በአምሳለ ሉሲፈር
...
እንደ በልግ አመዳይ
እንደ ክረምቱ ማይ
ሳግ አልባ ዓለም ከማይ
ልወርወር ከሰማይ!
...
ምን ቢስብ፣ ቢያምርበት በሽፋን በገፁም
እምባ የለሽ ገነት ይሆናል ወይ ፍፁም?
[እንጃ]
...
እስኪ ኖህን ጠይቁት። እውነት "ግራህን ለመታህ ቀኝህን ስጠው" የሚለው የፈጣሪ ቃል ይሰራ እንደሆነ። የኖህ ዘመን ተጋሪዎች የተናጋሪውን የፈጣሪን ግራ ሲመቱ ቀኙን ሰቷቸው እንደሆነ ጠይቁት።
ፈጣሪ የሚሰጠው ቀኝ ጉንጭ ፤ የሚያጎነጨው ጭላጭ ይቅርታ እንደሌለው ይነግራችኋል።
ያለቅስ ይሆን ይሆናል እንጂ ፣ እንባ ያዘንብ ይሆን ይሆናል እንጂ ፣ ከምድር ላይ መቺውን ያጥብ ይሆን ይሆናል እንጂ...
ግራውን መተዉት ያተረፉት ሌላ ተመቺ ጉንጭ ሳይሆን ሞት ብቻ ነው ይላቹሀል።
ኖህን ጠይቁት እሱ ያውቃል።
27/12/2014
Nawa
@snasb_hasab
Repost from N/a
Swords That Cut pt.1
Cold, curt text responses / being left on read (abruptly) by someone you love / being misunderstood / criticism on anything you've created / visibly seeing someone lose interest in what you're saying so you cut yourself off / talking and being ignored completely / when you check your phone after a long time only to see nobody has texted / seeing your friends have a good time without you
/ not being invited and included into plans, extra points if it happens in front of you / having a voice that sounds like an apology every time you speak / this voice is small and is an addition to the inferiority complex / when you talk about something you're passionate about and the other person is either indifferent or not as enthusiastic about it as you are
/ when you've just told someone something and they don't react the way you want them to / when someone is texting you quickly because they're busy and you feel like you're bothering them so you want to leave / feeling alone in your intensity
–Christiana
@kkwrites
