395
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from የፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል
በተጨማሪም ውጤታችሁ (ተናጠላዊ ውጤት) ከ50% በታች የሆነባችሁ ተማሪዎች ውጤታችሁ ዝቅ ያለበት ታይቶ እንደውጤታችሁ በአሳይመንት እና በፈተና ወደ ተፈለገው ውጤት (ማወቅ) ከፍ እንድትሉ ይደረጋል።
ዓላማው እንደላይኛው🙏
Repost from የፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል
አንዳንድ ተማሪዎች በተለያዩ ምክንያቶች ሁለት ትምህርት እና አንድ ብቻ ትምህርት የተማራችሁ በመሆኑ ቀድሞ የነበራችሁበትን ክፍል የምትደግሙ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን( የምትደግሙት ዓላማችን ማወቅ እንጂ መቁጠር እንዳይሆን በሚል ነው።)
Repost from የፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል
የተከበራችሁ ተማሪዎች በድጋሚ ለማስታወስ ያህል
የምድብ ሦስት እና አራት በነገው ዕለት (24/02/2016ዓ.ም.) የሰንበት ትምህርት ቤታችን አዳራሽ ከ11:30 ጀምሮ ነገረ ማርያም ትምህርት ይረጣል/ይጀመራል።
ሌላው የምድብ ሁለት ተማሪዎች የማቴዎስ ወንጌል አንድምታ ከ12:00 ጀምሮ በክርስትና ቤቱ ይሠጣል።
በመሆኑም ከላይ የተገለጻችሁ ምድቦች በሰዓታችሁ ተገኝታችሁ ትምህርቱን እንድትከታተሉ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን፤እናስታውሳለን።
👉የምድብ አንድ መማሪያ ቦታ የሰ/ት/ቤት አዳራሽ
👉 የምድብ ሁለት መማሪያ የክርስትና ቤት
👉 የምድብ ሦስት መመሪያ ደጀ ሰላም👉 የምድብ አራት መማሪያ (ለጊዜው) የሰ/ት/ቤቱ ጽ/ቤት ቢሮ
👉 የምድብ አራት ትምህርት (ለነገ) 4:00 ላይ ይጀምራል።
Repost from የፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል
የተከበራችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሁሉም ምድብ ያላችሁ ተማሪዎች ከፊታችን እሁድ ትምህርታችሁ ስለሚጀምር ስለሚጀምር በዕለቱ እና በሰዓቱ ተገኝታችሁ ትምህርታችሁን እንድትከታተሉ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
የሁሉም ምድብ ትምህርቱ የሚሠጠው እሁድ ጠዋት ሲሆን፣
ምድብ አንድ ጠዋት ከ3:30 -6:30
ምድብ ሁለት ጠዋት ከ3:30-6:30
ምድብ ሦስት ጠዋት 4:30-7:00
ምድብ አራት ጠዋት ከ2:00- 4:00
ድረስ የሚሠጥ ሲሆን፣ሁላችሁም ተማሪዎች በሰዓቱ (መውጣት እንደምትፈልጉ ሁሉ) በመገኘት ትምህርቱን እንድትከታተሉ በድጋሚ በእግዚአብሔር ስም እናስታውሳለን።
ሰላመ እግዚአብሔር አንለየን።
እነደምን አመሻቹ ነገ እረብ መስከረም 23/2016 ዓ.ም በ ወለተ ማርያም ወላጆች ቤት በመገኘት የፀሎት እና የማጽናናት መርሐግብር ይካሄዳል ከሞሽቱ 11:00 ሰዓት ላይ ቤ/ክ ተሰባስበን ጣፍ ይዘን በመሄድ እህታችንን እናስባታለን
አድራሻ ...ባጃጅ ተራ መጨረሻ ከፓሊስ ጣቢያ ጀርባ
በእህታችን ወለተ ማርያም /ጊዜ ግርማ / እረፍት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በሰንበት ት/ቤታችን እና በአባላቶቻችን ስም እንገልጻለን የአገለገለቻት እመብርሀን በእቅፋ ታስቀምጥልን አጽናኝ መላክን ይላክልን
"በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳውም ጠልን ይጠግባል።"
መዝ ፷፬(፷፭) ፥ ፲፩
ውድ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት እና ወዳጆች እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም በጤና አሸጋገረራቹ አዲሱ ዓመት ንሰሀ የምንገባበት በአገልግሎታችን የምንበረታበት ፍሬ የምናፈራበት የተመኘነውን በጎ መሻት የምንፈጽምበት የሀገራችንን ሰላም የምናይበት ዓመት እንዲሆንልን እንመኛለን
መልካም በዓል
.
