en
Feedback
ማጣላ ዋላና ሐዋርያዊት ቤተ-ክርስትያን

ማጣላ ዋላና ሐዋርያዊት ቤተ-ክርስትያን

Open in Telegram

“በሕይወቴ ሳለሁ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ፥ ለአምላኬም በምኖርበት ዘመን ሁሉ እዘምራለሁ።” — መዝሙር 104፥33

Show more
3 773
Subscribers
-324 hours
+337 days
+16530 days
Posts Archive
እንኳን ለ4ኛው ዓመት የአረካ ሳሌም ወጣቶች የወንጌል ኅብረት ጉባዔ በሠላም አደረሳችሁ❕ ሠላም የተወደዳችሁ የአንድ አምላክ ልጆች የሆናችሁ ወንድሞች እና እህቶች እንደምን ቆያችሁ❓ "ወጣቱ ብንያም በጕልበቱ በዚያ አለ፥" በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ በሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን በደቡብ ኢትዮጵያ ሰበካ በአረካ እናት አጥቢያ "የአረካ ሳሌም ወጣቶች የወንጌል ኅብረት" የተሰኘ ልዩ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ እናንተን በመጠበቅ ላይ ይገኛል። ይኸውም ከነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜ 01 ድረስ ለ2 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ስሆን በዚህ ልዩ ግብዣ ላይም፦ ✅ የእግዚአብሐር ቃል፣ ✅ የህብረት እና የግል ዝማሬዎች፣ ✅ እንዲሁም የተለያዩ ወጣት ተኮር የሆኑ አዝናኝና አስተማሪ ዝግጅቶች ተሰናድተዋል። ስለሆነም ሁላችሁም መጥታችሁ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጥሪ እናቀርባለን ተባረኩ❕ የአረካ ሳሌም ወጣቶች የወንጌል ኅብረት

የማልፈልገው ሰው በውስጤ አለ አብሮኝ በሰላም በጤና እየኖረ ከአምላኬ ሊያርቀኝ ምሎ ተገዝቶ ሌተ ቀን ያደባል ባጎረስኩት ነክሶ ስቀልልኝ ስቀልልኝ ግሩም ፈሪሳዊ ውጬን ብጠነቀቅ ከክፉ ሰዎች አፍ ከዋዘኞች ብርቅ ትልቁ ጠላቴ ልሸሸው የማልችለው አብሮኝ የሚኖር ይኀው ስጋዬ ይኀው ስቀልልኝ ስጋዬን መሻቴት ስቀልልኝ ስቀልልኝ ሞት የሃጢአት ደመወዝ የስጋዬ መዝዝ ላንተ እንዳልታዘዝ አያድርገኝ ስቀልልኝ ቅዱስ የጽድቅ ባሪያ የመንፈስ ማደሪያ ልዑል ምታርፍበት ንጹህ ልብን ፍጠርልኝ መንፈስህ ያግኘኝ ጸጋህ ብቻ ፍቅርህ ብቻ ካንተ ጋር ልስማማ እንዳልጠፋ ያዘኝ ጌታ ያላንተ እንዳይሆን የተናጠል ጉዞ ኃይልህ በሌለበት መልክ ብቻ ሆኜ ባዶ አድርገኝ የጽድቅ ባርያ የመንፈስ ማደሪያ የሱስ የሱስ የሚሸት የሚያፈራ በሁሉ ወቅት መንፈስህ ያግኘኝ ጸጋህ ብቻ ፍቅርህ ብቻ ካንተ ጋር ልስማማ እንዳልጠፋ ያዘኝ ጌታ ስቀልልኝ ስጋዬን መሻቴት ስቀልልኝ ስቀልልኝ @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

