en
Feedback
Mizan Tepi University Students Union Channel

Mizan Tepi University Students Union Channel

Open in Telegram

Our mission is to unite students from all years, fostering a sense of community and facilitating the exchange of information.Buy ads: https://telega.io/c/MTU_Main_Campus contact us at:  @Sablaw  @MTU13bot  @SeudEmpire  group: @mizan_tepi_university

Show more
5 099
Subscribers
+824 hours
+187 days
No data30 days
Posts Archive
Mizan tepi university The light of the green valley! congratulations ✨ to 2018 E.C. grade 12 students who scored passing mark
Mizan tepi university The light of the green valley! congratulations ✨ to 2018 E.C. grade 12 students who scored passing marks! Here is our undergraduate program in collages Are you ready to join us ? ....

+7
Congratulations 👏👏👏 This is 2018 freshman student's department placement

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲን አንደኛ ምርጫ መድረግ እንዳትረሱ!!! በ2018 ዓ.ም የተሰጠውን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስዳችሁ ላለፋችሁ ተማሪዎች ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ እንኳን ደስ አላችሁ ይላል። ዩኒቨርሲቲያችን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በተፈጥሮ ልምላሜያቸው በሚታወቁት የመቻቻልና የአንድነት ተምሰሌት በሆኑት በቤች ሸኮና ሸካ ዞኖች ዋና ከተሞች እብርትላይ ይገኛል። ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ጥራት በፍጹም የማይደራደር ፣ በምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች ጎልቶ እየወጣ ያለና በክልሉ አንጋፋ የሆነ ላለፉት 18 ዙሮች ከ50ሺህ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቀ ነው። ዩኒቨርሲቲያችን በቅድመና ድህረምረቃፕሮግራሞ በኢንጅነሪንግና ቴክኖሎጅ ፣ በተፈጥሮ ቀመር ሳይንስ፣ በኮምፒቲንግና ኢንፎርማቲክስ፣ በግብርና ተፈጥሮ ሀብት ፣ በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ በህክምናና ጤና ሳይንስ በማህበራዊ ሳይንስና ሰብዓዊነት ኮሌጆቹ እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ  ዩኒቨርሲቲው በሚታወቅበት የህግ የትምህርት መስኮች ትምህርት ይሰጣል። ስለሆነም  በገበያ ተፈላጊ በሆኑ የሙያ መስኮች ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለመማር የምትፈልጉ በኮሌጆቻችን በፍላጎታችሁ  ተቀብለን በእውቀትና በስነ ምግባር አንጸን ልናስመርቃችሁ በበርካታ ልምድ ካካበቱ መምህራኖቻችን ጋር ዝግጅታችንን አጠናቀናል። ስለሆነም ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲን ምርጫችሁ አድርጉ ጥራት ባለው ትምህርት አሰጣጣችን እንደምትረኩ ከወዲሁ በደስታ እንገልጽላችኋለን። ተማሪዎቻችን ከመማር ማስተማር ስራ ባሻገር በምንሰጣቸው ምቹ የመኝታ ፣ የምግብና የህክምናና ሌሎች አገልግሎቶች አሰራሮቻችንን በማሻሻል ለተማሪዎች ውጤታማነት ብዙ ሰርተናን እየሰራንም እንገኛለን። በካምፓሶቻችን ፡ በቴፒ ከተማ በሚገኘው ቴፒ  ካምፓስ የሚገኙ ኮሌጆች ምህንድስናና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ፣ ኮምፒቲንግና ኢንፎርማቲክስ ትምህርት ቤት ፣ የተፈጥሮ ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ፣ ሚዛን አማን ከተማ በሚገኘው ዋናው ካምፓስ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ  ፣ ግብርናና የተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ፣ ማህበራዊ ሳይንስና ሰብዓዊነት ኮሌጅ ፣ህግ ትምህርት ቤት ፣ አማን ከተማ በሚገኘው አማን ካምፓስ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኙ መሆናቸውን እንገልጻለን ፤ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲን ስትመርጡ በምርጫችሁ የምትደሰቱ ትሆናላችሁ። 👇👇👇👇👇👇👇 https://www.facebook.com/100087238861353/posts/1055517114032908/?app=fbl

