ch
Feedback
Mizan Tepi University Students Union Channel

Mizan Tepi University Students Union Channel

前往频道在 Telegram

Our mission is to unite students from all years, fostering a sense of community and facilitating the exchange of information.Buy ads: https://telega.io/c/MTU_Main_Campus contact us at:  @Sablaw  @MTU13bot  @SeudEmpire  group: @mizan_tepi_university

显示更多
5 125
订阅者
-224 小时
-47
-7430
帖子存档
እሮብ ብሔራዊ Exit Exam ለምትፈተኑ የህግ ተማሪዎች በሙሉ ​ውድ እና የተከበራችሁ የህግ ቤተሰቦቼ፣ ታናናሾቼ እንዲሁም የነገው የፍትህ ማማ ተረካቢዎች! ​የነገው እሮብ ለእናንተ ተራ ቀን አይደለም፤ ላለፉት አምስት አመታት ሌት ከቀን የደከማችሁበት፣ እንቅልፍ አጥታችሁ ያነበባችሁበት፣ በፅንሰ ሃሳቦችና በሕግ አንቀጾች መሃል ስትሟገቱ የኖራችሁበትን ጥረት ፍሬ የምታዩበት ትልቅ የታሪክ ምዕራፍ ነው። ምንም እንኳን እኔ ግቢውን ለቅቄ በአሁኑ ወቅት  በስራው ዓለም ላይ ብገኝም፣ ተማሪ እያለሁ በህግ ተማሪዎች ህብረት በነበረኝ የፕሬዝዳንትነት ቆይታ ከሁላችሁ ጋር የነበረኝ ቅርበትና ትስስር ዛሬም ድረስ በውስጤ ትልቅ ቦታ አለው። በመሆኑም ይህንን ወሳኝ ምዕራፍ ስትሻገሩ ከጎናችሁ መሆኔን ለመግለፅና ጥቂት የማነቃቂያ ቢጤ ላካፍላችሁ ወደድኩ😊። ​ ​ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁንና የ2017 ዓ.ም. የኛ ባች በኤግዚት ፈተና ወቅት እጅግ አስደናቂ ታሪክ ነው የሰራው። ካለን ጠንካራ ዝግጅት የተነሳ ሁላችንም በከፍተኛ ውጤት ፈተናውን አልፈናል። በአንድ ነጥብ 49 በማምጣት የቀረችብን አንድ እህታችን ብቻ የነበረች ሲሆን፣ እሷም በሁለተኛው ዙር ፈተና እጅግ ምርጥ ውጤት አስመዝግባ አልፋለች። ​ዛሬ ላይ ኩራት በሚሰጥ መልኩ ከ95% በላይ የምንሆነው የ2017 ዓ.ም. የሕግ ተመራቂዎች በፌደራልና በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ የፍትህ ተቋማት ውስጥ በዳኝነት እና በአቃቤ ሕግነት ሙያ ላይ ተሰማርተን ሀገራችንን በታማኝነት እያገለገልን እንገኛለን። ጥቂቶቻችንም በግል እና በመንግሥት ድርጅቶች የሕግ ማማከርና ተያያዥ ስራዎች ላይ ተሰማርተን ስኬታማ መሆን ችለናል። አሁን ደግሞ ይህንን የፍትህ አደባባይ እንድትቀላቀሉ እናንተን በጉጉት እየጠበቅናችሁ ነው። ​ "የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪ በስራው አለም ምርጥ ተፎካካሪ ነው!" ​ይህንን የምላችሁ በባዶ መፈክር አይደለም፤ በተጨባጭ በተግባር ያረጋገጥነው እውነታ ስለሆነ ነው። የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በማንኛውም የውድድር መድረክ ላይ የማይበገሩ መሆናቸውን በቅርቡ የታዩ ስኬቶች ምስክር ናቸው፡ ​ለምሳሌ ያክል በቅርቡ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ፍትሕ ቢሮ በወጣው የዳኞች እና አቃቢያን ሕግ የቅጥር ውድድር ላይ 12 የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተወዳድረው፣ 12ቱም የመግቢያ ፈተናውን በማለፍ በዳኝነት እና በአቃቤ ሕግነት ሙያ ተቀጥረዋል። በኦሮሚያ እና  በደቡብም በተመሳሳይ። ​እንድሁም በፌደራል ፍትህ ሚኒስቴር በደረጃ 3 