en
Feedback
ኡመተ ረሱል

ኡመተ ረሱል

Open in Telegram

የአላህ ሰላም እና እዝነት በናንተ ላይ ይውረድ ውድ የአላህ ባሮች በዚህ #channel ላይ የተለያዩ ♥ ኢስላማዊ አስተምህሮቶች ♥ አስተማሪ ታሪኮች ♥ ቀልዶች እና ♥ ወቅታዊ አሳሳቢ ነገሮችን ወደናንተ እናደርሳለን ፨ ፨ ፨ ለማንኛውም አስተያየት @Ummate_resul_bot ይጠቀሙ

Show more
1 977
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2930 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '24
September '24
+3
in 1 channels
August '24
+5
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '23
+2
in 0 channels
Get PRO
November '23
+3
in 0 channels
Get PRO
October '23
+8
in 0 channels
Get PRO
September '23
+3
in 0 channels
Get PRO
August '23
+2
in 0 channels
Get PRO
July '23
+10
in 0 channels
Get PRO
June '23
+9
in 0 channels
Get PRO
May '23
+3
in 0 channels
Get PRO
April '23
+3
in 0 channels
Get PRO
March '23
+6
in 0 channels
Get PRO
February '23
+3
in 0 channels
Get PRO
January '23
+2
in 0 channels
Get PRO
December '22
+3
in 0 channels
Get PRO
November '22
+11
in 0 channels
Get PRO
October '22
+12
in 0 channels
Get PRO
September '22
+8
in 0 channels
Get PRO
August '22
+17
in 0 channels
Get PRO
July '22
+17
in 0 channels
Get PRO
June '22
+25
in 0 channels
Get PRO
May '22
+43
in 0 channels
Get PRO
April '22
+147
in 0 channels
Get PRO
March '22
+202
in 0 channels
Get PRO
February '22
+330
in 0 channels
Get PRO
January '22
+575
in 0 channels
Get PRO
December '21
+790
in 0 channels
Get PRO
November '21
+350
in 0 channels
Get PRO
October '21
+162
in 0 channels
Get PRO
September '21
+75
in 0 channels
Get PRO
August '21
+181
in 0 channels
Get PRO
July '21
+357
in 0 channels
Get PRO
June '21
+24
in 0 channels
Get PRO
May '21
+12
in 0 channels
Get PRO
April '21
+104
in 0 channels
Get PRO
March '21
+75
in 0 channels
Get PRO
February '21
+38
in 0 channels
Get PRO
January '21
+35
in 0 channels
Get PRO
December '20
+2 398
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
20 September0
19 September0
18 September0
17 September0
16 September0
15 September0
14 September0
13 September0
12 September0
11 September0
10 September0
09 September0
08 September0
07 September0
06 September0
05 September+2
04 September0
03 September0
02 September0
01 September+1
Channel Posts
በሀገረ ሞሮኮ በሐውዝ ከተማ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ሰውነቷ ቆስሎ ከፍርስራሽ መሐል ተጋግጣ ወደ ሆስፒታል አቀናች። ራሷን አውቃ ስትነቃ ጋዘጠኞች ጥያቄ ሊያቀርቡላት ከሆስፒታሉ ቅጥር ከተሙ። ስ
በሀገረ ሞሮኮ በሐውዝ ከተማ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ሰውነቷ ቆስሎ ከፍርስራሽ መሐል ተጋግጣ ወደ ሆስፒታል አቀናች። ራሷን አውቃ ስትነቃ ጋዘጠኞች ጥያቄ ሊያቀርቡላት ከሆስፒታሉ ቅጥር ከተሙ። ስለሰለባው ሊጠይቋት ማይካቸውን አስጠጉ። ንፁኋ ሴት ግን ባሏ እስካልፈቀደላት ካሜራ ፊት ቀርባ ክስተቱን ለማውጋት ፈቃደኛ አለመሆኗን ተናገረች። @yesheh_kalidrashid_daewawoch @yesheh_kalidrashid_daewawoch

2
መነሻውን በሞሮኮ ያደረገው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር 6.7 ስኬል አልፎ በአልጄሪያና በሞሪታኒያ ድንበር ከተሞች እየተዛመተ ይገኛል። እስካሁን የሟቾች ቁጥር ከ 1000 ማለፉን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙ
መነሻውን በሞሮኮ ያደረገው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር 6.7 ስኬል አልፎ በአልጄሪያና በሞሪታኒያ ድንበር ከተሞች እየተዛመተ ይገኛል። እስካሁን የሟቾች ቁጥር ከ 1000 ማለፉን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን ዘግቧል። ጌታዬ ሆይ! ኃያልነትህን እንዳሳየካቸው እዝነትህን ቸራቸው @yesheh_kalidrashid_daewawoch @yesheh_kalidrashid_daewawoch
0
3
ካነበብኳቸው ልብ አስለቃሽ ታሪኮች 1- በስኳር በሽታ ለደከመችው እንስት "ህመሙ ሰውነትሽ ውስጥ እየተሰራጨ ነውና እጅሽ መቆረጥ አለበት" ተባለች። ደንገጥ ብላ እየተመለከተች "ልጄ ወደ ሌላ ሀገር ሊጓዝ ትንሽ ቀናት ስለቀረው አይሮፕላን ውስጥ ሲገባ እጄን አወዛውዤ እንድሰናበተው አንድ ሳምንት መጠበቅ እችላለሁን?" በማለት ጠየቀች። 2- ከምሽቱ 2 ሰአት ፈጣሪ አለመኖሩን የሚያትት ጽሁፍ በማስታወሻ ደብተሬ ላይ አስፍሬ ጎኔን ላሳርፍ አልጋዬ ላይ ተጋደምኩኝ። አላህ የሆነ ነገር እንዳያደርገኝ በመስጋት ማብራቱን ለማጥፋት ፈራሁ። 3- የእናቴን ጀናዛ በሲድር አጥቤ እንዳበቃሁ ከፈኗን ሚስክ እየቀባሁ የአፍንጫዋን ቀዳዳ ለመክደን ጥጥ ፈልጌ ተጣራሁ ጮክ ብዬ "እማ! ያንን ጥጥ ስጪኝ" አልኳት። 4- ባለቤቴ ከሚቀርበው ምግብ ውስጥ የረገፈ ፀጉሬን ሁሌ ስለሚያገኝ ንፅህናሽን የማትጠብቂ ቸልተኛ ሴት ይለኛል ካንሰር እንዳለብኝ ግን አያውቅም። #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
4
እንደ አውሮጳውያን የዘመን ቀመር 2016 በፍቅር የቀለሱት ጎጆ በእርሱ ህመም ደበዘዘ። በሽታ እያንፈራፈረ አልጋ ላይ አኖረው። ህመሙ በጠናበት አንድ ዕለት እንዲህ ተከሰተ። ፍራሹ ላይ ተንጋሎ ዓይኖቹ
እንደ አውሮጳውያን የዘመን ቀመር 2016 በፍቅር የቀለሱት ጎጆ በእርሱ ህመም ደበዘዘ። በሽታ እያንፈራፈረ አልጋ ላይ አኖረው። ህመሙ በጠናበት አንድ ዕለት እንዲህ ተከሰተ። ፍራሹ ላይ ተንጋሎ ዓይኖቹን እንደምንም እየገለጠ ያ ኡሙል-ሙቅረአይን ሲል ተጣራ። ሲወዳት አምሳያ የሌላት ሚስቱ ናትና እንዲህ ነው የሚጠራት። ሰባቱን ልጆቹን ቁርአንን እንድትሐሳፍዛቸው አደራ እያለ እስትንፋሱ ተቋረጠ። ወሲያ መሆኑ ነው። እርሷም አደራውን ተቀብላ ከዱንያ ውጣ ውረድ ጋር ታግላ እናትም አባትም ሆና ልጆቿን እያሳደገች ተራ በተራ ቁርአንን አስሐፈዘች። ከቀናት በፊት የመጨረሻው ሰባተኛው ልጇ ቁርአንን ሐፍዞ በመጨረሱ የምስክር ወረቀት ተበረከተላት። እንዲህ ያሉ እናቶች ሲኖሩ የኢስላም ክብር ዳግም ያብባል ኢንሻ አላህ። @yesheh_kalidrashid_daewawoch @yesheh_kalidrashid_daewawoch
0
5
ሰለዋት እናብዛ‼️ 🌴☘🌴☘🌴☘ ምን ያህሎቻችን ነን ጁምዓ ተጠባብቀን በረሱል [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] ላይ ሰለዋት የምናወርደው❓❓ ለምንድን ነው ከዚህ ትልቅ ስራ የምንዘናጋው❓❓ 📚እስኪ አላህና መልዕክተኛውን ምን እንደ ሚሉን እንመልከት 👇👇👇 🌴💥🕋🌴💥🕋 قال الله تعالى ﴿إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلّونَ عَلَى النَّبِيِّ يا أَيُّهَا الَّذينَ آمَنوا صَلّوا عَلَيهِ وَسَلِّموا تَسليمًا﴾ [الأحزاب: ٥٦] አላህ እንዲህ ይላል፦ {አላህና መላዒካዎቹ በነብዩ ላይ ሰለዋት ያወርዳሉ; እናንተ ያመናችሁ ሆይ በእሱ (በነብዩ) ላይ ሰለዋትና ሰላምን አውርዱ} 📖የአላህ መልዕክተኛም እንዲህ ይሉናል👇👇 "أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشرا " و حـسـنه الألباني في السلسلة الصحيحة 1407 {ጁምዓ ቀንና ጁምዓ ሌሊት በእኔ ላይ ሰለዋት አብዙ። በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰለዋት ያወረደ ሰው በእሱ ላይ አላህ አስር ጊዜ ሰለዋት ያወርድበታል} "من صلى علي مرة كتب الله له بها عشر حسنات" وصـحــحه العلامة الألباني رحمه الله في السلسلة الصحيحة (٣٣٥٩) {በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰለዋት ያወረደ ሰው አላህ ለእሱ በዚህ ምክንያት አስር ምንዳ ይፅፍለታል} " من صلى علي من أمتي صلاة مخلصا من قلبه صلى الله عليه بها عشر صلوات ورفعه بها عشر درجات وكتب له بها عشر حسنات ومحا عنه عشر سيئات " وصـحــحه العلامة الألباني رحمه الله في السلسلة الصحيحة ( ٣٣٦٠) {ከኡመቶቼ ውስጥ ከቀልቡ ጥርት አድርጎ በእኔ ላይ ሰለዋት ያወረደ የሆነ ሰው; አላህ በእሷ ምክንያት አስር ሰለዋት ያወርድበታል፣ አስር ደረጃም ከፍ ያደርግለታል፣ አስር ምንዳም ይፅፍለታል፣ አስር ወንጀልም ይሰርዝለታል} " من صلى علي واحدة صلى الله عليه عشرا " رواه أبو داود في سننه (١٥٣٠) وصححه الألباني رحمه الله {በእኔ ላይ አንድ ሰለዋት ያወረደ በእሱ ላይ አላህ አስር ያወርድበታል} 🌴🌱🌴🌱🌴🌱 "اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد، اللهم بارك على محمد وعلى آل محمد كما باركت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد" ✍"ወደ መልካም ያመላከተ እንደ ሰሪው ነው"‼ #share #Join @smithhk
0
6
"ያስተነትኑም ዘንድ ታሪኮችን ተርክላቸው" ፒ ዲኤ ፍ @yesheh_kalidrashid_daewawoch @yesheh_kalidrashid_daewawoch
0
7
ይህ መፅሐፍ ....... በሚያናውዝ የስቃይና የግፍ ትውስታ ጀምሮ ልብን በሐዘን አየናጠ በቁጭት ቀልብን አተራምሶ ወደ ጀግንነት መንደር ይዘልቃል። ገድላቸውን አያተተ በሀሴት ውስጥን ያረሰርሳል። የማ
ይህ መፅሐፍ ....... በሚያናውዝ የስቃይና የግፍ ትውስታ ጀምሮ ልብን በሐዘን አየናጠ በቁጭት ቀልብን አተራምሶ ወደ ጀግንነት መንደር ይዘልቃል። ገድላቸውን አያተተ በሀሴት ውስጥን ያረሰርሳል። የማር ወለላን የተላበሱ የአርአያዎቻችንን የፍትሕ ብርሐን ይተርካል። በምናብ ሰመመን ውስጥ አስጥሞ ያለንበትን የኑረት ሹረት አስወግዶ ከግሳንግስ ትርክምርኪ አርቲፊሻል ገጽታ አውጥቶ ውብ ከሆነው ዘመን ወደ ተምሳሌቶቻችን የሕይወት ገጽ ያዘልቀናል። አንዲያ ያለ ዓለም፣ አንዲያ ያለ መጣፈጥ፣ አንደዚያ ያለ ፍትሕ በተዋበ ልዕልነት ልስልስ ባለ ሙቀት ውስጥ ጥዶ አጀብ የሚያሰኝ ፍትሕን ይዳስሳል። ታሪክ መስራት ላቃተን ለአኔው ዘመን እርቃነ ገላዎች በከፊሉም ቢሆን ዓውራችንን በመሸፈን ከቦታው ያለን እስክንመስል ዱር ሸንተረሩን አልፈን አብረን አንዘልቃለን። በንዴት በደስታ በፈገግታ አየታጀብን እንነጉዳለን። እየዋለሉ የሚተራመሱ ነፍሶች ላይ ሕይወትን የዘሩ ተምሳሌቶችን በአስገራሚ የኑረት ኃይል ንዝረትን እየቃኘ ድንቃድንቅ ክስተቶችን አያወሳ ይጠናቀቃል። ትንፋሽ አያቆራረጠ በጥልቁ ወደ ኃያልነት ይመጥቃል። በጥልቅ ማንቀላፋት ውስጥ ያሉትን ወደራስጌያችው ጠጋ ብሎ የተጠቀለሉበትን አንሶላ ገፎ ንቁ እያለ ይጣራል። አንደጠዋት ፀሓይ በመስኮት ዘልቆ ያበራል አንሻአላህ። በ410 ገፅ ተሰናድቶ የተዘጋጀውን ይህን የፅሑፎቼን ስብስብ ኢንሻ አላህ ፒ ዲ ኤፉን ነገ በዚህ የቴሌግራም ቻናል እለቀዋለሁ አላህ የምንጠቀምበት ያድርገን። @yesheh_kalidrashid_daewawoch @yesheh_kalidrashid_daewawoch
0
8
አልጄሪያዊቷ ጋዜጠኛ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካን እየጎበኘሁ ነበር በማለት ገጠመኟን ማውጋት ጀመረች። "ዕቃ ለመግዛት ወደ አንድ ሱፐር ማርኬት አቀናሁ። ሒሳብ ለመክፈል ወረፋዬን እየጠበቅኩ ሳለ ሂጃቧን ጠንቅቃ የለበሰች አንዲት ሴት ወደ ሱፐር ማርኬቱ ገባች። የድካም ምልክቶች ይታይባታል። የሳር ማጨጃ ማሽን በእጇ ይዛለች። ክፍያ ለመቀበል ወደተቀመጠችው ሰራተኛ ዘንድ አቀናች። "ይህንን ማሽን በ500 ዶላር ከሌሎች ዕቃዎች ጋር ገዝቼ ነበር... በማለት ንግግሯን ጀመረች ደንበኛ በማስተናገድ የተጠመደችው ሰራተኛ ከአፏ ቀበል አድርጋ "መመለስ ፈልገሽ ነው ታዲያ?" በማለት ጠየቀቻት። ሙተሐጂባዋ ቀጠለች "ዋጋውን መክፈል ፈልጌ ነው....." ካሽ ሪጅስተር ማሽኑ ላይ የተጣደችው የሒሳብ ሰራተኛ "አልገባኝም ትናንት ገዛሁት አላልሽኝም? ሌላ ሱቅ ርካሽ አጊኝተሽ ከሆነ የዋጋው ማረጋገጫ እስካለሽ ድረስ ልዩነቱን አስልተን የምንመልስበት ፖሊሲ አለን" አለች። "ይሄም ያም አይደለም" በማለት ለማስረዳት መናገር ጀመረች "ትላንት በክሬዲት ካርዴ ይህንን ማሽን ከሌሎች ዕቃዎች ጋር ገዛሁ። መኖርያ ቤቴ ከሱፐር ማርኬቱ ሁለት ሰአታት ያህል ይርቃል። ቤት ገብቼ ሂሳቡን ማየት ስጀምር የዚህን ማሽን ዋጋ ከክፍያ ሪሲቱ ላይ አጣሁት። በዚህ ምክንያት በስራሽ ክፍተት እንዳይፈጠር ደረሰኙ ላይ ባገኘሁት ቁጥር ደግሜ ደጋግሜ ደወልኩኝ። የስራ ሰዓቱ አልፎ ነበርና ሊነሳልኝ ግን አልቻለም። ዛሬ ስራ አስፈቅጄ ማሽኑን ይዤ መጣሁ። መዝግበሽ ከሂሳብ እንድትከችውና ክፍያውን እንደ አዲስ እንድፈፅም አንቺ በእኔ ምክንያት ስራሽን እንዳታጪ እኔም ባልከፈልኩት ነገር እንዳላገለግል" ይህን የሰማችው ሰራተኛ ከመቀመጫዋ ተነሳች። ሙተሐጂባዋን እያየች አይኖቿ እንባ እንዳቀረሩ አቅፋ ትስማት ጀመር። "የእኔ ጥፋት ሆኖ ሳለ ገንዘቡን ለመክፈል እንዴት ተመልሰሽ ለመምጣት ወሰንሽ?" በማለት ጠየቀቻት። በአግራሞት ተጭራ "ይህን ከባድ ሳጥን ተሸክመሽ ከስራ ገበታሽ አስፈቅደሽ ደርሶ መልስ አራት ሰአታት የሚያስኬድ መንገድ አቋርጠሽ እኮ እንዴት?!" ሰራተኛዋ ተገረመች። ሙስሊሟ ሴት ምላሽ ሰጠች፡- "ምክንያቱም ይህ አማና ነው" አለቻት። በእስልምና የታማኝነትን ትርጉም አስረዳቻት የአማናን ክብደት አስተማረቻት። ቢሮ ውስጥ ወዳለው ስራ አስኪያጇ ወሰደቻት። ተያይዘው ገቡ። ከቢሮው መስታወት ጀርባ ብንመለከታቸውም የሚያወሩት ግን አልተሰማንም። የሱፐር ማርኬቱ ሰራተኛ ሙስሊሟ ሴት ያደረገችውን ​​ለማናጀሯ ስትነግራት ስሜታዊ ትመስላለች። ከደቂቃዎች በኋላ... ሥራ አስኪያጁ ሰራተኞቹን በመደብሩ ውስጥ ሰብስቦ ስለ ሙስሊሟ ሴት ማውራት ጀመረ። እሷ ሃይማኖቷ ያዘዛትን ግዴታዋን እንጂ ሌላ ምንም እንዳላደረገች በዓይን አፋርነት ስሜት አንገቷን ሰበር አድርጋ መግለፅ ጀመረች። ስለ እስልምናና አስተምህሮቱ ይጠይቋት ጀመር። እሷም በሚገርም የራስ መተማመን ቅንነትን በተላበሰ ትህትና መለሰች። ሥራ አስኪያጁ ማሽኑ እንደ ስጦታ ድርጅቱ ሊሰጣት ማሰቡን ነገራት። ነገር ግን ሽልማቷን ከአላህ ዘንድ እንጂ ማሽኑን ከፍላ መግዛት እንደምትችል ተናገረች። ይህ መልካም ስራዋ እንዲያበላሽላት እንደማትፈልግም ይቅርታ ጠይቃ አልቀበልም አለች። እነሱ እየተገረሙ እርሷም በዝግታ እየተራመደች የማሽኑን ዋጋ ከፍላ ከሱፐር ማርኬቱ ወጣች። ውስጤ በሐሴት ተናጠ። አንዳች ኩራት ተሰማኝ። ከሄደች በኋላ ስለ እሷ በሠራተኞቹ ብቻ ሳይሆን ዕቃ ሊገዙ በተሰበሰቡት ደንበኞች መካከልም ቀጠለ። ስለ ኢስላም መወራት ጀመረ። ይህ ኢስላም ነው ትክክለኛው የአላህ ዲን ተባለ። ድሮ ድሮ ሙስሊሞች ከአማና ጋር የጠበቀ ግንኙነት ነበራቸው አማናው የተቀመጠበትን የፌስታል ቋጠሮ እንኳ ሳይፈታ ዘመናትን ተሻግሮ ባለቤቶቹ ሲመጡ ዕቃቸውን እንዳስቀመጡት ያገኙት ነበር አሁን አሁን ግን የአማናችን ነገር ...... #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
9
ከአላህ ጋር ነግዶ ማን ከሰረ በሰባዎቹ መጀመሪያ በሀገረ ግብፅ ግዛት ተፈህና አል-አሽረፍ በምትሰኝ ትንሽዬ መንደር ውስጥ ምንም የሌለው ደሀ የግብርና መሃንዲስ ጣራዋ በተቀደደ፣ ግርግዳዋ በተፈረፈረ ደሳሳ የጭቃ ቤት ውስጥ ከወላጆቹ ጋር ጎጆውን ቀልሶ ይኖር ይዟል። ግርግዳው በጋዜጣ የተሸፈነ ቤት!! በወላጆቹ ልፋት ተምሮ ለወግ ማዕረግ በቅቶ ቢመረቅም ስራ ማግኘት ግን አልተቻለውም። ሰላህ አጢያ ይሰኛል። ያረጀ እንጂ አዲስ ልብስ ለብሶ አያውቅም። ትክክለኛው የጫማ ቁጥር 42 ቢሆንም ከቆሻሻ ገንዳ ያገኛትን 44 ቁጥር ጫማ እንዳታልቅበት በቀስታ እየረገጠ ይጓዝባታል። በግብርና ፋኩሊቲ ተመርቀው በከፋ ድህነት የሚሰቃዩ፣ ስራ ለመጀመር የሚፈልጉ ዘጠኝ የመንደራቸውን ሰዎች ሰብስቦ አነስተኛ ፕሮጀክት ለመጀመር ወሰነ። አማከራቸው ተስማሙ። አስረኛ አጋር እየፈለጉ እያንዳንዳቸው 200 የግብፅ ፓውንድ አዘጋጅተው ጠበቁ። ተሰብስበው ሻይ እየጠጡ ወደነበሩት አጋሮቹ ዘንድ አቀናና "አስረኛውን አጋር አግኝቻለሁ" አላቸው። "ማን እነደሆነ ንገረን" ሲሉ ጠየቁ "አላህ ነው" በማለት መለሰላቸው። "ገንዘባችንን ከአደጋ ለመጠበቅ፣ ኃብታችንን ለማፋፋት እርሱ አንደኛው አጋራችን ይሆናል" በማለት ንግግሩን አከለ። ሁሉም ተስማሙ። በጋራ የተቋቋመው የህብረት ኩባኒያ ውሉ ፀድቆ "አስረኛው ባለድርሻ አላህ የትርፉን አንድ አስረኛ ይወስዳል" የሚለው ቃል ከውሉ ወረቀት ላይ ሰፍሮ ሁላቸውም ፊርማቸውን አኖሩ። እውነተኛ የህብረት ስራ፣ ግልፅ ስምምነት ተደረገ። የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ዙር ውጤት ጥሩ ትርፍና የተለየ ምርት ማስተናገዱን ሲመለከቱ ለተገኘው ትርፍ ለአላህ ምስጋና ይሆን ዘንድ የምርት ዑደት ውጤቱን "የታላቁ አጋር ድርሻ" በሚል መጠኑን ለመጨመር የአላህን ድርሻ ወደ 20% ለማሳደግ ወሰኑ። በየአመቱ ከፍ እያለ የአላህ ድርሻ 50% ደረሰ። አርሰው ቡቃያውን ወቅተው ምርቱን ይሸጣሉ። ነግደው ካተረፉት የአላህን ድርሻ ሳያጓድሉ ሀቁን ጠብቀው ትክክለኛ ቦታ ላይ ያውላሉ። መስጂዶች፣ የሴቶች ሒፍዝ ማዕከል የአይታሞች ማደርያ የአቅመ ደካሞች መመገብያ ተቋማትን በአላህ ድርሻ ገነቡ። ትርፉ እያደገ ሲመጣ ለመሳኪኖች የዕርዳታ ድርጅትን አቋቋሙ.. በግብፅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ትንሽዬ መንደር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ አራት ኮሌጆችን ገነቡ። እያንዳዳቸው ለ600 ተማሪዎች የሚሆን ማደርያ 1000 ተማሪዎችን የሚያስተናግዱ ኮሌጆች! ማንኛውም የኮሌጁ ተማሪ ወደ ቀዬው ለመሄድ ሲፈልግ ነፃ ትኬት ማግኘት እንዲችል በይተል ማል የሚል ቢሮን አቋቋሙ። በመንደሩ ደሃ እስኪጠፋ ተቋሙ ፋፋ። ኸይራቱ ወደ ጎረቤት መንደሮች ጭምር ዘለቀ። ስራ አጥ ወጣቶች ከድህነታቸው ተላቀው እንዲሰሩ ተመቻቸላቸው። ለጎረቤት ሀገራት አትክልቶችን ኤክስፖርት ማድረግ ጀመሩ። ምርት በሚሰበሰብበት ወቅት ለከተማዋ ነዋሪ ከትልቅ እስከ ትንሹ የአትክልት ከረጢት በስጦታ ይበረከትላቸው ገባ። በረመዳን የመጀመሪያዎቹ ቀናት