en
Feedback
Creative G hub

Creative G hub

Open in Telegram
835
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
... ሙና፤ አፈ-ጽባህ ሙና የነብስ አቻ ከዚሁሉ መንገድ ወደ አንቺ ጋር ብቻ? ምነው? በቃ እንደዚህ ልሁን? ሙና እንዲህ ታረጊኝ? .... መና የልጅ አካል ሙና የህጻን ጠረን መጣለሁ ያልሺኝ ቀን እኔና ያቺ ቀን እንዴት ነው ሚጨንቀን። .... ወፌ ላላ ላላ!! እንዴት ሰው ዝም ይላል አንጀቴን ስትበላ .... አወናበደቺኝ አወሳሰበቺኝ እየናፈቀቺኝ። ... ሙና ሙና አንቺ የሥዕል ቤት አንቺ ቀለማም ቃል እውነት ነው ምሰማው መጣለሁ ብለሻል ? ... አትመጪም አውቃለሁ ምድር አትበቃሽም የት አደርግሻለሁ። ... ጥል ጥል አንጠለጠለቺኝ ሙና ቀጠረቺኝ ዛሬን ጠንቅቄ ሳላውቅ ለነገ ኪዳን ሰጠቺኝ ... አወናበደቺኝ አወሳሰበቺኝ ከንበል ፍስስ አልኩኝ አየናፈቀቺኝ። ... ሙና አንቺ እንደመለኮት ለስጋዬ ርቀሽ ለነፍሴ የቀረብሺኝ እንዴት እንዲ አረግሺኝ። ሙና አፈ ፅባህ ሙና የነፍስ አቻ ከዚህ ሁሉ መንገድ ወደ አንቺ ጋ ብቻ ምነው? ... ሙና! የአማልክት ሳቅ አንድ ቃል ተናግረሽ እመጣለሁ ብለሽ ነፍሴን አስጨነቅሻት መንፈሴን። አናጋሽ። ... ሙና አንቺ እንዴት ሆነልሽ? መንገድ ጀመርሽ እንዴ መንገድ አጣሽ እንዴ እኔ ቀልብ ነሳኝ በለጠኝ መውደዴ። ____ [ ምግባር ሲራጅ ] 🖤 @yourpoim @yourpoim

"ባታረሰርሰኝ ፈሰህ ባትደርሰኝ ዝናብ መኾን ባትችል እስቲ ዛፍ ሁን ፍቅሬ እንደው ፍኩ እንደው ለምለም ዛፍ ሁን የኔ ዓለም ። እሱ'ንኳ ቢያቅትህ ሁን ድንጋይ ሁን ኣለት እንደሉል የሚያንጸባርቅ ለጋ ምንጭ የሚዋኝበት እሱም ከቀረ . . . ድንጋይ መኾኑን ልብህ ባይመርጠው ጨረቃ ሁንና በ'ልሜ ተመላለስ ምናቤን ኣስጊጠው ። " ትላለች ኣንዲት ሴት ሚስኪን. . . ኣግዳሚት . . . ኣላፊት . . . እንዳቀረቀረች ቆማ የምትባዝን የልጇ ቀብር ፊት ። [ ሞሃመድ ኢድሪስ ] Translated from : Mahmoud darwish - if you were not the rain, My love

እንደ ፡ ለጋነታችን ፡ ቅጠል ፥ መዳፌን ፡ መስቀለኛ፥ ምታኛ! እውነታችን ፣ እምነታችን ፥ ሳይገነትር ፡ ገር ፡ እንዳለ፣ ልብ ፡ ያበለ! ያልበደለ። አንተን ፡ ለመቅደስ ፡ ያሳጨ ፥ እኔን ፡ ለሹመት ፡ የጠራ፣ ነበራ! በየሜዳ ፣ በየመስኩ ፥ የሚመዘዝ ፡ መታረጃው፣ ምን ፡ አገኘን ፡ ስንሸመግል ፡ ሙቅ ፡ ገላችን ፡ በመብረጃው?! እስቲ ፡ ምኔ ፡ ተጋፋህ ፥ ተአፈር ፡ ብነሳ ፡ ያው ፡ አፈር፣ ለኩርማን ፡ እንጀራዬ ፡ ሞፈር። ደጄ ፡ ብታድር ፡ ማጀቴ ፡ ክፍት ፥ ፍቅር ፡ የምፈተፍት ፡ ለጉርሻ፣ ማን ፡ ፈታብነ ፡ ውሻ?! [ አስካለ ልቅና ] @yourpoim @yourpoim

