en
Feedback
Creative G hub

Creative G hub

Open in Telegram
835
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
አረም ነኝ አዝመራ መሃል ስፈጠረ ገለባ መዛኝ ወደሽኝ ሰው አድርገሽኝ ፤ መሃላሽ ነፍሴን የገዛኝ አረም ነኝ ደበሎ ለባሽ ፍጥረቴ ካዘነ ጎጃም ማርያምን ማዕተብሽን እንጂ ልደሰት መሳቅ አላሻም እንበላ የተከልሽው ዳስ ዘፋኝም አልቃሽ ያለበት ለኖረ አርባ ተደርሶ ለሞተ ተዘፈነበት እንበላ ህልም እልም እንጂ አልቆየን አልኖርነው ነገር ብናምር ብንስቅ  ኖሮ እንደ ሰው እንኖር ነበር ። አንገትሽ የቀይ ዳማ በ'ያ ላይ እናቱ ስማ ያወዛች ያጊያጌጠችው የነካሽ እንዲጣፍጠው ገላሽን ከማር ሰራችው ።    .. ይገፋል የጎጃም እጁ ይንጣል የጎጃም እጅ ተገፍቶ ተገፍቶም እርጎ ተንጦም አይብ እንዲያበጅ ወንድምሽ ቁመተ ሎጋ በ'ያ ላይ ጥርሰ በረዶ ቀረ እንጂ እሱም እንደሰው የዘመን አሟሟት ለምዶ እንኳን ወንድምሽ ጥይት ያለው ሰው እንኳን ወንድምሽ ትጥቅ ያላነሰው ምድረ ጎጃሜ ሆዱን ሲብሰው እሳት አይደል ወይ የሚተኩሰው ምነ' ሃገሩ ተቀጣጠለ ምነይ ሐገሩ ተመሳቀለ ከጠላ - ውሃሽ ፣ ደም የቀለለ እያት ወገቧ ፣ የ እግዜር ሁለት እጅ እኔን ህጻኑን የታቀፈበት ዝናር ማዕረግህን አስታጥቀንና እባክህ በላይ እንመርበት @creativ_hub

HEnok Bekele
+1
HEnok Bekele

HEnock bekele
HEnock bekele

እንደተፋሰሰው ◦◦◦ባይኖረው ማበሻ እንደመጣነው ልክ ◦◦◦ባይኖር መመለሻ ◌ አደግን እንዳልነው ◦◦◦ባይኖር ሕጻንነት ሲኦል እንደከረምን ◦◦◦ባይኖር ደሞ ገነት ◌ እንደሸመጠጥነው ◦◦◦ባንሆን ሀቀኛ እንቅልፍ እንዳጣነው ◦◦◦“ጧ!” ብለን ባንተኛ ◌ ሰውን እንዳማነው ◦◦◦መውደድ ባንችልበት እንደ ጥጋባችን ◦◦◦ዝቅ ባንልበት ◌ አውሬ እንደሆንነው ◦◦◦ሆዳችን ባይብሰው የጎዳነውን ልብ ◦◦◦አፍቅረን ባንክሰው ሕይወት ምን ነበረ ? ◦◦◦ምንስ ነበረ ሰው ? ◌ ብቻ ብዙ ጊዜ . . . ሰባብረን የጣልነው ◦◦◦ስላየን ሲጠገን መኖርን ወደድነው ◦◦◦እግዚአብሔር ይመስገን።
ሄኖክ በቀለ ለማ

°°°ስለዚህ እግዚአብሔርን፥ ቤተሰቦቼን፥ የቅርብ ወዳጆቼን፥ የመጀመሪያ (ትዝታሽን ፡ ለእኔ ፥ ትዝታዬ ፡ ለአንቺ) መጽሐፌን በማንበብ፥ በማኄስ እና በማስተዋወቅ ሰው ጋር እንዲደርስ ያደረጋችሁትን አ
°°°ስለዚህ እግዚአብሔርን፥ ቤተሰቦቼን፥ የቅርብ ወዳጆቼን፥ የመጀመሪያ (ትዝታሽን ፡ ለእኔ ፥ ትዝታዬ ፡ ለአንቺ) መጽሐፌን በማንበብ፥ በማኄስ እና በማስተዋወቅ ሰው ጋር እንዲደርስ ያደረጋችሁትን አንባቢያን ከልብ አመሰግናለሁ። “ፀሓይ ከጨለማዬ ምን አለሽ?” የተሰኘ የረዥም ልብ ወለድ መጽሐፌ በጃዕፈር መጻሕፍት አሳታሚና አከፋፋይ በኩል በዋናነት በዕለተ ረቡዕ ወደ እናንተ ይደርሳል። Esubalew Abera N.