ኢፍጣር ተዘጋጅቶ ወንዶች በአደባባይ ሴቶች በየቤታቸው በፍቅር በአብሮነት ተሰብስበው ያፈጥራሉ። ወላጅ አልባ ሴቶች ለትዳር ሲደርሱ ወጪያቸው ተሸፍኖ ይዳራሉ። ይህ ሁሉ በአላህ ድርሻ የሚሰራ መልካም ተግባር መሆኑ ያስገረማቸው መስራቾቹ የፕሮጀክቱ ባለቤትነት ወደ አላህ እንዲዞር ወሰኑ። እነርሱም የአላህ ሰራተኛ የረቢ አገልጋይ ሆኑ። ባለቤትነቱን ወደአላህ ሲያዞሩ "ትርፉ ሳይቋረጥ ድሆች ይጠቀሙ ዘንድ ጌታችን ሆይ አደራ!" የሚለውን ቃል ከውሉ ወረቀት ላይ አሰፈሩ። አትራፊ ንግድ!! መልካም ግብይይት!! "አላህ ከምእምናን ነፍሶቻቸውንና ገንዘቦቻቸውን ጀነት ለእነሱ ብቻ ያላቸው በመኾን ገዛቸው" ይሉሀል ይህ ነው። ኢንጂነር ሰላህ አጢያ በ70 አመታቸው በጉበት በሽታ ሲሰቃዩ ቆይተው እንደ አውሮጳውያን የዘመን ቀመር ጥር 11 ቀን 2016 ሩሐቸው ከጀሰዳቸው ተላቀቀች። ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ ጀናዛቸውን ሸኘ። እየተላቀሱ ጀሰዳቸውን ከለህዱ አሳረፉ። ልጅ አልነበራቸውም። አላህ ከምህረቱ አጎናፅፎ ጀነተል ፊርደውሱን ይወፍቃቸው። ╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍ ምንጮቼ:- - الشيخ خالد الجندي ينعي صلاح عطية نسخة محفوظة 25 فبراير 2020 - تفهنا الأشراف قرية بلا عاطل أو فقير نسخة محفوظة 17 مايو 2017 - صلاح عطية رجل أعمال تاجر مع الله نسخة محفوظة 12 مايو 2017 على موقع واي باك مشين #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
10
"ሡልጣን ሆይ! ሰላትህን በጀመዓ አትሰግድምና ምስክርነትህ ተቀባይነት የለውም..." ╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍ አሁን የምንገኝው በሙስሊሞች ዋና ከተማ ቡርሳ ነው። በታላቁ መሪ በሱልጣን ባየዚድ ቢን ሙራድ ዘመነ መንግስት! ቡልጋሪያን፣ ቡርሳንና አልባኒያን ድል አድርጎ የከፈተው የክፍለ ዘመኑ ኃያል መሪ ቃዲ ሸምሰ ድ-ዲን ዘንድ በአንድ ጉዳይ ላይ የምስክርነት ቃሉን ሊሰጥ ከፊታቸው ተጥዷል። እንደማንኛውም ምስክር እጆቹን አጣምሮ ከችሎቱ ፊት ቆሟል። ዳኛው ዓይኑን አማትሮ ሡልጣኑን እየተመለከተ ከእግር እስከ ራሱ በትኩረት ቃኘ "ሡልጣን ሆይ!" አለ ዓይን ዓይኑን እያየ። ታዳሚው በዝምታ ተውጦ የዳኛውን ንግግር ለመስማት ጆሮውን ቀሰረ "ሡልጣን ሆይ! ሰላትህን በጀመዓ አትሰግድምና ምስክርነትህ ተቀባይነት የለውም። ሰላቱን በጀመዓ የማይሰግድ በምስክርነት ቃሉ ሊዋሽ ይችላልና አይታመንም ተብሎ ስለሚገመት ያንተን ምስክር አንቀበልህም ሂድ" አሉት። በፍርድ ቤቱ የተገኙ የዳኛውን ንግግር የሰሙ ታዳሚያን በድንጋጤ አይናቸውን ለጠጡ። ሡልጣን ባይዚድን በሰዎች ፊት ዝቅ ያደረገውን ዳኛ መጨረሻ ለማየት፣ ለዳኛው እየፈሩ ባሉበት ቦታ ተቀመጡ። ችሎቱ ፀጥ ረጭ አለ። ሡልጣን ባየዚድ አንዲትም ቃል ከአፉ ሳያወጣ አንገቱን ከመሬቱ እንደደፋ በእርጋታ እየተራመደ ፍርድ ቤቱን ለቆ ወጣ። በዚያው ቀን ከቤተ መንግስቱ አጠገብ መስጂድ እንዲሰራ አዘዘ። ተገንብቶ እንዳለቀ ሰላቱን ሳያዛንፍ አምስቱንም አውቃት በጀመዓ የሚሰግድ የአላህ ባርያ ሆነ። ይህ ፍትህ የንግስና መሰረት፣ የኢስላም ዳኞችና ዑለማኦች ከአላህ በቀር ማንንም በማይፈሩበት ወቅት የተገኘ አስገራሚ ታሪክ ነው ╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍ ምንጮቼ:- إنباء الغمر بأنباء العمر الشقائق النعمانية في علماء الدولة العثمانية حديقة السلاطين روائع من التاريخ العثماني، سيرة السلاطين الأوائل #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
11
https://t.me/serionlineshoping
0
12
የጌታዬን ውዴታ ተችሬ በፊርደውሱ እንፈላሰስ ዘንድ በመላኢካኦች ታጅቤ ወደ ውስጥ ስዘልቅ ወደ ፊርአውን ሚስት ወደ አሲያ ዘንድ አቀናለሁ "እንዴት ነበር" ብዬ እጠይቃታለሁ "ግዙፉን ድንጋይ በሆድሽ ተሸክመሽ የፀሐዩ ሐሩር እያነደደ በወላፈኑ ሲገርፍሽ ረሐብና ጥሙ ሲጠናብሽ እንዴት ነበር የቻልሽው ግርፋትና ስቃዩን?! እንዴት ነበርስ ስሜቱ" ወደ ሙስዓብ አመራለሁ ዱንያን እርግፍ አድርገህ ስትሰደድ እንዴት ነበር ያ ፅናትህ?! በኡሁድ ዘመቻ ከሸሂድ ተርታ ተሰልፈህ ከአንዲት ቁራጭ ፎጣ በቀር መከፈኛ ታጣልህ። ጭንቅላትህ ሲሸፈን እግርህ እየተገለጠ እግርህን ሲያለብሱህ ጭንቅላትህ እየታየ ሲቸገሩ ነቢ ውስጣቸው በሐዘን ደምቶ ጀናዛህን ሊሰናበቱ ሲመጡ ከአይናቸው እምባ እየረገፈ የተከፈንክባትን ሸካራ ቁራጭ ልብስ እያዩ "መካ ውስጥ ለስላሳና በጌጥ የተሸቆጠቆጠ ልብስ ለብሰህ አይቼሃለሁ፡፡ ዛሬ ደግሞ ፀጉርህ በአቧራ ተሸፍኖ መከፈኛ አጣህ!" ብለው ስቅስቅ ብለው ሲያለቅሱ ብታይ እንዴት