en
Feedback
ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

Open in Telegram
1 734
Subscribers
-124 hours
-27 days
+2530 days
Posts Archive
🌼በአዲስ አመት አበባየሽወይ(አበባየሆሽ) አገልግሎታችን ላይ የተነሱ የፎቶ እና የVideo ማስታወሻዎችን ለማግኘት ይህን የግቢ ጉባኤያችንን የቴሌግራም ገጽ ይጎብኙ🌼 👇👇👇
https://t.me/peterosphotos
ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

🌼በአዲስ አመት አበባየሽወይ(አበባየሆሽ) አገልግሎታችን ላይ የተነሱ የፎቶ እና የVideo መረጃዎችን ለማግኘት ይህን የግቢ ጉባኤያችንን የቴሌግራም ገጽ ይጎብኙ🌼 👇👇👇
https://t.me/peterosphotos
ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

🌼አበባየሆሽ🌼 የዛሬው የአዲስ አመት አገልግሎታችን አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔርን አገልግሎታችንን ቀና እንዲያደርግልንና በሰላም እንዲያስፈጽመን በጸሎት ጠይቀን ከሰፈረ ሰላም የጀመርን ሲሆን እሰይ
+3
🌼አበባየሆሽ🌼 የዛሬው የአዲስ አመት አገልግሎታችን  አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔርን አገልግሎታችንን ቀና እንዲያደርግልንና በሰላም እንዲያስፈጽመን በጸሎት ጠይቀን ከሰፈረ ሰላም የጀመርን ሲሆን
እሰይ ደስ ደስ ይበላችሁ ቅዱስ ዮሐንስ መጣላችሁ ደስ ደስ ይበላችሁ
በማለት የአዲሱን ዓመት ብስራት እያበሰርን፣እግዚአብሔር አምላካችን እድሜ ለንስሃ ብሎ አዲስ ዓመት ስለጨመረልን እያመሰገንን፣ለቀጣዩም አመት ይህን ምርቃታችንን መርቀን አገልግሎታችንን በጸሎት ፈጽመናል።
ከብረው ይቆዩን ከብረው ከዓመት አውደ ዓመት ደርሰው ንስሃ ገብተው ቆርበው የፍቅር ሸማን ለብሰው በተዋህዶ ጸንተው ከብረው ይቆዩን ከብረው
አሜን ለቀጣዩም አመት በምግባር በሃይማኖታችን ጸንተን በሰላም እንድንደርስ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁን፣አገልግሎታችንንም ይቀበልልን🙏 በዛሬው አገልግሎታችን ለተሳተፋችሁ እህት ወንድሞቻችን፣በአገልግሎት የጀመራችሁት አዲስ አመት እግዚአብሔርን ደስ በማሰኘት የምትፈጽሙት የበረከት የጸጋ ዓመት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን። ስለ ቀና አገልግሎታችሁ ስላሳያችሁን ፍቅርና ታዛዥነት እግዚአብሔር ያክብርልን ብለናል🙏 መሳተፍ ፈልጋችሁም በልዩ ልዩ ምክንያት መገኘት ያልቻላችሁ የግቢ ጉባኤያችን አባላት፣እግዚአብሔር አምላክ አዲሱን አመት የፍሬ የበረከት ያድርግላችሁ፣ለቀጣዩም አመት በሰላም ደርሰን አብረን እንድናመሰግን እግዚአብሔር አምላካችን ይርዳን🙏 🌼መልካም አዲስ አመት!🌼 ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

