cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

አቦል

https://t.me/nathanErmias በዚህ አድራሻ አስተያየትዎን ሊያደርሱኝ ይችላሉ! @UniqueDy

Show more
Advertising posts
592
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1530 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailableShow in Telegram
#ሙት_ገላሽ_ነኝ_እኔ !!! . . . ፍቅረ ፅላት ለማደሪያው ከህብረ ዕፅ እንደ ግራር፣ በነፍሱ ልክ ለቀመሰ ጣፋጭ ቢሉሽ ልክ እንደ ማር። አሰማምሮ አበጃጅቶ እግዜር ቤቱን ቀማመረሽ፣ "ሴት" የመሆን ረቂቅ ጥበብ ታድኚኝ ዘንድ ገድሎ ማረሽ። አንቺ የልጅ ነፍስ !!! በበዓሉ በሰንበት ቀን ማን ሸለመሽ ልብ እንደ እናት፣ ከየትኛው ደብር ይሆን የተማርሽው "አጀብ" ፅናት። ያደማሁት ምስኪን ልብሽ ሳይሽርለት ትኩስ ህመም፣ እንዴት ያለ ከፍታ ነው የበደለኩሽ እኔን ማርመም። አፅም አካሌን ስትዳብሺኝ፤ ቃል ወልጄ ከሙት ገላ እንዲህ ብዬ አልጠይቅም፣ አፌ እንደሆን ተለጉሟል አልፏል በቃ ቃል አያውቅም። ብቻ አንቺ በምታውቂው "የኔ ፍቅር ይቅር" ስልሽ፣ በይ ስሚልኝ ድኩም ቃሌን ይቅር በይኝ እንደ ልብሽ። ይቅር በይኝ እንደ ልብሽ፤ ይቅር በይኝ እንደ ፍቅርሽ ሩቅ አይደለም የኔ መሻት፣ በመዓዛሽ አከላቴን በነካ እጅሽ ነፍሴን ዳብሻት። ✍ ዓቢይ ( @abiye12 ) Join & share 👇👇👇👇 @hasabawian @hasabawian @hasabawian
Show all...
3
[ The Disappointment Series - 7 ] (Idiotic Experiment ፩ - ስድ ግጥም እንደ ደብዳቤ) ... ስትመጣ መሻሽቶ ነበር ቀን ጠልቆ ከፀሐይ ጋራ ናት ብዬ የእግዜር እንግዳ ታዛዬን ከ'ሷው ልጋራ እልፍኜኝ ለሰው የማልከፍት የማልቀል ለመወዳጀት እሷ ግን ባንዳች ትንግርቷ ዘለቀች ከልቤ ማጀት ፀሎቴን በእምባ ለውሳ ወደአምላክ አሳረገችው ቦግ አለች በድቅድቄ ላይ ሌሊቴን ቀን አረገችው እምባዬን እያበስኩባት - ሳቅ ሆናኝ ከልቤ ሳቅኳት በሥጋ አልደረስኩባት - በነፍሴ ነፍሷን አወቅኳት! [ ውብስ ነበር አመጣጧ - አስደንቆኝ ነበር እንደመልአክ በብርሃን መንቆጥቆጧ - ድንቅ ነበረች ልጅት ትንግርታዊ ክሱት - መስሎኝ ነበር እኔስ የተገፋው ልቤን አማልክት ሊክሱት - የተዘጋው በሬ ሳይከፈት ገባች - በሀሴት ልንዘምር በደስታ ልንንቧች - ትንሿ ጎጆ ውስጥ ሀገር እየሰራን - ውበት እየዘራን - በቁልምጫ ቃላት እየተጠራራን - ሕያው ነፍሳችንን በፍቅር አጠራን - አላስፈራኝም ነበር ዙፋን ሆኜላት በኔ ላይ መቀመጧ - ኋላ ሊከፋ አቀጣጧ - ውብስ ነበር አመጣጧ! ] ... ሳይማልድ ማለዳው፣ ከቀን ቀድማ ነቅታ የሳቋን ማሚቶ፤ የእምባዋን