ትሆን ነበር ቢገለፅ የውስጥ ስሜትህ?! በጀነት ወደተበሰሩት አስሩ ሰሐቦች ዘንድ በዝግታ እራመዳለሁ የኔ ውዶች እንዴት ናችሁ እያልኩ ግንባራቸውን ደጋግሜ እስማለሁ ለመሆኑ ጀነት እንደምትገቡ እያወቃችሁ እንቅልፍ እንዴት ወሰዳችሁ?! ስል እጠይቃቸዋለሁ። ያለህን ሁሉ ተቀምተህ የምትለብሰው የምትቀምሰው አጥተህ ከሞቀው ከደላው ቤትህ ስትባረር ገላህ እንዳይታይ ጆንያ ለሁለት ከፍለህ አንዱን አሸርጠህ ሌላኛውን አገልድመህ ነቢን ለመገናኘት የፀሀዩን ግለት የበረሃውን ሙቀት ተቋቁመህ መካ ደርሰህ የናፈቅካቸውን ረሱልን ለመመልከት አይኖችህን ሽቅብ ስታንከራትት ያን ጊዜ ድንገት ከፊትህ ስታያቸው እንዴት ነበር ስሜቱ? እስኪ ንገረኝ ዙል ቢጃደይኑ?! ወደ ሠይዲ ቢላል አቀናለሁ አንተ ጥቁር ባርያ ስለስቃይህስ አላወራ ግን ግን አሳዳሪህ በጋለ ድንጋይ ላይ አስተኝቶ ሲያሰቃይህ ጣዖት ወደማምለክ ከመመለስ ይልቅ "አሐድ... አሐድ... በማለት ፅናትህን ስትገልፅ ብርታትህ እንዴት ነበር?! አንተ የአላህ መልእክተኛ ባልደረባ እባክህ አዛንህን ልሰማ?! እያልኩ እማፀነዋለሁ። ወደ አሊይ ዘንድ አቀናለሁ ገና ለጋ ወጣት ሳለህ የአላህ መልእክተኛ ፍራሽ ላይ ለመተኛት ምን አስቻለህ ስል እጠይቀዋለሁ?! አቡበከር ሆይ አንተ ሲዲቁ ሰው ሐቢቢ መሞታቸውን ስትናገር ፅናቱን ከየት አምጥተኸው ይሆን? ከቶ በምን ብርታት በሰሐቦች መሐል የአላህ መልዕክተኛ ሞተዋል ብለህ ለመናገር ከሚንበሩ ተሰየምክ? በልብህ ስስነት፣ በርህራሄህና በለስላሳነትህ የምትታወቀው አንተ የእንባህን ዘለላ ከዓይኖችህ አብሰህ እንዴት በጥንካሬ መቆም አስቻለህ?! ከሰዪዲ ከሐቢቢ ጋር ተቀምጬ አወራለሁ። ግንባራቸውን ደጋግሜ እየሳምኳቸው አወጋለሁ። በቅርቢቱ ዓለም በዱንያዋ ህይወት እርስዎን ማየት ሳልምና ሳስብ ኖርያለሁ። በፍቅርዎ ሰመመን ስምዎን ስደጋግም፣ ዓይኖቼ በዕንባ ተሞልተው ናፍቆትዎ አዋለለኝ። እርስዎን በማየቴ ያከበረኝ አላህ የተመሰገነ ይሁን እላቸዋለሁ። ፊቱን ለመመልከት ከታጨሁ መጋረጃው ተገልጦ ጌታዬን ለማየት ከታደልኩ ከድንጋጤዬ ብዛት ላወራው እንኳ የምችል አይመስለኝም ግን ግን በእንባዬ ዘለላ ታጅቤ እንደምወደው እነግረዋለሁ አዎ ደግሜ ደጋግሜ እወድሀለው እለዋለሁ ጌታዬ ሆይ!! ከምንወዳቸው ሰዎች ጋር በጀነትህ ታቀማጥለን ዘንድ እጠይቅሀለው!!! #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
13
የጓደኛው ቤት ደጃፍ እንደቆመ ሲፈራ ሲቸር እያመነታ በሩን በቀስታ አንኳኳ። ተከፈተለት አይኑን ከመሬቱ እንደተከለ ለጓደኛው እንዲህ አለ፡- "ብዙ ጊዜ የሆነኝ ዕዳ ሰላም ነሳኝ ጧት ማታ አበዳሪዬ ሲጠይቀኝ የምከፍለው ገንዘብ አጣሁ። የማደርገው ግራ ቢገባኝ ችግሬን ላካፍልህ ወዳንተ መጣሁ" ወደ ውስጥ ተመለሰና አራት መቶ ዲርሀም ቆጥሮ ሰጠው። በደስታ ሲፍለቀለቅ ተሰናብቶት እያለቀሰ ወደቤት ዘለቀ። ይህን ሁሉ ተደብቃ ስትከታተል የነበረችው ሚስት የባሏን ለቅሶ ስታይ "ለምን ታለቅሳለህ? ብሩን መስጠት ከብዶህ ከሆነ ይቅርታ የለኝም ብለህ ምክኒያት ፈጥረህ አትመልሰውም ነበር?" አለችው "ያስለቀሰኝስ ያለበትን ሁኔታ ሳልከታተል በመቅረቴ ተቸግሮ እስኪጠይቀኝ ድረስ ቸልተኛ መሆኔ ነው" አላት። ኡኹዋ #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
14
"ዓለምን ያለሰይፍ የከፈታችሁ! የኢስላምን ጦር ያሳረፋችሁ ብርቱዎች! ስብስባችሁ ሁሉም ሥፍራ የደረሰ! ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ጎናችሁ ያላረፈ! በዘመናችሁ የኢስላም ጠላቶችን ረፍት ነሳችሁ! ሚሽነሪዎ
"ዓለምን ያለሰይፍ የከፈታችሁ! የኢስላምን ጦር ያሳረፋችሁ ብርቱዎች! ስብስባችሁ ሁሉም ሥፍራ የደረሰ! ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ጎናችሁ ያላረፈ! በዘመናችሁ የኢስላም ጠላቶችን ረፍት ነሳችሁ! ሚሽነሪዎችን አደከማችሁ! ዱር ገደሉን አልፋችሁ እልም ካለው ገጠር መሐል ከተማችሁ! ምቾታችሁን ትታችሁ ወንድሞቻችሁን ለማዳን ራሳችሁን ሰዋችሁ! እናንተ የዳዕዋ ሰዎች ሆይ! ማንም ጋር ያላየነው ሺህ ፍቅርና መውደድ በእርግጥም እናንተ ዘንድ ነበር። አኽላቅና ዙህድን የተማርነውም ከናንተው ነው። በር አንኳኩታችሁ ዘይራችሁ ተሰድባችሁ ተባራችሁ በትዕግስት እንደፀናችሁ ስንቱን ከመስጂድ ጋር አስተዋወቃችሁ" በታላቁ ሙጃሂድ ዐብደላህ ኢብኑ አዛም ንግግር ፅሑፌን ልቋጭ "ምርጥ ስነ ምግባርን የተላበሱ ሙጃሂዶች" ይሏቸዋል ስለነርሱ ሲያወጉ። "ሰካራሞችን ከቡና ቤት ወደ መስጂድ እጃቸውን ይዘው እየተራመዱ ረጅሙን መንገድ አብረዋቸው ይጓዛሉ። መስጂድ አድርሰዋቸው እነርሱ ይመለሳሉ። በእርግጥም ስህተት የሌለበት ጭፍራ የለም። በውስጡ ያለውን መልካም ነገር እናጣጥላለን ማለት ግን አይደለም" @yesheh_kalidrashid_daewawoch @yesheh_kalidrashid_daewawoch
0
15
