Lideta Sub City Small Tax Payer Branch Office
Open in Telegram
This is official Telegram Channel of Lideta Sub City Small Tax Payer Branch Office. Join the channel.
Show more1 153
Subscribers
+524 hours
+237 days
+11130 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+36
in 0 channels
August '26
+91
in 0 channels
Get PRO
July '26
+79
in 0 channels
Get PRO
June '26
+61
in 0 channels
Get PRO
May '26
+29
in 0 channels
Get PRO
April '26
+14
in 0 channels
Get PRO
March '26
+18
in 0 channels
Get PRO
February '26
+39
in 0 channels
Get PRO
January '26
+36
in 0 channels
Get PRO
December '25
+36
in 0 channels
Get PRO
November '25
+37
in 0 channels
Get PRO
October '25
+34
in 0 channels
Get PRO
September '25
+36
in 0 channels
Get PRO
August '25
+84
in 0 channels
Get PRO
July '25
+62
in 0 channels
Get PRO
June '25
+12
in 0 channels
Get PRO
May '25
+48
in 0 channels
Get PRO
April '25
+43
in 0 channels
Get PRO
March '25
+37
in 0 channels
Get PRO
February '25
+12
in 0 channels
Get PRO
January '25
+10
in 0 channels
Get PRO
December '24
+14
in 0 channels
Get PRO
November '24
+48
in 0 channels
Get PRO
October '24
+462
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 10 September | 0 | |||
| 09 September | +5 | |||
| 08 September | +4 | |||
| 07 September | +1 | |||
| 06 September | +3 | |||
| 05 September | +1 | |||
| 04 September | +6 | |||
| 03 September | +5 | |||
| 02 September | +4 | |||
| 01 September | +7 |
Channel Posts
| 2 | 2018_የሂሳብ_መዝገብ_ማቅረቢያ_ቅጽ_ከነማብራሪያው.xlsx | 326 |
| 3 | የ2018_በጀት_ዓመት_አመታዊ_ግብር_ለማሳወቅ_የሂሳብ_መዝገብ_በኦንላይን_ሲቀርብ_በe_mail_ሊላኩ_የሚገባቸዉ.docx | 395 |
| 4 | በሂሳብ_መዝገብ_ለ2018_ግብር_ዘመን_የሚያሳውቁ_ግብር_ከፋዮች_ማያያዝ_ያለባቸው_ሰነዶች1.docx | 232 |
| 5 | በአዲስ አበባ ከመኪና አስመጪዎች ጋር በተያያዘ የታክስ ስወራ ወንጀሎች በመከላከል ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት ለማስፈን በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ነሀሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፣ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በዛሬው ዕለት ከመኪና እመጪዎች ጋር በተያያዘ ጋዜጣዊ መግለጫውን ሰጥቷል፡፡
በቢሮው የህግ ተገዢነት ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዱራሃማን በጋዜጣዊ መግለጫው እንዳሉት በተለያዩ የክልሎች ንግድ ፈቃዶች መኪኖችን ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገቡ፣ ማንነታቸው የማይታወቅ የመኪና አስመጪዎች በአዲስ አበባ ውስጥ በኮምሽን ሰራተኞች አማካኝነት ለኮምሽን ስራ በወጣ ንግድ ፈቃድና አድራሻ በመጠቀም ሽያጭ ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡
በታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ማንኛውም የመኪና አስመጪ ሽያጭ ሊያከናውን የሚችለው ንግድ ፈቃድ ባወጣበት አድራሻ መሆኑን የገለፁት አቶ መሀመድ የከተማ አስተዳደሩ ከወራዊ ቫትና ከዓመታዊ ግብር ማግኘት የሚገባውን ግብር ላለመክፈል በተለያዩ ክልሎች በወጣ ንግድ ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ በኮምሽን ሰራተኞች አማካይነት የሚካሄድ የመኪና ሽያጭ ህገወጥ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አስመጪዎች በክልል ንግድ ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ ሽያጭ ለማከናወን በቅድሚያ ንግድ ፈቃዳቸውን አዲስ አበባ ውስጥ ማስጠቀስ፣ ደረሰኝ መለየት፣ የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽኑን ማስተካከል፣ አዲስ አበባ ውስጥ ለተካሄደ ሽያጭ ወራዊ ቫት እና ዓመታዊ ግብር ለከተማ አስተዳደሩ በወቅቱ የመክፈል ግዴታ እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ውጭ አሁንም አንዳንድ አስመጪዎች ከታክስ አስተዳደር አዋጁ በተፃረረ መልኩ በተለያዩ ክልሎች ንግድ ፈቃድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ተሸከርካሪዎችን በአዲስ አበባ ለመሸጥ ንግድ ፈቃዳቸውን ሳያስጠቅሱ በየመንደሩ የሚካሄዱ ሽያጮች ህገወጥ በመሆናቸው ቢሮው የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም በአዲስ አበባ የመኪና ሽያጭ ሥራ የሚያከናውን ማንኛውም አስመጪ በቅድሚያ መኪኖቹን አዲስ አበባ ውስጥ ለመሸጥ የክልል ንግድ ፈቃዱን ማስጠቀስ፣ የመሸጫ ስፍራ በመከራየት በሕጋዊ የንግድ ቦታ መሸጥ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም በአዲስ አበባ ውስጥ ላካሄደው ሽያጭ ተገቢውን ደረሰኝ ለይቶ በመስጠትና የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን በማስተካከል ለከተማ አስተዳደሩ ወርኃዊ ቫት ማሳወቅና ዓመታዊ ግብር መክፈል እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
የኮምሽን ስራ ፈቃድ ያላቸው ግለሰቦችም በምንም መልኩ አዳዲስ መኪኖችን ከአስመጪዎች በመቀበል መሸጥ እንደማይችሉ የተናገሩት ኃላፊው ይሁንና ያገለገሉ ተሸከርካሪዎችን ግን ተገቢውን መረጃዎች ለክፍለ ከተማቸው የገቢዎች ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በማሳወቅ ሽያጭ ማከናወን እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በከተማዋ ከመኪና ሽያጭ ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ የታክስ ስወራና የሕግ ጥሰቶችን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመቀናጀት የቁጥጥርና የሕግ ማስከበር ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በተጨማሪም በከተማዋ የሚከናወን ማንኛውም የመኪና ሽያጭ ግልጽ፣ ሕጋዊና በትክክለኛው የታክስ ሥርዓት ውስጥ እንዲካሄድ ለማድረግ አስመጪዎችና ነጋዴዎች የሕግ ግዴታቸውን እንዲወጡ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል። | 477 |
| 6 | ለታክስ ከፋይነት መመዝገብ ያለባቸው እነማን ናቸው?
ማንኛውም ሰው ማንኛውንም የንግድ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ቀደም ብሎ በታክስ ከፋይነት መመዝገብ ይኖርበታል። ለዚህም አስቀድሞ የተመዘገበ ካልሆነ በስተቀር በታክስ ሕግ መሠረት ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት ሰው በባለሥልጣኑ ዘንድ ለመመዝገብ ማመልከት አለበት፡፡
• ለታክስ ከፋይነት መመዝገብ ያለባቸው …
👉 በንግድ ወይም በሙያ ሥራ (መቀጠርን ሳይጨምር) የተሰማራ ግለሰብ፣
👉 ቤት በማከራየት ገቢ የሚያገኝ ግለሰብ፣
👉 ተቀጣሪ፣
👉 የመንግሥት የልማት ድርጅት፣
👉 የመንግሥት ባለበጀት መሥሪያ ቤት፣
👉 መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣
👉 የሃይማኖት ተቋማት፣
👉 የንግድ ማህበር፣
👉 በኢትዮጵያ ነዋሪ ባልሆነ ኩባንያ በቋሚነት የሚሠራ ድርጅት፣
👉 የወጪ መጋራት ተጠቃሚዎች፣
👉 በጋራ ሃብትነት ያልተመዘገበ ሃብት ያላቸው ሰዎች፣
👉 ባለ ልዩ መብት፣
👉 በመንግሥታት መካከል የሚደረግ ስምምነት በጽሕፈት ቤት ማቋቋሚያ ስምምነት የሚቋቋም ድርጅት እንዲሁም
👉 የኩባንያ አክሲዮን ባለድርሻ ናቸው። | 571 |
| 7 | No text... | 762 |
