en
Feedback
የፍኖተ ሰላምሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ

የፍኖተ ሰላምሰ/ት/ቤት ዋና ገጽ

Open in Telegram

የእመብርሃን ልጆች

Show more
206
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
February '24
February '24
+206
in 1 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
15 February+1
14 February0
13 February0
12 February0
11 February0
10 February0
09 February0
08 February0
07 February0
06 February0
Channel Posts
እግዚአብሔር ይመስገን ጥር 8/1996 ዓ.ም የዛሬ 20 ዓመት.......................................................................................

2
ሰላም እንዴት አመሻችሁ የተወደዳችሁ አባላት ዛሬ የተነገረችሁ የአመራር የኅላፊነት ሽግሽግ በተመለከተ ይህ እንዲሆን የተደረገበት መሠረታዊ ምክንያት እኔ በአጋጠኝ የግል ጉዳይ ምክንያት አሁን እያገለገልኩ ባለሁበት ኃላፊነት መቀጠል አልቻልኩም ከአቅሜ በላይ ስለሆነ በምትኩቀለል ያለ ኃላፊነት ያለበትን የአገልግሎት ክፍል እንዲሰጠኝ በጠየኩት መሠረት በምክትል ጸሐፊነት ሆኜ እንዳገለግል በሥራ አመራር ጉባኤ በመወያየት ይህን መፍትሔ ተደርጎ የተወሰደ መሆኑን ለማሳወቅ እወዳለሁ
247
3
"ከአባቱ ሳይወጣ መጣ፣ ከአነዋወሩ ሳይለይ ወረደ። ከሦስትነቱ ሳይለይ መጣ፣ ከአንድነቱም ሳይለይ ወረደ። ከዙፋኑ ሳይለይ በሥጋ ልጅ አደረ። ምላቱ ሳይወሰን በማኅፀን ተጸነሰ፣ በላይ ሳይጎድል በማኅፀን
"ከአባቱ ሳይወጣ መጣ፣ ከአነዋወሩ ሳይለይ ወረደ። ከሦስትነቱ ሳይለይ መጣ፣ ከአንድነቱም ሳይለይ ወረደ። ከዙፋኑ ሳይለይ በሥጋ ልጅ አደረ። ምላቱ ሳይወሰን በማኅፀን ተጸነሰ፣ በላይ ሳይጎድል በማኅፀን ተወሰነ፤ በታችም ሳይጨመርበት ተወለደ። ከኃጢአት በቀር ፈጽሞ ሰው ሆነ። እንደ እግዚአብሔር እየሠራ እንደ ባርያ ታዬ። ወንጌሉን ያስተማሩ እንደመሰከሩ። ከአባቱ ዘንድ ተመሰገነ፣ ከራሱም ከበረ። የጌትነቱም ምስጋና በሰማይና በምድር መላ። እኛም እንግዲህ በልቡናችንዘወትር አናርፍም። ቅዱስ እያልንም የጌትነቱን ምስጋና እንናገራለን።" /ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ/ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን። በግርግም ተወልዶ የእኛን ራቁትነት ያራቀ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በትልቅ መከራ እና ችግር ውስጥ ያለችውን ሀገራችንን ከመከራ እና ከችግር አላቅቆ የምሕረት እና የይቅርታ ልብስ ያልብስልን።
690
4
ከድንግል ያለወንድ ዘር በሥጋ ተወለደና አዳነን ቅዱስ ኤፍሬም የወደዳችሁ የእግዚአብሔርን ልጆች እንኳን ለ2016ዓም ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሳላም አደረሰን አደረሳች
ከድንግል ያለወንድ ዘር በሥጋ ተወለደና አዳነን ቅዱስ ኤፍሬም የወደዳችሁ የእግዚአብሔርን ልጆች እንኳን ለ2016ዓም ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሳላም አደረሰን አደረሳችሁ በዓሉ የፍቅር በዓል ይሁንልን
524
5