Good news fellas 💚

አሻም አሻም internet  ትንሽ ስለ ጠጅ እንጨዋወት :  በነገራችን ላይ አብሾ ያለበት ሰው ካልሆነ በቀር ጠጅ በቁም እና በጥፊያ አይጠጣም ።  ዝግ ብለው ያልጠጡት ጠጅ ላይበሌ ይባላል ። ስለ - ላይበሌ   በኋላ እናወራለን ። በለው ተሰማን ታውቁታላችሁ ? ጠጅ እንዳሁኑ ለ ሰፊው ህዝብ ከመፈቀዱ በፊት የነገስታት ብቻ መጠጥ ነበር ። ካባ ጥለው ገበታ ዘርግተው የሚጠጡት የክብር መጠጥ ።  መኳንንት ጠጅ አዛዥ የሚባል ሹም ነበራቸው ። ከ ጠጅ አጣጣል እስከ አቀራረቡ ድረስ ይቆጣጠራል ። የጠጅ አዛዡ በስሩ የሚሰሩ ባለሟሎች አሉት ። በጊዜው ከሃገሩ ሁሉ ከፍ ያሉ እድለኞች ማለት የጠጅ አዛዥ ባለሞሎች ነበሩ ። ጠጅ ንጉስ ፊት ከመቅረቡ በፊት መብላላቱ ፣ መብሰሉ እና አስፈላጊውን ጥንካሬ ማግኘቱ ይቀመሳል ። ታዲያ እነዚ ባለሟሎች ከህዝብ መሃል ጠጅ እንዲቀምሱ የሚፈቀድልቅቸው ብቸኛ እድለኞች ናቸው ።  ስማኝማ internet  :  ኢንግሊዛዊ ሃገር ተጓዥ በአይኔ አየሁ ብሎ በግል ማስታወሻው ላይ እንደዘገበው አንድ ባለሟል ሙሉ ብርሌ ጠጅ ሲጠጣ በመገኘቱ ንጉሱ  2 ዋንጫ ጠንካራ ጠጅ ከጋበዙት በኋላ ሞት ተፈርዶበታል ። በጊዜው ጠጅ በ ብርሌ ሳይሆን በ ፈረንሳይ ብርጭቆ ነበር የሚጠጣው ። ከዛ በፊት ደግሞ ከ ቀንድ በተሰራ ዋንጫ እንደቀሲስ ከላዩ በ ነጭ ነጠላ መሳይ ጨርቅ ይከናነብ እና ንጉስ ፊት ይቀርባል ። የፈረንሳዩ  ብርጭቆው አፉ ሰፊ ስለሆነ የጠጁ ሽታ አፍንጫ ጋር ይደርስና ቶሎ አናት ላይ ይወጣል ። ብርሌን ግን አስተውለሃት ከሆነ እዛው አፍ ላይ ግጥም ትላለች እንጂ አፍንጫ ጋር አትደርስም ።  ለዛ ነው በጊዜ ሂደት ብርሌ እየተለመደ የመጣው ።  ከ አጼ ዩሃንስ በፊት ቤተ መንግሥትን አልፎ የወጣ ጠጅ አይገኝም ።  ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ስለ በለው ተሰማ ላጫውትህ ። ሰውየው የ ጎጃም በረንታ ብቸና ሃብታም ገበሬ ነበር  ከጓሮው ጌሾ እና  ብዙ ቀፎዎች አሉት።  እንደነገሩ የ አካባቢው ገዢ ነበር እና  ፍሪዳ አርዶ ድግስ ሲደግስ ለአምሮቱ ደግሞ ጠጅ ይጥላል ። ይሄን ያየች እህቱ ብትመክረውም " ንጉስ ድሃ ሲደሰት ደስ ይለዋል እንጂ እንዴት ይከፋል " ብሎ ይቆጣት ነበር  ። ታዲያ ጠጅ ጥሎ ግብር ሰብስቦ ዳስ ድሶ ማብላት ማጠጣቱን የሰሙት ንጉስ ተክለሃይማኖት በ 2 ቀን መንገድ በረንታ ድረስ መጥተው በለው ተሰማ ጋር ለ 3 ቀን ይቆያሉ ። 3 ቀን ሙሉ የታሰበለትን ያላወቀው በለው ጠጅ እያጠጣ ቁርጥ እያበላ ቢያቆያቸውም የንጉስን ትዕዛዝ ተላልፎ ጠጅን ለጣለበት ትምክህቱ በ አደባባይ የ ቀኝ እጁን እና የግራ እግሩን እንዲቆረጥ ፈርደውበታል ። ይሄን ያየች እህቱ  እኔ እየነገርኩህ አንተ እየተቆጣህ የኔም መቀመጫ ያንተም መሄጃ አጣህ እነማይ ሳይሰማ በረንታ ሳይሰማ የጁ ተለቀሰ ለ በለው ተሰማ  ።  ብላ አልቅሳለታለች ። እዚህ ጋር የ ሃገሬውን ስንኝ ቋጣሪነት እና የግጥም ጥልቀት የጨዋታችን ግብ ስላልሆነ ለ internetኡ እንተወዋለን ። በነገራችን ላይ ጠጅ ቤት አግዳሚ መቀመጫው አረንጓዴ ፣ ብርሌው አንገቱ እና የወገቡ ስፋት እኩል የሆነ ነጭ ፣ መቅጃው እና አስተናባሪው የሚለብሰው ካባ ደግሞ ሰማያዊ እንደሆነ አስተውለሃል ? ይሄን እንተወውና ጠጅ ቤቶች ከመፈጠራቸው ጠጅ ለህዝብ ከመፈቀዱ በፊት እንዲሁ ጊዜ ጌታሁን የሚባል ጠጅ ወዳጅ የጎጃም ሃብታም ገበሬ ነበር ስለሱ ላጫውትህ ። ጊዜ ጌታሁን የደጋ መቄት ባለ ብዙ ቀፎ ገበሬ ድግስ ካለ ጠጅ ሳይፈራ የሚጥል  ደብዛ ማርያም የምትባል ደብርን ጎረቤቱ አርጎ ይሚኖር ትጉህ ገበሬ ነው ። ለ አስተርዮ ማርያም ጥቂት ካህናትን ሰብስቦ በዝግ አልፍኝ ውስጥ ከደገሰው ድግስ ሲያበላ ከጣለው ጠጅም ያቀምሳቸዋል ። ታዲያ ካህናቱ ለ ወዳጃቸው እየተናገሩ በ አመቷ አስተርዮ አንዱ ካህን 5 ሌላው ካህን 4 ወዳጃቸውን አስከትለው መምጣት ጀመሩ እና  እንዲህ እንዲህ እያሉ በ አንዱ የአስተዮ ማርያም እለት ጊዜ ጌታሁን ቤት ብዙ ካህናት የታደሙበት ድግስ ተደገሰ ይሄ ጠጅ እንደ ውሃ ፈሰሰ እንደ ጉድ ተጠጣ ። ያን ያዪ ጎረቤቶች ጊዜ ጌታሁንን ይከሱት እና ደብረታቦር አጼ ዩሃንስ ፊት ተከሶ ይቀርባል ። ንጉስ ተክለ ሃይማኖት እና ራስ ሚካኤልም ግብር ይዘው አጼ ዩሃንስ ቤት ደብረታቦር መጥተው ነበር ። ከሳሾች አባት አያቶቻችን ከጎሮዋቸው ቀፎ ፣ ከጎራቸው ጌሾ ጠጅ ጥለው ተወርሰዋል ይወረስ አሉ ። ተከሳሽ ደግሞ " ሃገሬ ዋሻው ሙሉ ማር እኔም 10 የንብ ቀፎ አለኝ ጠጅ ጥዬ መጠጣት ማጠጣቴን አልካድኩም ይፈረዱ ፍረዱ አለ "  አጼ ዮሃንስም ለማርያም ቀን ነው አይደል የደገሰው ? አዎ እና ድግስ ደግሶ ጠቦት ፍሪዳ  አርዶ ጠጅ ጥሎ እመቤታችንን በዘከረ ለምን ጽዋዋን አጠጣህ ብዬ ነው የምከሰው ? ከራሱ ጓሮ ጣለ እንጂ አልሰረቀ አላጠፋ ሲሉ ከዛ ጊዜ ጀምረው ለ ክፍለ ሃገሩ ሰው ጠጅ ጥሎ ማጠጣትን ፈቀዱ ። ከተሜ አያቶቻችን ገጠር ጎራ የሚሉት ዘመድ ጥየቃ ሳይሆን ጠጅ ቀመሳ ነበር ልልህ ነው ። ጠጅ ከዛ ጊዜ ጀምሮ እያደገ መጥቶ የመጀመሪያ በ ጠርሙስ ታሽጎ የሚሸጥ አገው ምድር የሚባል ጠጅ በ 1940 መጥቶ ነበር ። በ 1955 ደግሞ በ ሃይለስላሴ የተመረቀ ኢትዮጵያውያን እና ጣሊያናውያን ባለሃብቶች የገነቡት ሳባ የጠጅ ፋብሪካ ስራ ጀምሯል ። ወላ " ንግስት የተጣራ የማር ጠጅ " የሚባል ብራንዱን ከ 1960 ጀምሮ ኤክስፖርት አድርጓል ። የሳባ ጠጅ በቀን እስከ 10,000 ሊትር ጠጅ የመጣል አቅም ነበረው ። ከጠጅ ቤት ጀብደኝነቶች አንዱ የሞላ ብርሌ ጭንቅላት ላይ አስቀምጦ መደነስ እንደሆነ ታውቃለህ ? ታዲያ ጠጅ ቁርጥ እና ጥብስ ተበልቶ በዝግታ እንጂ ወጣወጥ አብሶ ቀይ ወጥ ተበልቶ አይጠጣም ። እንደሱ አይነት አጠጣጥ ላይበሌ ይባላል ። እዛው ጠጥተህ እዛው ትውከት ። ጠጅ  ትክክለኛ ያልኮል መጠኑ አለመታወቁ አንዱ ችግር ነው ።  የሳባ ጠጅ የሚጥላቸው ግን ከ 6 % - 11 % የአልኮል ይዘት በ ሊትር አለው ተብሎ ይገመታል ። በነገራችን ላይ ጠጅ ቤቶች ከጠዋት 11 ሰዓት ጀምሮ ነው የሚከፈቱት ። ጠዋት ላይ ወይራ ይጨሳል ማጣጫ ምናምን ይቀራረባል በዛው አንጋግተው ውሎ ይጀምራሉ ። በ ደርግ ጊዜ በቀን መጠጥ ቤቶች እንዲከፈቱ ስለማይፈቀድ ከ ምሽቱ 11 ሰዓት በፊት ጠጅ ሲሸጥ ወይም ሲጠጣ የተያዘ የጠጅ መቅጃውን አሊያም ብርሌውን ይዞ ከተማ እንዲዞር  በማድረግ አብዮታዊ ቅጣት ይቀጣል ። የከተማችን ጠጅ ቤቶች ከምንም በላይ ስማቸው ልዩ ነው ። ለዛሬ አንዳንዱን እናስታውስ እና እናብቃ ;  ይገባዋል ጠጅ ቤት ፣ እድሜ ቀጥል ጠጅ ቤት ፣ ገደል ግቡ ጠጅ ቤት ፣ መግቢያው በዚህ ነው ጠጅ ቤት ፣ አፋጀሽኝ ጠጅ ቤት ፣ ማሚቴ ጠጅ ቤት ፣ ውቂያኖስ ጠጅ ቤት ... ሙሉበት ።   አሻም አሻም internet 👐🏼