ቃሉን የሚያስተምረኝ ወደ እውነት የሚመራኝ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል የኢየሱስን ፍቅር በልቤ የሚያኖርልኝ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል ሰላምን ደስታን እረፍትን የሚሰጠኝ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል በመከራ ጊዜ ሳዝን የሚያጽናናኝ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል በድካሜ ጊዜ ኃይልን የሚያበዛልኝ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል መጸለይ ሲሳነኝ የሚቀሰቅሰኝ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል ህይወትን የሚቀድስ ነፍሴንም የሚያድስ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል ወደ ሰማይም የሚያነጥቀኝ የጌታ የኢየሱስ መንፈስ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገኛል መንፈስ ቅዱስ ሁሉንም የሚችል የአምላክ እስትንፋስ የሚባርክ የሚለውጥ ኃይል ነው ልቤን ከፍቼ ልቀበለው አንቀሳቅሰን ጌታ ሆይ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚከለክልህ ሰው ክንዱ ይሰበራል አንተ በክብር ስትመጣ በፊትህ እንውደቅ ስምህ ይገለጥ በይፋ በየትም ይታወቅ የአምልኮ ነፃነት የመንፈስ ብርታት እልልታ ጭብጨባ ምስጋና ጩኸት የደስታ የምልጃ እንባ መራጨት በጭራሽ እንዳይቀር ጌታ አደራህን መልእክተኞች መስራቾች ያስተጋቡ ይዝመቱ በጌታችን ቅዱስ ቃል እየተበረታቱ ፍቅሩ የሚደርስ ለነፍሳት የኢየሱስ ነፃነት ከውኃ ዳግም ተወልዶ መንፈስ ቅዱስ ማግኘት @matalapochurch

ፊትህ [ዛሬ] መጥቻለሁ አንተን ፈልጌ መጥቻለሁ ክብርህን ናፍቄ |፪ እንዳልመለስ በባዶ እኔን አስበኝ እንዳልመለስ በከንቱ አቤቱ ማረኝ ከብዙ ሸክም ጋር ወደ አንተ መጥቼ ባዶ እንዳልመለስ ደጅህ ቆይቼ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝና አጽንተህ አቁመኝ ፍትህ እንደገና ያለ ገደብ ያለ ልክ መንፈስህ እንድወርድ ሰማይ ተከፍቶ ክብርህን እንዳይ አዎ እኔን ማረኝ ደዌው እንድፈወስ ዕውሩ እንድበራ ታላላቅ ታአምራት እንድሰራ አዎ እኔን ማረኝ ማረኝ እያልኩ ጥለህ አትሂድ ማረኝ እያልኩ የሱስ ሲልህ ትተህ አትሂድ የሱስ ሲልህ በህዝብህ መሃል አንተ እንድሰራ ሰማይ እንድከፈት ክብርህ እንድያበራ አብዝቼ ጮሃለሁ እኔን ማረኝ ብዬ ቶሎ እንድያገኘኝ ይቅርታህ ጌታዬ ያለ ገደብ ያለ ልክ. ከኃጢአቴ ብዛት ምህረትህ ይበልጣል ፍቅርህ ልዩ ነው በኔ ላይ በርትቷል ታምኜ ቆምያለሁ በምህረትህ ዛሬ ትምረኛለህ አሜን አልጠራጠርም ማረኝ እያልኩ ጥለህ አትሂድ ሰማይ ምድርን የሞላህ አንተ ነህ እሩቅ አይደለህም ቅርብ ነህ የተሰወረ የለም በአንተ ፊት እኔንም አይተህኛል የኔ አባት ዛሬ በፊትህ ተንበርክኬ ዛሬ ከእግሮችህ ስር ወድቄ ዛሬ ምህረትህን ለምናለሁ ዛሬ ማረኝ እልሃለሁ ማረኝና አቤቱ አድምኝ ማረኝና ኢየሱስ ባርከኝ ማረኝና እኔንም አስበኝ ምህረትህ በቶሎ ያገኝኝ @matalapochurch @matalapochurch

