en
Feedback
DBU Daily News

DBU Daily News

Open in Telegram

Youtube https://youtu.be/_0l6c0I7ouM 👉ስለ ግቢው ወቅታዊ መረጃ 📌ዲፓርትመንቶች ፡⚽️ስፓርት፡🎤ኪነጥበብ ምሽቶች ፡📄የጊቢ ማስታወቂያ ፡ ምልከታወችና ታሪክ ወግ ፡📷📷አስገራሚ ፎቶወች ፡ እውነታዎች እና መረጃወች📃 መፀሀፍት ፡ ሳይኮሎጂ ሁሉም ይዳሰሱበታል:: Contact

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel DBU Daily News

Channel DBU Daily News (@dbu11) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 508 subscribers, ranking 14 413 in the News & Media category and 2 337 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 508 subscribers.

According to the latest data from 06 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -63 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 40.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 21.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 823 views. Within the first day, a publication typically gains 3 082 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 20.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Youtube https://youtu.be/_0l6c0I7ouM 👉ስለ ግቢው ወቅታዊ መረጃ 📌ዲፓርትመንቶች ፡⚽️ስፓርት፡🎤ኪነጥበብ ምሽቶች ፡📄የጊቢ ማስታወቂያ ፡ ምልከታወችና ታሪክ ወግ ፡📷📷አስገራሚ ፎቶወች ፡ እውነታዎች እና መረጃወች📃 መፀሀፍት ፡ ሳይኮሎጂ ሁሉም ይዳሰሱበታል:: Contact

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

14 508
Subscribers
-224 hours
-247 days
-6330 days
Posts Archive
ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ከታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ጋር በመተባበር ለህፃናት ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና እየሰጠ ነው =================== ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (አ/ወ/ጤ/
+4
ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ከታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ጋር በመተባበር ለህፃናት ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና እየሰጠ ነው =================== ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (አ/ወ/ጤ/ሳ/ካ) ፡፡ የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ከታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ጋር በመተባበር ለህፃናት ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ተገለጸ። በሆስፒታሉ በመገኘት የቀዶ ሕክምና አገልግሎቱን እየሰጡ ያሉት የታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ.ር አንተነህ ይርጋለም እንደገለጹት የልብ ቀዶ ሕክምና ለሚያስፈልጋቸው ህፃናት ነፃ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን፣ ለቀዶ ህክምናው የሚያስፈልጉትን ዋና ዋና ማሽነሪዎች ከአዲስ አበባ ይዘው እንደመጡ አስታውቀዋል፡፡ ዶ.ር አንተነህ አክለውም መርሃ ግብሩ ሶስት ዋና ዋና ዓላማዎችን ያሳካል ብለዋል። የመጀመሪያው ውድ በሆነው የልብ ቀዶ ሕክምና ወጪ ምክንያት ለመታከም አቅም የሌላቸውን ህፃናት ተደራሽ ማድረግ፤ ሁለተኛው ከዩኒቨርሲቲና ከሌሎች ሆስፒታሎች ጋር የሙያ ልምድና እውቀት መለዋወጥ እና ሶስተኛው ደግሞ በመንግስት ሆስፒታሎች የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት እንዲስፋፋ የባለሙያ አቅም ግንባታን ማጠናከርና ድጋፍ ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። በዕለቱ ከታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ከመጡ የሕክምና ባለሙያዎች እና ከሀኪም ግዛው ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች በተደረገ የጋራ ሥራ ለ3 ህፃናት ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና መደረጉንም ዶ/ር አንተነህ ተናግረዋል።