Yeshak abrham
Yeshak abrham

-------- አልጣልኩት አላቸነፍኩት አላባረርኩት ዛሬም እንደ እግረኛ ጦር ጥቁር ሀዘን..... ዳግም ጦሩን ሰብቆ ወጋኝ አዬ! ቁስሌን እንኳ የማክበት ቁስል የሌለው ገላ ጠፋኝ! : ሀዘን ሆይ..... ምን ብሆን ነው የምትራራው? እንዴት ብሞት ነው የምትረካው? : እድሜዬ ከማላውቀው ጋ ምን ተዋውለሻል? ህይወቴ'ስ ለሀዘን ስንቴ ሰግደሻል?
Yeshak abrham
Creativ_hub

#Wede_gtm 🎬 A stage scheduled for Saturday december 23 📍kazanchis fendika cultural center 🕰 starting from 8 : 30 am local
#Wede_gtm 🎬 A stage scheduled for Saturday  december 23  📍kazanchis fendika cultural center 🕰 starting from 8 : 30 am local #ወደ_ግጥም 🗓 ታህሳስ 13 ከ 8 : 30 ጀምሮ ካዛንቺስ ፈንድቃ የባህል ማዕከል ይካሄዳል

Henok bekele creativ_hub
Henok bekele
creativ_hub

በወጀቡ መሃል እነኋት ... እየተንገላታሁ አየኋት እየተንገላታች አየችኝ እግዜር ይስጣት ስለወደደችኝ። . በወጀቡ መሃል በጎርፉ በጦርነት መሃል በሰልፉ በብዙ ጻማ እየራደች ልትወደኝ ስለፈቀደች ፀጥታን ይስጣት አምላኳ `ያማልክት ይሁናት መልኳ። በሞትና ሕይወት ድንበር በተዘጋ የግዞት በር በእልፍ አእላፍ አቀበት በብዙ ብዙ ቁልቁለት በተዳከመች ‘ለት ዞር ብላ ልታየኝ ፣ ፈቅዳ ስለነበር። ምናቧ ይባረክ ፣ ክንፏም አይሰበር
ሄኖክ በቀለ
@creativ_hub

Khalid yohannes @crativ_hub
Khalid yohannes @crativ_hub

“ሀቁን ልንገርሽ፤ ሀፍረት የሌለሽ ውለታ-ቢስ ነሽ፡፡” ፅጌረዳዋን ወደ መተላለፊያ መንገዱ ወረወራት፤ በዚያ በኩል ሲያልፍ የነበረ ሰረገላ ጨፈለቃት፡፡ “ምንድነው ያልከው አንተ?! ውለታ-ቢስ ነው ያልከው? እንግዲያውስ እኔም እውነቱን ልንገርህ፤ በጣም ባለጌ ነህ እሺ፡፡ ደሞ ማናባህ ነኝ ልትል ነው? ተማሪ እኮ ነህ! በቃ፤ ተማሪ ብቻ፡፡ እስኪ ቆይ ዛሬ ማታ ለዳንስ እንደጋበዘኝ እንደ ሰለሞን ዘመድ ፤ አንዲት እንኳ ከንፁህ ብር የተሰራች የጫማ ዘለበት አለችህ? የለችህም፡፡ ቻው፡፡” አውረገረጋት “ፍቅር ይሉት ነገር ምን አይነት የማይረባ ነገር ነው፡፡” መሬቱ ላይ የተፈረሩትን ድንጊያዎች ይጠልዛል “የሎጂክን ግማሽ ያክል እንኳ ጠቀሜታ የለውም፡፡ አመክንዮን ተጠቅመን ነገሮች እውነት መሆን ወይም አለመሆናቸውን እናረጋግጣለን፡፡ ፍቅር ግን ምን ያረጋግጥልናል? ምንም፡፡ ሁሌ ቂል እንዳደረገን ነው፡፡ ከእውነቱ ይልቅ ሀሰቱን፣ ከሚከሰተው ይልቅ የማይከሰተውን እንድናምን ያደርገናል ፥ያቄለናል! ቲሽ!ፍቅር ተግባራዊ ነገር አይደለም፤ በዚህ ዘመን ደግሞ ተግባራዊ ያልሆነ ነገር ምንም አያደርግም፡፡ ወደ ፍልስፍና ተመልሼ ስለ ሜታፊዚክስ ባጠና ይሻለኛል፡፡ ዲበአካላዊነት ፍቅርን ይበልጣል። ሁለቱም ግን በባሕርይ አንድ አይደሉም...?” ከራሱ እያወራ ክፍሉ ደርሷል፡፡ ከመደርደሪየው ላይ አዋራ የጠገበ መፅሀፍ መርጦ አወጣ፤ ማንበብ ጀመረ... ___ [ Khalid yohannes ] @crativ_hub