በዛሬው የአበባየሆሽ አገልግሎታችን መሀል ላይ መቀላቀል የምትፈልጉ ልጆች በእነዚህ ስልኮች ደውሉልን። 0984540057 0938807056 ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! እንኳን ለርኅወተ ሰማይ፣ለቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!  
ጳጉሜ 3 ቀን የከበረ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሩፋኤል በዓሉ ነው፡፡ እርሱም ከመላእክት አለቆች ሦስተኛ የሆነ ነው። ደግሞም ከእስክንድርያ ውጪ በደሴት የታነጸች ቤተ ክርስቲያኑ በከበረ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የተገለጠባት የከበረችበት ነው።
🕊  ርኅወተ ሰማይ 🕊 ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት፣አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፣ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን" ትባላለች:: አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ። እመቤታችን ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል። በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት [መሪነት] በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል:: 🕊 ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት 🕊 ቅዱስ ሩፋኤል ከሰባቱ ሊቃነ-መላእክት አንዱ ነው። ሊቀ-መላእክትነቱም "መናብርት" በሚባሉ መላእክት ላይ ነው፡፡ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊትም ለማማለድና ትእዛዝ ለመቀበል ከሚቆሙት ሰባቱ መላእክት ሦስተኛው መልአክ(ከቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ገብርኤል በመቀጠል) ሩፋኤል ነው፡፡​
ቅዱስ ሩፋኤል የሚለው ስም ከዕብራይስጥ ሁለት ቃላት ጥምረት የመጣ ሲሆን፣ ዋና ትርጓሜውም፦ ​ሩፋ:- ጤና፣ ፈውስ፣ መድኃኒት ማለት ነው። ​ኤል ስመ እግዚአብሔር ነው። ​ሩፋኤል በአጠቃላይ ሲተረጎም “የእግዚአብሔር ፈውስ/መድኃኒት” ወይም “እግዚአብሔር ያድናል/ይፈውሳል” ማለት ነው። ዳግመኛም "ሩፋኤል" ማለት ልቡናን ደስ የሚያሰኝ፤ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፤ መፈውስ፣ የዋህ፣ ይቅር ባይ ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ከፈጣሪው የተቀበላቸው የረድኤት እና የፈውስ ሥራዎች በዋነኛነት የሚከተሉት ናቸው። ✨ፈዋሴ ድውያን (ሕሙማንን የሚፈውስ) ​በጦቢት መጽሐፍ እንደተጻፈው የጦቢት ዓይኖች በንጽሕናቸው ምክንያት በወፍ እዳሪ ሲታወሩ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ተልኮ የዓሣ ሀሞትን በመጠቀም ዓይኑን መልሶ አብርቶለታል። የሄኖክ መጽሐፍ እንደሚያስረዳው በበሽታዎች ሁሉና በሰው ልጆች ቍስል ላይ የተሾመ መልአክ ነው። ደዌ ሥጋንና ደዌ ነፍስን ይፈውሳል። ✨ፈታሔ ማኅፀን (ማኅፀንን የሚፈታ) ​እናቶች (እንደ ቅድስት ሣራ) ማኅፀን ተፈትቶ የተባረከ ልጅ እንዲወለድ የማድረግ ጸጋ ተሰጥቶታል። ነፍሰ ጡር ሴቶች በእርግዝናቸው ወቅት ጥበቃ የሚያደርግ፣ በምጥ ጊዜም ሕመምንና ጭንቀትን በማቅለል የሚረዳ መልአክ ነው።​ ✨ሰዳዴ አጋንንት (አጋንንትን የሚያሳድድ) ​ወለተ ራጉኤል የነበረችውን ሣራን ጋኔኑ አስማንድዮስ እያሰቃያት ባሎቿን ሲገድልባት፣ ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስወጥቶ አዳናት (ጦቢት 3፥8-17)። ለቃየን ልጆች ክፉ ትምህርቶችን (ሰይፍ መሥራት፣ ምንዝር ጌጥ መሥራት...) ያስተማረውን አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ ቀጥቶ ወደ ጥልቁ የጣለው እርሱ ነው። ​✨መራኄ ፍኖት (መንገድ መሪ) ለጦቢት ልጅ ለጦቢያ በሰው አምሳል ተገልጦ (በአዛርያስ ስም) ከነነዌ ወደ ሜዶን በሄደበት ጉዞ ሁሉ መርቶታል፣ ከጉዞ ችግር ጠብቆታል፣ ወደ ቤቱም በሰላም መልሶታል። ✨​በጸሎቱ የሰዎችን ልመና ወደ እግዚአብሔር ማሳረግ እርሱ ራሱ ለጦቢት እንደገለጸው የቅዱሳንን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ጌትነት ከሚያሳርጉት ሰባት ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው። “የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ።” (ጦቢት 12፥15) ✨​የቤተክርስቲያኑ ተአምር በእስክንድርያ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት በስሙ በታነጸች ቤተክርስቲያን ብዙ ምእመናንም በቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጸች ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና። የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው።ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔርም በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮኹ ያን ጊዜ ይህ የከበረ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ እንዲህ አለው "እግዚአብሔር አዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጽ ጸጥ ብለህ ቁም።" አንበሪውም ጸጥ ብሎ ቆመ አልታወከም በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆነ። ይህ ድንቅ ነገር በቤተክርስቲያኑ ምዕመናን ሁሉ ድኅነት እንዲሆን የተሰጠው ኃይል ማሳያ ነው። ✨የተሰጠው ቃል ኪዳን (የምሕረት ቃል) ​ቅዱስ ሩፋኤል በስሙ ለሚማጸኑ ሁሉ ፈውስ ስሙን ለሚጠሩ፣ ለሚማጸኑት እና በዓሉን ለሚያከብሩ ሁሉ ከደዌ ሥጋና ከደዌ ነፍስ መፈወስ፤ መርዳት፣ መባረክ እና ጸሎታቸውን ማቅረብ ተሰጥቶታል። የቅዱስ ሩፋኤል አማላጅነት ሁላችንንም ይጠብቀን፣ቃልኪዳኑም ከእኛ ጋር ትኑር፣አሜን። (ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር) 🌼ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ🌼