የደብረብርሀን ዩንቨርስቲ 2018 ተመራቂዎች ሻምፒዮን የሆነው ብሩክ ደግነት ከ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ከፋርማሲ ትምህርት ክፍል በ 3.9741 የዩንቨርስቲውን ዋንጫ አንስቷል። በጥቂት
+1
የደብረብርሀን ዩንቨርስቲ 2018 ተመራቂዎች ሻምፒዮን የሆነው ብሩክ ደግነት ከ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ከፋርማሲ ትምህርት ክፍል በ 3.9741 የዩንቨርስቲውን ዋንጫ አንስቷል። በጥቂት የሽርፍራፊ ነጥብ ልዩነት ብሩክን በመከተል የሴቶችን ዋንጫ ያነሳችው ታታሪዋ ዕንስት ደግሞ ከ ቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የ ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ምሩቋ ትርንጎ ገዛህኝ ናት። የሜዳልያ አዋርድ አሸናፊዎች ከ Medical school pharmacy የዋንጫው ባለቤት ብሩክ ደግነት ፣ ከማኔጅመትንት የዋንጫ አሸናፊዋን ዕንስት ሜዳልያ የነጠቀው ብሩክ ደግነትን በጥቂት ነጥብ ልዩነት የሚከተለው ይኽነው አንሙት ነው ። ደመቀ መንገሻ በ 3.9 ፣ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መኳንንት አያሌው በ 3.918፣ ኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጅንጅነሪ 3.918 ፣ ከ ህግ ትምህርትቤት ትዕግስት ምህረት ታዬ በ3.92። የ Graduated class of 2026 Gold cup አሸናፊዎች ብሩክ ደግነትን እና ትርንጎ ገዛህኝን interview ይዘን እንመለሳለን። ውድ ተመራቂዎች በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ daily news መልካም ዕድል መልካም የስራ ዘመን ይመኝላችሗል። @dbu11 @dbu111

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ (ሰኔ 23) ይጀምራል‼️ የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ኢትዮጵያ በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል:: ለፈተናው በድምሩ 563 ሺህ 501 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን ፣ 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257 ሺህ 45 የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው:: @DBU11 @DBU111

‎የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን መቀበል ጀመረ ‎═══════ ❁✿❁ ═══════ ‎​ደብረ ብርሃን - ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ደ.ብ.ዩ)- ‎​የደብረ ብርሃን
+4
‎የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን መቀበል ጀመረ ‎═══════ ❁✿❁ ═══════ ‎​ደብረ ብርሃን - ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ደ.ብ.ዩ)- ‎​የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል። ለፈተናው ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲው ግቢ መግባት የጀመሩ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው የተቋቋመው የፈተና አስተባባሪ ግብረ ኃይልም ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ እየተቀበለ ይገኛል። ‎ ‎​በቀጣዮቹ ቀናት ከሰሜን ሸዋ ዞን እና ከደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ጣቢያቸው እንደሚገቡ ይጠበቃል። ‎ ‎​እንደ መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናቸውን ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 03፤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ከሐምሌ 06 እስከ 16/2018 ዓ.ም የሚወስዱ ይሆናል። ‎ ‎ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በሰላማዊ ሁኔታ ፈተናቸውን እንዲያጠናቅቁ የሚያስችል አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ20ኛው ዙር የተማሪዎች ምርቃት የዋንጫ ተሸላሚ ተማሪዎቻችን እንኳን ደሰ አላችሁ ═══════ ❁✿❁ ═══════ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሰኔ 21/2018። ደብረብርሃን
+3
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ20ኛው ዙር የተማሪዎች ምርቃት የዋንጫ ተሸላሚ ተማሪዎቻችን እንኳን ደሰ አላችሁ ═══════ ❁✿❁ ═══════ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሰኔ 21/2018። ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ20ኛው ዙር የተማሪዎች ምርቃት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገባችሁ የዋንጫ ተሸላሚ ተማሪዎቻችን ኮርተንባችኋል እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ በምርቃት ስነ-ስርአቱ ከማኔጅመንት ትምህርት ክፍል አጠቃላይ ከሴቶች 3.9684 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት በማስበዝገብ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነችው ተማሪ ትርንጎ ገዛኸኝ አበራ የተለያዩ የአጠናን ዘዴዎችን በመጠቀም፤ ጠንክራ በማጥናቷ ለስኬት በመብቃቷ ከፍተኛ ደስታ የተሰማት መሆኑን ገልፃለች፡፡ አጠቃላይ ከዩኒቨርሲቲው 3.9741 የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫ ተሸላሚ ከፋርማሲ ትምህርት ክፍል ተማሪ ብሩክ ደግነት በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም ትምህርቱን በትኩረት ሲከታተልና ሲያጠና እንደነበር የገለፀ ሲሆን በሽልማቱ በጣም ደስተኛ እንደሆነና በቀጣይም በሚሰማራበት የስራ መስክ ያስተማረውን ማህበረሰብ በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። የትምህርት አመታትን ጽኑ አላማ ለማሣካት ለፍታችሁ በጥረታችሁ ይኸንን ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ በመቻላችሁና የዋንጫ ተሸላሚ በመሆናችሁ የዩኒቨርስቲያችን አምባሳደሮች ናችሁና እንኳን ደስ አላችሁ።