“ህይወት ለፍጡራን ሁሉ ብርቅ ነው፡፡ አረንጓዴ ዛፍ ላይ ቁጭ ብሎ ፀሐይን ከወርቅ በተሰራው ሰረገላው ቀስ ብሎ ሲሄድ ማየት፣ ጨረቃ ደግሞ በሉል ሰረገላዋ ስትንፈላሰስ ማየት ግሩም፣ ድንቅ ነው፡፡ ሜዳው እና ሸለቆው የት ደብቀዋቸው ቆይተው ነበር የሚያስብሉ የአበቦች መአዛ ማራኪነት ከየትም አይገኝም፡፡ ከዚሁ ሁሉ ግን ፍቅር ይልቃል፡፡ ቆይ ደግሞ ከአንዲት ሚጢጢዬ ወፍ ህይወት እና ከአንድ ለግላጋ ወጣት ህይወት የቱ ይበልጣል?” ድንገት ሰማያዊ ክንፎቿን ዘርግታ አየሩ ውስጥ ዋኘች፡፡ ጥላ መስላ ጢሻውን አለፈች፤ ልክ እንደጥላ ወደ አትክልት ቦታው ቀዘፈች፡፡ ተማሪው አሁንም ሳሩ ላይ እንደተኛ ነው፡፡ የሚያማምሩ አይኖቹ በእንባ እንደረጠቡ ናቸው፡፡ “አሁን ማልቀስህን አቁም፤ ደስም ይበልህ፡፡ ሀሴት ይሁንልህ፡፡ ቀይ ፅጌረዳ ታገኛለህ፡፡ በጨረቃ ብርሃን በማደርገው ዝማሬ ፈክታ፣ በደሜ የምትቀልም ቀይ አበባ ታገኛለህ፡፡ በልዋጩ የምጠይቅህ ነገር ቢኖር እውነተኛ አፍቃሪ መሆንን ብቻ ነው፡፡ ፍቅር ፍልስፍና የማያውቀውን ታውቃለች፡፡ ፍቅር ከሀይል ትልቃለች፡፡ የሀይልን ታላቅነት ግን መርሳት የለብንም፡፡ ክንፉ እንደ ነበልባል ነው፣ የላባውም ቀለም ነበልባል ይመስላል፡፡ የሚናገረው ሁሉ ይጣፈጥለታል፡፡ መአዛውም እንደ ውድ እጣን ነው፡፡ ለዚህም ነው ሀይል ብዙ ጊዜ ፍቅርን የሚያሸንፋት፡፡” ተማሪው ከሳሩ ላይ ቀና ብሎ ወፏን ሰማት፡፡ ግን ምን ያደርጋል? እሱ የተፈጥሮ ቋንቋ አይገባውም፡፡ የሚረዳው መፅሃፍ ላይ የተቸከቸኩትን ነገሮች ብቻ ነው፡፡ የግራር ዛፉ ግን ያለችውን ሁሉ ሰምቷል፡፡ አዘነ፡፡ ቅርንጫፉ ላይ ጐጆ ከሰሩ ወፎች ሁሉ፣ ይህችን ሚጢጢ ወፍ አብልጦ ይወዳታል፡፡ “ለመጨረሻ ጊዜ ዘምሪልኝ፡፡” አላት ጎጆዋን የሰፋችበት ዛፍ በሹክሹክታ “እስከመጨረሻው ልትሄጂ ነው... ያኔ ብቸኝነቱን አልችለውም፡፡” ዘመረችለት፡፡ ዝማሬዋ ከብር ከተሰራ የውሃ መያዣ እንደሚቀር ውሃ ለስላሳ ነበር፡፡ ማኅሌቷን እንደጨረሰች ተማሪው ከወደቀበት ተነሳ፡፡ ከኪሱ እርሳስ እና ማስታወሻ ደብተር አወጣ፡፡ ስለፍቅረኛው አንዳንድ ነገሮች መፃፍ ያዘ፡፡ “ቅርፅ አላት፡፡” አለ ጢሻውን አቋርጦ ወደ ክፍሉ እያመራ፡- “ቅርፅ እንዳላት ማመን አለብኝ፡፡ ይዘት ግን አላት? ለምሳሌ ስሜት አላት? ይህን እጠራጠራለሁ፡፡ ይዘት የላትም፤ እንደ አብዛኞቹ አርቲስቶች ናት፤ ቄንጥ ብቻ፣ ቁም-ነገር ባዶ፡፡ አሁን እሷ መስዋዕት መሆን የሚባል ነገር ይገባታል? ኣኣ... መቼም አይገባትም፡፡መቼም። የአለም ምሰሶ የተሰራው ከሙዚቃ ይመስላታል፡፡ አንድ ያልገባት ነገር አለ፤ የጥበብ ስራዎች የሚፈጠሩት ለእሷ ተብለው አይደለም፡፡ እንደሆኑት ሆነው የሚፈጠሩት አርቲስቱም እንዲያ እንዲሆኑ ስለፈለገ አይደለም፤ የጥበብ ስራዎቹ እንዲያ ሆነው መፈጠር ስለፈለጉ ብቻ ነው፡፡ እንደ ጥበብ ስራዎች እራስ ወዳድ ማንም፣ ምንም የለም፡፡ … ይህንንም ማመን አለብኝ፡- ድምጿ ውስጥ ጣፋጭ ምቶች አሉ፡፡ የሚያሳዝነው ነገር በዛ ድምጿ የሚረባ ነገር ተናግራበት አታውቅም፤ አንድም የሚጠቅም ነገር ወጥቷት አያውቅም፡፡” እንዲህ እያሰበ ክፍሉ ደረሰ፡፡ ገብቶ አልጋው ላይ ተዘረጋ፡፡ ስለፍቅረኛው ማሰብ ቀጠለ፤ ብዙም አልቆየ፤ እንቅልፍ ወሰደው፡፡ ጨረቃ ስትወጣ ወፏ የተማሪው መስኮት ስር ወዳለው ፅጌረዳ በረረች፡፡(የአክናፎቿ ምት አልተሰማችሁም?) ደረቷን በእሾሁ ትይዩ አስተካከለች፡፡ እንዲያ ሆና ዝማሬዋን ጀመረች፡፡ ብሩኋ ጨረቃ ቁልቁል እያየቻት ዝማሬዋን ሰማች፡፡ ወፊቷ ደረቷን ወደ እሾሁ እየለጠፈች ዝማሬዋን ቀጠለች፡፡ ዝማሬዋ ስለ እውነተኛ ፍቅር መፀነስ እና መወለድ ነበረ፡፡ ቀጠለ፡፡ «ሰማይ ሲላወስ ደመና ሲነፍስ ብርሃን ሲጠፋ ጨለማ ሲነግስ። ጨረቃዋ ስትደምቅ ፥ ከዋክብት ሲወጡ ድምፅሽ ይነፍሳል ከዛፍ ከቋጡ...» (የምትል ይመስላችኋል? ወይስ ከዚኽ የሚልቅ ነው..?) ..ቀስ እያለች አንዲት ፈዘዝ ያለች ቀይ ፅጌረዳ በደሟ ፈካች፡፡ ፅጌውም ወፏን አላት፡- “ተጠጊው እሾሁን፤ በጣም ተጠጊው፤ አለበለዚያ የምታምር ቀይ ፅጌረዳ የማግኘት ምኞታችን አይሰምርምና ፡፡” እንደተባለችው አደረገች፡፡ የዝማሬዋ ድምፅ ከፍ እያለ መጣ፡፡ «...መውደድሽ ግሎ ልቤን ተኮሰው እኔስ የት ልግባ ወዴት ልድረሰው ?!» እረፍት የሚነሳ ስሜት በሁለት ልቦች ውስጥ ስለ መወለዱ ከፍ ባለ ድምፅ ዘመረች፡፡ ስሷ ፥ ቀዩኣ ፣ ፈዛዛዋ ፅጌረዳ እየፈካች መጣች፡፡ ሙሽራ፣ ሙሽሪትን የሰርጓ እለት ሲስማት ከንፈሯ እንደሚቀላው አይነት ነበር የፅጌዋ መቅላት፡፡ እሾሁ የወፏን ደረት በስቶታል፡፡ ልቧን ገና አላገኘውም፡፡ የፅጌረዳ ተክሉ፤ ወፏን ዳግም አላት፡- “ተጠጊው እሾሁን፤ በጣም ተጠጊው፡፡ አለበለዚያ የምታምር ቀይ ፅጌረዳ የማግኘት ምኞታችን አይሰምርም፡፡” እንደተባለችው አደረገች፡፡ እሾሁ ልቧን በሳው፡፡ ህመሙ ሀያል ነበር፡፡ ሕማሙ መራራ ነበር፡፡ የዝማሬዋ ድምፅ ከፍ እያለ መጣ፡፡ ሞት እንከን አልባ፣ ፍፁም ስለሚያደርገው ፍቅር ዘመረች፡፡ ከመቃብር ጋር ስለማይተዋወቅ ፍቅር ዘመረች፡፡ ፅጌረዳዋ ብሩህ ቀይ እየሆነች መጣች፡፡ ድምጿ እየደከመ... እየደከመ መጣ፡፡ አይኗ ደመና በሚመስል ነገር ተሸፈነ፡፡ ድምጿ እየደከመ፣ እየደከመ… የመጨረሻውን ዝማሬ ከፍ ባለ ድምፅ አለች፡፡ ጨረቃ መጥለቂያዋ ሰዓት ቢደርስም ፤ አኮቴቷ መሄዷን አስረሳት፡፡ ባለችበት ቆማ መስማት ያዘች፡፡ ፅጌዋ ፈነደቀች፡፡ ቅጠሎቿ ተከፈቱ፡፡ የገደል ማሚቴዎች የወፏን ዝማሬ አስተጋቡት፡፡ እረኞቹ ነቁ፡፡ ወንዞች ዝማሬውን ተሸክመው በየአቅጣጫው ተጓዙ፡፡ ባህሮች በዝማሬው አሸበሸቡ፡፡ “ተመልከች ወፊቷ ሆይ! ምን አይነት የምታምር ፅጌረዳ እንዳፈራን፡፡” አለች ፅጌዋ ። እርሷ ግን አልሰማችም...ምክንያቱም ሞታለች፡፡ እሾሁ ልቧ ወስጥ ተቀርቅሯል። ሳሩ ላይ ወደቀች፡፡ ... ተማሪው እስከ ምሳ ሰዓት ተኛ፡፡ እንደ ነቃ የመኝታ ክፍሉን መስኮት እንደከፈተው አበባዋን አየ “ምን?! እንዴት አይነት መታደል ነው፡፡ በህይወቴ እንዲህ የምታምር ቀይ ፅጌረዳ አይቼ አላውቅም፡፡ እንዲህ በጣም ካማረች ሳይንሳዊ ስሟ በጣም ሳይረዝም አይቀርም፤ መፅሃፍ ባገላብጥ አገኘዋለሁ፡፡” በሞት መስዋዕት ስላገኘው ውብ ፅጌ ... ባያውቅም እየተደሰተ። ውቧን ፅጌረዳ ቀጠፋት፡፡ ኮፍያውን አድርጐ ወደ ፍቅረኛው ቤት ተጣደፈ፡፡ ፍቅረኛው በር ላይ ተቀምጣ፣ የሀገር ጨርቅ በኪሮሽ እየሰፋች ፥ ድንክ ውሻዋም እግሯ ላይ ተኝታለች፡፡ “ቀይ ፅጌረዳ ካመጣሁልሽ አብረሽኝ እንደምትደንሺ ቃል ገብተሽልኛል፡፡” አጠገቧ እንደደረሰ ነው የተቅለበለበለው። “በአለም ላይ ታይታ የማታውቅ ቀይ አበባ እነሆ! ዛሬ ማታ የደረትሽ ክፍተት ላይ፣ ልብሽ ጋር ባለው ቦታ ላይ ትሰኪያታለሽ፤ እንዲያ ሆነሽ ጣፋጭ ዳንስ እንደንሳለን፡፡ አፈቅርሻለሁ እሺ?” “አዝናለሁ፤ የፅጌረዳዋ ቀለም ለምሽቱ ከመረጥኩት እና ከምለብሰው ቀሚስ ጋር አብሮ የሚሄድ አይመስለኝም፡፡ በዚያም ላይ ሌላ ሰው አብሬው እንድደንስ ጠይቆኛል፡፡ ታውቀዋለህ፡፡ የ'ነ ሰሎሞን ቤተሰብ ነው፡፡ ከቀሚሴ ጋር የሚሄድ ምርጥ እና ውድ ጌጦች ልኮልኛል፡፡” ቀና ብላም አላየችው “እኔ እምልህ ከፈርጥ እና ከአበባ የቱ ይወደዳል? መቼስ የዚህን ጥያቄ መልስ ሁሉም ሰው ያውቀዋል፡፡” ስትስቅ ማፈር የላትም። ምክንያቱም የተከፈለውን አላየችም። ስንት ፅጌ ሕይወት ተቀጠፈ?