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! እንኳን ለርኅወተ ሰማይ፣ለቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!  
ጳጉሜ 3 ቀን የከበረ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሩፋኤል በዓሉ ነው፡፡ እርሱም ከመላእክት አለቆች ሦስተኛ የሆነ ነው። ደግሞም ከእስክንድርያ ውጪ በደሴት የታነጸች ቤተ ክርስቲያኑ በከበረ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የተገለጠባት የከበረችበት ነው።
🕊  ርኅወተ ሰማይ 🕊 ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት፣አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፣ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን" ትባላለች:: አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ። እመቤታችን ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል። በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት [መሪነት] በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል:: 🕊 ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት 🕊 ቅዱስ ሩፋኤል ከሰባቱ ሊቃነ-መላእክት አንዱ ነው። ሊቀ-መላእክትነቱም "መናብርት" በሚባሉ መላእክት ላይ ነው፡፡ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊትም ለማማለድና ትእዛዝ ለመቀበል ከሚቆሙት ሰባቱ መላእክት ሦስተኛው መልአክ(ከቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ገብርኤል በመቀጠል) ሩፋኤል ነው፡፡​
ቅዱስ ሩፋኤል የሚለው ስም ከዕብራይስጥ ሁለት ቃላት ጥምረት የመጣ ሲሆን፣ ዋና ትርጓሜውም፦ ​ሩፋ:- ጤና፣ ፈውስ፣ መድኃኒት ማለት ነው። ​ኤል ስመ እግዚአብሔር ነው። ​ሩፋኤል በአጠቃላይ ሲተረጎም “የእግዚአብሔር ፈውስ/መድኃኒት” ወይም “እግዚአብሔር ያድናል/ይፈውሳል” ማለት ነው። ዳግመኛም "ሩፋኤል" ማለት ልቡናን ደስ የሚያሰኝ፤ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፤ መፈውስ፣ የዋህ፣ ይቅር ባይ ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ከፈጣሪው የተቀበላቸው የረድኤት እና የፈውስ ሥራዎች በዋነኛነት የሚከተሉት ናቸው። ✨ፈዋሴ ዱያን (ሕሙማንን የሚፈውስ) ​በጦቢት መጽሐፍ እንደተጻፈው የጦቢት ዓይኖች በንጽሕናቸው ምክንያት በወፍ እዳሪ ሲታወሩ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ተልኮ የዓሣ ሀሞትን በመጠቀም ዓይኑን መልሶ አብርቶለታል። የሄኖክ መጽሐፍ እንደሚያስረዳው በበሽታዎች ሁሉና በሰው ልጆች ቍስል ላይ የተሾመ መልአክ ነው። ደዌ ሥጋንና ደዌ ነፍስን ይፈውሳል። ✨ፈታሔ ማኅፀን (ማኅፀንን የሚፈታ) ​እናቶች (እንደ ቅድስት ሣራ) ማኅፀን ተፈትቶ የተባረከ ልጅ እንዲወለድ የማድረግ ጸጋ ተሰጥቶታል። ነፍሰ ጡር ሴቶች በእርግዝናቸው ወቅት ጥበቃ የሚያደርግ፣ በምጥ ጊዜም ሕመምንና ጭንቀትን በማቅለል የሚረዳ መልአክ ነው።​ ✨ሰዳዴ አጋንንት (አጋንንትን የሚያሳድድ) ​ወለተ ራጉኤል የነበረችውን ሣራን ጋኔኑ አስማንድዮስ እያሰቃያት ባሎቿን ሲገድልባት፣ ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስወጥቶ አዳናት (ጦቢት 3፥8-17)። ለቃየን ልጆች ክፉ ትምህርቶችን (ሰይፍ መሥራት፣ ምንዝር ጌጥ መሥራት...) ያስተማረውን አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ ቀጥቶ ወደ ጥልቁ የጣለው እርሱ ነው። ​✨መራኄ ፍኖት (መንገድ መሪ) ለጦቢት ልጅ ለጦቢያ በሰው አምሳል ተገልጦ (በአዛርያስ ስም) ከነነዌ ወደ ሜዶን በሄደበት ጉዞ ሁሉ መርቶታል፣ ከጉዞ ችግር ጠብቆታል፣ ወደ ቤቱም በሰላም መልሶታል። ✨​በጸሎቱ የሰዎችን ልመና ወደ እግዚአብሔር ማሳረግ እርሱ ራሱ ለጦቢት እንደገለጸው የቅዱሳንን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ጌትነት ከሚያሳርጉት ሰባት ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው። “የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ።” (ጦቢት 12፥15) ✨​የቤተክርስቲያኑ ተአምር በእስክንድርያ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት በስሙ በታነጸች ቤተክርስቲያን ብዙ ምእመናንም በቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጸች ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና። የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው።ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔርም በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮኹ ያን ጊዜ ይህ የከበረ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ እንዲህ አለው "እግዚአብሔር አዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጽ ጸጥ ብለህ ቁም።" አንበሪውም ጸጥ ብሎ ቆመ አልታወከም በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆነ። ይህ ድንቅ ነገር በቤተክርስቲያኑ ምዕመናን ሁሉ ድኅነት እንዲሆን የተሰጠው ኃይል ማሳያ ነው። ✨የተሰጠው ቃል ኪዳን (የምሕረት ቃል) ​ቅዱስ ሩፋኤል በስሙ ለሚማጸኑ ሁሉ ፈውስ ስሙን ለሚጠሩ፣ ለሚማጸኑት እና በዓሉን ለሚያከብሩ ሁሉ ከደዌ ሥጋና ከደዌ ነፍስ መፈወስ፤ መርዳት፣ መባረክ እና ጸሎታቸውን ማቅረብ ተሰጥቶታል። የቅዱስ ሩፋኤል አማላጅነት ሁላችንንም ይጠብቀን፣ቃልኪዳኑም ከእኛ ጋር ትኑር፣አሜን። (ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር) 🌼ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ🌼

🌼የአበባየሆሽ መዝሙር ጥናት🌼 ሰላም ውድ የቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ልጆች እንዴት ናችሁ ? ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን!!! 👉እነሆ በቀጠሯችን መሰረት ልዩ የአበባ
🌼የአበባየሆሽ መዝሙር ጥናት🌼 ሰላም ውድ የቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ልጆች እንዴት ናችሁ ? ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን!!!
👉እነሆ በቀጠሯችን መሰረት ልዩ የአበባየሆሽ አገልግሎታችን 1 ቀን ብቻ ቀረው!!!
ስለሆነም ዛሬ ሰኞ ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም የመጨረሻ የመዝሙር ጥናት ይኖረናል። የመጨረሻ ቀናችን ስለሆነ የመዝሙር ልምምዳችንን ከእንቅስቃሴ እና ከከበሮ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ ስለምናይ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንዳትቀሩ። እንዴት እንደምንዘምር፣ የጎደለንን፣ የምናስወግደውን ሁሉ እርስ በእርስ እያየን እንተራረማለንና ሁላችንም  በአንድነት በመገኘት የመዝሙር ጥናቱን እንድንሳተፍ  በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። ሰዓት ፡ 11፡ 45 ቦታ ፡ ደብረ ገሊላ ቅዱስ ዐማኑኤል ቤተክርስቲያን የምናጠናቸውን መዝሙሮች ለማግኘት ይሄን ግሩፕ👇 ይቀላቀሉ።
https://t.me/+f9HJXeyothNhMzg0
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን! ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📥 @Gibi_Gubae_hasab_bot ጻፉልን 🏷 @kidus_petros_mereja ተከታተሉን 📷 @peterosphotos የፎቶ ማኅደራችን Instagram | YouTube | Digitallibrary | ጉባኤ ዘቅዱስ ጴጥሮስ|Website ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

🌿 ወርኃ ጳጉሜን 🌿 ጳጉሜ የሚለው ስያሜ «ኤፓጉሜኔ» ከሚለው የፅርዕ ወይም ግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጓሜው «ተረፍ» ወይም «ተጨማሪ» ማለት ነው። አውሮፓውያን ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ያደርጓታል፡፡ ይኸውም ይታወቅ ዘንድ እኛ የወርን ቁጠር 30 ስናደርግ እነርሱ 31 ብለው የሚቆጥሩት ወር አላቸው፡፡ ይኹን እንጂ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ሳያደርጉ የዓመት ተጨማሪ አድርገዋታል፡፡ ጳጉሜን በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ትመጣለች፡፡ በአራት ዓመት አንዴ ማለትም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ መግቢያ ጳጉሜን ስድስት ቀን ትሆናለች፡፡ በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ የአስራ ሦስት ወራት ጸጋ በመባል ትታወቃለች፡፡ ጳጉሜን ስድስት በምትሆንበትም ጊዜ ጾመ ነቢያት /የገና ጾም/ ህዳር 14 ቀን ይገባና ታህሳስ 28 ቀን ጾሙ ተፈትቶ የልደት በዓል ይከበራል፡፡ የጳጉሜ ጾም ወይም ጾመ ዮዲት ይህች ጾም እንደ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ናት። የጳጉሜ ጾም ጾመ ዮዲት በመባልም ትታወቃለች። ይህም ዮዲት እራሷ ስለፆመችው ነው። ታሪኩም እንዲህ ነው፣ የፋርስ ንጉስ ናቡከደነፆር በሰራዊቱ ተመክቶ"ሹም ጠላት አጥፋ፤ ድንበር አስፋ፤ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልክ ያላመነውን እያሳመንህ ና" ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ። (ዮዲት 2:2-7) እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡትን 12ሺ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሄድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ፣ በዚያም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ። ዮዲት ባሏ ሞቶባት ከወንድ እርቃ ንጽህ ጠብቃ በፆም በቀኖና በሀዘን ተወስና ትኖራለች፣በሆነው ጥፋት ህዝቡ ላይ ለመጣው መከራ ማቅ ለብሳ በራሷ ላይ ትቢያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች። የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር ህዝቡን የሚያድንበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን መለሰላት።(ዮዲ 8÷2) ከዚህም በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላዊያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል። ዮዲት ጠላቷን ማጥፋት የቻለችው በጾም እና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይልን አግኝታ ነው። ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንን፣ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን መጎናጸፍ አለብን ብለው ጳጉሜን በፈቃድ ይጾማሉ፡፡ የጳጉሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብባትም ወር ነች፡፡ ይህም ጳጉሜን የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