አልፈራም ከቶ እንዳልፈራ አድርጎኛል አልሰጋም ከቶ እንዳልሰጋ አድርጎኛል አያዝንም ልቤ እንዳያዝን ሆኖልኛል በኢየሱስ ሙሉ በሆነው በእርሱ ሁሉ ተሰጥቶኛል     ሁሉ ደህና ደህና ነው     የሞተውን አኣላየው     ሁሉ ሰላም ነው ሰላም    ግድ የለኝም ቢቀበርም እንኳን ከባድ እንኳን ችግር ሙቱ ይወጣል ከመቃብር ይህን ልቤ ጠንቅቆ ያውቃል በኢየሱስ ይታመናል አምነዋለሁ ባዶ ማሰሮ በቤቴ ሞልቶ አምነዋለሁ ነገሬ ሞቶ ተስፋውን አጥቶ አምነዋለሁ ባልተመለሰው ፀሎቴም ቢሆን አምነዋልለሁ በእርሱ ተስፋ አለኝ አልፈራም ነገን     ባዶ ማድጋ ሞልቶ ይፈስሳል     የሞተው ህያው ሆኖ ይቆማል     ይስተካከላል ከባዱ ነገር     ሁሉ ይሰምራል ቃልን ሲናገር አምነዋለሁ ተስፋ ሚያደርገው አያፍርምና አምነዋለሁ ሕይወቴ ያለው በእጁ ነውና አምነዋለሁ በአፉ ተናግሯል በእጁ ይፈጽማል አምነዋለሁ ሊወድቅ አይችልም ከቶ አንድም ቃል       ሁሌ መልካምን በሚያደርገው       በበጎነቱ በሚታወቀው       ትናንትናዬን በእርሱ አልፌአለሁ       አያሰጋኝም ሊመጣ ያለው @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

በእየለቱ እንደ አዲስ በሚሆነው ነገር መገረሚያዬ ነህ ጌታዬ እግዚአብሔር መገረሚያዬ ነህ የእኔ አንተ የእኔ እግዚአብሔር በህይወቴ እንደ አዲስ በሚሆነው ሁላ መደነቂያዬ ነህ ኢየሱስ የእኔ ጌታ መደነቂያዬ ነህ አንተ የእኔ ጌታ አኖርከኝ ከልለህ መራኸኝ ተጠንቅቀህ ከበበኝ ማዳንህ በዛ ቸርነትህ ይበቃኝ ነበረ የበራልኝ ፊትህ በምህረት በፍቅርህ እኔን መቀበል ጠጋ አድርገህ ድምጽህን እያሰማኸኝ ደግሞ እንዲህ በእርጋታ የምታኖረኝ በሕይወቴ ለሊቶች ምስጋና እየወጣ ይገርመኛል ስቆም ልቤ እየበረታ የሚረዳኝ ጸጋ የሚያግዘኝ መንፈስ ጎሎብኝ አያውቅም ተባረክ ኢየሱስ አመሰግንሃለሁ ሁሌ እየበራ ሁሌ እየደመቀ በሚሄድ ፊትህ ፊት እጣዬ ወደቀ ዘለዓለሜን የክብር ተስፋ የሞላበት አረክልኝ ጠገብኩ በሰማይ በረከት መዳኔ ሳያንሰኝ ሕይወትን ማግኘቴ ክብርህን እያሳየኝ በእየለት ሕይወቴ ነገሬ በሙሉ ለምስጋና ሆኗል ሌላውም ስለእኔ ደስ ብሎት ይስቃል እኔ አመሰግንሃለሁ አመሰግንሃለሁ ምስጋና መልካም መልካም መልካም አምልኮ መልካም መልካም መልካም ዝማሬ ድል ማድረጊያ ጎዳና ስለሆነው ብቻ አይደለም ስለተደረገዉ በሁሉ ጌታን ማመስገን መልካም ነው የድልም ሁሉ ሚስጥር ማሸነፊያዉ ምስጋና ነው የተዘጋዉን ማስከፈቻዉ ድል ማድረጊያዉ ይብዛ ይብዛ ምስጋናዉ ይጨመርለት እልልታዉ ቤቱን ይሙላው ደመናዉ የበዛ ክብር ሙገሳዉ @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