Repost from አቦል
በምጓዝበት ሀዲድ ለኔ ብቻ የበራች 'ምትመስለኝ ኮከብ ነበረች። እስክነቃ ህልሜን ተንተርሳ የወጣች ጨረቃ አውቃለሁ። አንግታ ምታሰማራኝ ፀሀይ፤በምወደው እንዳልቃጠል ጥላ አጥልቶ የከለለኝን ሰማይ ታድያለሁ። ብርሃናትን ተፈጥሮ ብዬ መጥራቴ  ያራኳቸሁ ያህል እስኪሰማኝ የ'ለት እንጀሮቼ አደረጋቸው። ቀትር'ና ምሽቴን በርተው ደገፏቸው። ከሰው ይልቅ ወገኑኝ፥ወጋገን እፁብ ድንቅ፣ ከጥም አስጣይ ለረሀብ ስንቅ። (ሆኑልኝ)! ተስፋ ሁነው፣ እትብት ሁነው፣ ነገ እንዳለ አበሰሩኝ። ብዙ ብዙ(...) ጣዕም ካለው የህይወት ሽታ እንዳልጎድል ደገፉኝ። (ከእለታት ባለፍኩት ቀን...) ፅልመት ምንድን ብዬ ከሴት ብውል ፍቅራቸውን(ብርሃናትን)ነፈጉኝ። ከኛ'ና ከሷ? ጠየቁኝ! ከኔ ርቄም እስክመለስ ግን ጠበቁኝ። (እንግዲህማ...) እንደ ፍቅር'ና፥ፍቅር መሀል፣ ያስገባኝ ቀን ለምን ይዘን? እኔ'ና እሷስ ምን 'ተረፍን ተያይዘን? (እሷ ብትጎልብኝ...) ከመኖር ቀጂ ጋን አላንስም ባላክል ጥላኝ ሄደች አልገጥም በሴት መሰናክል (ብርሃን ቢጎል...) እንኳንስ የኔ ህይወት ነበረች ምድርም፥ፅልመት የወረሳት በሚል የኦሪት ህግ... ላፍታ አልፅናናም እንኳንስ ልረሳት(ብርሃንን) (ታዲያማ እንዲህ እንዲህ አልኳት...) ብሄድብሽ አትፍረጂ፣ አኗኗር የገባው ቀላጭ እንኳ ይረጋል፣ ቀን ሲጥል እንዲያ ነው፣ ተመራጭን መራጭ ገልብጦ ያደርጋል።   የፈጠረሽ ጌታ.. ቆንጅተሻል ብሎ በስራው ቢረካም፣ አምሳል ቢልሽ ቆንጆ፥መልካም መልከ-መልካም፣ እሱ ልሹ አንድ መልኩን፣ ብርሃን ትቶ ባንቺ አይለካም! ©ናታን ኤርሚያስ Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias

"... (...ምናለበት ልክ እንደከክ ተፈግፍጎ ናፍቆት ቢለቅ ጥፍሬን በላኝ፤ ልብ አጥንቴን ማይታከክ ማንነቴን።) አንድ ቀረሁ። ብቻ ቀረሁ። መቼም... ለቃል ባይመከርም... አንድ ለፅድቅ የሰራሁት ለፍቅሯ ግጥም የፃፍኩት። ??? ሌላው ጎኔ ፀፀት... ሀጥያት ነው.... ያለበት። ታዲያ... (ለስንት ሀዘን... ለስንት እንባ .... ስንት ይቅርታ) " © ምግባር ሲራጅ Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias

አምና የሆነ ቀን ራሱን ሊያጠፋ፣ ከገመድ ሲታገል ከዛፍ ጋ ሲላፋ፣ ድንገት አገኘነው... እረፍ አትሙት አልነው... 'በዚች አፍላ ዘመን በጉብልነትህ፣ የህይወት ጣም ምሬት እንዴት አርጎ ገባህ? አንድ እውነት ስለሰው፣ በህፃንነቱ ይክፋው ወይም ይድላው የጎለመሰ ቀን የልጅነቱ ነው የደስታ መለኪያው' 'መቼ ምን አይተሀል? ከቁመትህ ጋራ ችግርህም ያድድጋል፣' '...ማደግ ማደግ ማለት? ማደግ ከዚ በላይ?' 'አዎ ከዚ በላይ! ምኑ ተገናኝቶ? ቀን የጠመመ ቀን መፅናናት ያማረው የልጅነቱን ነው የሚያወራው ኮርቶ' 'እህ' ብሎን ሄደ 'ቻል' ብለን ሸኜነው፣ ዘንድሮ ባመቱ ሞቱን ተረዳነው! ናሂሊዝም ነገር፣ የኑሮና ሞት ጣም ስለማወዳደር፣ አንብቦ ለማወቅ እድሜው ገና ነበር፣ ለካ ማወቅ ሌላ....መሆን ሌላ ነገር! እርግጥ ይገባናል፣ ካልተካበደለት ካልተጋነነለት ሰው የገዛ ስሙን እስኪረሳ ቢኖር እድሜው ቢረዛዝም፣ የህይወት ታሪኩ ከአንድ ገፅ አያልፍም፣ (ቢሆንም ቢሆንም.....)