በወጣው ከፍተኛ የአቃቤ ሕግነት ስራ ላይ ሁለት የሚዛን ተመራቂዎች ተሳትፈው፣ አንደኛው 100 ከ 100  ከፍተኛውን ውጤት በማምጣት አንደኛ ሲወጣ፣ ሁለተኛዋም እንዲሁ እጅግ አስደናቂ ውጤት በማምጣት ተቀጥራ ማገልገል ጀምራለች። ​ይህ ታሪክ የሚያሳየው አንድ ነገር ብቻ ነው፤ እናንተ የተማራችሁት በብዙ ፈተናዎች አልፈው በመጡ፣ ምርጥና አንቱ በተባሉ መምህራን እጅ ነው። በፈተና ውስጥ አልፋችሁ የወጣችሁ የወርቅ ጥራጥሬዎች በመሆናችሁ፣ ከፊታችሁ የሚጠብቃችሁ የኤግዚት ፈተና ለእናንተ ቀላልና የማትበገሩለት ነው። ለቀጣዩ እሮብ ፈተና ጥቂት የወንድማዊ ምክሮችቸን ልስጣችሁ ​አሁን የዘራችሁትን የምታጭዱበት ጊዜ ነው፡ ባለፉት ዓመታት፣ ወራትና ቀናት፣ አልፎ ተርፎም በነበሩት ረጅም ሌሊቶች ከደብተርና መጽሐፍ ጋር የታገላችሁት ለዚህ ቀን ነው። የለፋችሁበት ጥረት መቼም ቢሆን ከንቱ አይቀርም። ​በስነ-ልቦና ዝግጁ ሁኑ ከእውቀት በላይ አሁን የሚያስፈልጋችሁ መረጋጋትና በራስ መተማመን ነው። ፍርሃትና ጭንቀት የምታውቁትን ነገር እንኳን እንዳታስታውሱ ሊያደርግ ስለሚችል፣ ቀሪዎቹን ቀናት አእምሯችሁን በማረጋጋትና እረፍት በመስጠት አሳልፉ። ​ፈተናውን በአሸናፊነት ስሜት ተገናኙት ወደ ፈተና ክፍል ስትገቡ "እችለዋለሁ!" የሚለውን ታላቅ ስነ ልቦና ሰንቃችሁ ይሁን። ሌላው ፈተናው ከሚጀመርበት ሰዓት ቢያንስ ከ30 እስከ 45 ደቂቃ ቀድማችሁ በቦታው ተገኙ።ቀድሞ መድረስ የመጨረሻ ደቂቃ መሯሯጥንና መቅበዝበዝን ያስቀራል። አእምሯችሁ እንዲረጋጋ እና የልብ ትርታችሁ መደበኛ እንዲሆን ይረዳል። የሰዓት አጠቃቀምን በተመለከተ ፈተናው ሲጀምር አጠቃላይ የተሰጣችሁን ሰዓት እና የጥያቄዎቹን ብዛት በፍጥነት አነፃፅሩ። ለአንድ ጥያቄ በአማካይ ስንት ደቂቃ/ሰከንድ እንደሚደርሰው አስሉ ለምሳሌ፦ 100 ጥያቄ ለ3 ሰዓት ከሆነ፣ ለአንድ ጥያቄ ከ1 ደቂቃ ከ40 ሰከንድ በላይ አታባክኑ።እየመለሳችሁ እለፉ። ​ ማሰብ የሚጠይቁ፣ ረጅም Case ያላቸውንና ያጠራጠሯችሁን ጥያቄዎች ምልክት አድርጋችሁባቸው አልፋችሁ፣ የመጀመሪያውን ዙር ስትጨርሱ ተመልሳችሁ በሰፊው አስቡባቸው። በአብዛኛዎቹ የኦንላይን መፈተኛ ሲስተሞች ላይ ያጠራጠራችሁን ጥያቄ በኋላ ተመልሳችሁ እንድታዩት ምልክት ማድረጊያ Flag  ቁልፍ አለ። እሱን በመጠቀም ጥያቄውን ምልክት አድርጋችሁ እለፉ። ሲስተሙ መጨረሻ ላይ ያልመለሳችኋቸውን ወይም ምልክት የተደረገባቸውን ጥያቄዎች ለይቶ ያሳያችኋል። እንድሁም በፍጹም አንድም ጥያቄ ሳትመልሱ በባዶ እንዳታልፉ። ጊዜው ሊያልቅ ሲል እንኳ ቢሆን ያጠራጠሯችሁን ጥያቄዎች የተሻለ ነው ያላችሁትን Educated Guess አድርጉ። አይበለውና የቴክኒክ ችግር ቢያጋጥማችሁ መረጋጋት ይኖርባችኋል ኮምፒውተሩ ቢዘጋ፣ ኔትወርክ ቢያስቸግር ወይም መብራት ቢጠፋ በፍጹም አትደንግጡ። ከእናንተ የሚጠበቀው ወዲያውኑ እጃችሁን በማውጣት በአቅራቢያችሁ ላለ ፈታኝ ማሳውቅ ብቻ ነው።ሲስተሙ የሰዓትና የሰጣችሁትን መልስ መረጃ በአግባቡ ስለሚይዝ የምታጡት ነገር የለም። ​የናንተ ስኬት የዩኒቨርሲቲያችን፣ የቤተሰቦቻችሁ እና የሀገራችን ኩራት ነው። እኛ በትላንቱ ስኬታችን መንገድ ጠርገናል፤ እናንተ ደግሞ በበለጠ ውጤት ያንን መንገድ ታደምቁታላችሁ ብዬ ሙሉ እምነት አለኝ። ​እሮብ ለሚኖራችሁ ብሔራዊ ፈተና ፈጣሪ ማስተዋሉንና ብሩህ አእምሮውን ይቸርላችሁ! መልካም ዕድልና መልካም ውጤት እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ! ​የእናንተው ወንድም፣ የቀድሞው የህግ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት! ©ስዑድ አህመድ