በእየለቱ እንደ አዲስ በሚሆነው ነገር መገረሚያዬ ነህ ጌታዬ እግዚአብሔር መገረሚያዬ ነህ የእኔ አንተ የእኔ እግዚአብሔር በህይወቴ እንደ አዲስ በሚሆነው ሁላ መደነቂያዬ ነህ ኢየሱስ የእኔ ጌታ መደነቂያዬ ነህ አንተ የእኔ ጌታ አኖርከኝ ከልለህ መራኸኝ ተጠንቅቀህ ከበበኝ ማዳንህ በዛ ቸርነትህ ይበቃኝ ነበረ የበራልኝ ፊትህ በምህረት በፍቅርህ እኔን መቀበል ጠጋ አድርገህ ድምጽህን እያሰማኸኝ ደግሞ እንዲህ በእርጋታ የምታኖረኝ በሕይወቴ ለሊቶች ምስጋና እየወጣ ይገርመኛል ስቆም ልቤ እየበረታ የሚረዳኝ ጸጋ የሚያግዘኝ መንፈስ ጎሎብኝ አያውቅም ተባረክ ኢየሱስ አመሰግንሃለሁ ሁሌ እየበራ ሁሌ እየደመቀ በሚሄድ ፊትህ ፊት እጣዬ ወደቀ ዘለዓለሜን የክብር ተስፋ የሞላበት አረክልኝ ጠገብኩ በሰማይ በረከት መዳኔ ሳያንሰኝ ሕይወትን ማግኘቴ ክብርህን እያሳየኝ በእየለት ሕይወቴ ነገሬ በሙሉ ለምስጋና ሆኗል ሌላውም ስለእኔ ደስ ብሎት ይስቃል እኔ አመሰግንሃለሁ አመሰግንሃለሁ ምስጋና መልካም መልካም መልካም አምልኮ መልካም መልካም መልካም ዝማሬ ድል ማድረጊያ ጎዳና ስለሆነው ብቻ አይደለም ስለተደረገዉ በሁሉ ጌታን ማመስገን መልካም ነው የድልም ሁሉ ሚስጥር ማሸነፊያዉ ምስጋና ነው የተዘጋዉን ማስከፈቻዉ ድል ማድረጊያዉ ይብዛ ይብዛ ምስጋናዉ ይጨመርለት እልልታዉ ቤቱን ይሙላው ደመናዉ የበዛ ክብር ሙገሳዉ @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

አድስ መዝሙር ማደሪያህ ይድረስ የሾኔ ሐ/ቤ/ያን መዘምራን የልቤ ሸለቆ ተከፍቷል ለምስጋና በድንኳኔም ይሰማል የእልልታ የድል ዜማ ስለገባህ ኢየሱስ ዘልቀህ ወደ ቤቴ ሁሉ ደህና ሆነልኝ በመድሃኒቴ ስላደረክልኝ ምን እመልሳለሁ እንደ ሰርክ መስዋት እጆቼን አነሳለሁ ይብዛልህ አሁንም አሁንም እንደገና ብዙ ክብር ለአንተ የበዛ ምስጋና ይድረስ ወደ ማደሪያህ ይድረስ ያርግ ወደ ዙፋንህ ያርግ ምስጋናዬ በመላእክት ታጅቦ /2× ይሂድ ያውድ ሰማያት ደርሶ ጎልማሳነቴን እንደ ንስር ጉልበት አድሰሃል መሻቴንም ሁሉ መልካም ነገር አጥግበሃል ምስራቅ ከምዕራብ እንዴ ሚርቅ ኃጢያቴን አርቀሃል ምስጋናን ያፈልቃል ልቤ ምረትህን ይዘምራል ለኔ የዋልክልኝ ውለታህ ብዙ ነው በቃላት አይገለፅ ከሃሳቤም በላይ ነው በሥራህ ተደንቆ የልብ አይኔም በርቶ በመንፈስ ያመልካል ታምራትህን አይቶ ዝም የማያሰኘኝ ብዙ ምክንያት አለኝ አመስግን የምለኝ ካሰብኩት በላይ ስራህ አስገረመኝ መደነቅ ወረሰኝ ሰማያት ያዜሙ ምድርም እልል ትበል ሥራህን ትመስክር እንደ ዳዊት ቅኔን ነፍሴም ትቀኝልህ ለክብርህ ትዘምር ጠይቄ ሳልጠይቅም ብዙ ነው ያረክልኝ አረ እኔስ ላመስግንህ እዳ እንዳይኖርብኝ በቅዱሱ ጉባኤ ስዕለቴን እሰዋለሁ ምስጋናዬን ይዤ ወደ መቅደስህ ገባለሁ ኦሆሆ ለአምላክነትህ ኦሆሆ ለጌትነትህ ኦሆሆ ለቅድስናህ ኦሆሆ ለጌትነትህ ኦሆሆ ለቅድስናህ ይብዛልህ ለክብርህ ምስጋና አመልክሃለሁ ክብርህን እያየሁ ብርሃንህ በርቶ ደምቆ እያየሁ አመልክሃለሁ ፍትህን እያየሁ በመንፈስ ሆኘ ቅዱስ እላለሁ @matalapochurch2 @matalapochurch2

