ቴዎፍሎሳውያን ሚዲያ | Theophilusian Media
Open in Telegram
ይኽ የመካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የተክለ-ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት የቴሌግራም አውታር ነው፡፡ የተክለ-ቴዎፍሎስ ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ኹኔታዎችን የሚገልጹ መረጃዎችን እንዲኹም ማስታወቂያዎችን በዚኽ ገጽ ለተከታታዮቹ ያደርሳል። Join Us: https://t.me/tekletewoflos https://www.instagram.com/tekletewoflos
Show more1 011
Subscribers
No data24 hours
+37 days
-330 days
Posts Archive
ይዘቱ🌹 የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት ምሥጢር፣ 🌹የእግዚአብሔር አምላክን ዓለምን ካለመኖር ወደ መኖር ማምጣቱ፣ መጋቢነቱ፣ ስለክብርና ልዕልናውና አምልኮአዊ ምሥጋናው ፣ 🌹ስለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነገርና ስለመጽሐፍቅዱስ ምሳሌዎቹ ፣ 🌹ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብርና ታሪክ፣ በቅዱሳን መላእክትና በሰዎች ስለሚደርስላት ምሥጋናና ክብር ፣ 🌹 ነገረ መላእክት ፤ 🌹ነገረመስቀል፤ 🌹ስለብሉይ ኪዳን ነቢያት ና ስለሐዲስ ኪዳን ሐዋርያት፣ ሰማዕታትና ተጋድሎ ልመናቸው አማላጅነታቸው፣ ስለ ሥዩማነ ቤተእግዚአብሔር ካህናት እንዲሁም ስለ ሥነፍጥረት ሁኔታ በጥልቀት ያትታል።
በፍልሰታ ለምን ይደረሳል (ይቆማል)?🌹 በገዳማትና በአንዳንድ ታላላቅ አድባራት ሰዓታት ከዓመት እስከ ዓመት ቋሚ ምሥጋና ነው ፡ 🌹 በልዩ ሁኔታ ግን በፍልሰታ የምናወሳው አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የእመቤታችን ድንቅ ወዳጅ የኾኑ እና በመልአከ ብርሃናት ቅዱስ ዑራኤል አማካኝነት የዕውቀት ጽዋን አስይዛ አጠጥታቸው ከ’ትምህርት አልረዳ’ ከማለት ወደ ታላቅ ሊቅነት የተሸጋገሩት በእመብርሃን ስለኾነ የሚወዷት የሚያፈቅሯት ሽልማት ምን እንደኾነ ምን እንደሚያገኙ ለማስገንዘብ፤ 🌹 እኛም በፍቅር በትሕትና ኾነን ከማያልቀው ክብርና ፍቅሯ በረከት ለመካፈል
አብነት አርኬ'ሃሌሉያ አአትብ ወእትነሣእ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ሠለስተ አስማተ ነሲእየ እትመረጎዝ እመኒ ወደቁ እትነሣእ ወእመኒ ሖርኩ ውስተ ጽልመት እግዚአብሔር ያበርህ ሊተ በእግዚአብሔር ተወከልኩ +++ ቅድመ ዓለም በነበረ ዓለምን አሳልፎ በሚኖር በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አማትቤ እነሳለሁ፡፡፤ የሦስቱንም ስም ይዤ እመረኮዛለሁ፡፡ ብወድቅም እነሳለሁ፡፡ ወደጨለማም ብሄድ እግዚአብሔር ያበራልኛል፡፡ በእግዚአብሔር አምኛለሁና፤ የአባጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እመቤት እመብርሃን በክንፍሽ ጥላ ሰውሪን ።
መልካም የጾመ ማርያም ፍጻሜ
መጽሐፈ ሰዓታት ዘመዓልት ወዘሌሊት