አስቸኳይ ማስታወቂያ ******* ለሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተፈታኝ ዕጩዎች (ተማሪዎች) በሙሉ፤ የዘንድሮውን የፈተና ሲስተም ለመጠቀም ማንነትን ማረጋገጥ (Identity Verification) የግዴታ በመሆኑ፣ ማንነታቸውን ያላረጋገጡ ተፈታኞች የተጠቃሚ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) ማግኘት የማይችሉ መሆኑንና በዚህም ምክንያት ፈተናውን መውሰድ የማይቻል መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን። ስለሆነም፣ ተፈታኞች በሙሉ አስቀድማችሁ የብሔራዊ መታወቂያችሁን (National ID) በመጠቀም ማንነታችሁን እንድታረጋግጡ በጥብቅ እናሳስባለን። ⚠️ ማሳሰቢያ፦ ይህንን ሳያደርጉ በመቅረታቸው ምክንያት ለሚፈጠር ለማንኛውም ዓይነት ችግር ወይም የፈተና መታለፍ ዩኒቨርሲቲው ምንም ዓይነት ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን ከወዲሁ እናስታውቃለን። በተያያዥም፣ ማንነታችሁን ያረጋገጣችሁ ተማሪዎች የተጠቃሚ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ

በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለ2018 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች በኦላይን ፈተና መሰጠት ተጀመረ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚቴዩ ፣ግንቦት 27/2018 ዓ/ም ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በዋ
+9
በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለ2018 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች በኦላይን  ፈተና መሰጠት ተጀመረ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚቴዩ ፣ግንቦት 27/2018 ዓ/ም ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በዋናው እና ቴፒ ግቢ ለሚገኙ 2018 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች በኦላይን  ፈተና በይፋ መሰጠት መጀመሩ ተገለጸ። ፈተናው በሰላማዊና በተደራጀ ሁኔታ እንዲካሄድ አስፈላጊ ዝግጅቶች ሲደረግ መቆየቱም የተገለጸ ሲሆን ፈተናውን በተገቢው ደረጃ ለማስፈፀም የመፈተኛ አዳራሾችን ከማዘጋጀት ጀምሮ በርካታ ስራዎች ለፈተናው ስኬታማነት ስለመሰራቱም ተገልጿል። ተማሪዎች ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ እንዲሰሩ  ያሳሰቡት የዩኒቨርሲቲው  ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዋቆ ገዳ የፈተናውን ሂደት ተዘዋውረው በተመለከቱበት ወቅት ለተፈታኝ ተማሪዎች ስኬትን በመመኘት መልዕክት አስተላልፈዋል። መልካም ዕድል ለሁሉም የ2018 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች! የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ Mizan-Tepi University

የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዋቆ ገዳ ለእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ክቡር ዶ/ር ዋቆ ገዳ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ የእስልምና እምነት ተ
የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዋቆ ገዳ ለእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ክቡር ዶ/ር ዋቆ ገዳ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሆኑ መምህራን ፣ አስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች እንዲሁም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን በዓሉ የሰላም የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆንም ተመኝተዋል።                                         መልካም በዓል ! ዋቆ ገዳ (ዶ/ር) ፕሬዚዳንት የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-አድሐ (ዐረፋ) በዓል በሰላም፣ በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን፡፡
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-አድሐ (ዐረፋ) በዓል በሰላም፣ በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን፡፡

👍የለውጥ ጉዞ እንደቀጠለ ነው!!!👍 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በአዲሱ አመራር ብዙ ለውጦችን እያሳየ መሆኑ ይታወቃል። ለአብነት ያክል በጭቃ ስንሰቃይ የነበረውን መንገድ አስፓልት ተሰርቶ ሳንሳቀቅ ግቢ
+4
👍የለውጥ ጉዞ እንደቀጠለ ነው!!!👍 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በአዲሱ አመራር ብዙ ለውጦችን እያሳየ መሆኑ ይታወቃል። ለአብነት ያክል በጭቃ ስንሰቃይ የነበረውን መንገድ አስፓልት ተሰርቶ ሳንሳቀቅ ግቢ ውስጥ መንቀሳቀስ ችለናል፣ የመመገቢያ አዳራሻችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ተሰርተው በጽዱ አዳራሽ መመገብ ችለናል። አሁን ደግሞ ፕሬዚዳንታችን ዶክተር ዋቆ ገዳ ባለፈው አመት ለተማሪዎቻቸው በገቡት ቃል መሰረት አዳዲስና ዘመናዊ ወንበሮች ገብተው ካፈው አሸብርቋል።  በሌላ በኩልም የምግብ ሁኔታን ሙሉ በሙሉ ለማሻሻል የእንጀራ ምጣድ እና ሌሎች ማሽኖች ዝርጋታ ተጠናቋል። በቀጣይ ሁሉንም ተማሪ የDigital library ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል። ለፕሬዚዳንታችን ዶ/ር ዋቆ ገዳና ማኔጅመንቱ ዩንቨርሲትያችንን ለተማሪዎች ምቹ ለማድረግ እየሰሩ ሲላሉት ነገር ሁሉ እጅግ አድርገን እናመሰግናለን። 🙏🙏🙏🙏

MTU ARSE Family Congratulations💞❤💞❤ Today is Unique days💞❤💞❤
+7
MTU ARSE Family Congratulations💞❤💞❤ Today is Unique days💞❤💞❤

ለመላው የጊቢያች የሀያሉ ክለብ አርሰናል ደጋፊዎች በሙሉ ዛሬ ማለትም በቀን 16/9/2018 ታላቅ ድግስ አዘጋጅተናል ስለሆነም መላው የአርሰናል ደጋፊዎች 4:00 ሰዓት ላይ እስታድየም አከባቢ የሙሽራውን ልብስ በመልበስ ሰርጋችንን በደማቅ ሁኔታ እናከብራለን ዛሬ የሚዜነት ጊዜ አብቅቶ ንጉሱ ሚሞሸርበት ቀን ነው ዛሬ የአርሰናል ሀያልነት የደጋፊው ፅናት ፍሬ ሚያፈራበት ቀን ነው ስለዚ ሁላቹም የኑጉሱ ክለብ ደጋፊዎች መቅረት የተከለከለ ነው አርስናል አርሰናል አርስናል🏆🏆🏆🏆🏆🔴🔴⚪️⚪️