አንድ ሁለት ስለ ትምህርት ተማሪ የነበርኩበት ጊዜ ሀገራችን ስውር የሆነ ግን ተጨባጫ transition ላይ የነበረችበት ወቅት ነበረ። እንዴት ማለት ነው? ስራ አለ። ተስፋ አለ። ግን ግን ደግሞ...ስራ እየጠፋ ነው። የሆነ ግራጫ አይነት ስጋት እያጠላ ነው። በጣም የማትፈራው ግን የሆነ ደብዘዝ ያለ ሰቀቀን ግን እየወረረህ ይመጣና በመጨረሻ ተመርቀህ ወጥተህ ትቀጠራለህ ሌላው ይደራጃል ከሁለቱ ከሌለህ ወይ ወደ ገጠር ገብተህ ታርሳህ የከተማ ልጅ ከሆንክ ሰፈርህ ተመልሰህ ድድ ታሰጣለህ። (ሌላም ሌላም ብዙ...) ትምህርት ከሚከበርበት ወደማይከበርበት ከሚያበላበት እድሜህን ወደምትበላበት ደረጃ እየወረደ ነው። ኢንጂነሪንግ ስራ እየጠፋ ነው ሲባል ደንግጠናል። በቃ አሁንማ ዶክተሮች ብቻ ናቸው ስራ ያላቸው ተባለ። የነገሩን ክብደት ለመረዳት ልክ እኛ ከተመረቅን በኋላ በቀጣዩ አመት የተመረቁ ዶክተሮችም ስራ የለም ተብለው ማትሪክ ካስኳረጇቸው ልጆች ጋር ሲቪ መበተን ጀመሩ። (እዚህ ጋር ትራዚሽኑ አልቆ አሁን ያለንበት ሲዝን ይጀምራል) ሶስተኛ አመት ስደርስ ነበረ የሆነ ነገር ገባኝ በትንሹም ቢሆን ምን እንደምፈልግና ምን እንደማልፈልግ አወቅኩ። እንደ እቅድ መመረቂያዬን ድሮን(Drone) መስራት እፈልጋለሁ አልኩና አሰብኩ። ይሄ ማለት እንግዲህ በኛ አቆጣጠር 2007 መሆኑ ነው። ድሮን ብዙም አይታወቅም ነበር ወይም ባህርዳር ብዙ አንሰማም ስለ ድሮን ቴክኖሎጂ። ተመርቄ ሀገሪቱ ላይ የመጀመሪያውን የድሮን ማምረቻ እከፍታለሁ ነበር እቅዴ። ምናልባት በአፍሪካም ቀዳሚ ለመሆን። አምስተኛ አመት ዲፌንስ ስናቀርብ ድሮኑ በረረ ከጣውላና ከምናምን የተገጣጠመው ትንሹ ፕሮጀክት አየር ቀዘፈና አንድ የአካል ክፍል ስለጎደለው( ነገርየው Gyro sensor ይባላል። ስልካችን ላይ አለ። ልክ የመኪና ጌም ስንጫወት መኪናው ወደቀኝ ግራ ሲታጠፍ simulate የሚያደርግልን ሴንሰር ነው ብዙ ጥቅም አለው) ሶስት ጊዜ ያህል ተከሰከሰ። እንደመታደል አብዛኛውን የአካል ክፍል (Airframe structure, propellor, circuit board የመሳሰሉት ዋና ዋና ነገሮች እዚሁ ዲዛይን አደረግኳቸው አመረትኳቸው ተሳካ አየር ኃይል ሁላ ተጠርቼበታለሁ በዚህ ረጅም ታሪክ ነው እዚሁ በቅንፍ ይቋጭ ) ብቻ በረረ። ኢንተርናሽናል ኮንፈረንስ ላይ ቀረበ በቴሌቭዥን ቀረብኩ በሬዲዮ አወሩኝ ከዛ…ከዛ…አሪፍ ፈንድ አገኘሁ ስል…መመረቂያችን ላይ የግቢው አንደኛ ፕሮጀክት የበቆሎ መፈልፈያ የሚባል ሁለተኛ አመት ላይ የሰራነው አይነት ቀልደኛ ማሽን አሸነፈ። ሁለተኛውም ሌላ አይነት የበቆሎ መፈልፈያ ሆነ። ሶስተኛው የጤፍ መዝሪያ። እነ ራዳር ሲስተም እነ ሮቦት እነ ድሮን የመሳሰሉ የኔና የጓደኞቼ ፕሮጀክቶች ውሃ በላቸው። ትምህርት ምን ይሰራል? አፍሪካ ውስጥ ልቆ መታየት አይነት መርህ ያለው የትምህርት ስልት አለን። እኛ ጋርም ተመሳሳይ ነው። ምናልባት የ እንግሊዞቹ ተጽዕኖ ይሁን እንጃ። “አንድ ነገር ገብቶሀል የሚባለው ለህጻን ልጅም ለትልቅ እናትም የሚሆን ማብራሪያ መስጠት ከቻልክ ነው” ይላል አልበርት አይንስታይን። እኛ ሀገር ለፊትለፊቱ ችግራችን የማይሆን ሎጋሪዝም ፈለጥን። ለነፍስም ለስጋም የማይጠቅም ካልኩለስ ፈለጥን። ፋይናል ፈተና ሁለት ጥያቄ ከ 15 ገጽ ጋር ተሰጠን። አስተማሪዎቹም እንዴት እንደሚከብድ አሳመኑን። ትምህርት የሚለካው በክብደቱ ሆነ። ሰሌዳ አራት ቦታ ከፍሎ አንድ ጥያቄ ቀኑን ሙሉ ያስተማረ አስተማሪ አመለክን። መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን የተማርነው ችግር መፍታት ወይም problem solving skill ሳይሆን ችግሩ እንዴት ከባድ እንደሆነ ማድነቅና መደነቅ በችግሩ ፈቺዎች በማሽን ፈጣሪ ፈረንጆች ምጥቀት መመሰጥ ነው። ካስተዋላችሁ ከኛ በፊት በነበረው የ “ምጡቅ አእምሮ ባለቤቶች” generation እከሌ እኮ አበደ ይባልና ምነው ሲባል ትምህርት አብዝቶ ፣ በጣም ያነባል፣ ሰቃይ ስለነበር ምናምን ይሉሀል። ያው ዋቴ ጀነሬሽን ስለሆኑ ነው። ክብደቱን የምንለካው በማስጨለሉ ስለሚመስለን ነው። እና ወደነገሩ ስንመለስ ትምህርት ምን ይሰራል? ለተማረው አእምሮውን ያንቦረቅቃል። ለሀገሪቱ ችግር ይቀርፋል። ሀገር ያሳድጋል። ከዛ የተማረው ሲበዛ ስራ ይፈጠርና ለሚመጡት አዳዲስ ምሩቆች እድል ይፈልጥራል። እንጂ አያሳብድም። አፍሪካን ዞሮ የማየት እድል ያለው ሰው አንድ ነገር መመስከር ይችላል። የምንኖረው ሳናስብ ነው። በዚህ የተነሳ ተመሳሳይ ፕሪሚቲቭ ስልጣኔ ላይ ነን ገና። ለምሳሌ ሁሌ የሚገርመኝ ነገር አለ። ታክሲ የሚለውን ሀሳብ ከየት አመጣነው? የወያላነት ideaን ማን ነው የፈጠረው? “ መገናኛ መገናኛ ሜክሲኮ የሞላ” ምናምን እንዴት አሰብነው? ይደንቀኝ ነበር። ልክ ከኛ የባሱ የድሀ ድሀ west አፍሪካ ሀገሮች ስሄድ ራሱን የታክሲ ሲስተማችንን አየሁት። መርካቶን እንዴት ስንል ፈጠርነው ብዬ ሳልደነቅ በመጠን አነስ ቢሉም የሆነ ደሀ ሀገር ላይ ታገኘዋለህ። ምንም ልዩ ፈጠራ አይደለም። Primitive ነው። ደሞ ወደ ጆሃንስበርግ ዘወር ስትል ይሄ የለም። ሰልጠን ስትል ትጥለዋለህ። አልሰለጠንም። ገና ነን። በዘንድሮ አመት ይሄ ሁሉ ተማሪ ወደቀ ሲባል እኔም ቤት አንድ ተፈታኝ ስለነበር ጉዳዩ ቀጥታ ተመልክቶኝ ነበረ። ፊታችን ያለው እውነታ ይሄ ነው። የትምህርት መንገዳችን መስተካከል አለበት አዎ ልክ ነው ብዙ ያስብላል ይሄ። እውነታው ግን ትምህርት ላይ Fail አድርገናል። ፕሪሚቲቭ ነን። ይሄን እንመን መጀመሪያ። ዝቅተኛ ክፍያ ያለበት ሴከተር ነው። ያልተማሩ ሰዎች የሚበዙበት ሴክተር ነው። እውነታው ይሄ ነው። በዚህ መንገድ ታናሽ ወንድሜ ዩኒቨርሲቲ እንዲማር አልፈልግም በኔ ዘመን የጀመረ ጠይም ኪሳራ አሁን ወንድሜን እንዲያጠለሽ አልፈቅድም። እኛ ተስፋ በቆረጥንበት ስርዓት ደግሞ ማንንም አልወቅስም። የወደቀው ሲስተሙ እንጂ ተማሪው አይደለም። አዲሱ ትውልድ ኑሮውን figure out እንዲያደርግ ትልቅ እድል ነው እንደውም። ቦብ ዲለን “ when got nothing u got nothing to lose” እንዲል ይሄ አሪፍ አጋጣሚ ነው። እንደዚህ ከምንም የምትጀምርበት አጋጣሚ ራስህን ሳይቀር design የምታደርግበት ነው። እና አሁንም እላለሁ። ያልጠፋብንን X አንፈልግም። ልጅነታችሁን የሆኑ ሰዎች የሰሩትን አካዳሚክ ዲዛይን በመከተል አትገብሩ። ቢሰራ ለኛ ትውልድ ይሰራ ነበር። መውጫዬን የአለቃ እስጢፋኖስ ኢዮብን(Steve Jobs) አባባል ላስገባ "your time is limited, don't waste it by living someone else's life"