| 8 | በቅ/ፅ/ቤቱ በኢ-ታክስ ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በልደታ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ ንግድ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ግብር ከፋዮች ኢ-ፋይልንግ እና ኢ- ፔይመንት ላይ በቀን 21/12/2018 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ፡፡
የዕለቱ ስልጠና በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የኤልክትሮኒክስ ታክስ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ፀደቀ ማዴቦ አመካኝነት ተሰቷል፡፡
በመጨረሻም ከተሳተፊ ግብር ከፋዮች የስልጠና ሰነዱን መሰረት በማድረግ የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄዎች ባለሙያዎች ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተሰቶ የዕለቱ ስልጠና ተጠናቋል፡፡ | 764 |
| 9 | No text... | 655 |
| 10 | No text... | 661 |
| 11 | No text... | 1 |
| 12 | No text... | 69 |
| 13 | ከቴምብር ቀረጥ ነጻ የሆኑ
👉 በመንግሥት በጀት የሚተዳደሩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፤
👉 የአስመጪነት ፈቃድ ያላቸው ነጋዴዎች ለሽያጭ የሚያስመጡት ንብረት በአስመጪዎቹ ስም ሲመዘገብ፤
👉 መንግሥት ባጸደቃቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች እና ኮንቬንሽኖች መሠረት ሰነዶች ነጻ ሊደረጉ ይችላሉ፤
👉 ተመሳሳይ መብት የተሰጠ መሆኑ ሲረጋገጥ ገንዘብ ሚኒስቴር ኢምባሲዎችን፣ ቆንስላዎችን እና ዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖችን ከቴምብር ቀረጥ ነጻ ሊያደርጋቸው ይችላል፤
👉 የአክሲዮን ድርሻ የምስክር ወረቀት ሲመዘገብ፤
👉 ለኢንቨስትመንት በሚወሰድ ብድር የመያዣ ሰነድ፤
👉 አዲስ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ንግድ ሥራ አክሲዮን ማህበር ለጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞቹ በዱቤ ግዥ የሚያቀርባቸው የካፒታል ንብረቶች በስሙ ሲመዘገብ፤
👉 በኤክስፖርት ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ለሥራ ማስከጃ ከሚወስዱት ብድር ጋር ተያይዞ የሚገኝ የመያዣ ሰነድ፤
👉 የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ሴቶች በገቢ ምንጭነት እንዲጠቀሙባቸው ከመንግሥት የተሰጡት ተሸከሪካሪዎች የባለቤትነት ስም ዝውውር ሰነድ፤
👉 የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅራቢ ድርጅት የማዳበሪያ አቅርቦት ለአርሶ አደር ለማደል ከሚወስደው ሜርቸንዳይዝድ ብደር ጋር በተገናኘ የመያዣ ሰነድ፤
👉 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለኢንተርፕራይዞች ለሊዝ ፋይናንስንግ ሥርዓት የሚያቀርባቸው ተሽከሪካሪዎች በባንኩ ንብረት ባለቤትነት ስም ማስመዝገቢያ፡፡ | 652 |
| 14 | No text... | 1 |
| 15 | 📣 ለግብር ከፋዮች በሙሉ፦ ስለ አዲሱ የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ አዋጅ (ቁጥር 1434/2018) ማወቅ የሚገቡዎት ዋና ዋና ነጥቦች! 📣
የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅን ለማሻሻል የወጣው አዋጅ ቁጥር 1434/2018 ከሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (July 30, 2026) ጀምሮ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ፀድቋል። አዋጁ የታክስ አሰራሩን ፍትሐዊ፣ ቀልጣፋ እና ዘመናዊ ለማድረግ በርካታ አዳዲስ መብቶችና ግዴታዎችን ይዞ ወጥቷል።
እነዚህን ዋና ዋና ለውጦች በአጭሩ ይወቁ፦
🔹 1. የታክስ አለመግባባትን በስምምነት (Conciliation) የመፍታት መብት
ከታክስ ባለስልጣኑ ጋር አለመግባባት ከተፈጠረ፣ ጉዳዩን በገለልተኛ አካል አመቻችነት በስምምነት/በዕርቅ መጨረስ ይቻላል።
አሰራሩ ሙሉ በሙሉ በፈቃደኝነት እና በሚስጥራዊነት ላይ የተመሰረተ ነው።
ልዩ ዕድል፦ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት ይግባኝ ብለው ክርክር ላይ ያሉ ግብር ከፋዮች፣ ጉዳያቸው በዕርቅ እንዲያልቅ አዋጁ ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ በ60 ቀናት ውስጥ ማመልከቻ ማቅረብ ይችላሉ።