Repost from N/a
​​🔺 የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በ0 ዓመት የሥራ ልምድ ለአታሼ የሥራ መደብ ያወጣው ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመስሪያ ቤቱ ስር በሚገኘው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል። ተቋሙ ያወጣው ማስታወቂያ በአታሼ የሥራ መደብ ላይ ሲሆን የሥራ ደረጃው 9 እና ወርሃዊ ደመወዙ 12566 ብር ነው። ለዚህ የሥራ መደብ የተመደበው የቦታ ብዛት 100 ሲሆን በማንኛውም የትምህርት መስክ የህግ ትምህርትን ጨምሮ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው እና 0 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው አመልካቾች ማመልከት ይችላሉ። ተወዳዳሪዎች ለምዝገባ በሚቀርቡበት ወቅት ስም ድልዝ የሌለው የትምህርት ማስረጃ ዋናውን እና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ማንነታቸውን የሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። የምዝገባ ጊዜው ማስታወቂያው ከወጣበት ከ September 2, 2026 (ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም.) ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የሚከናወን ይሆናል። የፈተናው ቀን በውስጥ ማስታወቂያ የሚገለጽ ሲሆን ሴት አመልካቾች እንዲወዳደሩ ይበረታታሉ። ምዝገባውን በአካል በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ ህንጻ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 በመገኘት ወይም https://forms.gle/R7PmwCNeqEE3EQBN6 የሚለውን የማመልከቻ ሊንክ በመጠቀም ማከናወን ይቻላል። መስሪያ ቤቱ የሚገኘው ከሂልተን ሆቴል ፊት ለፊት ከኮሌጅ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንሰቲቲዩት ጎን ሲሆን ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር +251115522079 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ። #የሥራማስታወቂያ #የህግሙያ #የውጭጉዳይሚኒስቴር #አታሼ #የሥራዕድል join us for more 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/articlee360 https://t.me/articlee360

#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Ex
#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል።

ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ በፍጥነት እንዲያከናውኑ እየተሠራ ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምልመላና ቅበላ ካከና
+1
ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎችን ቅበላ በፍጥነት እንዲያከናውኑ እየተሠራ ነው። የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምልመላና ቅበላ ካከናወኑ በኋላ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም በፍጥነት ጥሪ እንዲያደርጉ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም እንዲጀምር መርሐ ግብር የተያዘ ሲሆን እሱን ለመጠበቅ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት  ከምሽቱ 1:00 ጀምሮ ማየት ትችላላችሁ ተባለ በዚህም መሠረት ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ የተመቻቹትን ዲጂታል አማራጮች በመጠቀም ውጤታቸውን መመልከት ይችላሉ። ውጤት መመልከቻ አማራጮች፡ 1ኛ በድረ-ገጽ (Website): https://result.eaes.et 2ኛ.በቴሌግራም ቦት (Telegram): https://result.eaes.et/telegram 3ኛ በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS): https://result.eaes.et/sms የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜና መንገድ አገልግሎቱ አያይዞ እንዳሳወቀው፣ በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳይጠበቅባቸው በኦንላይን ማቅረብ ይችላሉ። ቅሬታ ለማስገባት https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ መጠቀም የሚቻል ሲሆን፣ ማመልከቻው ከዛሬ ነሐሴ 19 እስከ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል። የተሰጠውን ምላሽም በተመሳሳይ ሊንክ መከታተል ይቻላል። ©️የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1501ኛው የነብዩ መሀመድ የመውሊድ በዓል በሠላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም እና የበረከት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ።
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1501ኛው የነብዩ መሀመድ የመውሊድ በዓል በሠላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም እና የበረከት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ።