መግቢያ🌹መጽሐፍ፡ ሚለው ጸሐፈ/ጻፈ ካለው ግስ ነቅቶ - በቁሙ መጽሐፍ - ጥራዝ ጽሕፈት ማለት ሲኾን ፤ ሰዓታት ማለት ደግሞ -ሰዓቶች (ሰዓት በብዙ) ማለት ነው። 🌹የዚህ ዘመን የማይሽረው ታላቅ ጣፋጭ ረቂቅ ድንቅና ጥልቅ ኢትዮጵያዊ መጽሐፍ ደራሲ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅር እንደ ደም ምልልስ በሕዋሳችው ተሰራጭቶላቸው፣ አመስግነዋት የማይጠግቡት ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስሟን እንደ እስትንፋስ ከአፋቸው፣ እንደምላስ ከአንደበታቸው የማይለዩት፣ የንጉሥ ወአምላከ ሰማይ ወምድር እናቱ እመቤታችን 5 እና 7 በፍጡር ልቡና የማይታወቁ ልዩ ቃላትና የማያልቅ ጥበብ ገላጭነት ዓለምን የሚያንቀጠቅጡት፤ የነገረ ሃይማኖት ሊቅ፣ ለአንድ ጥያቄ አንድ መጽሐፍ ሚጽፉ፣ የተዋሕዶ መዶሻ የመናፍቃን ጭንቅ፣ የዜማ ሊቁ ድጓን 17 ዓመት ያስተማሩት መልክም ያበጁለት የቅዱስ ያሬድ የልጅ ልጅ፣ የመልክአ መልክ ጠንቃቂው 2500 ቤት ግጥም ለእመብርሃን ክብር በ7ቱ ፊደላት በእያንዳንዱ (ሀ ሁ ሂ ሃ. . .) እስከመጨረሻው (በሕጹጻን ፊደላትም ጭምር በኵ ኲ ኰ ኳ) የደረሱ፣ ከ41 መጽሐፍት በላይ የደረሱት ታላቁ ተጋዳዩ መነኩሴ የእመብርሃን ምርጥ ወዳጅ ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ ቅዱስ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ናቸው። 🌹 ሰዓታት - ስያሜውን የሰጡትም ስለኹለት ምክንያት ነው ፡ 1. እግዚአብሔር በአንድነት ሦስትነቱ 24 ሰዓታት ያለማቋረጥ ሲመሰገን የሚኖር አምላክ በመኾኑና ይህም የሱ ምሥጋና በመኾኑ 2. ካህናት አባቶቻችን በቀንና በሌሊት የሚያመሰግኑበት ምሥጋና ስለኾነ ።
ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል (መዝ. 88፥12)ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ወደ ገለጸበት የደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
በፍልሰታ ለምን ይተረጎማል ?🌹ፍልሰታ (ጾመ ማርያም) ፣ ስለ እመቤታችን ነገር የምናወሳበት ጾም ስለኾነ 🌹በዐቢይ ጾም የጌታን ነገር መዝሙረ ዳዊትን፣ ትምህርተ ኅቡዓትን የመሳሰለውን ሁሉ በመተርጎም ሕማሙን ስቅለቱን ሞቱን እንደምናዘክር፡ በእመቤታችን ጾምም ስለእመቤታችን ለማውሳት 🌹ከማያልቀው ክብርና ፍቅሯ በረከት ለመካፈል
አብነትአንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት። የውሃቱ ለአቤል ዘተቀትለ በዓመጽ ኂሩቱ ለሴት ወምግባራቱ ለኄኖክ .." ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺኘሽ ፤ በግፍ የተገደለ የአቤል የዋህነት፣ የሴት ቸርነት፣ የኄኖክ በጎ ሥራ አንቺ🙏 ።
መልካም ጾመ ማርያም🙏🏽
ቅዳሴ ማርያም🌹ቅዳሴ፡ ሚለው ቀደሰ - አመሰገነ፤ አወደሰ፤ አደነቀ፤ ከፍ ከፍ አደረገ ከሚለው የወጣ ጥሬ ዘር ሲሆን ትርጉሙም ከፍ ያለ ምስጋና ማለት ነው (እንደ ውዳሴ) 🌹ቅዳሴ ማርያም - ማለትም ኅብስቱን ሥጋ አምላክ፤ ወይኑን ደመ መለኮት በማድረግ ሒደት ላይ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የምትመሰገንበት ምስጋናዋ እንደማለት ነው (መቅድመ ትርጓሜው) 🌹የዚህ ዘመን የማይሽረው ታላቅ ጣፋጭ መጽሐፍ ደራሲ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅሯ እንደ ምድር አሸዋ እንደሰማይ ከዋክብት የበዛለት የብህንሳ ሀገር ጳጳስ (ኤጲስ ቆጶስ) አባ ሕርያቆስ ሲሆን ባለመማሩ በብዙዎች ቢናቅም ቢጠላም እንደስሙት ሳይጠላቸው እንደናቁት ሳይንቃቸው በትዕቢት ሳይሆን በትህትና በፍርደኝነት ሳይሆን በጸሎትና በመታዘዝ በያገለግል እመቤታችንም ደግነቱን አይታ በምልጃዋ ተረድታ ምስጢር ተገልጦለት ጎሥዓ ልብየ ብሎ ቅዳሴ ማርያምን ደርሷል።