🔹 2. በሁኔታ ላይ የተመሰረተ የታክስ ምስክር ወረቀት (Conditional Tax Clearance)
የታክስ ዕዳ ያለበት ግብር ከፋይ በቅሬታ/ይግባኝ ሂደት ላይ ከሆነ ወይም የክፍያ ስምምነት (Installment Agreement) ከፈጸመ፣ በሁኔታ ላይ የተመሰረተ ክሊራንስ ማግኘት ይችላል።
ጥቅሙ፦ የንግድ/የሙያ ፈቃድ ለማደስ፣ በጨረታ ለመሳተፍ፣ የተሽከርካሪ/ማሽነሪ ምርመራ ለማድረግ እና የባንክ ብድር ለማግኘት ያገለግላል።
🔹 3. የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ማስተካከያ እና ይርጋ
ስህተትን ማረም፦ በታክስ ውሳኔ ላይ የሂሳብ/የስሌት ስህተት፣ አዲስ ማስረጃ ወይም የህግ ትርጉም ግድፈት ካለ ባለስልጣኑ ወይም በግብር ከፋዩ ጥያቄ ውሳኔው ሊስተካከል ይችላል።
የይርጋ ጊዜ፦ በመደበኛ ሁኔታ የራስ ታክስ ስሌት ከቀረበበት ወይም ውሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ የ5 ዓመት የይርጋ ጊዜ አለው። የታክስ ማጭበርበር ከተረጋገጠ ግን የይርጋ ጊዜው ወደ 10 ዓመት ከፍ ይላል።
🔹 4. ደረሰኝ አለመስጠት እና አስተዳደራዊ ቅጣቶች
ደረሰኝ አለመስጠት፦ ደረሰኝ ሳይሰጥ በሚቀርብበት በእያንዳንዱ ግብይት ላይ 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ብር አስተዳደራዊ ቅጣት ይጣላል። ይህ ቅጣት በባለስልጣኑ ሊነሳ አይችልም።
የወንጀል ተጠያቂነት፦ ደረሰኝ አለመስጠት ወደ ወንጀል ክስ የሚቀየረው በአንድ የግብር ዘመን ውስጥ ለሁለት ጊዜያት ያህል አስተዳደራዊ ቅጣት ከተቀጡ በኋላ ድርጊቱ ለ3ኛ ጊዜ ከተፈጸመ ብቻ ነው።
የሃሰት ደረሰኝ/ዋጋ ማሳነስ፦ በአንድ ግብይት ላይ ተመሳሳይ ደረሰኝ ላይ የተለያዩ ዋጋዎችን በመመዝገብ ዋጋ ማሳነስ 100,000 ብር ቅጣት እና ከ5 እስከ 7 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።
🔹 5. የድርጅቶች እና የኃላፊዎች ተጠያቂነት
በድርጅት ደረጃ የታክስ ጥሰት ሲፈጸም፣ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ወይም የፋይናንስ ኃላፊ ተጠያቂ ይሆናሉ።
ነገር ግን ድርጊቱ ከእውቀታቸው ውጭ መሆኑን፣ ያላዘዙ/ያልተባበሩ መሆኑን ወይም መከላከል የሚያስችል የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት የዘረጉ መሆኑን ካስረዱ ነፃ ይሆናሉ። | 832 |
| 16 | No text... | 981 |
| 17 | በቅ/ፅ/ቤቱ በተጨማሪ እሴት ታክስ ላይ ስልጠና ተሰጠ።
በልደታ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት አዲስ ለተጨማሪ እሴት ታክስ ለተመዘገቡ ግብር ከፋዮች በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 አፈጻጸም እና ድንጋጌዎች ጋር ተያይዞ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
የዕለቱ ስልጠና በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና ድጋፍ ከፍተኛ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ከድር ሀምደላ አመካኝነት የተሰጠ ሲሆን ስልጠናው በአዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጁ አፈጻጸም ላይ እና በአዲሱ አዋጅ የተካተቱ አሰራሮች፣ የህግ ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የዕለቱን ስልጠና የሰጡት አቶ ከድር ሀምደላ እንደገለፁት ስልጠናው አዲስ ለተጨማሪ እሴት ታክስ ለተመዘገቡ ግብር ከፋዮች በአዋጁ አፈጻጸም ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ግብር ከፋዮች ህጉን ተረድተው በግንዛቤ ላይ የተመሰረተ የታክስ ህግ ተገዥነት ባህል እንዲያሳድጉ አሳስበዋል ።
በመጨረሻም ከተሳተፊ ግብር ከፋዮች የስልጠና ሰነዱን መሰረት በማድረግ የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን የዕለቱን ስልጠና በሰጡት በአቶ ከድር ሀምደላ አመካኝነት ለተነሱ ጥያቄዎች ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተሰቶ የዕለቱ ስልጠና ተጠናቋል፡፡ | 850 |
| 18 | +2 VAT Regulation 570-2017.pdf (2).pdf | 721 |
| 19 | No text... | 703 |
| 20 | አዲስ የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 | 687 |
