የሠራተኛ ድምፅ Voice of Workers
Open in Telegram
በኢሠማኮ የውጭና ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በየሁለት ሳምንት የሚዘጋጅ የ‹‹ሠራተኛው ድምጽ›› ዲጂታል ቅጂ
Show more1 635
Subscribers
+124 hours
-37 days
+530 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+10
in 0 channels
August '26
+41
in 0 channels
Get PRO
July '26
+54
in 0 channels
Get PRO
June '26
+48
in 0 channels
Get PRO
May '26
+45
in 0 channels
Get PRO
April '26
+63
in 1 channels
Get PRO
March '26
+35
in 0 channels
Get PRO
February '26
+23
in 0 channels
Get PRO
January '26
+21
in 1 channels
Get PRO
December '25
+72
in 1 channels
Get PRO
November '25
+58
in 1 channels
Get PRO
October '25
+37
in 1 channels
Get PRO
September '25
+48
in 1 channels
Get PRO
August '25
+27
in 0 channels
Get PRO
July '25
+37
in 1 channels
Get PRO
June '25
+41
in 1 channels
Get PRO
May '25
+39
in 0 channels
Get PRO
April '25
+24
in 0 channels
Get PRO
March '25
+41
in 0 channels
Get PRO
February '25
+39
in 1 channels
Get PRO
January '25
+79
in 1 channels
Get PRO
December '24
+82
in 1 channels
Get PRO
November '24
+51
in 0 channels
Get PRO
October '24
+36
in 0 channels
Get PRO
September '24
+65
in 1 channels
Get PRO
August '24
+60
in 1 channels
Get PRO
July '24
+42
in 2 channels
Get PRO
June '24
+67
in 1 channels
Get PRO
May '24
+60
in 0 channels
Get PRO
April '24
+30
in 2 channels
Get PRO
March '24
+26
in 0 channels
Get PRO
February '24
+49
in 0 channels
Get PRO
January '24
+30
in 0 channels
Get PRO
December '23
+33
in 0 channels
Get PRO
November '23
+839
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | +1 | |||
| 07 September | +1 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | +3 | |||
| 03 September | +1 | |||
| 02 September | +1 | |||
| 01 September | +3 |
Channel Posts
ስለዚህ ለአሽከርካሪዎች ህጋዊ የሥራ ውል፣ፍትሀዊ ክፍያ፣ የማህበራዊ ዋስትና ሽፋን፣ በቂ እረፍት ማግኘት እና የሙያ ደህንነትን በማረጋገጥ ረገድ ሰፊ ሥራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
የብዙ ችግሮች መፍቻ ቁልፍ ማህበራዊ ምክክሮሽ ነው ያሉት አቶ ካሳሁን በአሠሪና ሠራተኛ መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት የኢሠማኮ የመጀመሪያ ምርጫ ማህበራዊ ምክክሮሽ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ዘላቂ ስለሆነ ማህበራዊ ምክክሮሽን ባህል አድርገን መሄድ አለብን ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
የITF ተወካይ ኢንጋ ሊና ባስተላለፉት የአጋርነት መልዕክት ከ150 በላይ አገራት ውስጥ የሚገኙ 16.5 ሚሊዮን የትራንስፖርት ሠራተኞችን የሚወክለው ዓለም አቀፍ የትራንስፖርት ሠራተኞች ፌዴሬሽን (ITF) የአጋርነት መልእክት ለማቅረብ በመቻላቸው አመስግነው፤ተቋማቸው በአለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ለሚገኙ ሁሉም የትራንስፖርት ዘርፍ ሠራተኞች፣ የስራ ሁኔታቸው ምንም ይሁን ምን፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና አስተማማኝ የሥራ አካባቢ እንዲኖር እንደሚሠራ ገልጸው፤ ይህ ጉዳይ ሁሌም ለሥራችን እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ ከሌሎች የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ለምናደርገው ግንኙነትና ትብብር ማዕከላዊ ትኩረት የምንሰጥበት ነው ብለዋል።
በትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ሠራተኞች የሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች በአገር ድንበር ብቻ የተገደቡ ባለመሆናቸው ለእነዚህ ተግዳሮቶች የምንሰጠው ምላሽም በአገር ድንበር ብቻ የተገደበ ሳይሆን በኢትዮጵያ፣ በመላው አፍሪካ እንዲሁም በዓለም ዙሪያ የሠራተኞችን ኃይል መገንባት ያስፈልገናል ሲሉም አክለው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሠሪዎች ፌዴሬሽንን የአጋርነት መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ብርሃኔ ዘሩ በበኩላቸው በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ ዘረፋዎች፣ ግድያዎች፣ የንብረት ውድመቶች በሀገር ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊና ማህበራዊ ገጽታዎች ላይ እየፈጠሩ ያለው አሉታዊ ተፅዕኖ በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት አሠሪውም ሆነ ሠራተኛው ዋስትና የሚየገኙበት የህግ ከለላና ጥበቃ የሚረጋገጥበት የአሠሪውና የመንግስት ውይይትና ትበብር ታምኖበት ተግባራዊ እርምጃ እንዲወሰድ የሚንቀሳቀስ ተቋም እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ፌዴሬሽኑ ከሐምሌ 1/2016 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ያከናወነውን የሁለት ዓመት የሥራ አስፈጻሚ ሪፖርት የቀረቡት የፈዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ አባትሁን ታከለ፤
በተለያዩ ድርጅቶች በርካታ ችግሮች ያጋጠሙ ቢሆንም ችግሮችን እንደ ችግሩ ክብደትና ቅለት አብዛኛውን በውይይት ለመፍታት መቻሉንና የተወሰኑትን ደግሞ በህግ ብይን እንዲሰጣቸው እንዲሁም የተወሰኑት ደግሞ በህግ በሂደት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
ከባለ ድርሻ አካለት ጋርም በተፈጠረ ግንኙነት ሰፊ ሥራ መሰራቱን የገለጹት የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ከኢትዮጵያ አሠሪዎች ፌዴሬሽን ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን፣ከአለም አቀፉ የትራንስፖርት ፌዴሬሽን ጋር በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ማህበራት የህብረት ስምምነት ተደራድረው መብታቸውን እንዲያስከብሩ ድጋፍ መደረጉን፣የህግ አገልግሎት ድጋፍ ለጠየቁ ማህበራት ፌዴሬሽኑ ድጋፍ መደረጉን፣ትምህርትና ስልጠናን በተመለከተም የድጋፍ ፈንድ በማፈላለግ፣ በራስ አቅምና በማህበራት እገዛ ለማህበራት አመራሮች ተደጋጋሚ ስልጠና መሰጠቱን፣የሥራ ላይ ጉብኝት መደረጉን፣የሴቶች ኮሚቴን ለመደራጀት የተያዘው እቅድ 100% መሳካቱን እና ሌሎችንም ከማህበራት የሚቀርቡላቸውን ጥያቄዎች መሰረት በማድረግ ሰፊ ሥራ መሠራቱን ለምክር ቤቱ ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ምክርቤቱ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን የሥራ አስፈጻሚ ምርጫ አፅድቆ የኦዲት ኮሚቴ ምርጫ አካሂዷል፡፡ በምርጫው አቶ አብዱል አዚዝ መሀመድን ሰብሳቢ፣ አቶ ማስተዋል ዘሪሁንን ፀሐፊ እንዲሁም አቶ እሱባለው በፍርዱን አባል አድርጉ መርጧል፡፡
https://t.me/voiceofworkers2013cetu
| 2 | ፌዴሬሽኑ 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ
የኢትዮጵያ ትራንስፖርትና መገናኛ ሠራተኞች ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም አካሄደ፡፡
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፤ የዘርፉ ሠራተኞች መብትና ጥቅም መከበር የሠራተኛ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የአገር እድገትና የአገልግሎት ጥራት ጭምር ነው፡፡ አሽከርካሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ርቀው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስለሚሄዱ ለአደጋ ይጋለጣሉ፤ህይወታቸውን ያጣሉ፤ባለንብረቶችም ንብረታቸው ይወድማል፤በኢኮኖሚውም ላይም ተፅዕኖ ያሳድራል፡፡ | 358 |
| 3 | ነሐሴ 27 2018
ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን አሁንም የውትወታ ሥራዬን አላቆምኩም ሲል የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ተናገረ።
በኢትዮጵያ ያለው የኑሮ ውድነት በተለይ በቋሚ ደመወዝ ኑሯቸውን ለሚገፉ ተቀጣሪ ሠራተኞች ላይ እየፈጠረ ያለው ጫና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መምጣቱን ኮንፌዴሬሽኑ ተናግሯል።
የኑሮ ውድነቱ የሚያድግበት ፍጥነት ሠራተኛው ከሚያገኘው ቋሚ ገቢ ጋር ሊመጣጠን ባለመቻሉ ደመወዝተኛው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንዲያልፍ እያስገደደው ነው ተብሏል።
በዚህም ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰንና የግብር ቅናሽ እንዲደረግ ኢሠማኮ የተለያዩ ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ አሰታውሰዋል።
የአሰሪና ሠራተኛ አዋጁ ሲሻሻል ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን የተደረገው የውትወታ ሥራ መሳካቱን ተናግረው ይሁንና ተግባራዊ እንዲሆን አሁንም እየጠየቅን ነው ሲሉ ያብራራሉ።
ሌላኛው በተደጋጋሚ ከሚጠየቁት መካከል የሥራ ግብር እንዲቀነስ የሚለው ይገኝበታል።
በዚህም በኩል ኢሠማኮ የተለያዩ ሥራዎችን እንደሰራ ያነሱት ፕሬዝዳንቱ ግብር እንዲቀነስ ከማይፈልጉት መካከል አንዱ IMF ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ይሁን እና የIMF ኢትዮጵያ ተወካይም ሆነ ዋና የIMF ዳይሬክተርን አግኝተን ለምን ግብር እንዲቀነስ እና ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል መወሰን እንዳለበት ለማስረዳት ሞክረናል ያሉት አቶ ካሳሁን በመጨረሻ መስማማት ላይ መድረሳቸውን አስረድተዋል::
አሁን ተስፋ ሰጭ ነገሮች እንዳሉት አክለዋል ።
ዘገባውን ያድምጡ....