🔔 ያረጋግጡ! የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባቹ በአስቸኳይ የማረጋገጥ ሥራ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል። ተከታዩን ሊንክ (https://verify.ethernet.edu.et/) ከተጫኑ በኋላ Remedial Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Start Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ። የሪሚዲያል ፈተና ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል።

የትራንስፖርት ምዝገባ ቀን 14-15/9/2018 ብቻ አዲስ አበባ........2600 1. ድሪባ 2. ማረኝ ወሎ........3650 1.ኤርሚያስ 2.ሬድዋን ሀዋሳ .......3350 1 ሙሴ ጋስ 2, አሻግሬ መሰረት ወላይታ ......3550 1,አበባው 2, ሳኦል ሲኖር ባህር ዳር .....4150, ደብረማርቆስ .... 3400 1 ,ፋሩክ 2, መንግስቱ ካጫ 3, ውብነህ ማሳሰቢያ የምዝገባ ቀን ዛሬ እና ነገ ብቻ ምዝገባ  በcash የምናስተናግድ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን። የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት

ለክቡር ፕሬዝዳንታችን ዶ/ር ዋቆ ገዳ እንኳን ደስ አለዎት! የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት ክቡር ዶ/ር ዋቆ ገዳ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በሚገኘው የህንድ ኤምባሲ ከህንድ ኢንተርናሽና
ለክቡር ፕሬዝዳንታችን ዶ/ር ዋቆ ገዳ እንኳን ደስ አለዎት! የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት ክቡር ዶ/ር ዋቆ ገዳ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በሚገኘው የህንድ ኤምባሲ ከህንድ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ማኔጅመንት እና ሪሰርች ሴንተር በኢንተርናሽናል ህግ (International Law) ሁለተኛ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በተሳካ ሁኔታ በመከላከላቸው ከልብ እንኳን ደስ አለዎት! ይህ ከፍተኛ የአካዳሚክ ስኬት የእርስዎን ያልተቋረጠ ትጋት፣ ብቃት፣ የአመራር ክህሎት እና ለዘላቂ ትምህርት ያለዎትን ቁርጠኝነት ያሳያል። ከዚህ በፊትም በሰው ኃብት አስተዳደር (Human Resource Management) የመጀመሪያ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ማግኘታቸው ይህንን ስኬት የበለጠ የሚያስደንቅና ተነሳሽ ያደርገዋል። መላው የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እና ማህበረሰብ በዚህ ታላቅ ስኬት ከፍተኛ ኩራት ይሰማዋል፤ ለወደፊቱም በአካዳሚክ፣ በአመራር እና በሙያ ዘርፍ የበለጠ ስኬት እንዲያስመዘግቡ መልካም ምኞታችንን እናቀርባለን። እንኳን ደስ አለዎት! የጀግና መሪያችን ዶ/ር ዋቆ ገዳ ተማሪ በመሆኔ ሁሌ ኩራት ይሰማኛል። እናንተስ👇👇👇👇👇 https://www.facebook.com/100087238861353/posts/965053869745900/?app=fbl

ለመላው የጊቢያችን የአርሰናል ደጋፊዋች በሙሉ ዛሬ ማለትም በቀን 12/9/2018 ከጥዋቱ 3:00 ሰዓት ላይ እስታዲየም እንድትገኙ አሳስባለው aresnal forever⚪️🔴⚪️🔴⚪️🔴

Arsenal The Champions
+1
Arsenal The Champions

Congratulatory Message to Our Esteemed President, Dr. Wako Geda! Heartfelt congratulations to the visionary leader, Dr. Wako
+2
Congratulatory Message to Our Esteemed President, Dr. Wako Geda! Heartfelt congratulations to the visionary leader, Dr. Wako Geda, President of Mizan-Tepi University, on the successful defense of his second PhD degree in International Law from the Indian International University of Management and Research Center today at the Indian Embassy in Addis Ababa. This outstanding academic achievement reflects his unwavering commitment to excellence, leadership, and lifelong learning. Dr. Wako Geda previously earned his first PhD degree in Human Resource Management, making this accomplishment even more remarkable and inspiring. The entire Mizan-Tepi University community is proud of this significant milestone and extends its warmest congratulations and best wishes for his continued success in academic, leadership and professional endeavors.