"ከሰውነቴ የቱን ልሸፍን" በማለት ነበር አባቷን የጠየቀችው። እሱም ዓይኖቿን እያየ "ከጀሀነም እሳት መቋቋም የምትችዪውን የአካል ክፍልሽን ከፍተሽ ተጓዢ" በማለት መለሰላት። #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
16
የአጭሩ ታሪክ መጨረሻ በመላኢካዎች ተቀፍድዶ የጀሐነም በራፍ ላይ ቆመ። ዓይኖቹን አሻግሮ ሲመለከት ጓደኞቹ የሉም። ወደ ኋላው ዞሮ ወላፈኑ እየለበለበው የታሉ ጓደኞቼ በማለት መላኢካዎቹን ጠየቀ። ካንተ ሞት በኋላ ቶበቱ ዓቢድ ሆነው ጌታቸውን ተገናኙ ብለው ይመልሱለታል። #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
17
ከዕለታት በአንዱ ውሸት ከእውነት ጋር ገላጣ ሜዳ ላይ ተገናኙ። "የዛሬው ቀን በጣም ያምራል" አለ ውሸት ዙርያውን እያየ። እውነት ይህንን ንግግር ስትሰማ በጥርጣሬ አካባቢውን ቃኘች። አይኖቿን ወደ ሠማይ አቅንታ ግራ ቀኙን ተመለከተች። በእርግጥም ቀኑን ውብ ሆኖ አገኘችው። አየሩም ለስላሳ ነበር። ዛሬን ከውሸት ጋር ለመዋል ወሰነች። በመንገዳቸው ላይ በፅጌረዳ የተከበበ ሐይቅ መሳይ ውሃን ተመለከቱ። "ምንኛ ያማረ ኩልል ብሎ የሚፈስ ጣፋጭ ውሀ ነው!" አለ ውሸት እግሮቹን ለመንከር እየተጠጋ። እውነት ለሁለተኛ ጊዜ ውሸትን በጥርጣሬ እየተመለከተች ውሃውን በመዳፏ ዳበሰች። ጥርት ያለ ቆንጆ ሆኖ አገኘችው። ልብሳቸውን አወላልቀው ወደ ሐይቁ ዘለቁ። ውሀውን በእጃቸው እየጨለፉ ሰውነታቸውን ታጠቡ። እየዋኙ ከወዲህ ወዲያ ተንጎራደዱ። የእውነትን ወደ መሐል መጠጋት ያየው ውሸት ተስፈንጥሮ ከውሃው ወጣ። በፍጥነት የእውነትን ልብስ አጥልቆ ወደፊት ሮጠ። እውነት ድንገት ስትባንን ውሸት አጠገቧ አልነበረም። ራቁቷን ወደዳርቻው ስትጠጋ ልብሶቿ የሉም። አሻግራ አየች። ውሸት የእርሷን ልብስ ለብሶ ሲሮጥ ተመለከተች። ልትይዘው ራቁቷን ወደርሱ እየሮጠች በመንገዷ ላይ ከሰዎች ጋር ተገናኘች። በቁጣ በንዴት እየተጠቋቆሙ አፈጠጡባት። ፊታቸውን አዙረው ጀርባቸውን ሲሰጧት በፍርሀት እንደተሸማቀቀች ወደ ሀይቀ ጉርጓዱ ተመልሳ ተደበቀች። ለሁለተኛ ጊዜም ከዚያ ስፍራ መውጣት አፈረች። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ውሸት የእውነትን ካባ ለብሶ ይዞራል። አለምም ይቀባበሉታል። በዚያው ልክ እርቃኗን የቀረችውን እውነት ግን ፈፅሞ ማየት አይፈልጉም። #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
18
እነዚህ ጫጩቶች ካጥለቀለቃቸው ጎርፍ በዚህ ነጠላ ጫማ ላይ ተንሳፈው ተደጋግፈው ቆመዋል። ህይወት ላንተ ዋጋ በማትሰጠው ነገር ሌሎችን ታስደስታለች። ላንተ ዋጋ ቢስ ርካሽ የሆነው ነገር ሌሎች ዘንድ የ
እነዚህ ጫጩቶች ካጥለቀለቃቸው ጎርፍ በዚህ ነጠላ ጫማ ላይ ተንሳፈው ተደጋግፈው ቆመዋል። ህይወት ላንተ ዋጋ በማትሰጠው ነገር ሌሎችን ታስደስታለች። ላንተ ዋጋ ቢስ ርካሽ የሆነው ነገር ሌሎች ዘንድ የህይወት ዋጋ ሊኖረው ይችላልና ትንሽ ናት ብለህ አትናቅ። @yesheh_kalidrashid_daewawoch @yesheh_kalidrashid_daewawoch
0
19
ከሱብሒ ሰላት በፊት ቀደም ብዬ ካይሮ ኤርፖርት ደረስኩ ይሉናል የታሪካችን ተራኪ ሸይኽ ሙሐመድ ሳዊ። ሰዓቱ ለሊት ስለነበር የመስጂድ ኢማም ወደሆነው ወዳጄ ዘንድ ደወልኩ። "ገና አሁን መግባቴ ነውና መስጂድ መጥቼ እስከ ንጋት አብሬህ እቆይ ዘንድ የመስጂዱን በር ክፍት ተውልኝ" አልኩት። ሻንጣዬን ሸክፌ በዝግታ እየተራመድኩ መስጂዱ በራፍ ላይ ደረስኩ። መብራቶቹ በርተዋል። አንድ ሰው ሚህራቡ አቅራቢያ ሱጁድ ተደፍቶ አላህን ያናግራል። "ጌታ ሆይ ከዚህ በላይ መታገስ አቃተኝ አልቻልኩም ደከመኝ ከአንተ በቀር ማንም የለኝ ወዴት ልሂድ ወደማንስ ልጠጋ አረ ተው ጌትዬ!..." እያለ እነዚህን ቃላት ይደግማል። ሰውነትን የሚያንቀጠቅጥ አስደንጋጭ ዱዓ!! ዕንባን የቀላቀለ አስቸኳይ መልስን የሚሻ ልመና!! ከነፍሴ ጋር አወጋሁ በአላህ እምላለሁ ይህ ለቅሶ ኃጢአት ከሠራ ሰው የሚመነጭ አይደለም ችግር ያቆረፈደው መከራና ሐዘን የከበበው ሰው ልመና ነው እያልኩ ባለሁበት ቆምኩ። እስኪጨርስ ጠብቄ ወደ ሰውየው ተጠጋሁ። ሲያየኝ ዝም አለ። "ወንድሜ!" አልኩት "ምን ነካህ? ምን አገኘህ?!" በማለት ጠየቅኩት። ከረዥም ዝምታና ውትወታ በኋላ፡- "በአላህ እምላለሁ ምን እንደምል አላውቅም ነገር ግን ባለቤቴ ነገ ጠዋት ኦፕራሲዮን ታደርጋለች። ለቀዶ ጥገናው የሚያስፈልገኝ 15,400 ፓውንድ ነው። ስባሪ ሳንቲም ስለሌለኝ ጌታዬ እንዲያበድረኝ እየጠየቅኩት ነው" አለኝ። "የምረዳህ ገንዘብ ባይኖረኝም አላህ የተደገፈበትን እንዲሁ የማይተው መሐሪ ጌታ ነውና አብሽር" ብዬው ዊትሬን ሰግጄ ተኛሁ። ጎህ ቀዶ ሙአዚኑ ለፈጅር ሰላት ቀሰቀሰኝ። ሱብሒን ባንተ መስገድ እንፈልጋለንና ተቀደም አለኝ። ሰግደን እንዳበቃን ከሦስተኛው ሰፍ ረጅም ካፖርት የለበሰ ሰው እኔ ወዳለሁበት አቅጣጫ ተጠጋ። ሞቅ ባለ ሰላምታ ፈገግታን እየቸረኝ እንዴት ነህ? አለኝ። ፕሮግራምህንና ትምህርቶችህን እከታተላለሁ ከመስጂዱ ፊት ለፊት የሚገኝን