https://tinyurl.com/4mxvt96a
ማርታ በቀለ | 661 |
| 4 | https://t.me/voiceofworkers2013cetu | 561 |
| 5 | የምክር ቤቱን ስብሰባ በንግግር የከፈቱት የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፤ የትራንስፖርትና የመገናኛ ዘርፍ በሀገራችን የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የማይተካ ሚና ያለው በመሆኑ በዘርፉ የተሰማሩ ሠራተኞች መብትና ጥቅም መከበር የሠራተኞች ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የአገር እድገትና አገልግሎት ጥራትም ጭምር ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የአሽከርካሪዎች ህጋዊ የሥራ ውል፣ ፍትሐዊ ክፍያ፣ የማህበራዊ ዋስትና ሽፋን፣ በቂ ዕረፍት እና ሌሎችም መብቶቻቸው እንዲከበሩ በተለየ ትኩረት መሥራት ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም ለማሳካት በአሠሪና ሠራተኛ አዋጁና በአለም ሥራ ድርጅት ድንጋጌዎች መሰረት አሽከርካሪዎች መብታቸውን ለማስከበር በህጋዊ ሠራተኛ ማኅበር ተደራጅተው የፌዴሬሽኑ አባል መሆን አለባቸው ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
ፌዴሬሽኑ ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ያከናወነውን የሥራ አስፈጻሚ ሪፖርት የቀረቡት የፈዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ አባትሁን ታከለ፤
ፌዴሬሽኑ በትራንስፖርት ዘርፍ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነቱ የሰመረ እንዲሆን ለማስቻል ከኢትዮጵያ አሠሪዎች ፌዴሬሽን ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙን፣
ማህበራት የህብረት ስምምነት ተደራድረው መብታቸውን እንዲያስከብሩ ድጋፍ መደረጉን፣
የህግ አገልግሎት ድጋፍ ለጠየቁ ማህበራት ፌዴሬሽኑ ድጋፍ መደረጉን፣
በበጀት ዓመቱ 11 አዳዲስ ማህበራትን ለማደራጀት ታቅዶ 9 ማህበራትን ለማደራጀት መቻሉን፣
ትምህርትና ስልጠናን በተመለከተም የድጋፍ ፈንድ በማፈላለግ፣በረስ አቅምና በማህበራት እገዛ ለማህበራት አመራሮች ተደጋጋሚ ስልጠና መሰጠቱን፣
የሥራ ላይ ጉብኝት መደረጉን፣
የሴቶች ኮሚቴን ለመደራጀት የተያዘው እቅድ 100% መሳካቱን እና ሌሎችንም ከማህበራት የሚቀርቡላቸውን ጥያቄዎች መሰረት በማድረግ ሰፊ ሥራ መሠራቱን ለምክር ቤቱ ገልጸዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ወደ ፌዴሬሽኑ በመምጣቱ መደሰታቸውን ገልጸው፤ ፌዴሬሽኑ ለመመለስ የደረገውን ጥረት አድንቀዋል፡፡ በህገ ደንቡ መሰረት በወቅቱ ክፍያቸውን የማይከፍሉ ማህበራት በግልፅ መቅረብ አለባቸው፤ተሸፋፍኖ ማለፍ የለበትም፣ ማህበራትን በማደራጀት ረገድ የተሰራው ሥራ አመርቂ ነው፣ የተሟላ የሥራ አስፈጻሚ ባልነበረበት ሁኔታ በርካታ ተግባራት መከናወናቸው የሚያስመሰግን ነው የሚሉና ሌሎችም አስተያየቶችን አቅርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በመጨረሻም ምክር ቤቱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የቀረበውን የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡ | 640 |
| 6 | የኢትዮጵያ የትራንስፖርትና መገናኛ ሠራተኞች ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ አካሄደ፡፡
የኢትዮጵያ ትራንስፖርትና መገናኛ ሠራተኞች ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 50ኛ የጠቅላይ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ፌዴሬሽኑን የሚመራ አዲስ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ አካሄደ፡፡