እንኳን አደረሳችሁ
ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕ. 4
22፤ ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥
23፤ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥
24፤ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።
25፤ ስለዚህ ውሸትን አስወግዳችሁ፥ እርስ በርሳችን ብልቶች ሆነናልና እያንዳንዳችሁ ከባልንጀሮቻችሁ ጋር እውነትን ተነጋገሩ።
መልካም አዲስ ዓመት
አዲስ ህይወት
እንደምን አላቹ የተወደዳቹ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት ከረጅም ዓመት በሃላ የአባላት አመታዊ ጉዞ ሐምሌ 2/2015 ዓ.ም ወደ አዲስ አለም ቅድስት ማርያም ገዳም ስለተዘጋጀ በልማት ክፍል በኩል ፈጥናቹ እንድትመዘገብ እናሳስባለን
የጉዞ ዋጋ 230 ብር ከመሰተንግዶ ጋር
ሰላም እንዴት አመሻችሁ የነገ የስብሰባ ሰዓታችን 3:30 የሚጀምር እና መፈጸሚያው ከ5:30_6:00 መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን።
በነገው ዕለት የሚኖረን ስብሰባ ወሳኝ እና አባልነታችንን የምናረጋግጥበት በመሆኑ ባለማርፈድ ሀላፊነታችንን እንወጣ፤ ስንል እናሳስባለን።
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በሀገር ውስጥ እና በውጪ ሀገራት ለሚገኙ ምዕመናን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በርቀት እና በኦንላይን ትምህርት ሊሰጥ ዝግጅቱን አጠናቆ ምዝገባውን የመጪው ሰኞ ሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚጀምር ገልጿል።
ዩኒቨርስቲው በልዩ ልዩ የሥራ መስክ ላይ ተሰማርተው በጊዜ እና በቦታ ርቀት ትምህርት መማር ላልቻሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በርቀት እና በኦንላይን ትምህርታቸውን እንዲማሩ በማሰብ ምዝገባውን ሊጀምር መሆኑን ነው የገለጸው።
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በርቀት እና በኦንላይን ትምህርት የሙሉ ጊዜ ሙያዊ ሠራተኞችን፣ ሀገርን በመከላከል ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ወታደሮችን፣ በስደት ምክንያት በአንድ ቦታ ነዋሪ መሆን ያልቻሉ ሰዎችና በተለያዩ የሥራ መስክ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችን ያላቸውን ሥራ እና ማኅበራዊ ግንኙነት እንዲሁም የአኗኗር ዘይቤ ሳይቀይሩ ካላቸው እውቀትና ጥበብ በተጨማሪ ከፍተኛ የኦርቶዶክሳዊ ነገረ መለኮት ትምህርት ማግኘት ያስችላልም ነው የተባለው።
በርቀት እና በኦንላይን ትምህርት ዘርፍ የሚሰጣቸው የትምህርት መስኮችም
በነገረ መለኮት የትምህርት ዘርፍ በዲግሪ
1, የዶግማ ትምህርት
2, የቅዱሳት መጽሓፍት ትምህርት
3, የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ትምህርት
4, የሥርዓተ አምልኮና ትምህርተ ኖሎት
5, ሥነ ምግባርና ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት
በኢትዮጵያ ጥናት ትምህርት ዘርፍን በዲግሪ
1, የኢትዮጵያ ታሪክ
2, የግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ
3, የሥነ ጥበብና ባህል ጥናት በተጨማሪም በዲፕሎማ የነገረ መለኮት ትምህርት እና በሠርተፊኬት የነገረ መለኮት ትምህርት መሆኑ ተገልጿል።
ትምህርቱን ለመማርም ከአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የአባልነት ማስረጃ፣ ከትምህርት ተቋማት የተማሩበት ማስረጃ (መልቀቂያ) እና 4 ጉርድ ፎቶ በመያዝ መመዝገብ እንደሚችል ተገልጿል።ይህም ተማሪዎች በአነስተኛ ወጪ ትምህርት እንዲያገኙ እና ዩኒቨርስቲው ለትምህርት የሚያወጣውን ከፍተኛ ወጪ በዝቅተኛ ደረጃ እንዲሆን እና የገቢ መጠኑም እንደሚጨምርም ተጠቁሟል።
Repost from የፍኖተ ሰላምሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ
የተወደዳቹ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የፊታችን ዓርብ ለሚኖረን ጉባኤ 19 ፀበል ጻዲቅ (ዳቦ ) ብንጠይቅ አባላት በነበራቸው ተነሳሽነት ከተጠየቀው በላይ 25 ዳቦ ስላገኘን በዚህ በረከት ያልተሳተፋቹ ጧፍ በማምጣት ሐሙስ ባንዲራ በመስቀል እንድትሳተፉ አደራ እንላለን
ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን
Repost from የፍኖተ ሰላምሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ
የተከበራቹ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የፊታችን ዓርብ የምናከብረውን የሰንበት ት/ቤታችን 19ኛ ዓመት የምስረታ ልዩ የአውደ ምህረት ጉባኤ የተመደባችሁበትን የአገልግሎት ድርሻ እና ሀላፊነት ለመወጣት ዝግጁ እንደሆናቹ ተስፋ እናደርጋለን
ውድ አባላት መቼም የራሳችንን ልደት ስናከበር ምን ያህል ወጪ እንደምናወጣ እናውቀዋለን ታዲያ ምግባር ከሐይማኖት ተምረን ያደግንባት የተዳርንባት ከሀዘናችን የተጽናናንባት ሰንበት ት/ቤታችንን በደመቀ መልኩ ለማክበር 19 ፀበል ጻዲቅ ( ድፎ ዳቦ ) እና ከ አንድ ሺ በላይ ጣፍ ያስፈልጋል እንደየ አቅማቹ ዳቦ ወይም ጣፍ በማምጣት ከበረከቱ እንድትሳተፉ እናሳስባለን
ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን
የተወደዳቹ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የአባላት ቤተሰቦች ወዳጆቻችን በሙሉ በድጋሚ እንኳን ለ 19ኛ ዓመት የሰንበት ት/ቤታችን የምስረታ በዓል በሰላም በጤና አደሳቹ አደረሰን
19ኛ ዓመታችንን ዓርብ መጋቢት 15/2015 ዓ.ም ከምሽት 11:00 ሰዓት ጀምሮ በልዮ ጉባኤ በድምቀት ይከበራል በእለቱ ከቤተሰብ ዘመድ ወዳጆቻቹ ጋር በመሆን በአገልግሎት እና በጉባኤ እንድትሳተፍ መልእክታችንን እናስተላልፋለን
ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን
መልእክቱን ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ
ውድ የቤተክርስቲያን ልጆች እንኳን ደስ አለን እግዚአብሔር ፀሎታችንን በቸርነቱ ሰማን የቤ/ክ አንድነቷን አፀናልን ደስም አለን እግዚአብሔር ይመስገን
"በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን"።
ውድ የተዋህዶ ልጆች እንደምን አላችሁ ይሄን ሰሞን እየተፈጠረ ያለውን ነገር ሁላችንም እናውቃለን እናም ሰሞኑን ሚዲያ ላይ የሚለቀቅ ስለ አባቶቻችን የሀሰት ዶክመንተሪ አለ እናም እንዳታምኑ አደራ
ይህን መልእክት ቢያንስ ለ10 ሰው share እናድርግ
@Abalibanos333