ሰማያዊቷ ወፍ እና ፅጌረዳዋ ___ ❨ከOscar Wilde ፡ "the nightingale and the rose " የሚለውን ታሪክ እጅግ በጥቂቱ የራስ ጫና ውስጥ አድርጌ እንደመለስኩት።❩ ___ “Love is wiser than Philosophy, though he is wise, and mightier than Power, though he is mighty.” - Nightingale .... “ «ቀይ ፅጌረዳ ካመጣህልኝ ዛሬ ማታ አብሬህ እደንሳለሁ» ብላኛለች...ግን... ግን ግቢያችን ካሉት አበቦች አንዲትም ቀይ ፅጌ አላገኘሁም” አፍቃሪው ተማሪ ነው። አጠገቡ ከቆመው ዛፍ፤ ጎጆዋን ቀልሳ የምትኖር አንዲት ወፍ መማረሩን ታደምጣለች፡፡ አንገቷን አሰግስጋ በዛፉ ቅርንጫፎች መኻል አየችው፡፡ “ይገርማል፡፡” አለች “አንዲት ቀይ ፅጌረዳ ከዚህ ሁሉ አበባ መሀል ልጣ!” አሁንም ይጮኻል ፡፡ ውብ አይኖቹ በእንባ ተሸፍነዋል፡- “ ቲሽ! ደስታችን የሚመነጨው እጅግ መናኛ ከሆኑ ነገሮች መሆኑ ያሳዝናል፡፡ በአለም ላይ አሉ የተባሉ ጠቢባን የፃፉዋቸውን መፅሐፍት አስሻለሁ ፤ የማላውቀው አንድም የፍልስፍና አንጓ ባይኖርም ፤ ዝንጣፊ አበባ ማግኘት ግን አልቻልኩም። አሁን አንዲት ቀይ ፅጌ በማጣቴ የማልረባ መናኛ ሆኛለሁ፤ ሁሉም ነገር ረብ የለውም! ከንቱ ነኝ” “ማፍቀር እና አፍቃሪ ካሉስ እንዲህ ነው ፡፡” ከጎጆዋ ሆና አስተያየቷን በተለጣጣቂነት ቀጠለች “እርሱን ባላውቀውም ፡ እኔ ሁሌም ምሽት የምዘምረው ስለ እውነተኛ ፍቅር እና አፍቃሪ መኾኑን የሰማይ ክዋክብት አድምጠዋልና ፤ ምስክሮቼ ናቸው፡፡ ዘመኔን ስለ እንዲህ አይነቱ አፍቃሪ ብዘምርም አንድም አይቼ አላውቅም ነበር ፡፡ አሁን ይኸው የተስፋዬ ቃል በእኔው ጊዜ ስጋ ለብሶ አየኹ ... ... ፀጉሩ እልም ያለ ጥቁር ነው፤ ከንፈሮቹ ለማግኘት የተንሰፈሰፈላትን ቀይ ፅጌረዳ ይመስላሉ፡፡ ምን ያደርጋል?! ውስጡ የሚንቦገቦገው የሚፋጅ ስሜት ፊቱን የገረጣ የዝሆን ጥርስ አስመስሎታል፤ ሀዘኑም በዚህ እድሜው ግንባሩ ላይ ጥልቅ መስመር አስምሯል፡፡” ተከዘች “ዛሬ ልዑሉ የራት ግብዣ አዘጋጅቷል፡፡ እኔ መገኘት የምሻው ከማፈቅራት ኮረዳ ጋር ነው ፡፡ ቀይ ፅጌረዳ ከሰጠኋት እስኪነጋ አብራኝ ከምትደንስ ፥ ክንዷን በክንዴ ሸበብ ማድረግ የምችል... ኸረ ስንደንስም አንገቷን ትከሻዬ ላይ ከንበል እንደምታደርግም እርግጠኛ ነኝ፡፡ እጆቼን በስሱ፣ ላባን በሚገዳዱሩ እጆቿ ትይዘኛለች ... ችግሩ ግን ቀይ ፅጌረዳ ከየት ላምጣ?! የትም አላገኘሁም፡፡ የማገኝም አይመስለኝም። ሰው ሁሉ ከፍቅረኛው ጋር ሲደንስ እኔ ብቻዬን እጅ-እግሬን አጣምሬ መቀመጥ ግድ ይሆንብኛል፡፡ እንዲያ ሆኜ አይታኝ ከቁብም ሳትቆጥረኝ፣ ስታልፈኝ ካሁኑ ይታየኛል፡፡ አቤት ያኔ ልቤ ምንኛ ይታመም ይኾን?!” አይደለም ክስተቱ፣ ሀሳቡ ብቻ ዘገነነው “በእርግጥም ይህ ተማሪ እውነተኛ አፍቃሪ ነው፡፡ የኔ እና የእሱ ነገር የተገላቢጦሽ ነው፡፡ እኔ ስለ እውነተኛ ፍቅር እዘምራለሁ፤ እርሱ በእውነተኛ ፍቅር ይሰቃያል፡፡ ለ'ኔ የደስታ ምንጭ የሆነው እውነተኛ ፍቅር ፤ ለእርሱ እረፍት የሚነሳ ህመም ሆኖበታል፡፡ እውነትም ፍቅር ልዩ ነገር ነው፤ እውነትም ፍቅር የማይፈታ እንቆቅልሽ ነው፤ እውነትም ፍቅር ድንቅ ነገር ነው፡፡ አለጥርጥር ከወርቅ ከአልማዝ፣ ከሉል ሁሉ ይልቃል፡፡ በምንም ነገር አይገዛም፡፡ ሲጀመር ገበያ ላይ የት አለና?! ነጋዴ ፍቅር የሚባል ሸቀጥ ገበያ ይዞ ወጥቶ አይቼ አላውቅም፡፡” ወፏ በፍቅር ጉዳይ ተገርማለች ፡፡ “እራት ከተበላ በኋላ የከተማችን ምርጥ ሙዚቀኞች መድረኩ ላይ ይወጣሉ፡፡ የሚቀር የክር መሳሪያ እና ተጫዋች አይኖርም፡፡ የኔ ፍቅር ከጊታሩ እና ከቫዮሊኑ ድምፅ ጋር አብራ ትፈሳለች፡፡ በላባ ቅ'ለት ነው የምትደንሰው፤ እግሯ መሬት አይነካም፡፡ የከተማው ታዋቂ ሴት - አውሎች በአንዴ ይከቧታል፡፡ እኔ ቀይ ፅጌረዳ የለኝም፤ ስለዚህ ከእኔ ጋር አትደንስም፡፡” ለጋው ተማሪ ቅዠት ተጸናወተው። ሕልም ጠለፈው ። በደረቱ ሳሩ ላይ ተደፋ ፡፡ ፊቱን በእጆቹ ሸፍኖ አለቀሰ፡፡ ሲቃው ከባድ ነበር “ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው የሚነፋረቀው?” ጠየቀ አረንጓዴ እንሽላሊት ጭራውን አየር ላይ ቀስሮ፡፡ “እውነትም ምን ሆኖ ነው?” በፀሀይ ጨረር ስትጫወት የነበረች ቢራቢሮ ቀጠለች ፡፡ “የምር-የምር ምን ሆኖ ነው?” ነጭ አበባ ያለው ተክል አጠገቡ ላለው ሌላ አበባ፤ በለስላሳ ድምፅ ፥ በቀስታ፡፡ “ቀይ ፅጌረዳ ፈልጐ፣ አጥቶ ነው፡፡” መለሰች ወፏ፡፡ “ለቀይ ፅጌረዳ ነው ይኼ ሁሉ መነፋረቅ?!” እኩል ጮኹ፡- “ምን አይነቱ ሞኝ ነው ባካችሁ!” አሁንም እኩል፡፡ አሽሟጣጩ እንሽላሊት ከት ብሎ ሳቀ፡፡ ወፏ ብቻ ናት የተማሪው ሀዘን የገባት፡፡ ዛፋ ላይ በዝምታ ተቀምጣ ስለ ፍቅር ጥልቅ ምስጢር ማሰብ ያዘች፡፡ ድንገት ሰማያዊ ክንፎቿን ዘርግታ አየሩ ውስጥ ዋኘች፡፡ ጥላ መስላ ጢሻውን አለፈች፤ ልክ እንደ ጥላ ወደ አትክልት ቦታ ቀዘፈች፡፡ሳር የበቀለበት ስፍራ መሃል ላይ አንዲት የፅጌረዳ ተክል አየች፡፡ ወደዚያው በረረች፡፡ “እባክሽ አንዲት ቀይ ፅጌረዳ ስጪኝ፡፡” ጮኸች ሰማያዊቷ ወፍ ፡- “በልዋጩ ምርጥ ዝማሬዬን አሰማሻለሁ፡፡” የፅጌረዳ ተክሏ በአሉታ እራሷን ነቀነቀች፡፡ “የማፈራቸው አበቦች ነጭ ናቸው፡፡ ወዲያ ማዶ አንድ የፅጌረዳ ተክል አለ፤ የሚሳካልሽ ከሆነ እሱ ጋር ሂጂ፡፡ የምትፈልጊውን ታገኚ ይሆናል፡፡” ወፏ የተባለው የፅጌረዳ ተክል ወዳለበት ስፍራ በረረች፡፡ “አንዲት ቀይ ፅጌረዳ ስጠኝ፡፡ እኔ በልዋጩ ምርጥ ዝማሬዬን አስደምጥሃለሁ ፡፡” ተክሉ በአሉታ እራሱን ነቀነቀ፡፡ “የማፈራቸው አበቦች ቢጫ ናቸው፡፡ ይኸውልሽ የተማሪው መስኮት ስር አንድ የፅጌረዳ ተክል አለ፡፡ እሱ ጋር ሂጂ፤ የምትፈልጊውን ታገኚ ይሆናል፡፡” ወደተባለው ተክል ከነፈች ፡፡ “አንዲት ቀይ ፅጌረዳ ስጠኝ፡፡ እኔ በልዋጩ ምርጥ ዝማሬዬን አሰማሃለሁ፡፡” በአሉታ እራሱን ነቀነቀ፡፡ “የማፈራቸው አበቦች ቀይ ናቸው፡፡” ብሎ መለሰ ፤ ቀጠለ “ግን ምን ያደርጋል፤ ክረምቱ ስሮቼን አኮማተራቸው፤ ውርጩ እንቡጦቼን አጠወለጋቸው፤ ውሽንፍሩ ቅርንጫፎቹን ዘነጣጠላቸው፤ እናም በዚህ አመት አበቦችን አላፈራም ፡፡” “አንዲት ዘለላ ቀይ ፅጌረዳ ብቻ ነው የምፈልገው፡፡” አለቀሰች ወፏ፡- “አንዲት ዘለላ ቀይ ፅጌረዳ ለማግኘት ምንም መላ የለም?!” “የምታገኚበት መንገድ አለ፡፡ ግን እጅግ በጣም ሰቅጣጭ ስለሆነ ልነግርሽ አይሆንልኝም፡፡” “ንገረኝ! አንዳችም ነገር አልፈራም፡፡” “የምትፈልጊው ቀይ ፅጌረዳ ከሆነ እኔ የምልሽን ሁለት ነገሮች በመፈፀም ልታፈኪው እና ልታገኚው ትቺያለሽ፡፡ አንድም ፡- በጨረቃ ብርሃን ትዘምሪያለሽ፤ ዝማሬሽ እንዲያብብ ያደርገዋል ፡፡ አንድም፡- ደምሽን ትሰጪኛለሽ፤ ደምሽ ያቀላዋል። በጨረቃ ብርሃን ደረትሽን እሾኼ ላይ ሰክተሽ ጨረቃ ወጥታ እስክትጠልቅ ድረስ ትዘምሪልኛለሽ፡፡ ቀስ እያለ እሾሁ ደረትሽን እየሰረሰረ፣ ልብሽን ይበሳዋል፡፡ እያንዳንዷ የደምሽ ጠብታ ካንቺ ወደ እኔ ትተላለፋለች፡፡ እንዲያ ነው፡፡” “ሞት?!... በሞቴ አንዲት ዘለላ ቀይ ፅጌረዳ ልግዛ?! ውድ ነው፡፡”