በምርጫው አቶ አባትሁን ታከለን የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት፣ ወ/ሮ አያልነሽ ካሳ የአስተዳደርና ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ፣ አቶ ፍርድአወቅ አብርሃምን የኢንዱስትሪ ግንኙነትና ማህበራት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ፣ አቶ ዳንኤል ተመቸውን የውጭ ግንኙነትና ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ እንዲሁም አቶ ገመቹ ካባን የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አድርጎ መርጧል፡፡ | 679 |
| 7 | https://t.me/voiceofworkers2013cetu | 766 |
| 8 | የፌዴሬሽኑን የ2017/18 በጀት ዓመት የአንድ ዓመት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሪፖርት በንባብ ያሰሙት የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳ ስጦት፤የመደራጀት ምጣኔን ከማሳደግ ባለፈ በ35 መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበራት ላይ የጋራ ውይይት ተደርጎ አለመግባባቶች እንዲፈቱ መደረጉን፣ የሥራ ዘመናቸውን የጨረሱ የማህበራት አመራሮች ምርጫ እንዲያደርጉ፣ የህብረት ስምምነት ድርድር ለማድረግ ድጋፍ ለሚፈልጉ ማኅበራት የተሻለ የመደራደር አቅም እንዲኖራቸው ድጋፍ መደረጉን፣ 68 የሠራተኛ ማኅበራትን በመጎብኘት የመደገፍና የማጠናከር ሥራ መሰራቱን እና የህግ ድጋፍ ለጠየቁ 34 ማኅበራት ፌዴሬሽኑ ባደረገው ድጋፍ 21 ፋይሎች ለሠራተኛው መወሰናቸውን እና ቀሪዎቹ በሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የኢሠማኮ ኢንዱስትሪ ግንኙነትና ማህበራት ማደራጃ ዘርፍ ም/ፕሬዝዳንት አቶ ድሪብሳ ለገሰ በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ኢሠማኮ ለሠራተኛው መብት መከበር ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና ከክልል የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች ጋር ጠንካራ ግንኙነት በመፍጠር እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ እስከዛሬ በነበረው ልምድ የአለመግባባቶች የሚፈጠሩት በሠራተኛው እና በአሠሪው መካከል የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደታዘብነው በማህበራት አመራሮች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶች እንቅፋት እየሆኑ መጥተዋል ብለዋል፡፡ ስለሆነም ውስጣዊ ችግራችንን ሳንፈታ ለውጫዊው ችግር መፍትሔ ማምጣት ስለማንችል እዚህ ላይ ትኩረት ልንሰጠው ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
አክለውም ኢሠማኮ ለሠራተኛው ተደራሽ ለመሆንና የመደራጀትና የመደራደር አቅሙን ለማጎልበት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን እያስፋፋ እንደሚገኝ ገልጸው ፌዴሬሽኑ ባለው ባህርይ ምክንያት የተለየ ትኩረት የሚጠይቅ በመሆኑ ኢሠማኮ ከዚህ በፊት ከፌዴሬሽኑ ጋር እያከናወናቸው ያሉትን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ቃል ገብተዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ለማኅበራት መሪዎች የሚሰጠው ስልጠና ከዚህ የበለጠ እንዲሆን ከአለም አቀፍ ተቋማት ጋር የሚያደርገው ግንኙነት ቢጠናከር፣ የሠራተኛውን ችግር ለማዳመጥ የሥራ ጉብኝቱ ተጠናክሮ ቢቀጥል፣የራስ አገዝ ስልጠና መጠናከር አለበት፣የሚሉና ሌሎችንም በርካታ ሀሳቦችና ጥያቄዎችን አንስተው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ምክር ቤቱ ፌዴሬሽኑን አሁን ካለበት ደረጃ ከፍ ለማድረግ ያስችላል በተባለው የአምስት ዓመት ስትራተጂክ ዕቅድ ላይ በመወያየትና ሰፊ ሀሳብ በመስጠት በሙሉ ድምጽ አፅድቆታል፡፡