በተፈጥሯዊ ልደት የተወለድን እኛ ከተፈጥሮ ውጪ በሆነ ልደት እንወለድ ዘንድ እንዲገባን ሊያስገነዝበን በባህሪው የእግዚአብሔር አብ የበኩር ልጅ የሆነው እርሱ ከባህሪው ውጪ በሆነ በሌላ ልደት ተወለደ። (ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ) እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ። በረከት የምናገኝበት በዓል ያድርግል።
173
6
እንደ ተፈጥሯችን ከሰው ወገን የተወለድን እኛ፣ ከተፈጥሯችን ውጪ በሆነ ልደት ከእግዚአብሔር ተወለደን ከባህርያችን ውጪ በመንፈስ እንድንጠመቅ ከባህሪው ውጪ ከድንግል በመወለድ በውሃ የተጠመቀ እርሱ በባህሪይው የእግዚአብሔር አብ ብቸኛ ልጁ ነው። (ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ) እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ። በረከት የምናገኝበት በዓል ያድርግል።
148
7
ስለዚህ ቅድመ ዓለም ከአብ የተወለደ እና ለሁለተኛ ልደቱ ወደዚህ ዓለም የመጣው እርሱ አስቀድሜ ወደ ሰበኩላችሁ ወደ ሁለተኛ ልደት እኛን ያመጣን ዘንድ የመጣ ነው ብልም፣ ቅድመ ዓለም ከአብ ዘንድ ያለው ልደቱን በእምነት ከመቀበል ውጪ መርምረን ልንደርስበት የማንችለው ነው። እንዲህም ስል ድህረ ዓለም ከሴት መወለዱን ማሳነሴ አይደለም። እጅግ የሚልቅ ነው እንጂ። (ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ) እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ። በረከት የምናገኝበት በዓል ያድርግል።
148
8
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!! ሁላችንም ሰላመ እግዝአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ።እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን። በዓሉን ምክንያት በማድረግ ልዩ ጉባኤ ለሶስት ቀን አዘጋጅተናል አርብ፣ቅዳሜ እና እሁድ ስለዚህ ሁላቹም በሰዓቱ በመገኘት የጉባኤው ተሳታፊ እንዲትሆኑ ሰንበት ትምህርት ቤት ጥሪዋን ታስተላልፋለች። አርብና ቅዳሜ 11:00 ጀምሮ እስከ 1:30 እሁድ 8:00 ጀምሮ እስከ 12:00 ማሳሰቢያ:-እሁድ መገኘት የማትችሉ ስጦታችውን ከወዲው ለስነስርዓት ክፍል እንድታስገቡ:: ታዳጊዎች የእሁድ መርዓ ግብራቹ ከ 5:30 ጀምሮ እስከ 7:30 ይሆናል። የሰዓት ለውጥ ከአለ እናሳውቃለን። እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
150
9
የተወዳቹ የመንፈስ ቅዱስ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን በክርስቶስ ኢየሱስ ሰላምታ ሰላም ለእናንተ ይሁን በአንዳንድ አጀንዳዎች ዙሪያ ስለሰንበት ት/ቤታችን እንድንወያይ ጥያቄ እንዳቀረባቹ የሚታወቅ ነው በጥምቀት በዓል ዝግጅት እና በሌሎች አገልግሎቶች ምክንያት በመዘግየታችን በድጋሜ ይቅርታ እንጠይቃለን በተነሱት አጀንዳዎች ዙራያ ለመወያየት እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ ታሕሳስ 21/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ቀጠሮ ተይዛል በእለቱ ተገናኝተን በጎና መልካሙን እንድንነጋገር እግዚአብሔር ይርዳን አሜን ማሳሰቢያ እሁድ ጠዋት የሚሰጡ ኮርሶች 3:30 ተጀምረው 5:30ይጠናቀቃሉ ስብሰባው 8:00 ሰዓት በሰዓቱ በተገኙ አባላት በጸሎት ይጀመራል 11:00 ሰዓት በጸሎት ይዘጋል የድንግል ማርያም ምልጃ እና ቸርነት አይለየን አሜን