🎤 ዮናታን ፍቃዱ ዋላ ውሃን ፈልጋ እጅግ ተጠምታ እንድታገኘው የኔ የሱስ አንተን ብዬ መች አፍሬ መች አፍሬ የደረቀችው በለስ ምንጭ አግኝታ እንደምትረካ የሱስ ቤቴን አረከው ከወንዙ ዳር ካንተ ቦታ አሃ እረካሁኝ እሰይ እረካሁኝ የነፍሴን ጌታ ስላገኘሁኝ እረካሁኝ እረካሁኝ እንዲው በነፃ ስላገኘውኝ እረካሁኝ እረካሁኝ በድካም ህይወት ስመላለስ ስኖር ምድረበዳው ፀንቶብኝ አቅሜም ክዶኝ ነበር ውኃህን አጠጥተህ አነሳኸኝ እንደገና ተሻገርኩኝ ባንተ ብርታት መንፈስህ አፀናኝና እጅጉን የደከመ ምድረበዳው አይሎበት እጁን ሊሰጥ የቀረበ መራመድ መሄድ ከብዶት አቅመ ቢሱን ደካማ አረ እንደምን እረዳኸው በራሴማ አይሆንም ነበር ሀይል የሆነኝ መንፈስህ ነው @matalapochurch @matalapochurch

አድስ የአምልኮ መዝሙር መገዛት ክብሬ ነው ክብሬ ነው መገዛት የነፍሴን ዝማሬ በፊትህ ማምጣት ከሆነልህ ለአንተ ክብር ኢየሱስ መዘመር ማምለኬ ቀብተህ አቁመኝ ልሁን መልካም ባለ ቅኔ እንደገና እንደገና አመልክሃለሁ በህይወቴ ላይ ሃይልህን ደርብ እንጂ አነግስሃለሁ አመልክሃለሁ ከልቤ አነግስሃለሁ ከነፍሴ @matalapochurch @matalapochurch

የርህራሄ አባት ምህረትህ ለልጅ ልጅ ጎዶሎን ሚሞላ ሰፊ ነው ያንተ እጅ በእምነት በተስፋ ደጅህ እጠናለሁ የናዝሬቱ ኢየሱስ እፈልግሃለሁ የምትፈለግ አምላክ ነህ የምትፈለግ ጌታ ነህ ለሁሉ የሚበቃ ምህረት በእጅህ አለህ የተትረፈረፈ ፀጋ በእጅህ አለህ ፩) ነፍሴ ሁልጊዜ አንተን ብቻ ትፈልግሃለች የህይወት ውሃ ምንጭ ነህ ኢየሱስ ፍፁም የማትሰለች የልቤ ወዳጅ ፍለጋዬ የሱስ የኔ ጌታ እሰጥሃለው ንገስበት የልቤን ከፍታ *2 ፪) ሁሉ በሞላበት በተራራ ነህ አንተ ጥማቴ በወሰንከው ስፍራ በሸለቆ ደግሞ በረከቴ እገስግሳለሁ ወደፊት ግርማህን እንዳይ አስፈላጊ ነህ አንተ ለኔ ከምንም በላይ *2 እንጨት እና ውሃ በሌለበት ምድረበዳ ትፈልግሃለች ነፍሴ የሱስ አንተን ወዳ ለጥያቄ ሁሉ የኔ ወዳጅ መልስ ነህ በትውልዱ መሃል ዛሬም ትፈለጋለህ ክብርህን ላይ ናፍቃለሁ ፊትህን እፈልጋለሁ ናና ፈልግሃለሁ አንተን ተጠምቻለሁ የሱስ ፈልግሃለሁ ፫) ክብርህን በአይኔ በመቅደስህ ወዳለሁ አይ ዘንድ በአንተ ፍቅር ለዘላለም ልቤ እንዲነድ ይለወጥልኝ በፀጋህ ሀይል ድካሜ በብርታት የህይወቴ አምባ ኑር በልቤ ነህ የማትሰለች *2 እንጨት እና ውሃ .... እንደልጅነቴ ወራት አንተን እንዳገኘሁበት በልቤ ዙፋን ላይ ነግስህ የሱሴ ሁሌ እያየሁ ወደ ልቤ ተጠግቼ ከመንፈስህ ሀይል አግኝቼ በከፍታ ላይ መብረር የእውነት ለአንተ መኖር አማረኝ *2 ኢየሱስ ደግፈኝ Join us👇👇👇 @andiamlak01 @andiamlak01