በመጨረሻም የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ባቀረበው የ2019 በጀት ዓመት የተግባርና የበጀት ዕቅድ ላይ ውይይት አድርጎ በሙሉ ድምጽ ያፀደቀ ሲሆን ለሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የደሞዝ ጭማሪ እና ቦነስ ላይ በተያዘው አጀንዳም የ2 እርከን ጭማሪና የሁለት ወር ደሞዝ ቦነስ እንዲሰጣቸው በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ | 775 |
| 9 | ፌዴሬሽኑ በዕቅድ ከያዘው በላይ ማኅበራት ማደራጀቱን ገለጸ
በተናኜወርቅ መኮንን
የቱሪዝም ሆቴሎችና ጠቅላላ አገልግሎት ሠራተኛ ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው የፌዴሬሽኑ 60ኛ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ በቀረበው ሪፖርት በበጀት ዓመቱ 50 ማኅበራትን ለማደራጀት ታቅዶ 55 ማህበራትን በማደራጀት እና ከተደራጁትም መካከል 30 ማኅበራትን የፌዴሬሽኑ አባል ማድረግ መቻሉ ተገለጸ፡፡ | 801 |
| 10 | የኢትዮጵያ ፋይናንስ ተቋማት ሠራተኞች ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ለጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች የደመወዝ እና የቦነስ ጭማሪ አደረገ
«የደመወዝ እና ቦነስ ማሻሻያው የሠራተኞችን የሥራ ተነሳሽነት እንደሚያሳድግ ተገለጸ»
የኢትዮጵያ ፋይናንስ ተቋማት ሠራተኞች ማኅበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን የጽሕፈት ቤቱን ሠራተኞች የሥራ አፈጻጸም፣ አሁን ያለውን የኑሮ ውድነት እና ሠራተኞቹ ለተቋሙ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ከግምት ውስጥ በማስገባት የደመወዝ እና የቦነስ ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ።
በዚህም መሠረት ለጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች የሦስት ወር ደመወዝ ቦነስ የተሰጠ ሲሆን፣ ከ3,000 እስከ 7,000 ብር የሚደርስ የወር ደመወዝ ጭማሪ ተደርጎላቸዋል።
ፌዴሬሽኑ እንደገለጸው፤ ይህ ውሳኔ ሠራተኞችን ለማበረታታት፣ የሥራ ተነሳሽነታቸውን ለማሳደግ እና ለሚያከናውኑት ኃላፊነት ተገቢውን እውቅና ለመስጠት የተወሰደ እርምጃ ነው። የሠራተኞችን የሥራ ሁኔታና የኑሮ ደረጃ ማሻሻል እንዲሁም የተሻለ የሥራ አፈጻጸም እንዲኖር ማበረታታት ከፌዴሬሽኑ መሠረታዊ የሥራ መርሆዎች መካከል አንዱ መሆኑም ተመላክቷል።
የተደረገው ማሻሻያ ሠራተኞች በተሻለ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት ሥራቸውን እንዲያከናውኑ፣ የጽሕፈት ቤቱን የአገልግሎት ብቃት እንዲያሳድጉ እና ለፌዴሬሽኑ ዓላማና ተልዕኮ ስኬት የበለጠ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑ ተገልጻል። | 399 |
| 11 | https://t.me/voiceofworkers2013cetu | 1 251 |
| 12 | በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢሠማኮ አስተዳደርና ፋይናንስ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አብዱልሀኪም ሙሰማ ከፌዴሬሽኖችና ከመሰረታዊ የሠራተኛ ማህበራት የሚቀርቡ ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግ አለመግባባቶችን በሁለትዮሽ ወይም በሶስትዮሽ እንዲፈቱ ካልተቻለም ወደ ፍትህ አካል እንዲሄዱ የህግ አገልግሎት እገዛ በማድረግ የሠራተኛው መብትና ጥቅም እንዲከበር እየሠራ መሆኑን ገልጸው ተደራሽ ለመሆን በሚሠራው ሥራም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹን ከስምንት ወደ አስራ አራት ማድረስ ተችሏል ብለዋል፡፡
የሠራተኛው አንገብጋቢ ጥያቄ የሆነውን የዝቅተኛ ደመወዝ የሚወስነውን ቦርድ መቋቋም በተመለከተ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ደንቡ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡንና ለዚህም አሠማኮ በየትኛውም ጉዳይ ላይ ለሚነሱ ክርክሮች በጥናት የተደገፈ በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ተናግረዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ባነሱት ሃሳብ