ሕቅታ ቧልትና ተረኳን፣ ስላቅና ምፀት የኩርፊያዋን ለዛ፣ የሳጓንም ድምፀት የአንገቷን ሥር ጠረን፣ የገላዋን ሽታ ግለት፣ ትኩሷቷን፤ ሳልና እንጥሽታ ሁሉንም ሸክፋ፤ በመውደዷ አዋዝታ አንዳችም ሳታስቀር እንዲሆን ትዝታ ከትራሴ ለቅማ የፀጉሯ ዘለላን ከመንገድ ልትኖር ሄደች እንደዘላን! [ ስትሄጂ ኮቴም የለሽ እንዴ? እንዲያው ጭልጥ፣ እንዲያው ጥፍት ባንዴ? ሰው ያስባልም አይባል? ወንድ ልጅም እኮ ይባባል! ቡራቄ ዛሬም ያምርሻል፣ አልሻረልሽም እንዴ ልጅነት? ሁሉን ይቅርና አይከበርም ወይ ወዳጅነት? እንዲህ ትርቂያለሽ ብሎ መች ያውቃል ልቤ ጠርጥሮስ - ሰበርሽኝ እንደአልባስጥሮስ - እንደው ለእኔ ባታዝኚ አታዝኚም አቅፎሽ ለነበረው ክንዴ? ስትሄጂ ኮቴም የለሽ እንዴ? ] ... ሕልም ነበረች ወይ ቅዥት ነበረች ወይ ስነቃ ያጣኋት? ሚራዥ ነበረች ወይ ጉምስ ነበረች ወይ በእውን ያላየኋት? ምነው ከመምጣቷ መሄዷ ቀደመ? ሽፋሽፍቶቼ ላይ እምባ ተጋደመ ቄስ አይደለሁ አቡን አልጠራት ገዝ'ቼ ሰው 'ንጂ አይደለች ቁስ አልወርሳት ገዝቼ ልኑር እንጂ እየጋትኩ የትዝታን እንገር በረረች ወፊቱ ሄደች ሳትናገር ከንፋስ ጋር እልም ከመንገድ ጋር እብስ ትዝታን ትታልኝ ከፍቅሯ የሚብስ! [ አልዋሽሽም የሔድሽብኝ ቀን አዘንኩ - ፍቅርሽን ፍለጋ በየመንገድ ባዘንኩ - አነባሁ ከሰው ተደብቄ - አለቀስኩ አንጀት ሰብቄ - የወንድነትን ወግ ያፈረስኩ መሰለኝ - እምባ ፊቴን ሳይሆን ልቤን አቆሰለኝ - ትምክቴ ትንፋሽ አሳጣኝ፣ አፈነኝ የልቤ ኩራት - አንድም መያዝ በልምምጫ፣ አንድም መልቀቅ የፍቅሬን በኩራት - ዋልኩና በፍቅርሽ ሚዛን ቀልዬ ልገኝ ተመዘንኩ - አልዋሽሽም የሔድሽብኝ ቀን አዘንኩ! ] ... አንዳንዴ ካሳብ ይመጥቃል አይገባም ፍቅር ስሌቱ ለብቻ ጧቱ ብራ አይሆን ካንቺ ጋር አይጨልም ሌቱ ቢደርብ ልቤ ላይሞቀው ሸማውን ይዘመዝማል ካንቺ ጋር ቅርብ ያልኩት መንገድ ብቻዬን ስሆን ይረዝማል አብሬሽ በእምባዬ እንዳልሳቅኩ ሳቅ መሀል እምባዬ አጠበኝ እያለሽ የሰፋን ጎጆ ብቻዬን ስሆን ጠበበኝ! [ ሰላም ለኪ ላንቺ በምትኖሪበት - በሰማይ ርቀት ወይ በምድር ቅርበት - ከወዳጅሽ ጋራ ለደመቀው ፍቅር - አበባ ነው እንጂ ደንጋይ አልደነቅር - ታነቢው አታነቢው አላውቅም ይሄን እንኳን ሙንጨራ - ምናልባት እራሴን እየጎዳኹ ነው ካራ እንዳወጣችው ዶሮ መሬቱን ጭራ ጭራ - ግን ይኼም አይገደኝ - መላው ዓለም ይቅርና አንዱ ልብሽም አልወደደኝ - ወንድ እኮ ነኝ ያባቴ ልጅ በሞቴ እንኳን የማሸንፍ - ባልድን እንኳ ካንቺ ውጋት እያነከስኩ የምከንፍ - አንድ ቀን አይቀርም መብረሬ ተላቅቄ ከፍቅርሽ ስበት - እስከዚያው ግን ሰላም ለኪ ላንቺ በምትኖሪበት! ] ፨ ፨ ፨ ©Yonathan Getachew Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias
Show all...