#እቀናለሁ . . . "ናፍቀኸኛል ስትይ፤ ከፀሃይ ብርሃን ከነፋስ ቀድሜ፣ በመናፈቅሽ ልክ፤ በማመዛዝናት በዚች ኢምንት እድሜ። በርሬ የምመጣው፤ ከንፌ የምመጣው፤ ለሳቅሽ ብዬ እንጂ ላይንሽ እፅብ ቀለም፣ "ተው አብቃኝ" ተስዬ፤ አንገትሽ ሾር ላለች የኔ "አንቺ"ን ዓለም። አይደለም እይደለም፤ አይደለም ለማየት፤ ላንቺ ያጎበደደን አለቃና ምንዝር፣ አይደለም ለመስማት፤ ከሎሌ እስከ ጌታ ያፍቃሪሽ ሰም ዝርዝር። አትንገሪኝ በቃ!!!! "ናልኝ" ባለኝ አፍሽ፤ ስታሚልኝ አዳም እውነት ያናድዳል፣ የጠበቀ ተስፋም፤ ሳቅ እንደናፈቀው በቅናት ይናዳል። እሰይ ደግ አደረኩ!! እኔን እስኪገርመኝ እቀናለሁ ገና፣ ወዶ አለመናፈቅ፤ አፍቅሮ አለመቅናት አይቻልምና።        ✍ ዓቢይ ( @abiye12 ) Join & share 👇👇👇👇 @hasabawian @hasabawian @hasabawian