159
10
Share 'የልደት ስጦታ።፳፻፲፮ ዓ.ም..doc'
154
11
በልደት የስጦታ ቀን ፈቃደኛ የሆናችሁ አባላት ፣ ከስር የተዘረዘሩትን የመጽሐፍ ዓይነቶች (ከዋጋቸው ጋር ተለጥፈዋል) ካያችሁ በኋላ አቅማችሁ የሚችለውን መርጣችሁ እንድትለግሱን በሰንበት ትምህርት ቤታችን ስም እንጠይቃለን። የቻላችሁ ገዝታችሁ፣ መግዛቱ ካልተመቻችሁ ደግሞ ገንዘቡን በመስጠት እንዲገዛ ማድረግ ትችላላችሁ። ይህንንም በዚሁ የትምህርት ክፍል መዋቅራዊ መወያያ ላይ መግለጽ ትችላላችሁ። (ይህንን መጽሐፍ እኔ እገዛለሁ እያላችሁ ማለት ነው)
152
12
"ኃጢአት ሲሠራ ባየኸው ወንድም ላይ አትፍረድ፥ አንተ ግልጽ የወጣ ኃጢአቱን እንጅ በስውር ለካህን የሚነግረውን ንስሐ አታውቅምና። ስለዚህ የራስህን ድካም ተመልከት።" #ታላቁ_ቅዱስ_ባስልዮስ
186
13
ልጆቼ፦ እግዚአብሔርን በእምነት በፀሎት እንሻው ከእኛ የጠፋ ገንዘባችንን ነቅተን ተግተን በብዙ ድካም እንድንሻው እንዲሁ ሃሳባችንን ወደ እግዚአብሔር ልናቀርብ ይገባናል፤ ልጃችን ቢጠፋብን ፈልገን በቅርብ ያላገኘነው እንደሆነ ሃይላችንን በድካም ድካማችንን በሃይል የምንለውጥ አይደለንምን? የጠፋውን ልጃችንን ስለመፈለግስ እናገኘው ዘንድ የብሱን በእግር ባህሩን በመርከብ የምንዞር አይደለንምን? ፈልገንም ያገኘነው እንደሆነ ዳግመኛ እንዳይጠፋብን ለመጠበቅ እንተጋ የለምን? እንዲህ ከሆነ መሓሪ እግዚአብሔርን በእምነትና በፀሎት እንሻው ዘንድ ምን ያህል ይገባን ይሆን? እግዚአብሔርን ፈልጉት ነጋዴ ወርቅ ቢጠፋበት ወርቁን ያገኘው እንደሆነ ሁሉን ቦታ እንደሚፈልግ እንዲሁ እግዚአብሔርን ፈልጉት እናት ልጇ ቢጠፋባት እስክታገኘው ድረስ አርፋ እንደማትቀመጥ እንዲሁ እግዚአብሔርን ፈልጉት እግዚአብሔርን እሹት ፈልጉት እስክታገኙት ድረስ በእምነት በፀሎት እሹት፡፡” ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
645
14
ከታላቅ ይቅርታ ጋር እንደነዚህ ዓይነት ጥያቄዎች የሰ/ት/ቤቷ መዋቅራዊ የውይይት ቻናል ላይ ማንሳት ይቻላል።
280
15
ሰላም የተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ እንደሚታወቀው ቅዱስ ሲኖዶስ የምህላ አዋጅ ማወጁ የሚታወቅ ነው እንደ አንድ የቤተክርስቲያን አካል ማድረግ ያለብንን ዛሬ በታዘዝነው መሠረት በጸሎቱ አልተገኘንም ይህ መደገም የለበትም ከዚህ በኋላ ያሉት ቀናት በማታው መርሀ ግብር ልብሰ ሰብሐት በመልበስ በጸሎቱ ተገኝተን ስለ ሀገራችን እና ሰለ ቤተክርስቲያን መጸለይ ሃይማኖታዊ ግዴታችን መሆኑን ተገንዘብን ሁላችንም እንድንገኝ ስንል ጥሪያችንን በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም እናስተላልፋለን ማሳሰቢያ የእኛ መርግብር በተመለከተ ምህላ ብቻ ከሆነ እንደተባለው በአውደምህረት ከጸሎቱ በኋላ የመዝሙር ጥናት እንዲሁም የወረብ ይደረጋል በአውደ ምህረት የሚደረገው ጸሎት ከትምህርት በኋላ ከሆነ ደግሞ ቀድሞ ጥናቱ አካሂዶ በጸሎቱ ሰዓት መገኘት ይኖርብናል ።
365
16