ይዘቱ🌹ከምንጩ ከአዳም መበደልና ምሕረትን ማግኘት እስከ ምክንያተ ርደት ዘክርስቶስ (የክርስቶስ እኛን ለማዳን የመወረዱ ምክንያት) ማዳኑና የሰጠንን ተስፋ ጭምር ፣ 🌹የእመቤታችንን ክብር ፣ ዘላለማዊ ድንግልና ቅድስናና የማይሻር የማያልፍ የማይጎድል የእናትነት ምልጃ ፣ ክብር ገናናትን 🌹ነገረ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት ሰማዕታትና ጳጳሳት ፣ 🌹ነገረ ሥጋዌ - የክርስቶስን ብሉየ መዋዕልነት (ከዓለም በፊት መኖር፡ ከዓለም በኋላም እስከዘላለም፡ )ዘመን የማይቆጠርለት የነበረ ከእመቤታችን በነሳው ሥጋ ዘመን እንደተቆጠረለት፡ 🌹በብሉይ ና ሐዲስ ኪዳን ሥርዓተ ክህነት እንዲሁም ንዋያት ውስጥ የእመቤታችንን የምሳሌ ፍጽሜ መኾንንን 🌹የብሉይ ኪዳን ጥልቅ ትንቢትና ታሪክ ከክርስቶስና ከእመቤታችን አንጻር
+5
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ (ዶ/ር) ፲፬ኛ ዓመት መታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐት ተካሄደ።
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ (ዶ/ር) ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉበትን ፲፬ኛ ዓመት መታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐት ተካሄደ።
በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በተካሄደው በዚሁ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ እንዲሁም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።
@EOTC TV
በፍልሰታ ለምን ይተረጎማል ?🌹 ፍልሰታ (ጾመ ማርያም) ፣ ስለ እመቤታችን ነገር የምናወሳበት ጾም ስለኾነ 🌹 በዐቢይ ጾም የጌታን ነገር መዝሙረ ዳዊትን፣ ትምህርተ ኅቡዓትን የመሳሰለውን ሁሉ በመተርጎም ሕማሙን ስቅለቱን ሞቱን እንደምናዘክር፡ በእመቤታችን ጾምም ስለእመቤታችን ለማውሳት 🌹 ከማያልቀው ክብርና ፍቅሯ በረከት ለመካፈል
አብነትማርያም ንጽሕት ድንግል ወላዲተ አምላክ ፡ ማዕመንት ሰአሊተ ምሕረት ለውሉደ ሰብእ፡ ሰአሊ ለነ ኀበ ክርስቶስ ወልድኪ፡ ይሥረይ ኃጢአተነ ሰአሊ ለነ ቅድስት ። (ውዳሴ ዘዐርብ) ንጽሕት ድንግል ማርያም አምላክን በመወለድ የታመነች ናት ፡ ለሰው ልጆችም የምሕረት አማላጅ ናት። ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን ዘንድ ወደ ልጅሽ ወደ ክርስቶስ ለምኝልን ቅድስት ሆይ ለምኝልን ። (የዓርብ ውዳሴ ማርያም ) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በማይጠረጠርና ፊት በማይመልሰው የእናትነት ምልጃዋ ጠለ ምሕረቱን ከልጇ ዘንድ ለሁላችን፣ ለሀገራችንም ለሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን ታዝንምልን። መልካም ጾመ ማርያም🙏🏽 #ቴዎፍሎሳውያን_ሚዲያ
ውዳሴ ማርያም በጾመ ፍልሰታ
🌹ውዳሴ፡
ሚለው ወደሰ - አመሰገነ፣ አወደሰ፣ አደነቀ፣ ከፍ ከፍ አደረገ ከሚለው የወጣ ጥሬ ዘር ሲኾም ትርጉሙም ምስጋና ማለት ነው፤
🌹 ውዳሴ ማርያም - ማለትም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሥጋናዋ እንደማለት ነው፤