✨የአንድነት መርሐ ግብር✨
"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።"    {መዝ 122÷1}
ሰላም ውድ የቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ልጆች እንዴት ናችሁ ? እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደቱ ወርሃዊ መታሰቢያ፣ ለታላቁ ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር ዓመታዊ የፍልሠት በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! ዛሬ ማለትም ዓርብ ነሐሴ 29 የአንድነት መርሐ ግብር ይኖረናል። የሚኖሩ መርሐግብራት  ꔰ ጸሎት ꔰ ትምህርተ ወንጌል ꔰ ዝማሬ ቦታ፦ ደብረ ገሊላ ቅዱስ ዐማኑኤል ቤተ ክርስቲያን(መሠረተ ወገራም) ሰዓት፦ 11:45
✝  ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር✝ በዚህች ዕለት በትሕትናው፣ በትዕግስቱ ይበልጡንም ደግሞ በመታዘዙ የሚታወቀው አባት ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የፍልሰቱ ዕለት ናት። ✞ አቡነ ዮሐንስ ሐጺር ቁመታቸው አጭር ስለነበር ‹‹ዮሐንስ ሐጺር›› ‹‹አጭሩ ዮሐንስ ተብለዋል››፤ በ309 ዓ.ም ከተወለዱ በኋላ በ18 ዓመታቸው አስቄጥስ ገዳም ገቡ፡፡ ✞ አቡነ ዮሐንስም ገዳሙ እንደገቡ በብዙ ተጋድሎ ሲኖሩ በታዛዥነታቸው በእጅጉ ይታወቃሉ፤ ይህንንም ለመፈተን አንድ ቀን አባ ባይሞይ የደረቀ እንጨት አንስተው ለአቡነ ዮሐንስ ሰጧቸውና ‹‹ይህን ደረቅ እንጨት ትከለውና ውሃ እያጠጣህ አብቅለው፣ ፍሬ እስኪያፈራም ተንከባከበው›› አሏቸው፡፡ ✞ አቡነ ዮሐንስም በፍጹም መታዘዝ እሺ ብለው ደረቁን እንጨት ተከለው ሦስት ዓመት ሙሉ ከሩቅ ቦታ በቀን ሁለት ጊዜ ውኃ እየቀዱ በማምጣት ማጠጣት ጀመሩ፤ በ3ኛውም ዓመት ደረቁ እንጨት ጸድቆ ለመለመ፣ ታላቅ ዛፍም ሆኖ አብቦ አፍርቶ ጣፋጭ ፍሬ አፈራ፡፡ ✞ አባ ባይሞይም ፍሬውን ቆርጠው ወስደው ‹‹የታዛዡን የትሑቱን ፍሬ እነሆ ቅመሱ›› እያሉ ለቅዱሳን ሰጧቸው፤ ቅዱሳኑም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ተመገቡት፤ ዛፉም ‹‹የመታዘዝ ዛፍ›› እየተባለ መጠራት ጀመረ፡፡ ✞ አንድ ሰው በኃጢአት ወድቆ ባዩ ጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር ‹‹ይህ ወንድሜ ኃጢአት የሠራው ዛሬ ነው፣ ምናልባት እኔ ደግሞ ነገ ኃጢአት እሠራ ይሆናል፤ እርሱን በፈተና የጣለ ሰይጣን እኔንም ይጥለኝ ይሆናል፤ እርሱ ዛሬ ቢበድል ነገ በንስሓ ይታጠባል፣ አቤቱ እኔ ግን ከኃጢአቴ የምነጻበት ሰዓት አይኖረኝ ይሆናል›› እያሉ አምርረው ያለቅሳሉ፡፡ ✞ የቅድስና ሕይወታቸውንም እንዴት ዕለት ዕለት እንደሚጠብቁ እንዲህ በማለት ተናግረዋል፣ ‹‹አንድ ሰው በጾምና በረሃብ ከጸና የነፍሱ ጠላቶች ይደክማሉ፤ እኔ በትልቅ ዋርካ ሥር የተቀመጠንና አራዊት ሊጣሉት የመጣን ሰው እመስላለሁ፣ ሊቋቋማቸው እንደማይችል ከተረዳ ሸሽቶ ወደ ዛፉ በመውጣት ነፍሱን ያድናል።በእኔም የተፈጸመው ይሄው ነው፤ በበዓቴ ተቀምጬ ክፉ ሀሳቦች ሊቃወሙኝ ሲመጡ ልቋቋማቸው እንደማልችል ባወቅሁ ጊዜ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ሸሽቼ እመሸጋለሁ፣ በዚያም ከጠላቶቼ ፍላጻ እድናለሁ›› በማለት እንዴት የቅድስና ሕይወታቸውን ይጠብቁ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ✞ አቡነ ዮሐንስ ሐጺር ሌላው የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ግብራቸው የአትናስያን ሞት ወደ ሕይወት የለወጡበት ነው፤ አትናስያ መጀመሪያ ላይ ጻድቅ ነበረች፣ በገንዘቧ ገዳማትንና መነኮሳትን የምትረዳ አገልጋዮችን የምትራዳ ደግ ሴት ነበረች ነገር ግን በኋላ ላይ ጠላት ሰይጣን በወጥመዱ ጣላትና በዝሙት እንድትወድቅ አደረጋት፤ ዘማዊ ሴትም ሆነች፤ በቀድሞ የቅድስና ሕይወቷ የሚያውቋት መነኮሳት ሁሉ መክረው ሊመልሷት ቢሞክሩ አልመለስላቸው አለች፡፡ ✞ በመጨረሻም መነኮሳቱ አቡነ ዮሐንስ ሐጺርን ላኳቸው፤ እርሳቸውም ተራ ሰው መስለው ወደ ቤቷ ገቡ፤ ለዝሙት የመጣ ተራ ሰው መስሏት ልታጫውተው ስትሞክር ዮሐንስ ሐጺር ማልቀስ ጀመረ ‹‹ለምን ታለቅሳለህ›› ብትለው ‹‹መልክሽ ደስ ብሎኝ›› አላት፤ እርሷም ‹‹ታዲያ ደስ የሚል መልክ ያስቃል እንጂ መች ያስለቅሳል›› ስትለው ‹‹የለም ነገ ገሃነም እንደምትወርጂ ታይቶኝ ነው፣ እነሆ የሰይጣን ማደሪያ ሆነሽ ብዙ አጋንንት በሰውነትሽ ሲወጡ ሲወርዱ አያለሁ…›› እያሉ ብዙ መክረው አስተማሯት፤ እርሷም ዓይነ ልቡናዋ ተከፍቶላት ወደ ልቧ ተመለሰች፡፡ ✞ አትናስያም በጣም ደንግጣ በመጸጸት ‹‹ታዲያ ምን ባደርግ ይሻለኛል›› አለቻቸው፤ ‹‹ንስሃ ግቢ›› አሏት ‹‹በውኑ አሁን እኔ ምሕረት አገኛለሁን ኃጢያቴ ብዙ ነው፣ ከእግዚአብሔር ጋር ማን ያስታርቀኛል›› ስትላቸው ‹‹እኔ አስታርቅሻለሁ ተከተይኝ›› ብለው ወጥተው ሄዱ፤ እርሷም ልዋል ልደር ሳትል በሯ እንደተከፈተ ቤት ንብረቷን ትታ አባ ዮሐንስን ተከተለቻቸው፣ሲመሽ ከገዳሙ በር ላይ ደርሳ የምታርፍበትን ቦታ ለይተው ሰጧትና እዚያ ተኛች፡፡ ✞ አባ ዮሐንስ ሌሊት ለጸሎት ሲነሡ መላእክት ሲወጡ ሲወርዱ ተመልክተው ‹‹ይህ የማየው ነገር ምንድን ነው›› በማለት አንዱን መልአክ ጠየቁት፤ ‹‹ትላንትና አንተን ተከትላ የመጣችው ሴት ሞታ ነፍሷን እያሳረግን ነው›› አላቸው፤ ‹‹እግዚኦ ንስሓ ሳትገባ›› ብለው ደነገጡ፡፡ ✞ መልአኩም ‹‹አንተን ልትከተል ገና አንድ እግሯን ከቤት ስታወጣ ኃጢአቷ በሙሉ ተፍቆላታል፤ አሁን ወደ ገነት እየወሰድናት ነው›› አላቸው።አባ ዮሐንስ ሐጺርም ተገርመው እግዚአብሔርን አመሰገኑ። ✞ በአንዲት ዕለት ወደ በዓታቸው ሲገቡ ጌታችን ተገልጦላቸው ዕለተ ሞታቸው መቅረቡን ከነገራቸው በኋላ ታላቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸው ጥቅምት 20 ቀን 409 ዓ.ም በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ዛሬ(ነሐሴ 29) ሥጋቸው የፈለሠበት ነው:: ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን፤እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን፤በረከቱም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።    (ምንጭ:-መጽሐፈ ስንክሳር)
ሁላችንም ከእኅት ከወንድሞቻችን ጋር ተቀሳቅሰን በመምጣት መርሐግብሩን እንድንሳተፍ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን! ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📥 @Gibi_Gubae_hasab_bot ጻፉልን 🏷 @kidus_petros_mereja ተከታተሉን 📷 @peterosphotos የፎቶ ማኅደራችን Instagram | YouTube | Digitallibrary | ጉባኤ ዘቅዱስ ጴጥሮስ|Website ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