የዝቅተኛ ደመወዝ ጉዳይ እስከ መቼ ነው በሪፖርት ብቻ የሚቀርበው፡፡ መቋጫ ማግኘት አለበት፣
ከኮምቦልቻ የመጡ አባል በድርጅታችን ከፍተኛ ችግር ነበር የፌዴሬሽናችን አመራሮች በአካል ተገኝተው ችግሩ እንዲፈታ ስላደረጉልን እናመሰግናለን፣
ማህበራት እርስ በእርስ ያደርጉት የነበረው የልምድ ልውውጥ እንዲቀጥል ቢደረግ፣የፌዴሬሽኑ ተግዳሮት ሆነው ከቀረቡት ጉዳዮች አንዱ ህብረት ስምምነትን ተግባራዊ አለማድረግ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የአሠሪዎች ፌዴሬሽን ችግሩን ለመፍታት ሚናው ምንድን ነው? ፌዴሬሽኑስ ከአሠሪዎች ፌዴሬሽን ጋር ያለው ግንኙነት እንዴት ነው?፣
ከአባላት የሚሰበሰበውን 1% በትክክል አለማስገባት ከተሰበሰበውም ላይ መሸራረፍ እንዳለ ተገልጿል፡፡ እስከ መቼ ነው በማግባባት እንዲልኩ ሚደረገው፤ ለምንድን ነው እርምጃ የማይወሰደው? ወቅቱን ጠብቆ የከፈለ ማኅበር ቢበረታታ፣
በኑሮ ውድነት ምክንያት የደመወዝ ጥያቄና ሌሎችም የመብት ጥያቄዎችን በሚያነሱ አመራሮች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ ይደርሳል፡፡ ከሥራ እንዲሰናበቱ በማድረግ ማኅበራትን የማዳከም ስራ ይሰራል፡፡ ሥራ አስፈጻሚዎች እየተዳከምን ነው እና ፌዴሬሽኑ ይህን ለማስቆም ምን አይነት እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው የሚሉና ሌሎችምንም ጉዳዮች አንስተዋል፡፡
ከፌዴሬሽኑ አመራሮች በተሰጠ ምላሽ
በአሁኑ ጊዜ የህብረት ስምምነት ድርድር ለማድረግ እጅግ ፈታኝ የሆኑ መሰናክሎች እያጋጠሙን ነው፡፡ አሠሪው ድርድር ማድረግ ተጨማሪ ወጪ ያስከትልብኛል በሚል ሰበቦችን እየደረደረ ሲያጓትት ነው የሚገኘው፡፡ የህብረት ስምምነት ድርድር የሌላቸውን ማኅበራት ማጠናከር እንዲሁም አንዱ በር ሲዘጋ ሌላውን ማንኳኳት ይገባል፡፡ መዋጮን በተመለከተ ለምን ቅራኔ ውስጥ እንገባለን፤በአግባቡ የማትልኩ የማኅበር አመራሮች ራሳችሁን ስለምታውቁ ወደ ትክክለኛው መንገድ ብትገቡ ፌዴሬሽኑ ከዚህ የተሻለ መሥራት ይችላል፡፡
የማኅበራት አመራሮችን ከሥራ መባረር በተመለከተ ለተነሳው ጥያቄ በየአካባቢው የኢሠማኮ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች አሉ፡፡ በአዲስ አበባና አካባቢው ባሉ ማኅበራት ፌዴሬሽኑ ሲቻል በመግባባት ካልተቻለ ደግሞ ወደ ህግ በመውሰድ እንዲፈቱ ያደርጋል፡፡ በክልል ያሉ ማኅበራት ከሆኑ ግን ጉዳዩን ወደ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመውሰድ መፍትሔ ማግኘት ይቻላል፡፡ የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ለማስከበር ቁልፉ አንድነት ስለሆነ በየድርጅታችን አባል ያልሆኑ ሠራተኞችን አባል አድርገን ትግላችንን አጠናክረን መቀጠል ለነገ የሚባል ጉዳይ እንዳልሆነ ከመድረኩ አፅንኦት ተሰጥቶ ተነግሯል፡፡
ከአሠሪ ፌዴሬሽን ጋር በተያያዘ ምላሽ የሰጡት የኢሠማኮ የውጭና የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ከአሠሪዎች ፌዴሬሽን ጋር በጋራ የፈቷቸው በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውን ገልጸው ለአብነትም ባህር ዳር ላይ የነበረው ችግር የተፈታው በጋራ ነው ብለዋል፡፡ ጋር በመጨረሻም ምክር ቤቱ በሠራተኛ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አካሂዷል፡፡ | 1 090 |
| 13 | ችግሮችን በድርድር መፍታት የተሻለ ተጠቃሚ ያደርጋል