ከቀን 11-12/09/2018 ዓ.ም ድረስ የሚሞላ ቅጽ ስላለ የክፍል ተወካዮች የሆናችሁ ዋናው ሪጅስተር በመምጣት እንዲትቀበሉ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ: ይህን ቅጽ ያልሞላ ተማሪ ክሊንራንስ የማይወስድ
ከቀን 11-12/09/2018 ዓ.ም ድረስ የሚሞላ ቅጽ ስላለ የክፍል ተወካዮች የሆናችሁ ዋናው ሪጅስተር በመምጣት እንዲትቀበሉ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ: ይህን ቅጽ ያልሞላ ተማሪ ክሊንራንስ የማይወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።

ማስታወቂያ ለተማሪዎቻችን የ2018 ዓ.ም የትምህርት ጊዜ ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜ ነው የቀረው።  በመሆኑም የተማሪዎች ህብረት ጉዟችሁን ቀላል፣ወጭ ቆጣቢ እንድሁም ከአላስፈላጊ መጉላላቶች ለመጠበቅ ወደ ተለያዩ  የሃገራችን ክፍሎች ለምትሄዱ ተማሪዎቻችን ትራንስፖርት ማመቻቸታችንን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው። ስለሆነም ቀድማችሁ በመመዝገብ እና ክፍያ በመፈፀም አገልግሎቱን እንድታገኙ ስንል እናሳዉቃለን። አዲስ አበባ........2600 1. ድሪባ 2. ማረኝ ወሎ........4650 1.ኤርሚያስ 2.ሬድዋን ሀዋሳ .......3350 1 ሙሴ ጋስ 2, ስንታየሁ ወላይታ ......3550 1,መንግሥቱ  ካጫ 2, ሳኦል ሲኖር ባህር ዳር .....4150,  ደብረማርቆስ .... 3400 1. ፋሩክ 2,  አበባው 3, ውብነህ ማሳሰቢያ: ስማቸው ከተዘረዘሩት ውጪ የየትኛውም አካል የምዝገባ እውቅና የሌለው መሆኑን እናሳውቃለን። ምዝገባው የሚካሄደው ከ ቀን 10/9/2018 ዓ.ም ጀምሮ  ለተወሰኑ ቀናት ብቻ መሆኑን  እና ምዝገባ  በcash የምናስተናግድ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን። የመመዝገቢያ ቦታ ካፌ በር አከባቢ የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት

እንኳን ደስ አላችሁ ! ** በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ባልደረባ የሆኑት ዶ/ር ገኤራ ጉደታ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍልና ዶ/ር ጌትነት ተሾመ ከማኔጅመንት ትምህርት ክፍል የ
+1
እንኳን ደስ አላችሁ ! ** በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ባልደረባ የሆኑት ዶ/ር ገኤራ ጉደታ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት  ክፍልና ዶ/ር ጌትነት ተሾመ ከማኔጅመንት ትምህርት  ክፍል የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን  በስኬት አጠናቀው በመመለሳቸው የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ የተሰማውን ደስታ ይገልጻል።  በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ! Congratulations! The staff members of the College of Business and Economics, Dr. Geara Gudeta from the Department of Economics and Dr. Getenet Teshome from the Department of Management have successfully completed their PhD studies. Mizan Tepi University extends its warmest congratulations to Dr. Geara Gudeta and Dr. Getenet Teshome on achieving this significant academic milestone. Their dedication, hard work, and academic excellence are truly commendable. Congratulations once again, and best wishes for continued success in your future academic and professional endeavors! የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ Mizan-Tepi University Light of the green Valley

ሰንበት እንዴት እያለፈ ነው ቤተሰብ

ማስታወቂያ ለካፌ ተጠቃሚዎች በሙሉ ዛሬ በቀን 03/09/2018 ምሳ 6:00 ሳዓት ሚጀምረው በዝናብ ምክንያት ወደ 6:30 መራዘሙን ከታላቅ ይቅርታ ጋር እናሳውቃለን:: የተማሪዎች ህብረት ጽ/ቤት