Apostolic_mezmur#apostolic_song#Hosaina_main_church_mass_choir#.mp313.45 MB

አውቃለው የሚሳን እንደሌለህ አውቃለው የሚያቅት እንደሌለህ አውቃለው ሁሉንም ትችላለህ አውቃለው የኔ ጌታ አውቃለው እየሱስ ነህ አውቃለው ኤልሻዳይ አምላክ እንደሆንህ ተራራው በፊትህ መቆሙ ምንድነው ልታፈርሰው መዶሻው በእጅህ ነው ጨለማውም ቢሆን ትርጉም አልባ ነው በብርሃን ይተካል ስትናገርህው ያለቀውንና የተቆረጠውን ዳግም የምትቀጥል ተስፋ የታጣለትን እምነት የምትሆን የምትጨብጥ ለሞተው ህይወትን ደግመህ የምትሰጥ ጥቂት በጥቂቱ ጠብ ጠብ እያለ ነገሬ ተባርኮ ሞልቶ ይህው አለ ባንተ የእኔ ጌታ የሆነልኝ ነገር ልቤን ደስ አሰኘው ሞላኸው ከጥንትም ጀምሮ ክንድህ የታወቀ ሀያል እና ብርቱ ጠላትን ያደቀቀ እኔም በዘመኔ አይቼዋለው አልጠራጠርም እታመናለው @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

አየን እንደሰማን እንዲሁ አየን ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደሆንክ አየን      አየነው ማዳንህን      አየነው ክብርህን      አየን እውነትም ኢየሱስ አምላክ [ጌታ ነህ] ተራራው ተንዶ ሲሆነን ደልዳላ አየነው ዮርዳኖስ ሲሸሽ ወደሗላ በአምላክነትህ በመቻልህ ጉልበት ሁሉን አንተ ሰራህ ሁሉን አንተ አደረክ      መልካምነት ምግባርህ ነው      ለሁሉ ደግ ምታደርገው      ለፍጥረትህ ሁሉ ቸር      ስራህ ብዙ እግዚአብሔር ከባዱ ተሰርቶ ከቶ ያልተቻለው ታምራት ተደርጎ ሆኖልን አየነው እምነታችን ፀና በቃልህ ጠንክሮ ህያው በሆነው ቃል አየነው ተፈጥሮ     ጊዜ የሚታዘዝህ     ዘመን የሚገዛልህ     እንደ ጥንቱ ዛሬም አለህ     አርገህልን እያየንህ በሰማይ በምድር ዙፋንህ ፀንቷል አንተ ስትሰራ ማን ለምን ይላል በባህር መካከል መንገድ ሚሆንልህ ሁሉን ቻዩ አምላክ ድንቅ ነው ተግባርህ     አይተንሀል ስትሰራ     ተዐምራትህን ልናወራ     ስታቆመን  ስታፀና     ስትራራልን እንደገና ከእሳት ውስጥ ድምጽህን ሰምተናል አለፈህ ስትሰራ አይተናል ልናመሰግን መተናል @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