ተለመነኝ ዝምታዬ ከልቤ መሐል ተኝተህ፣ እንደባህር ተዘርግተህ፣ አንደበቴ እንደማዕበል፥ ላንቃዬ ላይ ሲገማሸር ፥ "ታገስ ታገስ" እያልህብኝ፤ ስንቱን ወዳጅ አሰመጥሁት ፥ ስንቱን ፍቅር ገደልህብኝ፤ ተ
ተለመነኝ ዝምታዬ ከልቤ መሐል ተኝተህ፣ እንደባህር ተዘርግተህ፣ አንደበቴ እንደማዕበል፥ ላንቃዬ ላይ ሲገማሸር ፥ "ታገስ ታገስ" እያልህብኝ፤ ስንቱን ወዳጅ አሰመጥሁት ፥ ስንቱን ፍቅር ገደልህብኝ፤ ተለመነኝ ዝምታዬ... ጀግኜባት በዓለም ላይ ፥ ሰልጥኜባት ከሰው እኩል፣ ሁሉን ችዬ ፣ ሁሉን ጥዬ፥ የምጠቃው በአንተ ብቻ ፤ የምሸነፍ በአንተ በኩል፤ ተለመነኝ ዝምታዬ... ወርቅ ሲሉህ ሲያዋድዱህ ፥ መወድሱ እያለፈኝ ሊፈትኑህ የለኮሱት ፥ እሳቱ ነው የተረፈኝ። እስመቼ በእሳትህ ፥ ተከድኜ ልንፈቀፈቀው? ወይ እንዳንተ ዝም ልበል ፤ ወይም ትቼህ ላደባልቀው፤ በቃኝ! ሁሉ በአፉ እግር፥ አንተን ረግጦ ፥ ሲያልፍ እያየሁት፥ ሁሉ አንደበቱን ፥ ስሎ እያፋጨ ፥ እየሰማሁት፥ እኔ ብቻ ነኝ፥ መጠባበቂያ ፥ ጩኸት ያጣሁት፤ በቃህ! የእድሜዬን ጉልበት፥ አንተን አዝዬ ፥ መቆም ጨረሰው፤ እባክህ ውረድ፤ ልናገርና ፥ ልውደቅ እንደሰው! [ ሚካኤል ምናሴ ] @crativ_hub