እንኳን ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳቹ ዘውትር በየሳምንቱ ማክሰኞ ይካሄድ የነበረው የታዳጊ ክፍል የፀሎት መርሐግብር ከክፍሉ አባላት ጋር በተደረገ ውይይት ታዳጊዎች ለትምህርታቸው ሰፊ ሰዓት እንዲሰጡ በማሰብ በወር አንድ ጊዜ እንዲሆን ስምምነት ላይ በመደረሱ በየሳምንቱ የነበረው መርሐግብር መቋረጡን እናሳውቃለን በመሆኑም በልዩ ሁኔታ በወሩ መጨረሻ በሚኖረው ማክሰኞ ቀን የፀሎት እና ውይይት መርሐግብሩ ይካሄዳል መርሀግብሩን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ በቅርብ የምናሳውቃቹ ይሆናል:: ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን
479
17
ቀደም ሲል ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት በመላው ዓለም ለሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን የታወጀውን አዋጅ አስተላልፈዋል፡፡ በዚሁ መሠረት ያለፈውን በይቅርታና በምህረት ዘግተን በእውነተኛ ንሥሓ ልቅሶና በምህላ፣ በጾምና በጸሎት ወደ ፈጣሪ እንድንቀርብ፣ በመካከላችንም ፍቅርና አንድነት እንዲመጣ ይኽንን ጾመ ነቢያት ወይም የገና ጾም በልዩ ሁኔታ እንድንጾም መንፈሳዊ አዋጅ ተላልፏል፡፡ ይኽ ጥንታዊ የአዋጅ ጾም ሁለት አበይት ታሪኮችን የያዘ ነው፡፡ የመጀመሪያው ክፍል ቅዱስ አብርሃም ሶርያዊ የተባለ ጻድቅ አባት በጸሎት፣ በጾምና በምኅላ ተራራን ከመሬት ከፍ በማድረጉ ኃይለ ጸሎቱና ክብረ አምለኩ የሚዘከርበት ነው፡፡ በሁለተኛው ክፍል ነቢያት የጌታችንን ሰው መሆን እያፈለጉ፣ ድህነትንና ሰላምን በመሻት መጾማቸው ይዘከራል፡፡ (፩ኛ ጴጥ ፩፡፲) እኛም ይኽንን አብነት አድርገን ታላቋ ቤተ ክርስቲያን፣ ኃላፊነቷን እንድትወጣ ስለችግራችን፣ ስለሀገር ሰላምና ስለ ሕዝቡ ደኅንነት በአንድነት ሆነን ወደፈጣሪያች እንድንጮኽ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጥቅምት ወር ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም ወስኖ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ሀገራችን እንድትፈወስ፣ የወገን በወገን ደም መፋሰስ እንዲቀር፣ ያለፈውን በይቅርታና በንሥሓ ዘግቶ ለወደፊቱ ብሩህ ዘመንን እንዲመጣ በንሥሓና በፍጹም ለቅሶ፣ በቁመትና በሰጊድ፣ በሰፊሕና በአንቅአድዎ፣ ወደፈጣሪ እንድንቀርብ የምልኣተ ጉባኤውን ውሳኔ መሠረት በማድረግ ቋሚ ሲኖዶስ በኅዳር ወር ፳፻፲ወ፮ዓ/ም የሚከተለውን ዝርዝር አፈጻጸም አውጥቷል፡፡ ፩ኛ. የጾሙ የመጀመሪያ ሳምንት ከቅዳሜ ኅዳር ፲፭ እስከ ኅዳር ፳፩ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም በሁሉም የሀገራችን ክፍልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ባለችበት በመላው ዓለም የንሥሓ፣ የጾም፣ የጸሎትና የምኅላ ሳምንት እንዲሆን፤ ፪ኛ. በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ በአጥቢያ አለቆችና በገዳም አበምኔቶች መሪነት ሁሉም ዲያቆናት፣ ቀሳውስት፣ መነኰሳት፣ ሰባክያንና ሊቃውንት በሙሉ በየመዐርጋቸው ልብሰ ተክህኖና ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ዩኒፎርማቸው ለብሰው፣ ሁሉም ምእመናን ጋር በአንድነት በዐውደ ምህረት ጸሎተ ምኅላውን እንዲያደርሱ፤ ፫ኛ. በላው ሕዝበ ክርስቲያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ እናቶች አባቶች አረጋውያን ሁሉ የቻለ በቤተ ክርስቲያን፣ ያልቻለ በያለበት ሆኖ የተጣላ ታርቆ፣ በፍቅርና በአንድነት፣ በእውነተኛ ንሥሓና ጸጸት በምኅላው እንዲሳተፍ፤ በማእከል የሚደረገው ጸሎተ ምኅላ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ገዳም ሆኖ በመገናኛ ብዙኀን የቀጥታ ሥርጭት ለመላው ዓለም እንዲተላለፍ፤ ፬ኛ. በመጀመሪያው የሱባኤ ቀን ኅዳር ፲፭ ቀንና፣ በሰባተኛው ቀን ኅዳር ፳፩ ቀን በጸሎተ ምኅላው በሚደረግበት ጊዜ ታቦቱ ከመንበሩ ተነሥቶ በዐውደ ምኅረት በቀሳውስት እንዲከብር ሆኖ፤ በሁሉም የምኅላው ቀናት ሥዕለ ማርያም፣ ወንጌልና መስቀል ወጥቶ በአራቱ መዐዝን ሥርዓተ ጸሎተ ምኅላው ከጸሎተ ወንጌል ጋር በየቀኑ በነግህና በሠርክ የሥራ ሰዓትን በማይነካ ሁኔታ እንዲፈጸም፤ ፭ኛ. በየዕለቱ የሚነበቡት የወንጌል ክፍሎችን ስለ ሰላም፣ ስለንሥሓና ጸጸት፣ ስለ ፍቅርና አንድነት፣ ስለ በጎነትና መደማመጥ፣ ስለመሰማማትና ጥላቻን ስለማራቅ እንዲሆን፤ ፮ኛ. በሰፊህና በአንቀዓድዎ፣ በሰጊድና በአስተብርኮ፣ ምኅላው ከደረሰና፣ ጸሎተ ወንጌል ደርሶ ዕለቱ ወንጌል ከተነበበ በኋላ በአንድነት የንሥሓ መዝሙር በመዘመር፣ ሕዝበ ክርስቲያን ስለሀገራቸውና ስለሰው ልጆ ደኅንነት እያሰቡ ወደቤታቸው እንዲሄዱ፤ ፯ኛ. ከመጀመሪው ሳምንት በኋላ እስከ በዓለ ልደት ድረስ የሰርክ ምህላ ሳይቋረጥ መደበኛው ሥርዓተ ጾምና ጸሎት እንዲቀጥል፣ የቤተ ክርስቲያንን ታላቅነት፣ የአበውን ተቀባይነት በሚገለጽ፣ በቀጣይም ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በመንፈሳዊ ጽናት የሰላም ልዑካን ሆነው እንዲቀጥሉ በሚያደርግ ሁኔታ እንዲፈጸም፤ ፰ኛ. አስቀድሞ የደረሰውንና፣ እየደረሰብን ያለው ችግር የጦርነትና የግጭት ብቻ ሳይሆን የረሀብ፣ የድርቅ፣ የኑሮ ውድነት፣ የመፈናቀልና የስደት ጭምር ስለሆነ ከጸሎትና ምኅላችን ጎን ለጎን መረዳዳትና መተዛዘን፣ ርኅራሄና መደጋገፍ አብሮ እንዲፈጸም፤ ፱ኛ. ይኽንኑ መልእክት መላው ዓለም እንዲውቀው፣ በተለይም የኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በጸሎት እንዲያስቡን፣ የጸሎታችንና የምኅላችን መነሻ ምክንያቱ የሀገራችን ወቅታዊ ችግር ቢሆንም የምንጸልየው ለመላው ዓለም መሆኑ ተገልጾ በደብዳቤ እንዲላክ እንዲደረግ፣ በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን በእንባና በንሥሓ የምናቀርበውን ጸሎተ ምኅላችንን በምህረቱ ተቀብሎ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን፣ ሕዝባችንን ይጠብቅልን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ኅዳር ፲፩ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም፡ አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ ለተጨማሪ መረጃ፦ 1. ድረገጽ:- https://eotceth.org 2. ፌስ ቡክ ገጽ:- የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ/Department of Public Relation 3. ስልክ፦ +251111262652 | +251111262818 4. ኢሜል፦ eotcprdepartment@gmail.com 5. ፖስታ፦ 1283 አዲስ አበባ
429
18
የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሙሉ መልዕክት እነሆ፦ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! “ሰላምየ አኀድግ ለክሙ ወሰላመ አቡየ እሁበክሙ፡- ሰላሜን እተውላችኋለሁ፥ የአባቴ ሰላምም እሰጣችኋለሁ” (ዮሐ.14፡27) ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትንና አንድነት ማስፈንን አስመልክቶ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፤ ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትና ደኅንነት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ቀዳሚ ተልእኮዎች ናቸው፡፡ በሃገራችን ሰላምን ለማስፈን ቅድስት እናት ቤተ ክርስቲያን ከቀድሞ ጀምሮ ብዙ ጥረት ስታደርግ ኑራለች፡፡ አሁንም ሊኖራት የሚገባውን ተግባራዊ ሚና መወጣት ይኖርባታል፡፡ በተለይም ሰላም በመንፈሳዊ፣ በማኅበራዊ፣ በግለሰብ፣ በተቋም፣ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ክበብ ውስጥ ያለውን የተሣሠረ ሁለንተናዊ ትርጉም ከግምት ውስጥ ያስገባ ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡ ለሰላም መደፍረስና መታጣት ምክንያት የሆኑ ጉዳዮችን በማንሳትና ያስከተሉትን የሰው ልጅ እልቂት፣ ሞትና ስደት፣ የአብያተ ክርስቲያናትና የመንፈሳዊ ቅርሶች ውድመት፣ የካህናትና የሊቃውንት ስደትና መከራ፣ የቋሚና የተንቀሳቃሽ ንብረቶች ውድመት፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት መናጋት፣ በዜጎች መካከል ጥላቻ መስፋት፣ መተማመን መጥፋት፣ የኑሮ ዋስትና ማጣት፣ በስጋት መኖር፣ የማያባራ መከፋፈል፣ የሰብአዊ ክብር ማጣት፣ የመብት ጥሰት፣ የኑሮ ውድነትና የሕዝቦች መፈናቀል በአደባባይ እየታዩ ያሉ ሰብኣዊ ሰቆቃዎች ናቸው፡፡ “ብፁዓን ገባርያነ ሰላም እስመ እሙንቱ ውሉደ እግዚአብሔር ይሰመዩ፡- የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው፣ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና” (ማቴ.5፡9) በማለት ጌታችን ያስተማረው ትምህርት የቤተ ክርስቲያን መመርያ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአስታራቂነት ድርሻ፣ የሃገር አንድነትና የሕዝብን ሰላም ለመጠበቅ በታሪኳ ያደረገችው አስተዋጽኦ በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፡፡ የቤተ ክርስቲያን ታላቅነት፣ የአበውን ተቀባይነትና የሊቃውንቷን ሰላምን የማስፈን ክሂሎት፣ ችግርን የመፍታት ጥበብ አሁንም ተጠናክሮ መተግበር ይኖርበታል፡፡ የሰላምን ወሳኝ ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባትና ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የሰላምና የዕርቅ ሰነድ በማዘጋጀት የመሪነት ተሳትፎ እንድትፈጽም ገለልተኛና ሰውን ማእከል በማድረግ ታገለግላለች፡፡ ካህናትና መላው አገልጋዮች የሰላም ልዑካን እንዲሆኑ፤ ሰላምን ግንባር ቀደም ሐዋርያዊ ተልእኮዋ አድርጋ ትንቀሳቀሳለች፡፡ በሃገራዊ የሰላምና የዕርቅ ጥረቶች አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር የሚያስችል ይፋዊ ውክልና እንዲኖራት፣ በሥነ ምግባርና በግብረ ገብነት ትምህርት የራስዋን ኃላፊነት እንድትወጣ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሃገራዊም ሆነ በራስዋ መዋቅር በሰላም ዙርያ አስተዋጽኦዋን ለማሳደግና የሚጠበቅባትን ለመወጣት ትችል ዘንድ የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚገባ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ለቤተ ክርስቲያን መመርያዋ ጽድቅን፣ እምነትን፣ ፍቅርን አጥብቀህ ተከተል ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ያዘዘው መመሪያ ነው፡፡ (፪ኛ ጢሞ. ፪፡ ፳፪) ሰላምን ሳታዳላ በሩቅም በቅርብም ላሉት ትሰብካለች፡፡ • “ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ” እንዲል (ኤፌ.፪፡፲፯)፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም መሣርያዋ፣ ሕይወቷ፣ ጸሎቷ፣ ቀኖናዋና ዶግማዋ ነው፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ ስለዚህ “ሰላም ከሌላችሁ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር የለም” በማለት የሰው ልጅ ሰላማዊ እንዲሆን ታስተምራለች፡፡ ጥላቻን አጥብቃ ትቃወማለች፡፡ “ጥልን በመስቀሉ ገደለ” የሚለውን መልእክት እንደ ሰንደቅ የምትጠቀምበት መለያዋ ነው፡፡ ስለዚህ በሰዎች መካከል የተከሰተውን ጥላቻ በተሰጣት መንፈሳዊ ጥበብ ማስወገድ ተልእኮዋ ነው፡፡ በሰላም ግንባታ ኢትዮጵያውያንን ያለ ልዩነት በማሳተፍ ቤተ ክርስቲያን የሰላም ሚናዋን በጥበብና በማስተዋል በቋሚነት ትሠራለች፡፡ ሰላምን ያሳጡን ጦርነቶችና ግጭቶች ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙና በአጭሩ እንዲቋጩ ጥሪዋን ታስተላልፋለች፤ እምቢ ባዮችንም በማውገዝ ዘላቂ መፍትሔ የሚገኝባቸውን ሂደቶችን ትቅይሳለች፡፡ የሰላም ሰነዶችን በማዘጋጀት አስቸኳይ የሆነ ሃገራዊ የሰላም ንቅናቄ በፍጥነት እንዲጀመርና በዚህም ውስጥ ውጤት ሊያመጣ የሚችል ሥልት ተቀይሶ ወደ ሥራ እንዲገባ ማድረግ ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የራስዋ የሰላም ከፍተኛ ልዑክ ኖሯት በመዋቅሯ ሁሉ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ የሰላም ሥምሪት ለማድረግ የሚያስችል ንቅናቄ ታደርጋለች፡፡ በሃገራዊ የሰላም ጥረቶች፣ የውይይትና የምክክር መድረኮች ባለድርሻ እንድንሆን ከሚመለከተው ጋር ተቀራርቦ መሥራት የሚቻልበትን አሠራር ትዘረጋለች፡፡ በማኅበራዊ ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪ ተቀባይነት እንዲኖረው በትጋት ትሠራለች፡፡ በሰብአዊ ድጋፍና በእርዳታ ማስተባበር ለወገኖቻችን መድረስ እንዲቻል ልጆቿን አስተባብራ ትንቀሳቀሳለች፡፡ በመግቢያችን እንደተጠቀሰው “ፈኑ እዴከ አንሥእ ኃይለከ” ብለው የለመኑ ነቢያትን የሰማ እግዚአብሔር አምላካችን ጸሎታችንን እንደሚሰማን ከልባችን በማመን በእርሱ ያለንን ትምክህታችን ይህ በመሆኑ ከጽኑ ተስፋና ፍቅር ጋር እንድንፈጽመው አደራ እንላለን፡፡ በተጨማሪ ይህንን መንፈሳዊ ሥርዓትና መደበኛ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ሁሉም በቅንነት እንዲረዳው በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ ዓለማውያን ምሁራን ሃገሮቻቸውን ለመጠበቅ፣ የሕዝባቸውን አንድነት ለማስቀጠል፣ የተረጋጋና እርስ በርሱ የሚተማመን