ታላቅ የምስራች 🙌 ከFeb/2025 እስከ March/2026 በአንድ አመት ውስጥ በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን፦ 81,369 አዳዲስ ነፍሳት ለኃጢአታቸው ስርየት በኢየሱስ ስም ተጠምቀዋል! 5,3
ታላቅ የምስራች 🙌 ከFeb/2025 እስከ March/2026 በአንድ አመት ውስጥ በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን፦ 81,369 አዳዲስ ነፍሳት ለኃጢአታቸው ስርየት በኢየሱስ ስም ተጠምቀዋል! 5,383 ነፍሳት በንስሐ ወደ አባታቸው ጉያ ተመልሰዋል! 54,021 ነፍሳት ለመጀመሪያ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው በአዲስ ቋንቋ ተናግረዋል! 53,177 ሰዎች ከተለያየ ደዌና በሽታ ተፈውሰዋል! 281 አዳዲስ አጥቢያዎች በሀገረስብከቱ ውስጥ ተከፍተዋል። ይህን ሁሉ ላደረገው ለአምላካችን ለኢየሱስ ክብርና ምስጋና ውዳሴና ኃይል ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን። አሜን! "ይህን የሠራና ያደረገ፥ ትውልድንም ከጥንት የጠራ ማን ነው? እኔ እግዚአብሔር፥ ፊተኛው በኋላኞችም ዘንድ የምኖር እኔ ነኝ።" (ት/ኢሳ 41፥4) ይሄ ደግሞ ቴሌግራም ቻናልችን ነው ይቀላቀሉን! 👉 @apostolic_tube2 @apostolic_tube2

ዘመኑ ደረሰ የተነገረው ኢዩኤል በትንቢት ይሆናል ያለው ሥጋ በለበሰ ፍጥረት ሁሉ ላይ የኋለኛው ዝናብ ሲዘንብ ልናይ ​ይወርዳል የተባለው የመንፈሱ ዝናብ ታላቅ ታናሽ አይልም ሁሉም ጋ ይዘንባል የደረቁ አጥንቶች ረስርሰው ነፍስ ዘርተው ይቆማሉ በመንፈስ ታላቅ ሰራዊት ሆነው ​ይወርዳል መንፈሱ አሁን /በኃይል ይወርዳል የተጠማችን ነፍስ ያረሰርሳል ይዘንባል ዝናቡ አሁን /በኃይል ይዘንባል ምድረበዳውንም ያለመልማል @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ! የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በምስራቅ አያት አጥቢያ የህብረት መዘምራን የተዘጋጀውን “ዛሬም ኢየሱስ ሙላቴ” የተሰኘውን የህብረት ዝማሬ
ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ! የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በምስራቅ አያት አጥቢያ የህብረት መዘምራን የተዘጋጀውን “ዛሬም ኢየሱስ ሙላቴ” የተሰኘውን የህብረት ዝማሬ ቁጥር 2 አልበም መለቀቁን ሲያበስር በታላቅ በደስታ ነው! አልበሙ እጃችሁ ባለው ስልክ ላይ በሚገኘው Apostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሆነ ሲሆን በኢትዮጵያ ያላችሁ ተጠቃሚዎቻችን ዝማሬዎቹን ለማውረድ የምትጠቀሙበትን ኮድ በቴሌግራም ቦት Apostolic Pay Bot ላይ፣ ከኢትዮጵያ ውጪ ያላችሁ ደግሞ ክሬዲት ካርድ በመጠቀም አልበሙን በመተግበሪያው ላይ ማውረድ እንደምትችሉ እንገልፃለን። በዚሁ አጋጣሚ የApostolic Songs መተግበሪያ የተለያዩ ማሻሻያዎች የተደረጉበት ሲሆን ወደ Play Store ወይም App Store በመሄድ አፕዴት እንድታደርጉ እያስታወስን የመተግበሪያው ስሪትም (APP Version 4.4.8) መሆኑን ታረጋግጡ ዘንድ ከአክብሮት ጋር እናስታውሳለን! የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል ሚያዚያ 2018 ዓ.ም