Eritrea music Abraham Afewerki - Semai/ሰማይ Official Audio Video

Repost from አቦል
ዘመስግን'ዩ ዕጉስ ዝዕገስ'ዩ ሓያል ዘዋህልል'ዩ ለባም ይኣኽለኒ ምባል ዝፈልጥ'ዩ ሃብታም ክበሃል ሰሚዐ እንተስ ኣሚነሉ እንተስ ክጸናናዕ ግን ተሰማሚዐ ድሓን ክሓልፍ'ዩ እንዳበሉኒ እኳ ብዓይነይ ርእየ ኣቤት እወ ክንደይ ድዩ ሓሊፉ) (...አመስጋኝ ነው ታጋሽ 'ሚታገስ ነው ሃያል፣ 'ሚቆጠ፞ብ ነው ልባም፣ ይበቃኛል ማለት የሚያውቅ ነው ሃብታም ሲባል ሰምቼ አምኜም ይሁን ፥ ለመፅናናት ግን ተስማምቼ ደህና ያልፋል እያሉኝ'ኳ ባይኔ አይቼ አቤት ስንቱ ነው ያለፈው?...) እወ ሙኻን ሕስብ ተበልክዎ ስፍሓት ህይወት ከም ዝተረዳእክዎ ነቲ ጽቡቕ ዝበለጸ 'ለዎ ነቲ ሕማቕ ዝበኣሰ 'ለዎ ነቲ ጣዕሚ ዝጠዓመ 'ለዎ ነቲ ሕሰም ዝመረረ 'ለዎ ጫፍ ጽቡቕን ሕማቕን ዓቂነ ከለልዮ ወላ እንተፈቲነ ኣበይ ከይክእሎ ኣነ ሰብ 'ዚ ኣነ (..አዎ ሁነትን ሳስበው፣ ስፋቱን ጥልቀቱንም ስረዳው፣ ለጥሩ(ለመልካምም) የበለጠ አለው። ለመጥፎውም የባሰ አለው። ለጣፋጩ የጣፈጠ አለው። ለኮሶውም የመረረ አለው። የጥሩ'ና የመጥፎ'ን ጫፍ ለክቼ ልለየውም ብፈተንም መች ሊሆን ሰው ነኝና...) ዓለም ከም ባሕሪ'ያ ከም ዝበሃል ክሕምብስ ዘይክእል ንኸይጥሕል ሓቢርና'ዶ ጸገምና ነቃልል ክንበላሓት ዝያዳ ክንጋደል ሾለ'ቲ ሽግር ትወልዳ ንጥበብ ብኣካል ብመንፈስ ንራኸብ ህይወት ከነማሓይሽ ክንላዘብ) (...ዓለም በባህር እንደምተመሰል፣ እንዳይሰምጥ፤መዋኘት ግን የማይችል አብረን ችግራችንን እናቃልል? መላ በሉ እንግዲህ እንጋደል(survival) (እንጎብዝ ችግራችንን ለመቅረፍ ሰው በዓለም እንዳይሰምጥብን፣ ችግር ጥበብን እንደ'ምትወልድ፣ በአካል በመንፈስ እንጋመድ። ህይወትን እንዲሻሻል እንዲል ለዘ፞ብ) ክሳብ ዝኾነለይ ክሳብ ዝሰምረለይ ውቅያኖስ'ዩ ዓቕለይ ትስፉው'ዩ ጠመተይ ኣይዕገትን'የ ሰማይ'ዩ ደረተይ) (...እስከ'ሚሆንልኝ እስከ'ሚሳካልኝ ውቅያኖስ ነው አቅሌ ተስፋ ነው እይታዬ(ወደፊቴ) አልታገትም(አልደናቀፍም) ሰማይ ነው ደረቴ..) ክሳብ ዝኾነለይ ክሳብ ዝሰምረለይ ኣይጽንቀቕን'ዩ ሓይለይ ትስፉው'ዩ ጠመተይ ኣይሕለልልን ሰማይ'ዩ ደረተይ) እስከ'ሚሆንልኝ እስከ'ሚሳካልኝ አይጨለጥም ሃይሌ ተስፋ ነው ወደፊቴ አልረታም ሰማይ ነው ደረቴ ሰማይ ሰማይ ሰማይ ሰማይ'ዩ ደረተይ (..ሰ..ማ..ይ   ሰ ማ ይ ሰማይ ሰማይ ነው ደረቴ..) ©ናታን ኤርሚያስ Share to your loved ones ለሚወዷቸው ያጋሩልን . @nathanErmias @nathanErmias