ማኅበረሰብን ለማጽናት በሕግ የሚያስቀጡ “የጥላቻ ንግግርን” የሚያስቀር አዋጅ ያወጣሉ፡፡ ሃገራችንም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃን የሚከለክል አዋጅ አላት፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ጥላቻንና ሐሰተኛ ትርክቶችን ታወግዛለች፡፡ የአሁኑ ጸሎተ ምኅላ የሚደረገው አለመግባባት በምክክር፣ በውይይት፣ በመደማመጥ እንዲፈታ፤ መከራን በመረዳዳት እንድንሻገር፣ እንደየ ኃላፊነታችን የሚጠበቅብንን ለመወጣትና የሕዝባችንን ጥያቄ ለመመለስ እንድንችል፣ ችግራችን ሁሉ ተፈትቶ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ከሃሊው አምላክ እንዲያግዘን በአንድነት ለመጮኽ ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ዓላማው መንፈሳዊ ብቻ የሆነ የጾም፣ የጸሎትና የምኅላ አዋጅ መሆኑን ተረድታችሁ የሚድያ፣ የትምህርትና የፍትሕ፣ መሰል ተቋማት በሚያስፈልገው ሁሉ እንድትተባበሩን በዚሁ አጋጣሚ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም አባታዊ ማሳሰቢያን እናቀርባለን፡፡ በአጠቃላይ ቤተ ክርስቲያን በታሪክም ሆነ በትውልድ የሚያኮራ ውጤታማ ሥራን እንድትሠራና ከቃል ወደ ተግባር እንድትሸጋገር ለማድረግ ይህ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ይቀድስ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሕዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ አፈጻጸም ፦ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትንና አንድነትን ለማስፈን የታወጀውን የጾምና የጸሎተ ምኅላው አፈጻጸም በቅደሱ ሲኖዶስ በተወሰነው መሠረት ከዚህ በመቀጠል አቀርባለሁ፡፡
265
19
በቅርቡ ፈተናውና አሳይመንቱ ስለሚሰጥ ተዘጋጁ ፣ በስማችሁ የተዘረዘሩትን የትምህርት ዓይነት ተዘጋጁ
178
20
አንድ ትምህርት ብቻ ያላሟላችሁ ተማሪዎች ( በአሳይመንትና በፈተና የቀጣዩ ክፍል ቋሚ የምትሆኑ) 👉👉👉👉👉👉👉 ካልዓይ ተማሪ የነበራችሁ (ምስጢራትን ያጓደላችሁ) 👉ትዕግስት አዳነ 👉ወይንሸት ኪሮስ 👉ሄለን ዳርጌ (የቤተክርስቲያን ታሪክ በዓለም ያያጓደለ 👉መስፍን ታምራት (በኢትዮጵያ ያጓደለ/ች) 👉 ዳግም ለጥቅ (የማቴዎስ ወንጌል አንድምታ) 👉 መቅደስ አረጋ 👉ብሩክታዊት ዘርዓይ 👉መሠረት ታደሰ 👉ሱራፍኤል ሰለሞን 👉ረድኤት ምስጋናው 👉እድላዊት አንተዬ 👉👉👉👉👉👉👉 ቀዳማይ የነበራችሁ (ትምህርት ሃይማኖት ያጓደላችሁ) 👉ፀደይ ደመላሽ 👉ቅዱስ ዘላለም 👉አብነት ዓለማየሁ 👉ሰጤ ሰይሶ 👉 መለሰ ዳምጤ 👉ማሬ ብዙዓለም 👉አዳነ ገዛኸኝ 👉ሃይማኖት ተዋበ 👉ሰናይት ይርሳው 👉ሄለን ማናዬ (መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ያያጓደላችሁ 👉 ተውህቦ ሞገስ 👉 አበራ አለበል 👉 ዘውዲቱ ቢነጋ 👉 ሃይለማርያም አንተነህ (ክርስቲያናዊ ስነምግባር ያጓደላችሁ) 👉 ዮሐንስ ጎሳ 👉 ህሊና ምንዋጋው (ትምህርተ ሃይማኖት ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና ክርስቲያናዊ ስነምግባር) 👉 ዳዊት በላይሁን 👉 ጽዮን ደምሴ (ትምህርተ ሃይማኖትና መጽሐፍ ጥናትና ታሪክ) 👉 አቤል በላቸው 👉 ሀብታለም ወልዴ 👉 እሙ ፍቅሩ 👉 ምንትዋብ ጸጋዬ 👉 ባዩሽ ጥላሁን
174