#ይድረስ_ለተከፋች_ሴት . . ይኸውልሽ የኔ አይናማ፤ አንዴ ብቻ እኔን ስሚኝ አታለቃቅሺ እርሺው እንባሽን፤ ሰው ከመሆንሽ ሳትሸራርፊ እጥፍ ውደጂው ያስለቀሰሽን። ልብሽን በእምነት አፅኚው የዛሬ ቀንሽም ያልፋል፣ ችግርሽ ምን ቢደራረብ በእግዜር እጆች ይገፋል። የምታምኚው አምላክሽ እኮ፤ ከሞት መንጋጋም ነፍስ ያስተርፋል። "ተሳሳትኩ " ?? አልተሳሳትኩም !!!!! የተስፋ መሃረብ ይዘሽ ትኩስ እንባሽን በይ አደራርቂው፣ መደነቃቀፍ ብርታት ከሆነ ገፊሽን ሁሉ ወደሽ መርቂው። ወርቅን እራሱ፤ "ወርቅ ሆነ" እንዲባል የተጋጋመ እሳት በልቶታል፣ ታድያ አምላክሽ ይመካብሽ ዘንድ ሺ ቢፈትንሽ ክፋቱ የታል ???? "እኔ አልታየኝም"። . . እናምልሽ ውድ ዓለሜ መፈተንሽን እንዳትጠዪው፣ ይልቅናሽስ ፈገግ ብለሽ "ፈጣሪዬ ሆይ ተመስገን" በይው።   ✍ ዓቢይ ( @abiye12 ) Join & share 👇👇👇👇 @hasabawian @hasabawian @hasabawian
Show all...
#ጅብ_የገራው_ወደል . . በነጭ በጥበብ አምሮ እንደተዋበ፣ እንደ ጦር አበጋዝ ምርኮ እንደታጀበ። እኔ ዕርም ለበረት እንብዛም ነኝ ጋጣ፣ ወይ በቅሎ ላሰግር ከመስኩም አልወጣ። ግና አምና ለታ፤ ማን አስቶኝ እንጃ ወይ ተልኮብኝ ፍርጃ፣ በወርሃ መጋቢት በዕለተ ተክልዬ፣ ሰይጣን ዘውዱን ሊጭን እኔ ደብሬን ጥዬ። መሃል ሜዳ ብገኝ ስንኩል ቀን ቢያቀብጠኝ፣ ሀገር ያስቸገረ የወደ'ለ አህያ ስስ ጎኔን ረገጠኝ። አቤት አቤት አቤት !!! አቤት አቤት አቤት !!! እንደምን ነረተው የልቤን ስር ስሩ፣ ጅብ የገራው ወደል፤ ሆዱ ከጠገበ መች ልክ ያውቃል እግሩ። ይላል አከላቴ፤ ይላል ሰውነቴ፤ ተረግጦ ተድጦ ደካክሞ ሲያበቃ፣ ወትሮስ የእግዜር ድሃ፤ ከፈጠረው በቀር መች አለው ጠበቃ። እናም አትጨነቅ፤ ኮቴህ እስኪታክተው፤ ዝም ብለህ 'ርገጥ ለምን ብለህ አታስብ፣ ለድፍን ሸሆናህ፤ እኛን የመሰለ ድኩም አካል ሰብስብ። ፀሃይ ስትወጣ ግን፤ ይቺን ቃል አትርሳት። የአካሌ ላይ ሰንበር አይቀርም ይፈርዳል፣ የቀለብከው መንጋም፤ እንደ እፉኝት ፍቅር አንተን በልቶህ ይሄዳል። ምን አካሉ ቢገዝፍ፤ ቢቦርቅ አህያ ቢያካልለው መስኩን፣ በሳቅ የታጀበ፤ ጅብ ጥርሱን ሲሞርድ አውቀዋለሁ ልኩን።            ✍  ዓቢይ ( @abiye12 ) Join & share 👇👇👇👇 @hasabawian @hasabawian @hasabawian
Show all...