አፓርታማ የገዛሁት ከጥቂት ጊዜ በፊት ነው። አንተን ለማየትና ሰላም ለማለት በመታደሌ አልሐምዱሊላህ" አለኝ። "እንኳን ደህና መጣህ አላህ ይባርክህ" አልኩት ሰላምታውን እየመለስኩ። ተመቻችቶ እየተቀመጠ ንግግሩን ቀጠለ:- "ጌታዬ ወሰን በሌለው ፀጋው አክብሮኛል፤ የፕላስቲክ ፋብሪካ ባለቤት ነኝ። ሁለተኛውን ቅርንጫፍም በቅርቡ ከፍቻለሁ። ምስጋና ለአላህ ይገባውና ዘካውን ሳሰላ 15400 ፓውንድ ... " ንግግሩን ሳይጨርስ በለቅሶዬ አቋረጥኩት። መላ አካሌ በድንጋጤ ተንቀጠቀጠ። ከሱ በቀር ሌላ አምላክ በሌለው ጌታ እምላለሁ ይህ ሰው የጠራው የገንዘብ መጠንና ያ ከሱብሂ በፊት ያገኘሁት ወንድም ቸግሮት የፈለገው የብር መጠን አንድ ነበር። ያን ሰው በአይኔ ፈለግኩት "ምን ነካህ ሸይኽ?" አለኝ በሁኔታዬ ግራ እየተጋባ "ትንሽ ታገሥ" አልኩት። ሰውየውን አየሁት። ወደ እኛ እንዲመጣ በምልክት ጠራሁት። ከፊታችን ተቀመጠ። አይኖቹ በለቅሶ ብዛት አሞጭሙጨዋል። እስኪ ሐጃህን በድጋሜ ንገረኝ አልኩት። "ሚስቴ ዛሬ ጠዋት ኦፕራሲዮን እንደምታደርግ፣ ገንዘብ እንደሌለኝ ነግሬሀለው" አለኝ "ቀዶ ጥገናው ስንት ብር ያስፈልገዋል" አልኩት። "15400 ፓውንድ" ነጋዴው በተክቢራ መስጂዱን እየናጠ ምርር ብሎ አለቀሰ! ወደ ደረቱ አስጠግቶ እያቀፈው እንዲህ አለ፡- "በአላህ እምላለሁ ባለቤቴ ይህንን የአላህ ሀቅ ለሚገባው ባለሐቅ ወስደህ ስጥ እያለች ጠዋት ማታ ትወተውተኛለች። ሐቢብቲ መቶ መቶ እየቆነጠርኩ መስጠት አልሻም። የቂያማ ቀን አላህ ከጭንቅ ይገላግለኝ ዘንድ ሙሉ ገንዘቡን ለተቸገረ አንድ ሰው ሰጥቼ ከጭንቀቱ ገላግዬ ለደስታው ሰበብ መሆን እፈልጋለሁ እላታለሁ" ገንዘቡን በሙሉ አመጣና ለሰውየው ሰጠ። እየሆነ ያለውን አላመነም። ገንዘቡን ሲቀበል እኔንም ነጋዴውንም ትቶ ገንዘቡን በእቅፉ እንደያዘ ሱጁድ ወረደና እንዲህ አለ:- "ጌታዬ ሆይ! እወድሃለሁ እንደምትወደኝም አውቃለሁ" ዩሒቡሁም ወዩሂቡነህ ይሉሀል ይህ ነው። ችክ ብሎ በሲድቅ አላህን የለመነና የተቸገረን ሰው ከጭንቅ ለመፈረጅ በኢኽላስ የታተረ ሁለትዮሽ ዱዓ ሲገጥም የሚሆነው እንዲህ ነው። እንደዚያም ተፈፀመ። ታሪኩ አልቋል የዓለማቱ ጌታ ስጦታዎች ግን አያበቁም....... ሸይኽ ሙሐመድ ሳዊ ገጠመኛቸውን ከተናገሩበት የድምፅ ቅጂ የተተረጎመ። #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0
20
ሳቋ ከልብ ነው በወጣሁ በገባሁ ቁጥር በመንገዴ ዳር አገኛታለሁ። እጅን በአፍ የሚያስጭን ውበትን ተላብሳለች። ስታምር እያስባለች ዓይንን ታዋልላለች። ሲበዛ አፈቀርኳት። በመልእክተኛው ሱና መሰረት ግን እጇን ስሜ ለጋብቻ ልጠይቃት አልታደልኩም ይላል ትረካውን ሲጀምር። እንዳፈቀርኳት እንኳ ሳልነግራት ሑቤን በልቤ ቋጠሮ ደበቅኩላት። ህመም የቀላቀለ ናፍቆቷ ሲለበልበኝ ሱጁድ ወርጄ ከአላህ ጋር መነጋገር ጀመርኩኝ። ለሊት እየተነሳሁ ጌታዬን እለምነው ገባሁ። ከቀን ወደቀን ቀልቤ ውስጥ የከተመው ፍቅሯ እያበበ መጨመሩ ኸይርን እንዳስብ አደረገኝ። ግና... አለን ትንፋሹን ሰብስቦ ንግግሩን ቀጠለ። የአላህ ውሳኔ ቀደመኝ። ፍቅሯ እየለበለበ በቅጡ እንኳ ማዘን መተከዝ ተሳነኝ። የልቤ ቁስል ደምቶ ሳይመረቅዝ ለሰርጓ ተጠራሁ። ከነቤተሰብህ ዝለቅ የሚል ጥሪ ቤታችን ደረሰ። አገባች። ከየት መጣ ሳይባል ወደቤቱ ወሰዳት። እያየኋት አጣኋት። ያቺን መሳይ ጉብል የራሴ አደርጋለሁ እያልኩ ከአፌ ጠልፎ ወሰዳት። በሰርጓ ቀን ቀላል ስጦታ ላኩላት። "ብታገቢም በአላህ ላይ ያለኝ እምነትና ቸርነቱ አልደፈረሰም" የሚል ደብዳቤ አያይዤ ሰደድኩላት። ለእሷ ያለኝ ፍቅር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በልቤ ውስጥ ላትረሳ ታተመች። በትዕግስት በዱዓ የተዋጀውን የአላህን ውሳኔ ከመልካም ጥርጣሬ ጋር ከመጠበቅ ያለፈ አቅም አነሰኝ። ከ3 ወራት በኋላ የባሏ እስትንፋስ ቀጥ ብሎ ጌታውን ተገናኘ። አጀሉ ደርሶ እሕል ውሐው ሲቋረጥ እርጉዝ ነበረች። የሐዘኗ ጊዜ ተጠናቆ ዒዳዋ እንዳበቃ ወንድ ልጅን ተገላገለች። ራሴን አዘጋጅቼ ጠበቅኳት። ሽማግሌ ልኬ ለጋብቻ ጠየቅኳት። በእሺታ ተስማምተው ኒካሐችን ፀደቀ። ዘወጅናከ ሲሉኝ ተስገብግቤ ቀቢልቱ አልኩኝ። የአላህ ቸርነት ለእኔ ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?! አላህ ለኔ የዋለልኝ መልካም ውለታ እርሷን የኔ እንድትሆን ማድረጉ አልነበረምን?! ለምን አትለኝም?! ምክንያቱም ከትዳራችን በኋላ ልጅ መውለድ እንደማልችል በምርመራ ተረጋገጠልኝ። ልጇ ልጄ ሆነ። እሷም ከእኔ ሳትነጠል ለመኖር ወሰነች። ቤታችን በፍቅር በደስታ ተሞላ። አዛኝ ለሆነው አላህ ምስጋና ይግባውና አሁን ሁለታችንም ቁርአንን ሐፍዘን ጨርሰናል ይላል ታሪኩን ሲቋጭ። አስታውስ! በአንድ ነገር ላይ ድርሻህ ከአላህ ዘንድ ከተወሰነ ሚዛኑ ተገልብጦ ታገኘው ዘንድ ይመቻችልሀልና ዱዓህን በስክነት እያደረግክ ውሳኔውን በእርጋታ ጠብቅ!! #ሼር #share #join Https://t.me/smithhk
0