አቶ ተስፋዬ አብዲሳ የጨርቃ ጨርቅ ቆዳና ልብስ ስፌት ተቋማት ሠራተኛ ማህበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ አብዲሳ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት የአንድ ዓመት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሪፖርት በሠራተኞችና በማህበራት አመራሮች ላይ የሚደርሱ የመብት ጥሰቶችን ለማስከበር በየተቋማቶቹ በአካል በመገኘት በማወያየት በርካታ ጉዳዮችን በድርድር መፍታትና ክፍተቶች እንዲስተካከሉ መደረጉ የተሻለ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የፌዴሬሽኑ 56ኛ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናገሩ፡፡
የፌዴሬሽኑን የአንድ ዓመት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሪፖርት ያቀረቡት አቶ ተስፋዬ ራሳቸውን ከፌዴሬሽን አባልነት አግልለው የነበሩ ማኅበራትን በተመለከተም ከማኅበራቱ አመራሮች ጋር በተደረገ ውይይት፤ እውነታውን በማስረዳት ወደ ፌዴሬሽናቸው ተመልሰው አባል እንዲሆኑ ተደርጓል ብለዋል፡፡ ከአቅም ግንባታ ጋርም በተያያዘ ከFNV, ከFES እና ከIndustry All ጋር በመተባበር በ15 ዙር ለ480 የማኅበር አመራሮች ሥልጠና መሰጠቱንም አክለው ገልጸዋል፡፡ | 815 |
| 14 | ማኅበራት የህብረት ስምምነት ድርድር እንድያደርጉ ፌዴሬሽኑ የሚያደርገውን እገዛም በተመለከተ ማህበራት ለሠራተኞች አዳዲስ ጥቅማ ጥቅሞችን በማካተት ጥራት ያለው የህብረት ስምምነት እንዲያዘጋጁ የሙያና የህግ ድጋፍ መሰጠቱን እንዲሁም በሂደት ላይ ላሉ አምስት ማህበራት በህግ ምክርና የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ድርድሩ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ ለፊርማ እንዲደርስ እየተሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
የጉባዔው አባላት ባነሱት ሃሳብ የፌዴሬሽኑ ዓላማ ማህበራት እንዳይወድቁ በመሆኑ በስንቄ ማህበር አመራሮች ላይ በደረሰው ችግር የወሰዳችሁት እርምጃ ጥሩ ነው፣ በሪፖርቱ ለማህበር አመራሮች ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል፤ ነገር ግን ማህበር ለመመስረት ከአባልነት ውጪ ያሉ ሠራተኞችንና የተቋማት አመራሮች ላይም ተደራሽ መሆን ቢቻል፣ ከማህበራት የሚሰበሰብ ገንዘብ ካልተሰበሰበ እያንዳንዱ አባል ማኅበር በወቅቱ ፈሰስ ካላደረገ የፌዴሬሽኑን ተግባር ያውካልና በዚህ ላይ ትኩረት ቢደረግ፣የንግድ ባንክ ጉዳይ እንደ ስጋት ነውና ፌዴሬሽኑ ትኩረት አድርጎ ቢሰራበት የሚሉ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ተነስተው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶበታል፡፡
የግሎባል ባንክ ሠራተኛ ማኅበር ጤናማ የህብረት ስምምነት በማድረግ፣ለአቶ ጋሪ መንገሻ የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ የሠራተኛ ማህበር እንዲመሰረት በሰሩት ሥራ ተምሳሌት በመሆናቸው የሰርተፍኬትና የገንዘብ ሽልማት ከፌዴሬሽኑ ተበርክቶላቸዋል፡፡
በመጨረሻም የጉባዔው አባላት በሥራ አስፈጻሚው የቀረበውን የ2018/19 በጀትና እቅድ ተወያይቶ ያጸደቁ ሲሆን ከቴክኖሎጂ ጋር በተያያዘ በሠራተኛውን የሥራ ዋስትና ላይ ብዙ ተግዳሮቶች ሊመጡ ስለሚችሉ ከወዲሁ ማህበራትም ሆኑ ፌዴሬሽኑ ምን ማድረግ አለበቸው በሚል በተያዘው አጀንዳ ላይ ውይይት አድርጎ ከየማኅበሩ ተወካዮች መጥተው ምክር ቤቱ የመነሻ ፅሁፍ ይዞ እንዲመጣ ወስነዋል፡፡
የዚህን ዜና ዝርዝር በቴሌግራም ገጻችን በምናሰራጨው የሠራተኛው ድምፅ ጋዜጣ ይዘን የምንመጣ ይሆናል፡፡
https://t.me/voiceofworkers2013cetu | 998 |
| 15 | የኢትዮጵያ ፋይናንስ ተቋማት ሠራተኛ ማህበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን 32ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሄደ፡፡
የኢትዮጵያ ፋይናንስ ተቋማት ሠራተኛ ማህበራት ኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን 32ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም 11ኛ ፎቅ በሚገኘው የኢሠማኮ መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ፡፡