#የድሃ_ሰው_ፀሎት . . በአየር ሰረገላ ጉም ደመና ጭኖ፣ መብረቅያ ታጠቆ ስግምታ ተክኖ። "ሀምሌ ነሀሴ መጣ ስሩ ደነደነ፣ የምበላው የለኝ ቤቴ አልተከደነ።" አንተ ሁሉን ገዢ የተፈጥሮ ጌታ፣ ድዊ የምትፈውስ ታሳሪ የምትፈታ። ህልሜን እየረታሁ እንድረሳው ቀኔ፣ የማነሳት አካል የምላት ወገኔ። ላክልኝ አንድ እሷን ልቤን ታሳርፈው፣ ጠራርጎኝ እንዲሄድ ወይ ዶፉን አጉርፈው። ብዬ ያልኩህ ለታ፤ ለደጅህ ባይደርስም የሌጣ ፀሎቴ፣ እራስ ያህል ሸንፈት ቢያህልም ውድቀቴ። 'ባክህ አትዘንብኝ አይክፋህ እግዜሩ፣ ቢያሳሳኝ ውሽንፍር ቢያደክመኝ ነው ቁሩ።              ✍ ዓቢይ ( @abiye12 ) Join & share 👇👇👇👇 @hasabawian @hasabawian @hasabawian
Show all...
'ውበቲክ ዲስኦርደር' (የእታች ሰፈሯ ልጅ በሽታ) ___ 1. የታች ሰፈሯ ልጅኮ አደገች። አማረባት። ቆነጀች። መስከረምን ተከትሎ ዳገትና ተራራን እንደሚወርሰው አደይ አበባ... ውበት ወረራት። ሸተተች፥ እንደአልባብ። አወደች እንደአልባስጥሮስ። 19 ዓመቷ። ቁንጅናዋ እንደኤርታሌ ተንተከተከ። አረማመዷ ፈር ያዘ። ተፈጥሮ ገራት። ይህ ብቻ? አይደለም። ስርዓት እጇን ያዛት። ትህትና ፈሰሰባት... ክብር ስጋዋ ላይ አረበበ... 2. ደነገጡ!! እነማን? የላይ ሰፈር ልጆች ናቸዋ! እነሊሊ እነኮኪ... ፥ የውበትን ወንዝ በዱቄትና በዊግ ጠልፈው ወደቤታቸው ያስገቡት። ምነው እንደውም እነቲቲ...? ወንዱን በፈርጣማ ጭናቸው የ'ገብር' አዋጅ ያወጡበት... እነሱ... ቁንጅናዋ ሰፈራቸው ላይ ሲያስገመግም ፥ ሰልፉ እንደተነካ የቁጫጭ መንጋ ተተረማመሱ...  ተደነባበሩ...። እውነት አላቸው።  ወንዱ ሁሉ ስጦታና ልቡን ይዞ ወደታች ሰፈር ወረደ... ወደእርሷ። 2.2 ተማከሩባት!! "ስሟ ይጥፋ" “አባቷኮ አይታወቅም”አሉ ... ያን ምስኪን ጥሩምባ ነፊ። ህዝቡ ወደቀብር የሚተመው፣ ድንኳን የሚተክለው በእሱ ድምፅ ነውና አልተሳካም። “እናቷ ሴተኛ አዳሪ ነች” አሉ... ሰፈሬው የሴትዮይቱን ሽልጦ ከጨዋ እጇ እየተቀበለ ልጆቹን አሳድጓልና ፥  ጆሮውን ዘጋባቸው። 2.3 ይሄኔ አንዷ ጎበዝ ተነሳች። “ውበቷን ለመቀማት ስለምን ትታገላላችሁ?” “እናስ  ምን ይበጀን?” “ባለችበት ውበቷን ትርሳው ።  ትናቀው። የተረሳ እርሻ አረም ይወርሰው የለምን? አረሟን ሰብል ነው ትበል። ሰብሏን እንደአረም እየነቀለች ወደእኛ ትወርውረው።” “እንዴት?” “ምን እንዴት አለው? ውበት እንጂ ልምድ የላትም። የያዝሽው ነገር በሽታ ነው እንበላት። መድሀኒቱ መሬት ነው ካልናት አላማዋ መውደቅ ይሆናል።” ሀዲዱን ለኛ ተዉት አለች ቻይና። ስብሰባው በዚህ ተዘጋ። 