🌻🌻🌻 “በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።” — መዝሙር 65፥11 🌻🌻🌻 ✨ልዩ የአበባየሽወይ መዝሙር ጥናት✨ ✝️እንዴት ቆያችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች? ከ
🌻🌻🌻 “በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።”   — መዝሙር 65፥11 🌻🌻🌻 ✨ልዩ የአበባየሽወይ መዝሙር ጥናት✨ ✝️እንዴት ቆያችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች? ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን!!! ከዘመን ዘመን ያሸጋገረንን አምላካችንን በዝማሬ ልናመሰግን፤ እንደ ዓደይ አበባ ፈክተን፤ "እሰይ ደስ ይበላችሁ ቅዱስ ዮሐንስ መጣላችሁ" እያልን አዲሱን አመት ልናበስር ከ1 ሳምንት የማይበልጥ ጊዜ ቀርቶናል።
እህቶች በዝማሬ፣ ወንድሞች ደግሞ በከበሮ ተጋግዘን በሚቀጥለው ሳምንት ጷጉሜ 4 ልናደርገው ላሰብነው አገልግሎት ግቢጉባኤያችን እናንተ ልጆቿን እየጠራች ነው🗣🗣🗣 👉 አቤት አትሉም❔❔❔
ከታች ያለውን link በመንካት የ መዝሙር ጥናቱን ተሳትፈን ለአገልግሎት እንድንዘጋጅ በልዑል እግዚአብሔር ስም አደራ እንላችኋለን🙏🙏🙏
https://t.me/+f9HJXeyothNhMzg0
💫💫ጥናታችንን ሐሙስ 11:30 ላይ እንጀምራለን!!! አደራ.... መቅረት ፈፅሞ አይታሰብም💫💫 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻   ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን   ቸርነቱን አይተን   ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን   አምናን አሳልፎን.............. 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🕊ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን!🕊 ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

✨የአንድነት መርሐ ግብር✨
"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።"    {መዝ 122÷1}
ሰላም ውድ የቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ልጆች እንዴት ናችሁ ? እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ወርሃዊ መታሰቢያ፣ ለታላቁ ነቢይ ቅዱስ ሚክያስ የእረፍት በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! ዛሬ ማለትም ዓርብ ነሐሴ 22 የአንድነት መርሐ ግብር ይኖረናል። የሚኖሩ መርሐግብራት  ꔰ ጸሎት ꔰ ትምህርተ ወንጌል ቦታ፦ ደብረ ገሊላ ቅዱስ ዐማኑኤል ቤተ ክርስቲያን(መሠረተ ወገራም) ሰዓት፦ 11:45
ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ሚክያስ✝ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ ሁለት በዚች ቀን ታላቅ ነቢይ የሞራት ልጅ ሚክያስ አረፈ። ይህም ነቢይ በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ትንቢት በመናገር አስተማረ። ስለ ጌታችን መውረድም እንዲህ አለ፣ "እነሆ እግዚአብሔር ከልዑል መንበሩ ወደዚህ ዓለም ይወርዳል።" ሁለተኛም ስለ ልደቱ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "የኤፍራታ ዕጣ የምትሆኚ አንቺም ቤተልሔም የእስራኤል ነገሥታት ከነገሡባቸው አገሮች አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቃቸው ንጉሥ ከአንቺ ይወጣልና።" ስለ ምኵራብ መቅረት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ሁሉ መታነፅ ትንቢት ተናግሮአል። ዳግመኛም ስለ ሕገ ወንጌል መሠራት ሕግ ከጽዮን የእግዚአብሔርም ቃል ከኢየሩሳሌም ይወጣል አለ። የትንቢቱም ወራት ሲፈጸም ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሔደ። የትንቢቱም ዘመን ከጌታችን መምጣት በፊት በስምንት መቶ ዓመት ነው ። ማርታ በምትባልም ቦታ ተቀበረ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ሁላችንም ከእኅት ከወንድሞቻችን ጋር ተቀሳቅሰን በመምጣት መርሐግብሩን እንድንሳተፍ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን። ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን! ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📥 @Gibi_Gubae_hasab_bot ጻፉልን 🏷 @kidus_petros_mereja ተከታተሉን 📷 @peterosphotos የፎቶ ማኅደራችን Instagram | YouTube | Digitallibrary | ጉባኤ ዘቅዱስ ጴጥሮስ|Website ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

+1
ትምክህተ ዘመድነ ትምክህተ ዘመድነ /፪/ማርያም እምነ ማርያም ትምክህተ ዘመድነ/፪/ የድኅነታችን አርማ የነፃነታችን ለሕይወት መሠረት ነሽ ድንግል እናታችን አንቺን ለእኛ ዘርን ባያስቀር እንደጥንቱ እንደሰዶም ምድር ኹላችንም በጠፋን ነበር        አዝ የአብርሃም ድንኳን ነሽ አምላክ ያደረብሽ የጌዲዮንም ፀምር ለይቶ ያከበረሽ የኛ ቤዛ በጉ የተያዘብሽ የዋህ ርግብ ከአበው ስር የተገኘሽ ዕፀ ሳቤቅ የሕይወት ሐረግ ነሽ        አዝ አምላክ ከሰማይ ሆኖ ይቺን ዓለም ሲቃኝ ንፅሕት ቅድስት ሆነሽ ማርያም አንቺን ቢያገኝ ትህትናሽን ሕይወትሽንም ወዶ ቃል ሰው ሆነ ከሰማያት ወርዶ አከበረሽ በፍፁም ተዋህዶ        አዝ የመዳናችን ምክንያት የሰው ልጆች ሰላም ከኃጢአት ከመርገም የዳነብሽ ዓለም አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን በሲኦል ውስጥ ተግዘን የኖርን ድንግል በአንቺ ነፃነት አገኘን