Repost from አቦል
“ቸርች ውስጥ የተከለከሉ መዝሙሮች” የምትል ስንኝ፤ ¹ነገረ ኤልያስ መልካ( ፀሀፊ ዮናታን ጌታቸው) የሚል አርዕስት ባለ፞ው ልጥፍ ሾር ከሶስት ቀን በፊት አነበብቤ ቀልቤን ገዛው። በ'ርግጥ ፅሁፉ ለኔ ሞጋችም፤የወደድኩትም ነበር። Secularism(specially secular songs(good songs))፤በወንጌላውያን አማኞች(aka Protestant) ዘንዳ ዘመን የተሻገረ አሟጋችነቱ አልተቋጨም። // ይሄንን ያነሳሁበትም ጉዳይ እንደ አንድ ወንጌላዊ አማኝ ሰለባ ስለሆንኩኝ ነው። ጉዳዩ ይቆየኝ'ና፤ ነገር መፈትፈቱንም ትቼ ወደ ፅሁፌ ልግባ።  ከሁለት ቀን በፊት በየኔ ዜማ Album፤አስመሪኖ truck inspired ሆኜ ሾለ ፀሀይቱ ባራኺ አባሻዉል ዝተባህል ዘፈኗ ጥቂት ነገር ብዬ ነበር። እዛው ፅሁፍ ላይ አብርሃም አፈወርቂ'ን(ሰማይ) እንደ መግቢያ ተጠቅሜ ሌላ ቀን በሰፊው እንደምመለስበት ተናግሬ(ቃል ገብቼ ) ነበር። ይሄም ፅሁፍ ሾለ አብርሃም አፈወርቂ አንዳንድ ጉዳዮችን እያወሳ ያወራል። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨                          ሰማይ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ (...በሙዚቃ ጥበብ ሚስጥር ባሳለፍነው ድብቅ ፍቅር ሰማይ ይዤ ናፍቆኝ መጣሁ አብርሃምን ያየው አጣሁ...) ሁለት አስርት የኩርፊያ አመታት፤የወንድማማቾችን ፈገግታ ተከረቸም አበጁለት። ሀያ አመት ጎረምሳነቱን የጨረሰ ወጣት እድሜ ነው። በፅሁፌ አመታትን ማንሳቴ በቂ ምክንያት አለው ለአሁኑ ግን ገታ ላ'ርገው'ና ሌላ ሀሳብ አንስቼ ልመለስ። አንድ ወዳጄ የኪነትን አቅም ሊቋቋም የሚችል ሀይል የለም ይላል። ኪነት...ስሜት ምትዘየርበት የጠቢብ መንገድ ነች። ኪን ግጥም ነች። ኪን ሙዚቃ ነች። ኪን..... ቃላት መፅሄት ቅፅ አንድ ላይ(የሄኖክ በቀለ አምድ) “ኪነትን የማያውቅ ጨካኝ ህዝብ” የሚል አርዕስት ያለው ፅሁፍ እንዲህ ይለናል። ቦታ ቋሚ እውነት አይደለም ይፈርሳል ይታደሳል። ጊዜ ግን መኳንንት ነው፤ ይጠይቃል እንጂ አይጠየቅም። ፀሀፊውም  ወረድ ብሎ አሁን ያለንበትን ዘመን Dystopian ዘመን እንደሆነ አረዳን። ምቾት ባይሰጠውም ለቃሉ የሰጠው አቻ ትርጉሞች እኚህ ናቸው....በሰው ስቃይ የፋፋ፣ ፍትህና ርትዕን የገፋ፣ጥዩፍም ንቁፍም(Dystopian)።  ፀሀፊው The live of other's(“das leben der andren) በተሰኘ የጀርመን ፊልም ላይ በፅሁፉ አውድ(context) ዳሰሳን አቀረበልን።(እኔም ይሄንን ሁሉ ስዘበዝብ ሾለ ኪን ብሎም ሾለ አብርሃም(ሰማይ) የጀመርኩትን ፅሁፍ አውድ(context) ረስቼ ስላልሆነ በትዕግስት አንብቡልኝ።) ፊልሙ ላይ “ዊስለር” የተባለ ልበደንዳና የስታሲ ሰላይ ለስላሳ የጆሮ ማዳመጫ ካደረገበት(ሊሰልለው) “ደራሲ ድሬይማን” ቤት በሚለቀቅ “sontana for a good man” በሚል ሙዚቃ ሲያለቅስ ይታያል። ተሰላዩ ደራሲም ዊስለር(ሰላዩ) እንደሚያደምጠው ባያውቅም እንዲህ ይላል.….can any one who hered this music, i mean truly heard it really a bad person?(ይሄንን ሙዚቃ የሚያደምጥ፤ማለቴ ከልቡ ይሄንን ሙዚቃ የሚያደምጥ መጥፎ መሆን ይቻለዋልን?) ኪነት ልብን ያራራል። ኪነት ልትገድለው ካሰብከው ሰው ጋር የጋራ ህልም፣ የ ጋራ ህመም ፣ የጋራ ስቃይ ፣ የጋራ ፍላጎት፣ የ ጋራ ተስፋ እንዳለህ ይነግርሃል። ይህንን እያወክ እንዴትስ ልትጨክንበት ትችላለህ? ጠላቴ ያልከው ሰው አንተ የምትወደውን ሙዚቃ እንደሚወድ ማወቅ፣ አንተ የምትወደውን መፅሀፍ እንደሚሳሳለት መረዳት፣ የወገንነት ስሜት እንዴት አይፈጥርብህም? በፊልሙ ማብቂያም “ዊስለር” እንዲሰልለው በታዘዘው የ“ድሬይማን” ህይወት ሲነካ'ና ያልተጠበቀ መልካምነት ሲያሳየው ይታያል። ለምን? ኪን የሚገባው ህዝብ ሾሾ ነዋ።(ቃላት መፅሄት ቅፅ ፊ) አብርሃም ከያኒ ብቻ አይደለም ለ'ኔ። ወደ ልሡ ኪን ይጠጋብኛል።  ሰማይ እያለ ሲያዜም ጠንከር እላለሁ። ምስጢር ፍቕሪን፣ ትምኒተይን ስሰማ አካሌ ይባባል። መለይ ሲል ከአውዱ 'ወጣለሁ። በ አባቷ ወገን ነው መኖር ምትችለው ተብላ ባፍላነቷ  ከ'ናቷ ያለውዷ ጦርነት የለያትን መለይ የምትባል cousinኔን አስታውስበታለሁ። ከ ሃያ ምናምን ዓመታት በኋላ ከኛ ከቤተሰቦቿ ስትገናኝ ያለቀሰችው ውል ይልብኛል። ብበዘሊናዮን ሲያቀነቅን ምናቤ ያፈቅራል። አይዞህ ባይ እያሻኝ የምናቤን እንስት አጆሂ እላታለሁ። አብርሃም በኔ ቤት ስሜቶቼን ምስልበት የድምፅ ቀለም ነው። ድባቴዬን ማባርበት ዛር። ከአብርሃም የተዋወኩት በምጠላው ሳይሆን በጣም እጠላው በነበረ ሰው ነው። ሰማይን ሲያደምጥ ጆሮዬ ውስጥ ገባ። ሰማይን ማድመጥ ጀመርኩኝ የትርጉም ችግር እያለብኝ። ከዛም ሰው ጋር ተወዳጀሁ ምን እንደሚልም ነገረኝ። የማላቀው ክራር ገራፊ ከዚህ ሰው አወዳጀኝ።  ታዲያ “can any one who hered this music, i mean truly heard it really a bad”?  ማለት ለኔ አይደለምን? አብርሃም ጥቅምት 7/2006 ኤርትራ ምፅዋ በ አርባ ዓመቱ ይቺን አለም ጥሏት ሄዷል(ቀረባት)። መንዛዛት እንዳይሆንብኝ ሰማይ የሚለው'ን lyrics ትግረኛውን ወርስ በሆነ የአማርኛ  ትርጉም አስቀምጬ ፅሁፉን እቋጫለሁ( ውርስ ትርጉሙን ካወላገድኩት ከወዲሁ ይቅር በሉኝ🙌)  ሙዚቃውንም ከዚሁ ፅሁፍ በታች አኖረዋለሁ። ÂŤ..ሰማይ... ኩሉ ሓላፋይ'ዩ ኢለ ገሚተ ስግር ጋሻ ውሕጅ ጠሚተ እጽዕር ኣለኹ ብተስፋ ነዛ ሕማቕ እዋን ክሓልፋ እጽዕር ኣለኹ ብዓቕመይ ቃልሲ'ሾ መናብርተይ ናይ ቀደመይ ንግዚኡ'ኳ እንተሓየለኒ እስዕሮ እምበር ኣይስዕረንን ጸገመይ ተስፋ'ዩ ደገፈይ ተስፋ እዩ ሓይለይ ደጋጊመ እጽዕር ክሳብ ዝሰምረለይ ይጥዓም ይሕሰም ፍሽኽታ ኣመለይ) (....ሁሉ አላፊ ነው ብዬ ስለገመትኩኝ እንግዳ ጎርፍ ብመለከትም ተሻገርኩኝ። እየጣርኩም ነው በተስፋ፣ ይህቺን መጥፎ ጊዜ ላልፋት፣ እየጣርኩ ነው ባ'ቅሜ። መታገልስ አብሮኝ ኗሪ ነው ከቀድሞም፣ ለጊዜው አየለብኝ እንጂ በረታ፣ ሆኖም እረታዋለሁ እንጂ አይረታኝም። ተስፋ ነው ድጋፌ ተስፋም ነው ሃይሌ ደጋግሜ እለፋለሁ እስከሚሰምርልኝ ይክፋም ይድላም(ይጣም፞ም፞ ይምረር) መሳቅ ነው አመሌ።) ፍሽኽታ ኣመለይ ኩሉ ጸይረ'የ ፍሽኽታ ኣመለይ ፍሽኽታ ኣመለይ ይጥዓም ይሕሰም ፍሽኽታ ኣመለይ ፍሽኽታ ኣመለይ ኣይሕለልን ክሳብ ዝሰምረለይ ፍሽኽታ ኣመለይ እስዕሮ እምበር ኣይስዕረንን ጸገመይ ) (...መሳቅ ነው አመሌ ሁሉን ችዬ መሳቅ ነው አመሌ መሳቅ ነው አመሌ ይጣም ይምረር መሳቅ ነው አመሌ መሳቅ ነው አመሌ አልንበረከክም እስከሚሰምርልኝ መሳቅ ነው አመሌ እረታዋለሁ እንጂ ችግሬ አይረታኝም..) ናብራ ከቢዱኒ እንዳማረርኩ፣ ጥዕና ዘይብሉ ምስ ረኣኹ፣ ኣጸናኒዐያ ንነብሰይ፣ ኣረጋጊአዮ መንፈሰይ። ለካ ወሃቢ እምበር ኣይኮንኩን ሓታቲ፣ ተጸባዪ ኣይኮንኩን ተመጽዋቲ፣ ጥዕና ኣይትኽልኣኒ ምስ ተስፋ፣ እምረር እምበር ህይወት ከሰንፋ፣ ሙኻነይ እነኹ ኣሚነ፣ ዝሓዝክዎ ሒዘስ ኣመስጊነ። ኑሮ ከብዶኝ እያማረርኩ፣ ጤና የለሌውን ተመለከትኩ። አፅናናኋት ነፍሴን፣ አረጋጋሁት መንፈሴን። ለካ ሰጪ እንጂ አይደለሁም ጠያቂ፣ ተመፅዋች አይደለሁኝ ጠባቂ። ጤናን አይሳኝ ከተስፋ ጋር ሂወትን ላሸንፍ ምንም ቢመር መሆኔን አለሁኝ አምኜ የያዝኩትን ይዤ አመስግኜ...)