3. ሀኪም መጣ። “በሽታ አለብሽ” አላት። “የምን በሽታ?” ደነገጠች። ዶፍተርዬ መነፅሩን አስተካከለ። ጉሮሮውን ጠራረገ። “’ውበቲክ ዲስኦርደር’ ይባላል።” “ምልክቶቹስ?” “ልብን በትህትና ያቅለሸልሻል። ጭንን ከመልካም ነፋስ ይጋርዳል። ከንፈርን ከደጀሰላም ፥ ጉልበትን ከቤተ-መቅደስ እየወሰደ ያላትማል። ዐይንን ወረቀት ላይ አፍዝዞ ያስቀራል። ጀርባሽ ላይ ስርዓት የሚባል ሽፍታ ወጥቶብሻል። ታፋሽ ሥር ድንግልና የሚባል እጢ አለ። እሱን እናነሳልሻለን።” “የቱ ጋር?" ብላ እጇን ስትሰድ "እኔን አዳምጪኝ አሁን!" ብሎ ሀኪሙ አንባረቀባት። ሀኪምን ይፈሯልና ፥ ያምኗልና... እጇን ሰበሰበች። መድሀኒቱስ? ውሀና አፈር አዘዘላት። የጭቃ አልጋ ያዘች። 3.1 ታሪኩን ቶሎ እንዝጋው (ለምን ቢሉ ፤ በሽታው ጥልቀት አይወድምና። 'ውበቲክ ዲስኦርደር' አጉል ሲመራመሩት ያሳብዳል አሉ።) ፈጣሪ የመስገን!!! ታድያ ዛሬ ዛሬ... ልጅት ተፈውሳ... ጠዋት ተነስታ... ዊጓን ሰክታ... ማድያቷን ቀብታ... ፓንት የሚበልጠውን ሚጢጢ ቀሚስ ታፋዋ ላይ ትታ... አባት የሌለውን ልጇን ለእናቷ ጥላ... ቦርሳዋን አንጠልጥላ...ልትወጣ ስትል ትፀልያለች። ለእሷ አይደለም... ከበሽታዋ የገላገሏትን ደጋግ ወዳጆቿን ፈጣሪ እንዲጠብቅላት እንጂ። Michael minasse Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias
Show all...
ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያው የተጀመረ challenge አለ #ግብረ_ሰዶሞችን_እቃወማለሁ የሚል! ይሄ ነገር የእያንዳንዷን በር ስለሚያንኳኳ አይመለከተኝም ማለት ዘበት ነው። ከዚህ በፊት እንደ sense of humer ተጠቅሜው ጓደኞቼ ኸረ ተው እስኪሉኝ ድረስ እንጨት እንጨት የሚሉ ቀልዶችን ቀልጄበታለሁ አሁን ላይ በዛ ጉዳይ ፊት መስጠት መዘዝ እንጂ ቀልድ እንደማይፈጥር ስለገባኝ የማውቀውን መረጃ በዝርዝር የመናገር ውዴታ ላይ ነኝ። Vent የተባለ የቴሌግራም bot አለ እናም እዛ ላይ የደበራቸውን'ና የቸገራቸውን share አድርገው experience ካደረገ ሰው እንደ ምክርም፣እንደ መልስ የሚያገኙበት site ነው። አሁን ላይ በብዛት በሚባል መልኩ የሚጠይቁት ጥያቄ የተመሳሳይ ፆታ አፋቃሪ መሆናቸውን በመንገር ጓደኛዬ እንዲህ አረገበኝ፣እንዲህ አደረኩበት ምን ይሻላል አይነት ነገር ነው even ከዚህ ነገር መውጣት እፈልጋለሁ የሚል vent አጋጥሞኝም አይቼም አላውቅም። ጭራሹን የት እንደተገናኙ የት እንደሚማሩ mention ሲያረጉ ከምማርበት ቦታ ጋር ሲገጣጠም ሚሰማኝን ስሜት፣ወጣ ያለ ባህሪ ያላቸውን ወንድ'ና ሴቶች ሳይ የኔን reaction አለመደበቅ አልችልም። ከአለባበሳቸው፣ከአኳሃን፣ከአነጋገር፣ከአረማመዳቸው አንፃር መገመት የምችልበት ደረጃ ላይ ነኝ። ፨ እዚሁ የ Facebook platform ላይ ደሞ የሆነ dawid