✨ዝክረ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ✨ 🔔ዘወርኃ ነሐሴ🔔 "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አን
ዝክረ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ✨            🔔ዘወርኃ ነሐሴ🔔
"ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።” [ራእ 12÷1]
ሰላም ውድ የቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ልጆች እንዴት ናችሁ ?
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወረኃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ !
ዛሬ ሐሙስ ነሐሴ 21 በግቢ ጉባኤያችን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዝክር የምንዘክር ይሆናል ።   የሚኖሩን መርሐ ግብራት: ꔰ ጸሎት እና ምስባክ ꔰ ትምህርተ ወንጌል ꔰ ጠበል ጸዲቅ ꔰ የጋራ ዝማሬ ꔰ የመዝጊያ ጸሎት    ሁላችንም ከእህት ወንድሞቻችን ጋር በመገኘት ከእመቤታችን ረድኤት በረከት እንድንካፈል በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን! ቦታ፦ ደብረ ገሊላ ቅዱስ ዐማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ሰዓት፦ 11:45  ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን! ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📥 @Gibi_Gubae_hasab_bot ጻፉልን 🏷 @kidus_petros_mereja ተከታተሉን 📷 @peterosphotos የፎቶ ማኅደራችን Instagram | YouTube | Digitallibrary | ጉባኤ ዘቅዱስ ጴጥሮስ ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

ሰላም የተወደዳችሁ የቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ልጆች እንደምን አላችሁ? ወንድማችን አቤልን ለማገዝ ሙዳየ ምጽዋት የወሰዳችሁ ወንድም እህቶቻችን ምጽዋታችሁን ከሙዳየ ምጽዋቱ ጋር በእነዚህ ስልኮች በመደ
+1
ሰላም የተወደዳችሁ የቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ልጆች እንደምን አላችሁ? ወንድማችን አቤልን ለማገዝ ሙዳየ ምጽዋት የወሰዳችሁ ወንድም እህቶቻችን ምጽዋታችሁን ከሙዳየ ምጽዋቱ ጋር በእነዚህ ስልኮች በመደወል ታቀብሉን ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ፍቅር እንጠይቃለን🙏 0925186355 0907421767 ሞያ እና በጎ አድራጎት ክፍልቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የትንሳኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ ✨
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የትንሳኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

የደብረ ታቦር አገልግሎት ተጨማሪ የፎቶ እና የ Video መረጃዎችን ለማግኘት ይህን የግቢ ጉባኤያችንን የቴሌግራም ገጽ ይጎብኙ ። 👇👇👇 https://t.me/peterosphotos ✨ቅዱስ ጴጥሮስ
+2
የደብረ ታቦር አገልግሎት ተጨማሪ የፎቶ እና የ Video መረጃዎችን ለማግኘት ይህን የግቢ ጉባኤያችንን የቴሌግራም ገጽ ይጎብኙ ። 👇👇👇 https://t.me/peterosphotosቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