ዜና ዕረፍት ፨፨፨፨፨፨ በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል የጤና ባለሙያ የነበሩት ሲ/ር ካሳዬ ሀጎስ በገጠማቸው የጤና እክል ምክንያት በማስተማሪያ ሆስፒታሉ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሀ
ዜና ዕረፍት ፨፨፨፨፨፨ በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል የጤና ባለሙያ የነበሩት ሲ/ር ካሳዬ ሀጎስ በገጠማቸው የጤና እክል ምክንያት በማስተማሪያ ሆስፒታሉ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሀሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል። መላው የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በሲ/ር ካሳዬ ሀጎስ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ፈጣሪ ለመላው ቤተሰባቸውና የስራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል ። የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ

Honorable Dr. Wako Geda የልማትና የለውጥ አምባሳደር፣ የአመራርና የመሪነት ጥበብ ማከማቻ መጋዝን፣የቅርብ ወራጅ ሳይሆን ለነገ አሻግሮ ለትውልድ አሳቢ፣ ቅንና ከሁሉም ሰው ጋር በአወንታዊ
Honorable Dr. Wako Geda የልማትና የለውጥ አምባሳደር፣ የአመራርና የመሪነት ጥበብ ማከማቻ መጋዝን፣የቅርብ ወራጅ ሳይሆን ለነገ አሻግሮ ለትውልድ አሳቢ፣ ቅንና ከሁሉም ሰው ጋር በአወንታዊ ሀሳብ ተግባቢ፣ ስራ ወዳድና የተግባር ሰው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ( ክብር ዶ/ር ዋቆ ገዳ) በርታ ፈጣሪ ሁሌም ከጎንህ ሆኖ ያግዝህ ያበረታታህ። እኛም በምንችለው አቅም ሁሉ ከጎንህ ነን🙏🙏

በጣም ልብ የሚሰብር ዜና ዕረፍት 😭😭😭 ውይኔ መልካም ሰው ፣ የሰው ተጨዋች ለሁለም ሰው አክባሪ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የጠቅላላ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ሰይፉ ከማል
በጣም ልብ የሚሰብር ዜና ዕረፍት  😭😭😭 ውይኔ መልካም ሰው ፣ የሰው ተጨዋች ለሁለም ሰው  አክባሪ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የጠቅላላ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ሰይፉ ከማል በገጠማቸው ድንገተኛ ሕመም ምክንያት ዛሬ ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል። ለመላው የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በአቶ ሰይፉ ከማል ህልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽኩ  ፈጣሪ ለመላው ቤተሰባቸውና የስራ ባልደረቦቻቸው  መጽናናትን እንዲሰጣቸው እመኛለሁ ። ፈጣሪ  ነፍሱን በገነት ያኑርልን 😭😭😭😭😭😭😭😭 https://www.facebook.com/100087238861353/posts/1018395081078445/?app=fbl

ስፔን የ23ኛው ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች። የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል። በጭማሪው ክፍለ ጊዜ 106ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ያስቆጠራት ግብ ስፔንን አሸናፊ አድርጋለች። በዚህም ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ውድድሩን አሸንፋ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ሆናለች።

የ2026 አለም ዋንጫ ሻምፒዮኑን ገምቱ
Anonymous voting

በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቴፒ ግቢ ለአራተኛ ዙር በወረቀት ተፈታኝ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና ስለ ፈተናው ገለፃ መርሃ ግብር ተካሄደ። ሚቴዩቴ:-ሐምሌ 05/218ዓም በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ
+5
በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቴፒ ግቢ ለአራተኛ ዙር በወረቀት ተፈታኝ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና ስለ ፈተናው ገለፃ መርሃ ግብር ተካሄደ። ሚቴዩቴ:-ሐምሌ 05/218ዓም በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቴፒ ግቢ ለ2018 ዓ.ም አራተኛ ዙር በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና ስለ ፈተናው አፈፃፀም ገለፃ የተሰጠበት መርሃ ግብር ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ እና የአስተዳደር ኃላፊዎች ተገኝተው ለተፈታኝ ተማሪዎች እንኳን ወደ ቴፒ ግቢ በደህና መጣችሁ በማለት በፈተና ወቅት ሊከተሏቸው ስለሚገቡ የፈተና ሕጎችና ሥነ-ምግባሮች ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል። በገለፃው ወቅት ተማሪዎች የፈተና ሰዓትን በጥብቅ እንዲያከብሩ፣ የተከለከሉ ቁሳቁሶችን ወደ ፈተና አዳራሽ እንዳያስገቡ፣ የፈተና መመሪያዎችን በአግባቡ እንዲከተሉ እና ማንኛውንም የፈተና ሥነ-ምግባር ጥሰት እንዲቆጠቡ አፅንኦት ተሰጥቷል። በተጨማሪም ተማሪዎች ፈተናቸውን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲወስዱ አስፈላጊ የመኝታ፣ የምግብ፣ የጤና እና የደኅንነት አገልግሎቶችን ማዘጋጀቱን ገልጿል። በመጨረሻም ለሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች መልካም የፈተና ጊዜ እና የተሳካ ውጤት ተመኝቷል።

ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በጀግናው የለውጡ ሞተር በዶ/ር ዋቆ ገዳ የሚመሩ አመራሮች ከመምጣታቸው በፊት የነበሩ ችገሮች እና ከመጡ በኃላ እየታዩ ያሉ አመርቂ ውጤቶች፣ በ17 ዓመት ውስጥ ያልታየ ለውጥ በ
+5
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በጀግናው የለውጡ ሞተር በዶ/ር ዋቆ ገዳ የሚመሩ አመራሮች ከመምጣታቸው በፊት የነበሩ ችገሮች እና ከመጡ በኃላ እየታዩ ያሉ አመርቂ ውጤቶች፣ በ17 ዓመት ውስጥ ያልታየ ለውጥ በሁለት ዓመት ውስጥ ያሳዩን ጀግኖች ከልብ ክብር እና ምስጋና ይገባቸዋል።

ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቃችሁ ወይም የመውጫ ፈተና ሳትፈተኑ የዲግሪ ባለቤት የሆናችሁ በሙሉ እንደገና የትምህርት ማስረጃችሁን
+3
ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቃችሁ ወይም የመውጫ ፈተና ሳትፈተኑ የዲግሪ ባለቤት የሆናችሁ በሙሉ እንደገና የትምህርት ማስረጃችሁን ለማረጋገጥ ሲባል ሊፈተኑ ነው ተብሏል። Via: FDRE Education and Training Authority Facebook page! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/hig_keld_ena_kumneger

የሚዛን አማን አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስራ በመጀመሩ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተሰማውን ታላቅ ደስታ ገልጿል። ሐምሌ 3/2018 በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አቢይ አህመድ የመሰረት ድንጋ
+2
የሚዛን አማን አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስራ በመጀመሩ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተሰማውን ታላቅ ደስታ ገልጿል። ሐምሌ 3/2018 በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አቢይ አህመድ የመሰረት ድንጋይ ተጥሎለት ፣ ግንባታው በስኬት ተጠናቆ ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረው የሚዛን አማን አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ለመላው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝብና ለሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፋች ሆንዋል ያሉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዋቆ ገዳ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለተቋሙ ማህበረሰብ ባስተላለፉት መግለጫ ፤ የአየር ማረፊያው ስራ መጀመር ለዩኒቨርሲቲው የትምህርት ፣ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎች መፋጠን የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ገልጸው የተሰማቸውን ጥልቅ ደስታ ገልጸዋል። በመጨረሻም ፕሬዝዳቱ በመልዕክታቸው ይህ አየር ማረፊያ ተጠናቆ ስራ መጀመሩ ለሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በርካታ እድሎችን ይዞ እንደሚመጣ በመግለጽ በተለይም የአካባቢውን የተፈጥሮ ሀብት ለልማት ለማዋል የሚያግዙና ያገናዘቡ የስልጠና ፕሮግራሞችን ከፍቶ ማህበረሰባችንን ተጠቃሚ ለማድረግ ፣ ምሁራን ከየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በቀላሉ እንዲመጡ የአየር መንገዱ በረራ መጀመር ፋይዳው እጅግ የላቀ ነው ብለው ለመላው የደቡብ ምዕራብ ክልል ህዝባችንና ለዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ ፤ እንኳን ደስ አለን! ብለዋል።