beloved የሚል አካውንት ይሄንን ፅሁፍ አጋርቶ አየሁ (የተቆረጠ ነው ሙሉውን comment ላይ ታገኙታላችሁ) “ወንድሜ የእኔ ተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪ መሆን ተፈጥሮዬ ነው። መርጬ ያመጣውት ማንነት አይደለም። አንተ ግን እኔን ከዚህ ማንነቴ የተነሳ መጥላትህ እና ልትጎዳኝ መነሳትህ ተፈጥሯዊ አይደለም። ስለዚህ ንግግህ እና ድርጊትህ በማስተዋል ይሁን። እውነት አንተ የክርስቶስ ተከታይ ነህ? ክርስቶስ ባንተ ቦታ ቢሆን ይህን አሳብ በእኔ ላይ ያስባል? ክርስቶስ ባንተ ቦታ ቢሆን ይህን ያደርግብኛል? ይጠላኛል?___ያሳድደኛል? ይደበድበኛል?___ያሳስረኛል? 'እገድልሃለው!' ብሎስ ይዝትብኛል? እና አንተ የክርስቶስ ተከታይ ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ ክርስቲያን ነኝ ባይ ይህን አሳብ እኔ ላይ ልታስብ እንዴት ቻልክ? የእኔ ማፍቀር ወይስ ያንተ ነፍስ ማጥፋት ፤ የትኛው ነው በእርግጥስ የሶዶም ስራ? የማንኛችን ስራ ይሆን እግዚአብሔርን የሚያስከፋው? መልሱን 'እኔ' ለምትለው አንተ እና ለሕሊናህ” ይላል የልጁ ፅሁፍ በአጭሩ! ይሄንን ከስር ያለውን ፅሁፍ ፣ note ላይ ፅፌ ካስቀመጥኩት ቆይቻለሁ may be አሁናዊ ስለሆነ ነው ያጋራሁት ከተማው አቅራቢያ ባለ ትልቅ ተቋም ውስጥ “ይመችሽ” የተባለ Community አለ። እዛው ጊቢ በሚማሩ'ና በከተማው ባሉ ወጣት ሴቶች የሚዘየር። እዛ ጊቢ እየተማረ ጭራሽ ስለዚህ ነገር ሰምተው የማያውቁ፣የሚያውቁትም የሴት ልጅ supportive group አድርገው ከመቁጠር የዘለለ ስለዛ community idea የላቸውም። ነገር ግን ከጀርባ የሚሰሩት የተመሳሳይ ፆታን supportive ነው። በሚገርም መልኩ የcommunityው አባላት ሴቶች ብቻ አይደሉም ብዙ ወንዶችም ይገኙበታል። እነሱን ለመቀላቀል የፈለገ በሴት 50 ብር፣በወንድ 1000 ብር ነው የአባልነት መመዝገቢያው። celebrity የምንላቸው tiktokers coffe time ከ'ነሱ ጋር ያሳልፋሉ። እዛ member ነኝ የሚል ሰው ወይ lgbt ነው ወይም fan ነው. I don't want to mention እነሱን አሁን ላይ። በአጠቃላይ ከምናስበው በላይ lgbt ሀገራችን ውስጥ እንቅስቃሴ አላቸው። እዚሁ መዲናችን ውስጥ ውስጥ የት ሰፈር ምን እንደሚካሄድ ሀገር ያወቀው ነው። ለእኔ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት normal ሁኖም አያውቅም፣ሊሆንም አይችልም። አጥብቄ እፀየፋለሁ አጥብቄም አወግዛለሁ። ሼር አረጉት #ግብረሰዶምን_እፀየፋለሁ #ትውልድ_ይዳን Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias
Show all...