🌹የዚህ ዘመን የማይሽረው ታላቅ ጣፋጭ መጽሐፍ - ደራሲ 'አቤቱ የጸጋ ማዕበልህን ግታልኝ' እስኪል ድረስ 14ሺህ መጽሐፍትን የደረሰው፣ ፍቅሯ በዝቶለትም ከዚህ ውዳሴዋ (ድርሰት) ሌላ ለእመቤታችን መዝገበ ምሥጢር 3 ሚልየን አንጓ ያለው የግጥም ምሥጋና የደረሰላት የነገረ ሃይማኖት ሊቁ አፈ በረከት ቅዱስ ኤፍሬም ነው፤
ይዘቱ🌹 ከምንጩ ከአዳም መበደልና ምሕረትን ማግኘት እስከ ምክንያተ ርደት ዘክርስቶስ (የክርስቶስ እኛን ለማዳን የመወረዱ ምክንያት) ማዳኑና የሰጠንን ተስፋ ጭምር ፣ 🌹የእመቤታችንን ክብር ፣ ዘላለማዊ ድንግልና ቅድስናና የማይሻር የማያልፍ የማይጎድል የእናትነት ምልጃ ፣ 🌹ነገረ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት ሰማዕታትና ጳጳሳት ፣ 🌹 የእመቤታችን ክብር ገናናትን (ከላይ ካሉት ቅዱሳንና ሰማይ ምድር ነገሥታት ንጽጽርና አንጻር) 🌹ነገረ ሥጋዌ - የክርስቶስን ብሉየ መዋዕልነት (ከዓለም በፊት መኖር፡ ከዓለም በኋላም እስከዘላለም፡ )ዘመን የማይቆጠርለት የነበረ ከእመቤታችን በነሳው ሥጋ ዘመን እንደተቆጠረለት፡ 🌹በብሉይ ና ሐዲስ ኪዳን ሥርዓተ ክህነት እንዲሁም ንዋያት ውስጥ የእመቤታችንን የምሳሌ ፍጽሜ መኾንንን 🌹የብሉይ ኪዳን ጥልቅ ትንቢትና ታሪክ ከክርስቶስና ከእመቤታችን አንጻር
+1
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው እንዲያገለግሉ መደበ።
መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩ ሲሆን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን ዋና ሥራ አስኪያጅነት እንዲያገለግሉ ተመድበዋል ።
መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሀገረ ስብከቱ አደራሽ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ አቀባበል እንደሚደረግላቸው ይጠበቃል ።
Repost from ቴዎፍሎሳውያን ሚዲያ | Theophilusian Media
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የጽንሰት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኍ!!!
በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ከበረና ከፍ ከፍ ወዳለ ጻድቅ ኢያቄም ላከው፤ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ጽንሰቷን እና ልደቷን በእርሷም ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት እና ተድላ ደስታ እንደሚሆን ነገረው።
የተክለ ቴዎፍሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት
On this day, the Lord sent the Archangel Gabriel unto the righteous and exalted Joachim, and Saint Gabriel declared unto him the conception and nativity of the Virgin Mary, who would bring forth the Son of God. Through her, peace and joy shall be granted unto all the earth.
Tekle Theophilus Sunday School
እንኳን አደረሰን አደረሳችኍ!
“ለነገዋ ፡ ቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ ዘመኑን ፡ የቀደሙ ፡ አገልጋዮች ፡ ማፍራት”
ብፁዕ ፡ ወቅዱስ ፡ አቡነ ፡ ቴዎፍሎስ ፡ ፓትርያርክ ፡ ዘኢትዮጵያ
ተክለ ቴዎፍሎስ Telegram
ተክለ ቴዎፍሎስ Instagram
ተክለ ቴዎፍሎስ Facebook
ተክለ ቴዎፍሎስ YouTube