ደብረ ታቦርእንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤አደረሰን! "አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማኅደረ" (ማቴ ፲፯፥፬)
‹‹ደብረ ታቦር›› የሁለት ቃላት ጥምር ሲሆን ‹‹ደብር›› ማለት ተራራ፣ ‹‹ታቦር›› ደግሞ በናዝሬት አካባቢ በሰማርያ አውራጃ በገሊላ ወረዳ የሚገኝ የረጅም ተራራ ስም ነው፡፡
በዓሉ ከጌታችን ዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው፤ ጌታችን አምላችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስምንቱን ሐዋርያት ከተራራው ሥር ትቶ ሦስቱን ማለትም ቅዱስ ጴጥሮን፣ ቅዱስ ያዕቆብንና ቅዱስ ዮሐንስን ይዟቸው ወደ ታቦር ተራራ በመውጣት የሞተውን ሙሴን ከ1644 ዓመታት በኋላ አስነሥቶ የተሰወረውን ኤልያስንም ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ የሕያዋን አምላክና የሙታን አስነሺያቸው እርሱ መሆኑን የገለጸበትና ታላቅ ምስጢር የተከናወነበት ነው፡፡ ☘ እነዚህም ሦስቱ ሐዋርያት ‹‹የምሥጢር ሐዋርያት›› ተብለዋል፤ ጌታችን ስምንቱን ሐዋርያት ይዟቸው ያልወጣበት ምክንያት ይሁዳ ከምሥጢረ መንግሥቱ ቢለየኝ ከሞቱ ገባሁበት ባለ ነበርና ነው፤ ነገር ግን በተራራው ላይ ለሦስቱ የተገለጸው ምሥጢር ከተራራው ሥር ላሉት ከይሁዳ በስተቀር ተገልጾላቸዋል፡፡ ☘ ጌታችን የታቦር ተራራን የመረጠበት ምክንያት ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ይደሰታሉ›› በማለት የተናገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ነው፡፡{መዝ 88፥12} ☘ ጌታችን ከነቢያት ለምን ሙሴንና ኤልያስን ብቻ መረጠ ቢባል ሐዋርያቱን ስለማንነቱ ሲጠይቃቸው እነርሱም ከቅዱስ ጴጥሮስ በቀር ማንነቱን በትክክል አላወቁትም ነበርና ይልቁንም ‹‹ከነቢያት አንዱ ነው ይሉሃል›› ስላሉት የሙሴና የኤልያስ ፈጣሪ መሆኑን ሲገልጽላቸው ነው፡፡ ☘ ጌታችን በብሉይ ኪዳን ከነበሩት ከነቢያት ሙሴንና ኤልያስን፣ በሐዲስ ኪዳን ከነበሩት ከሐዋርያት ሦስቱን በታቦር ተራራ ላይ ማውጣቱ የታቦር ተራራ የቤተክርስቲያን ምሳሌ ስለሆነች ሲሆን፣በቤተ ክርስቲያናችን ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን እንደሚነገሩ ለማመልከት ነው፡፡ ☘ አንድም ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት በማመን የነቢያትንና የሐዋርያትን ክብርና ምልጃ እንደምታስተምር ለማሳየት ነው፡፡ ☘ ሌላው የታቦር ተራራ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ስትሆን ይኸውም ጌታችን ነቢያትንና ሐዋርያትን በተራራዋ ላይ መሰብሰቡ መንግሥተ ሰማያትን ነቢያትም ሐዋርያትም እንደሚወርሷት ለማመልከት ነው፤ ሙሴ ያገባ ሕጋዊ ሲሆን ኤልያስ ግን ድንግል ነውና መንግሥተ ሰማያትን ደናግልም ያገቡም እንደሚወርሷት ለማጠየቅ ነው፡፡
ቡሄ ማለት ብራ ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ከስሙ ትርጉም እንደምንረዳው ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል ስለሆነ ብራ፣  ብርሃን ደማቅ የሚል ፍቺ ያለው ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ አንድም ቡሄ ማለት ወቅቱ የክረምት ጨለማ አልፎ የብርሃን ወቅት ስለሚመጣ ሰማይም ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ስለሆነ ብራ ተብሏል፡፡ ☘ ሙልሙል ዳቦ አመጣጡ ጌታችን ብርሃናዊ መለኮቱን በገለጠበት በዚህ ዕለት በደብረታቦር አካባቢ የነበሩ ህፃናት እረኞች ቀኑ የመሸ ስላልመሰላቸው /ጌታችን በብርሃን አካባቢውን ሞልቶት ስለነበረ/ በዛው ሆነው ከብትና በጎቻቸውን እየጠበቁ ሲቆዩባቸው የሰዓቱን መግፋት የተመለከቱ ወላጆች በችቦ ብርሃን ተጠቅመው ለልጆቻቸው የሚቀመስ ሙልሙል ዳቦ ይዘው ወዳሉበት መምጣታቸውን ያሳያልና ታሪኩን እየዘከርን በዓሉን እናከብራለን፡፡ ☘ ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥን የሚያመለክት ነው፡፡ ጌታችን በደብረ ታቦር መለኮቱን ሲገልጥ ብርሃን አካባቢውን ሞልቶት ነበርና ያንን በዘመናችን ለመግለጥ ችቦ አብርተን አምላካችንን እናመሰግናለን፡፡ አንድም ደግሞ የችቦ ታሪክ ከላይ እንደገለፅነው የእረኞቹ ወላጆች ይዘውት የመጡት ብርሃን ነው፡፡ ☘ ጅራፍ: የጅራፍ ምሳሌነት በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ሚስጥር በእየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ሞቱ ምሳሌ ነው፡፡ በዚህ በዓል ጅራፍ መገመዱ እና ማጮሁ ሁለት አይነት ምሳሌ አለው፡፡ # የመጀመሪያው ምሳሌ - ጌታችን በዕለተ ዓርብ የደረሰበትን ግርፋትና ህማም እናስብበታለን፣ # ሁለተኛው ምሳሌ -  ደግሞ ድምጹን ስንሰማ የባህሪ አባቱን የአብን የምስክርነት ቃልና በግርማው ሲገለጥ የተሰማውን ነጎድጓድ ያስታውሰናል፡፡
በታቦር ተራራ በተመሰለች ቤተክርስቲያን በሃይማኖታችን ጸንተን የመንግሥቱ ወራሽ የስሙ ቀዳሽ እንድንሆን የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁን፣ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን።          መልካም በዓል! ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ

✨ ደብረ ታቦር ✨ በዛሬው የደብረ ታቦር አገልግሎታችን:- ጠዋት እግዚአብሔር አምላክ አገልግሎታችንን ቀና እንዲያደርግልን በጸሎት ጠይቀን ከቅዱስ ዐማኑኤል አገልግሎታችንን የጀመርን ሲሆን በዝማሬ፣በጭ
+4
ደብረ ታቦር ✨ በዛሬው የደብረ ታቦር አገልግሎታችን:- ጠዋት እግዚአብሔር አምላክ አገልግሎታችንን ቀና እንዲያደርግልን በጸሎት ጠይቀን ከቅዱስ ዐማኑኤል  አገልግሎታችንን የጀመርን ሲሆን በዝማሬ፣በጭብጨባ፣በእልልታ አምላካችንን እያመሰገንን እናት አባቶቻችንን፣ ወንድም እህቶቻችንን እንኳን አደረሳችሁ ብለን በመጨረሻም ለአመቱ በሰላም እንዲያደርሰን
ዓመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ዓመ ከመዮም
ብለን  አገልግሎታችንን በሰላም አስጀምሮ ላስፈጸመን አምላካችን ምስጋናችንን አቅርበን በጸሎት ፈጽመናል። አሜን አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ከቁጥር ሳያጎድል ለቀጣይ ዓመት በሰላም ያድርሰን፣አገልግሎታችንንም ይቀበልልን🙏 በዛሬው አገልግሎታችን የተሳተፋችሁ ወንድም እህቶቻችን ስለ ትህትናችሁ፣ስለ ቀና አገልግሎታችሁ ስላሳያችሁን ፍቅርና ታዛዥነት በረከተ ቡሄን ያድልልን፣ከደብረታቦር በዓል ረድኤት በረከት ያካፍልልን፣ እግዚአብሔር ያክብርልን ብለናል🙏 ✨ቅዱስ ጴጥሮስ ግቢ ጉባኤ