ትላንት ከደንበኞቼ መሀል አንዱ "ጎበዝ ጠበቃ ጠቁመኝ" ሲለኝ ካሉኝ ብዙ ጠበቃ ጓደኞች መካከል "ሥራ ቀዝቅዟል፣ ሥራ ላክልኝ" ስላለኝና በሥራም ጎበዝ ስለሆነ፣ የጠበቃ እንዳሻውን ስልክ ሰጠሁት። ዛሬ በጠዋቱ ደውሎ "ምን አይነት እብድ ነው የላክብኝ?!መጫወቻ መሰልኩህ?" ብሎ ጮኸብኝ - ጠበቃ እንዳሻው። "ምን አጠፋሁ? ሥራ ላክልኝ አልከኝ፣ ላኩልህ!" "ሰውዬውን በደንብ ታውቀዋለህ?!" "የሶስት ዓመት ደንበኛዬ ነው፣ እብድ እንዳልሆነ አውቃለሁ። ቆይ ምን አድርጎህ ነው?" "የሆነ ሰው ልከስስ ነው ብሎ የክሱን ጭብጥ እንዳለ ዘርዝሮ ነገረኝ፤ እህ ብዬ ሰማሁት" "እሺ..." "የክሱን ጭብጥ ዘርዝሮ ሲጨርስ 'እና በእዚህ ጉዳይ ላይ ክስ ብንመሰርት የምናሸንፍ ይመስልሀል?!" ሲል ጠየቀኝ። "ምኑ ላይ ነው ታዲያ ጥፋቱ?!" "አትቸኩል! እንደምናሸንፍ በጣም እርግጠኛ ነኝ ብዬ ያለ የሌለ የህግ አንቀጽ ጠቅሼ ነገርኩት፤ ይሁንና እየደጋገመ 'እርግጠኛ ነህ እናሸንፋለን?!' ሲል ጠየቀኝ። 'ማንኛውም ይሄ ጉዳይ የቀረበለት ችሎት ሁለቴ እንኳ ማሰብ ሳያስፈልገው ይፈርድልናል፣ የተሟላ ማስረጃ ያለው ጉዳይ እኮ ነው? እንደምናሸንፍ 100% እርግጠኛ ነኝ' አልኩት።" "እሺ ከእዛስ?..." "...ከእዛማ ለጥቂት ደቂቃዎች የቀረበለትን ቡና በጸጥታ ሲጠጣ ከቆየ በኋላ...'እንደዛ ከሆነ ነገውኑ ሽማግሌ ልኬ መታረቅ ይኖርብኛል!' አለኝ" "እንዴ??? ክሱን በእርግጠኝነት እንደሚረታ እየነገርከው የምን ሽምግሌ መላክ ነው?" - ስል ጠየቅሁት። "እኔም ይሄንኑ ጥያቄ ነበር የጠየቅኩት!" "እና ምን መለሰልህ?" "ተከሳሹ እኔ ነኝ፣ ጉዳዩን በሙሉ ገልብጬ ነው የነገርኩህ!' ብሎኝ የጠጣነውን ቡና ከፍሎ በቅጡ እንኳ ሳያመሰግነኝ ጥሎኝ ሄደ! ወይኔ እንዳሻው! የማንም መጫወቻ ልሁን?!' Tilahun girma Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias
Show all...
Repost from Creative G hub
Photo unavailableShow in Telegram
እማ ወዲያ ዳሩን እየሳቅሽ ያለፍሽው ፣ ለ ህይወት አይበቃም ( ትንሽ ያ'ደይሽታ ) ትንሽ የቡና ጣዕም ካላጎናጸፉት አውቆ የተኛ እድሜ ፣ በ እግዜር ጥሪ አይነቃም። እማ ወዲያ ዳሩን "አንድ" ያልሽውን ህመም ፣ አልፏል አትቁጠሪው ይልቅ ከ ደጃፍሽ ሲጣራ የከረመ ፣ እግዜርሽን ጥሪው አሁን ናርዶስ ናርዶስ አሁን አደስ አደስ ፣ ይላል ያንገት ሽታሽ ያለሱ ለሳቅሽው ፣ ለዚያ መከራ ቀን... በይ እግዚአብሔር ይፍታሽ እኔን ለ ትላንትሽ
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
Here is the poem I mentioned
Show all...