ኑሮ ሲጥለን - ገጥሞን እጅ በ'ጅ አሜንታ ላይቀል - ለምንታም ላይበጅ ሕይወት እንደ ሰው - መች ትታማለች ሥጋ ደህና አይደል - ነፍስም ታማለች ሞት ቆሞ በሩቅ - ሲል እንቁልልጭ ኩታ ደርቦ - የሚያብለጨልጭ አዘጋኝ ጠፍቶ - እፍኝ ጠመዡን ማልቀስ ተረፈን - እያስጎመዡን ግን ማልቀስ ከንቱ.. እምባውን ይዞ - ስንቱ አነጅቧል? ይህ ግጥም እንኳ - በእምባ ታጅቧል ግን መች ተውቧል? መቼ ተውቧል - የኑሮ ማጀት በቃ እጣችን ነው - ሕመም ማቆንጀት? ሳይነጉ መምሸት - ሳያድጉ ማርጀት? በዘበት ማለፍ - እንደዳከሩ ክረምቱስ አልፏል - የታል መከሩ? ባከነች ነፍሴ ዘጋኝ በዛባት ባይኖሯት እፊያ ምን አደከማት? - ኩርፊያና ልፊያ! ነፍሴን ሸክፏት - አካሌን ቋጥሩት ንብረቱን ይውሰድ - እግዜርን ጥሩት እግዜርን ጥሩት - እንድታገለው ነገን ና በሉት - ይምጣ እንድገለው በቃ አይግደደኝ - ስለሕልሞቼ ሊገሉን ሲሹ - ላሸንፍ ሞቼ! ሁሉንም ወድዶ ሁሉንም አጥቶ እንዴት ይኮናል?! እንዲህ ላለው ጣር - እግዜር ልኮናል! እግዜር ልኮናል - ኩታ እንባ አልብሶ ሞት ምን ቢከፋ ያስለቅሰናል ከሕይወት ብሶ? ብቻ ደክሞናል! ብቻ አሞናል! ባንቀምሰው እንኳን - መሞት ጥሞናል! [ ዮናታን ጌታቸው ] @yourpoim @yourpoim

ቃላት 10 | Words | ኪናዊ መጽሔት https://t.me/Words2014 . . ለአስተያየታችሁ :‑ words5102@gmail.com 📝Soon—Qalat as a Newsletter

Repost from አቦል
እናቴ እኔን አራስ ሁና የተነሳችውን ፎቶ አጋጣሚ አይቼው ይቺን ፃፍኩኝ(ልደቴ ሁኖም አይደለም)! አፍላነቷ ላይ የተባእት ነፍስ ስር አስነቀለች ሲመስለኝ ደሞ ወደድኩሽ ሲሏት የሴት ወግ ኑሯት ትንሽ ስቃለች! ይህ ሳይታያት አቅሏን ጥላ ጠቃሽ ሲገጥማት ስትወድ ስጠላ ወንድ ሳቅ መሃል ያጣችው ኩራት ስለደብራት የምወድላት አስተዋይ ልቧን ከ'ኔ በቀደም ጎረምሳ ሰብሯት እንደሆን ፤ ጊዜ ይቁጠርላት! ወዲህ ደግሞ እኔ . . . የተሸነፈ ፤ ያንዲት እናት ልብ መስኮት ማህጸኗ የባለ ዕምባ እዳ ፣ ከፋይ ህጻኗ! ወንድ ሸላዩን እንዳስለቀሰች አንደ'ዜ ብቻ ሳለቅስ ስቃለች ይቺን አቂሜ እንዳልበድላት የሳቀችብኝ ስወለድላት! ©ናታን ኤርሚያስ Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias

photo content
+1

repost ከቃልህ ውስጥ ነው የደበቅካት ወስደህ የፀበሌን እቃ ከመኖር ጭቅቅት ከሰብ-ነት እድፍ ነፍሴ የምትፀዳው መፅሀፍህ ሲገለጥ ሲቆረስ ከስጋህ :: አጥምቀኝ ላጥምቅህ እግርህን ልሳመው በእንባ ያጠበህ ነው ከአይንህ 'ሚሞላ ሚዛን 'ሚጥለው:: ልረዳህ ላንብብህ እንደ እጆቼ መዳፍ ሀጥያት ባይሆንብኝ:: ፅድቅህ ቢገዝፍብኝ ቋንቋህ ቢረቅብኝ ያንዠረገግኩትን ቁሻሻ ሰው-ነት እርቃኔን አይቼ እንዳልሰወርህ ከክብርህ ለክቼ ከመራቄ በፊት ቤትህ ከመቅረቴ ከወገሩኝ መሀል ራስክን ለይተህ ድምፅህን አሰማኝ ልጅነቴን አይተህ:: ፍቅር ሞኝ አይደለ?? ግዙፍ ማንነትን እንደ ውሀ አሟምቶ ያለሰልስ የለ?? ያንተ አለትነት በሀጥያቴ ፍም ቀልጦ ውህደትክን ለይቶ ቅድስናህ ወልቆ ይታየኝ ያንተ ገፅ ኮስማና እኔነቴ መልኬን ይመስለኛል ሰው-ነትህን ሳይ አብ-ነትክን 'ርቄ:: አጥምደኝ ልሰገር ከመረብህ ልግባ አንድ ወር በማይሞላ የሸጥኩት ጌታ አለኝ ከመንጎቹ መሀል እርቄ ብሄድም እኔን ሚከተለኝ:: 'ምትዳክረውን ባልተከፈለ ባህር ሙሴዋችክን ንቃ መርምራት ሀሳቤን ከነአለማወቋ:: ደካማ ውላጅክ መሆኗን ሳትረሳ ያስፈራሩበትን የፍርድህን ጅራፍ በ'ጅህ ሳታነሳ:: ቀድሳት እርስቴን ትባረክ መቅደሴ ትርሳ ዝሙቶቿን ትሞላ ቅዳሴ አንተ ስታያት ነው ወይን የምትሞላ ውሀ እንስራነቴ:: አትግዘፍ ላይኖቼ በህግ' ልክ አልይህ አባትነትህ ውስጥ ይታይ እኔነትህ የኔ-ቢጤ-ነትህ ከበራፌ አትቁም ይብቃ ማንኳኳትህ ከነእድፌ እቀፈኝ ፍቅርህ ይግባ ቤቴ ሰው-ነትክን ሳይ ነው ሰው ምሆን እራሴ:: [ ፍቅራዲስ ሶሎሞን ] @yourpoim @yourpoim