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ በርሀ ባቀረቡት የስድስት ወራት ሪፖርት የማኅበራት አመራሮችን አቅም ለማሳደግ በአመራር ብቃት፣ በሠራተኛ መብትና ግዴታ፣በሥራ ህግ፣በድርድር ክህሎትና በድርጅታዊ ግንኙነት ዙሪያ ስልጠና መሰጠቱንና በዚህም በ34 ማህበራት የሚገኙ 300 ሰልጣኞች መሸፈን መቻሉን ገልጸዋል፡፡ | 813 |
| 16 | https://t.me/voiceofworkers2013cetu | 1 077 |
| 17 | የዘንደሮው የ2018 ዓ.ም የኢሠማኮ የበጋ ወራት የስፖርት ውድድር በስኬት ተጠናቀቀ
ከታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በደመቀ ሁኔታ ሲካሄድ የቆየው የዘንድሮው የ2018ዓ.ም የኢሠማኮ የበጋ ወራት የስፖርት ውድድር ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተደረጉ የፍጻሜ ውድድሮች ተጠናቀቀ፡፡
በ1ኛ ዲቪዚዮን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ባደረጉት የፍጻሜ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 3 ለ 1 በማሸነፍ የ2018 ዓ.ም ሻምፒዮና ሆኗል፡፡ በሌላ በኩል ከ2ኛ ዲቪዚዮን ለፍጻሜ የደረሱት ረጲ ሳሙና ዲተርጀንት እና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ባደረጉት አጓጊ ጨዋታ ረጲ ሳሙና ዲተርጀንት በመለያ ምት በማሻነፍ ዋንጫውን አንስቷል፡፡በሌላ በኩል በዕለቱ በተከናወነው የሴቶች የገመድ ጉተታ ውድድር የኢትዮጵያ ክፍያ መንገድ ፋፋ ምግብ አክሲዮን ማህበርን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ በተቃራኒው በወንዶች የገመድ ጉተታ ፋፋ ምግብ አክሲዮን ማህበር የኢትዮጵያ ክፍያ መንገድን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ በአትሌቲክስ በተካሄዱ ውድድሮች በሴቶች 400 ሜትር ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ኤደን ሰለሞን 1ኛ፣መልካም አናጋው 2ኛ፣ ቤተልሔም ባህሩ 3ኛ ሆነዋል፡፡ በወንዶች 800 ሜትር በተደረገው የሩጫ ውድድር ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን አኔቦ ዋጋሪ 1ኛ፣ በላቸው ተሾመ አናጋው 2ኛ ሲሆኑ አሰግድ አብርሃም ከብርሃንና ሰላም 3ኛ ሆኗል፡፡
የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ኢሠማኮ ከራሱ በጀት በመመደብና እና ቀና የሥራ መሪዎችና ባለሀብቶች በሚያደርጉለት የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በየዓመቱ የበጋና የክረምት ሻምፒዮናዎችን የሚያዘጋጀው አካላዊ ብቃቱ የዳበረና ምርታማ ሠራተኛ ለማፍራት፣ አሠሪና ሠራተኛን ለማግባባት፣ የልማት ተቋማትን ገፅታ ለመገንባትና የሠራተኞችን አንድነት ለማጠናከር መሆኑን አፅንኦት ሠጥተው ተናግረዋል፡፡
የኢሠማኮ የውጭና ህዝብ ግንኙነት መምሪያ እና የስፖርት ክፍሉ ኃላፊ አቶ አያሌው አህመድ በበኩላቸው ውድድሮቹን ለማካሄድ የነበሩባቸውን የሜዳና የቴክኒክ ችግሮች ለመቅረፍ የተለያዩ የልማት ድርጅቶችና ተቋማት ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸው ላለፉት 7 ወራት በተካሄዱ ውድድሮች 25 የስፖርት ቡድኖች ተሳትፈዋል ብለዋል፡፡ በውድድሩ በእግር ኳስ 21 ቡድኖች፣ በቮሊቦል ወንዶች 9 ቡድኖች ሴቶች ደግሞ 5 ቡድኖች፣ በጠረጴዛ ኳስ ወንዶች 9 ሴቶች 4 ቡድኖች፣ በዳርት ወንዶች 7 ሴቶች 5፣ በከረንቡላ ወንዶች 5፣ በአትሌቲክስ ወንዶች 5 ሴቶች 3፣ በገመድ ጉተታ ወንዶች 5 ሴቶች 5፣ በዳማ ወንዶች 4፣ በቼዝ ወንዶች 3 ማህበራት ውድድር ማካሄዳቸውንና በውድድሩም 1080 ወንዶች 241 ሴቶች በድምሩ 1321 ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡ | 1 051 |
| 18 | https://t.me/voiceofworkers2013cetu | 1 |
| 19 | No text... | 983 |
| 20 | No text... | 701 |