Repost from አቦል
ስዒርናዮም አንበርኪኽናዮም         (አሸነፍናቸው አንበረከክናቸው) በፅዮን ማሪያም ቅዳሴ ፣ ነጠላ አገልድመው ወደ አድባራቸው በሚተሙ ምዕመናን እንደነጋ ለወፎቹ ይበሰራል እንጂ የናይት ኤንጅልን ዝማሬ ሰምቶ የሚነቃ የለም! የእጅ ሰዓቴን አየሁት ከጠዋቱ 1:40 ይላል። ቀኑ እሁድ እንደመሆኑ ነጭ የለበሱ ምዕመናንን ማየት የሚጠበቅ ነበር። ቁርስ ልበላ ከአንዱ በረንዳ ጠጋ አልኩኝ ደስ የምትል አስተናጋጅ ታዘዘችኝ። ጨዋታ ልፈጥር ብሞክርም የአክሱም ልጆች ፊት በቀላሉ አይፈታም መሰል ሳትስቅልኝ ትዕዛዜን ተቀብላኝ ሄደች።  የነበርኩበት ቦታ መሄድ ከምፈልገው ቦታ ትንሽ ራቅ ስለሚል ለ ጓደኛዬ ደውዬ የት እንዳለ ጠይቄው እዳጋ ሓሙስ  እያለ የሚጣራ ባጃጅ ተሳፈርኩ። ጓደኛዬንም ረዘም ካለ ጊዜ ቡሀላ አገኘሁት። የስራ ቦታው ወሰደኝ። በሁለት እግሩ ለመቆም እየተንገዳገደ እንዳለ እሁድን መስራቱ መሰከረልኝ። በተናጥል ስላሳለፍናቸው ቀናት ብዙ አወራን፤ ሳይታወቀን የምሳ ሰዓት አልፎ ነበር። ምሳ ሊጋብዘኝ የሆነ ቦታ ይዞኝ ገባ። ቤቱ ለኔ አዲስ አልነበረም። ድሮለታ ጠጠር መጣያ ያልነበረው ቤት አስር የማንሞላ ሰዎች ብቻ ነበርንበት። ገራፊ ያጣ ክራር' ካልተቃኘ ማሲንቆ ጋር ግድግዳው ላይ ቅኔ ይዘርፉበታል።  ለየት ያረገው ነገር ቅኔያቸው በየልቡ መለያየቱ ነው። እኔን እንዲህ ነበር የተሰማኝ....      ከሞት ብለን ገለን መጣን መንገድ ሰርተን መሄጃ አጣን! ከዚህ ስሜት መለሾ ስል የጓደኛዬ አፍ ማይኮ የሚባል የከተማው ተራራ ላይ ጣለኝ! እዛ ምን ነበር ብዬ ጠየኩት የነገረኝ ነገርም  ሳይጨምር ሳይቀንስ ይሄ ነው፤ ትግራይ ውስጥ TDF የሚባለው መዋቅር ከመፈጠሩ በፊት የሻዕቢያ ወታደሮች ሽረ ፣አክሱም ፣ አድዋ'ና አዲግራት ከተሞችን ተቆጣጠሩ። በወቅቱ የነበረው የአከባቢው ሚሊሻ'ና ፖሊስ መንገስት መሳሪያ የሚያስቀምጥበትን መጋዘን ክፍቱን ጥለው ሸሹ። ይሄንን ያየው የአከባቢው ወጣትም መጋዘኑ ያለበት በመሄድ ቃታ መሳብ የሚችለውም የማይችለውም መሳሪያ ወስዶ ማይኮ የሚባለው ተራራ ላይ ወጥቶ ያገኙትን የሻዕቢያ ሰራዊት አጠቁ። ይሄን ጊዜ ሻዕቢያ አብዛኛው ሀይሉ አድዋ ስለነበር ወታደሮቹን ከአድዋ አምጥቶ ውጭ ላይ ያገኘውን ወጣት ፣ በመስኮት የሚያየውን ኗሪ አንድ ላይ ጨፈጨፈ። የሟቾች ቁጥር ከ ሰባት መቶ በላይ እንደሆነም ነገረኝ። ሾለ Axum massacre የጦርነቱ ጊዜ ተፅፎ የነበረውን ከእማኝ በመስማቴ እውነታነቱን ደመደምኩ። ማኅበረ ዴጎ ላይ የነበረውን ሰቆቃ አነሳልኝ  ጨዋታችን በብዙ ቀጠለ። ምሳ ከበላንበት ቤት ወጥተን እያዘገምን ዳእሮ ፒያሳ ደርሰናል። ቦታው ለከተማው አድባር ነው። ከፊት ለፊት ማርያም ፅዮን አለች። የምናልፍባቸው ቤቶች የጥንት ከመሆናቸው የተነሳ እድሜዬን ብነግራቸው ስቀውብኝ ይፈርሳሉ ። እነሱ እንዳለቁ አርባእተ ንሽሀ ቤተክርስቲያንን ጓደኛዬ እየተሳለመ የኔ አይኖች ግን ከዳእሮ ኢላ በላይ ወዳሉት ሰፈሮች አማትረው ነበር። ሰፈሩ ዜሮ ሽሙንተ ይባላል የስዋ(ጠላ) ሰፈር ሲሆን ለመለያ ይመስል ኒኬል ቆብ ያረገ ቀጭን ዱላ በየበረንዳው ተተክሏል። ላፍታ አይኔን ነቀል አድርጌ አቅጣጫ ቀየርን። የንጉስ ባዜል መቃብር ያለበት ጋር ስለደረስን ከቦታው ጋር የተያያዘች የሆነች አክሱማዊ አባባል አለች ብሎ ጀባ አለኝ... ዝዘገነውን ሓዚኑ ዘይዝገነውን ሓዚኑ የዘገነም አዘነ ያልዘገነም አዘነ እንደማለት ነው። ሰዓቴን ሳይ እየመሸ ስለነበር ወደ አድዋ መመለሾ እንዳለብኝ ነገርኩት። ባጃጅ ጠርቶ መሄድ ጀመርን ሀሳቤ ግን ስላሳለፉት ወረራ'ና ዝርፊያ ፣ ስላዩት ጭካኔ'ና ስለተነፈጉት ምሕረት ነበር። ኳስ ላይ የማውቃትን ስድብ ለበደለኞቹ እንዲህ ብዬ በልቤ አደረስኩ። What do you think of Shabia ? Shit. What do you think of shit? Shabia. That's aright! በእርግጥ ወያኔም ብስብስ ነው! ©ናታን_ኤርሚያስ Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias

📌 ቃላት መጽሔት ቅጽ 10 . 👋ሰላም የቃላት መጽሔት ቤተሰብ እንዴት ናችሁ? “ቃላት ቅጽ 10”ን ወደ እናንተ ለማድረስ ዝግጅታችንን እያጠናቀቅን እንገኛለን። በዚህኛው ክፍል ብርቱ ተጋባዥ ጸሐፍት ተቀላቅለውናል። የደከሙበትን የሥነ ጽሑፍ ሥራ ለመጽሔቱ በማበርከት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርገውልናል። ከወዲሁ ስለተሳትፏቸው እናመሰግናለን። . ቃላት ቅጽ ዐሥር በቅርቡ ወደ እናንተ ይደርሳል። እስከዚያው ድረስ እንደ መቆያ የቃላት ዲጂታል መጽሔት አዘጋጆች ከ “Meet your podcasters” መርሐግብር አዘጋጅ በኃይሉ ተስፋሁን ጋር ያደረጉትን ቆይታ እንድትመለከቱ እንጋብዛለን ! 📎 https://youtu.be/CeLFLbfmgfU?si=DKPXUnXQ-2NwIPME

የብዕር አሟሟት ሌላ! የቃል-ልሳን ቅመሙ የባለቅኔ ቀለሙ ነጠበ እንጂ ፈሰሰ አንበል፣ ቢዘነበል እንኳ ደሙ ሰከነ እንጂ ከሰለ አንበል፣ ቢከሰከስ እንኳን አፅሙ የቃል እሳት ነበልባሉ አልባከነምና ውሉ የዘር-ንድፉ የፊደሉ ቢሞት እንኳን ሞተ አትበሉ፡፡ እስካልተዳፈነ ፍሙ እስካልተሰበረ ቅስሙ እስካልተቀበረ ስሙ የደራሲ ዐፅመ-ወዙ፣ የብዕር ቀስተ-መቅረዙ ህዋሳቱ እስልቀዘዙ አልፏልና ከስጋ ሞት፣ በቃለ ሚጠት ስልባቦት በፊደል አድማሰ-ፍኖት፣ በህብረ ቀለሙ ማኅቶት በስነ-ግጥሙ ምትሃት፣ በግሱ ንጥረ-ልሳናት፣ በነባቢቱ ነፍስ እሳት ይነዝራልና ደም-ስሩ፣ አይሞትምና ፀዳሉ ቢሞት እንኳ ሞተ አትበሉ … [ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ] @yourpoim @yourpoim

ስበር መጣሁ … ሳላድር አንቺን ብዬ አንቺን ብቻ … የሕይወት ጣዕም ፤ መሃዛ … መንደሪን … መንደሪን … የኔ መንደሪን ለምልክት ... አደይ ጸጉሯ መሀል ሰክታለች ( ጠይም ምልክት መሆን አቃተው? ) እውነት እውነት ትሸታለች። እንዳልነካት ... ከጢስ ይሳሳል ጸጉሯ እንዳልርቃት ... ከሞት ይቀርባል ፍቅሯ ግራ እንደገባኝ ፤ እንደተመሳጠረብኝ ነገሯ ለሰው ላወራ አስብና ... ፉጨት ይሆንብኛል ቃሌ ፤ ( ጥላሁንን አፏጫለሁ ... እንደማይሰለቻት ታውቀዋለች ዐይኔ 'ን ... ) ልጽፍላት አስብና ይሳቅብኛል ቃሌ ( አንቺሆዬ እስቃለሁ ... አምባሰል እስቃለሁ ) ( ህልምን ከዕውን ያልለየሁ እኔ ። ፍጡርን ከፈጣሪ ድንበር ያላካለልኩ እኔ። እኔ … ስል ማንን እንደምል ያልለየሁ እኔ ... እሰቃያለሁ። ) የእውነት አትመስለኝም መኖሬን ታስጠረጥረኛለች። ነጠላዋ ከገላዋ እንዴት ተቀመጠ? ነበልባል ናት። እንዴት ደመራ ሳባት? ( አበራ ... አበራ ... መስቀል አበራ ) እንደጊዜ ከስር ከስሯ እከተላታለሁ። ወደየት ይሆን የምትሄደው? ( ሥዕል በደመራው ጢስ ይሳላል ... ) ኢየሱስ ከፊት መስቀል ይዞ ... እሷ ... ነጠላ አቅፏት ስትከተለው ... እኔ ... በነጠላ የሚያስቀና የፍቅር መስቀል በልቤ ይዤ ከኋላቸው ... ከንፈሯን እንደንጋት ቀስ አድርጋ ትገልጣለች ( መዘመሯን ማመን አልፈልግም። ገና ተዘምሮላት መች አበቃና ... ) እጆቿን ከነጠላዋ ውስጥ ቀስ አድርጋ አወጣች። ( እንዲህም ያለ ዳንስ የለ ... እንደ አበባ ፍካት ያለ ነገር ... ) ዕንባ ዐይኖቼን ሞላ። መዳፎቿን አሳሳመች አጨብጭባ ነው? ባርካ? ብቻ ... አሜን! ( አበራ ... አበራ ... መስቀል አበራ ) ቆማለች። እኔ ግን መከተሌን አላቆምኩም ... ነዶ በሚከስም እሳት ፊት የማትጠፋ ፋኖስ። እሷ ደመራ ታያለች እኔ እሷን አያለሁ መንገዷ ወደ ገነት ነው። ሌላው ሌላው ቢቀር ... ተከትያት ገነት ገባለሁ ድንቅ ናት ... ( አበራ ... አበራ ... መስቀል አበራ ) @yourpoim @yourpoim

የሐሙስ ዘፈን ሙና ነይ ሰውነት ሙና ነይ ሴትነት መልክ እንደ ታቀፈች ፣ ወንድ እንደ ሰለቻት ማልቀስ አልቻለችም ፣ መሳቅ አይመቻት ኑ እናልቅስ ለሸጋ ኑ እናልቅስ ለ ፀይም ስትሳለም እንጂ ፣ ስትወድ አትታይም አታምንም አታምርም « የጫካ ፅጌ ናት » አጀብ ከ ወጀብ ጋር ያመላልሳታል ያም አቅፎ ያም ስሞ ፣ ያቆሳስላታል ያም አቅፎ ያም ስሞ ፣ ዕድሜ ነሽ ይላታል ዕድሜ ነሽ የከንፈር ዕድሜ ነሽ የ ዕምባ ናና ፣ ናና እናቱ ፣ ናና ፣ ናና አበባ ዕድሜ ነሽ ይላታል ፣ ዕድሜ ነሽ የልኬት ቢ'ኖር ይታጣል ወይ ፣ የ እሷን ታህል ደስታ የእሷን ታህል ስሜት የሐሙስ ዘፈን እኑር አንሙት ፣ እንሳቅ እናንባ ጊዜ ያብሰዋል ፣ የሴትን ለቅሶ የሴትን ዕንባ @yourpoim @yourpoim

ጀርባዋን በጅራፍ ደረቷን በብረት ልቧን በሰው «ወገል» ፣ እንደ ጉድ ገረፏት ፣ በእሳት ለበለቧት ፣ እሳት አሳቀፏት ፣ . አቅፋ ትስቃለች መሬቱን ታያለች ሰማዮን ታያለች . የሆነ ዘመን ላይ ምን እንደነበረች እንዴት እንደኖረች ማስታወስ ያምራታል ፣ ወዲያው ይከፋታል ። ወዲያው ያስጠላታል ። . ጀርባዋን ሰጥታቸው ጅራፉን ሰጥታቸው ግረፉኝ ትላለች ፣ በሚችሉት መጠን ፣ እንባዋ ጎርፍ ሁኖ ፣ መንገድ እስኪሰጠን ። . ወዲያው ይገርፏታል ይደበድቧታል ደም ውሃ እስኪመስል ፣ እስኪ'ቀይር መልኩን ፣ ገራፊው አያውቅም ፣ ያለፈ ታሪኳን ፣ ያለፈ ታሪኩን ። . እየደበደቧት እየቀጠቀጧት እሷ ትስቃለች ፣ ስቃይ ያላቀፈው መኖር እንደማይችል ፣ አውቃለሁ ታውቃለች ። . ደስታ ያው ደስታ ነው ፣ ስስ ነው ግራ ጎኑ ፣ ሁሌም አይገባውም እንባ ከጥርስ ጋር ፣ እንባ ከዘፈን ጋር ፣ ስለመጎንጎኑ ። . የሃዘን ሚሥጥር ነው ሁሉም አሪፍ ዜማ ሁሉም አሪፍ ዘፈን ፣ ጤናዋን ይውሰዱት ፣ ሕመሟ ይትረፈን ። [ ሰሎሞን ሽፈራው ታገል ] @yourpoim @yourpoim