የህግ እና ጤና ሳይንስ ምሩቃን ቃለመሓላ ፈፅመዋል። አሁን የማዕረግ ተመራቂዎች ሽልማታቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ ።
+3
የህግ እና ጤና ሳይንስ ምሩቃን ቃለመሓላ ፈፅመዋል። አሁን የማዕረግ ተመራቂዎች ሽልማታቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ ።

The graduate special vibe, special moment and special days congratulations you graduate 🎉

‎ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች እያስመረቀ ነው ‎═══════ ❁✿❁ ═══════ ‎​ዩኒቨርሲቲው ለ20ኛ ጊዜ በመደበኛ፣ በኤክስቴንሽን፣ በክረምት እና
+4
‎ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች እያስመረቀ ነው ‎═══════ ❁✿❁ ═══════ ‎​ዩኒቨርሲቲው ለ20ኛ ጊዜ በመደበኛ፣ በኤክስቴንሽን፣ በክረምት እና በርቀት መርኃ ግብሮች በቅድመ ምረቃ እና በድህረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን 807 ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የመመረቂያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል። ‎ ‎​ተመራቂዎቹ በቅድመ ምረቃ መርኃ ግብር በ8 ኮሌጆች ሥር በሚገኙ 31 የትምህርት መስኮች እንዲሁም በድህረ ምረቃ መርኃ ግብር በ16 የትምህርት መስኮች የትምህርት ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ናቸው። ‎ ‎​በታሪካዊው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ የኢትዮጽያ ደረጃዎች ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር፤ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባልና የእለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር መሰረት በቀለ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የሴኔት አባላት፣ የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ‎ ‎​ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ @DBU11 @DBU111

ይህ አዲስ የህይወት ምዕራፍ ነው ። ምርቃት እልፎች የተመኙት ጥቂቶች ያሳኩት ህልም ነው ። እዚህ ግቢ ስትመጡ በእድል አይደለም የመጣችሁት ስለቻላችሁ :ለቦታው ስለምትመጥኑ ነው : ያሳለፋችሁት ጉዞ
ይህ አዲስ የህይወት ምዕራፍ ነው ። ምርቃት እልፎች የተመኙት ጥቂቶች ያሳኩት ህልም ነው ። እዚህ ግቢ ስትመጡ በእድል አይደለም የመጣችሁት ስለቻላችሁ :ለቦታው ስለምትመጥኑ ነው : ያሳለፋችሁት ጉዞ ውስጥ አንድም  በጤና እንድም በውጤት ወደ ኃላ የቀሩ አሉ :እነሱ እንድ ቀን ይመጣሉ እናንተ ቀን ዛሬ ቀናችሁ ነው እንኳን ደስ አላችሁ ። ዛሬ ተመርቃችሁ በምትጀምሩት አዲስ ህይወት ብዙ ደስ የሚሉ ግዜያቶችን ታሳልፋላችሁ ። ግን አንድ ነገር !  ለሁሉም ግዜ እንዳለው እውቁ በምርቃት ማግስት ቤተሰብ ከእናንተ  ተአምር አይጠበቅም : ስኬታማ በምትሆኑበት የስራ መስክ በንፁህ አእምሮ ጥሩ መመኘት ወደ ቦታው መቅረብ እንጂ ለአሉታዊ ስሜት መጋለጥ የለባችሁም ። ምንም እንኳን ሚዲያው :አየሩ : ሰፈሩ ሁሉ ስለተስፋ መቁረጥ ቢያወራ : አንድ ነገር አትርሱ ለእናንተ ያለው የትም አይሄድም ። ከመምህር ከተማራችሁት ትምህርት ቀጥሎ የምትማሩት የህይወት ትምህርት እጅግ  ትዕግስት የሚጠይቅ ነው ማስታወሻችሁን ይዛችሁ ሰህተት ላለመድገም ሞክሩ ። እንኳን ደስ አላችሁ መልካም የስራ ዘመን ። wende abebe (መ'ኪያ ) @DBU11 @DBU111

ውድ ተመራቂዎች እንኳን ለ2018 ዓም የምርቃት ጊዜ አደረሳችሁ እያልን አሪፍ አሪፍ ፎቶ እናንተን ለማንሳት ዝግጅታችንን ጨርሰናል ከዚህ በፊት የሰራናቸውን ስራዎች ለመመልከት ቻናላችንን ይቀላቀሉ በድጋሚ እንኳን ለምርቃታችው ቀን በሰላም አደረሳችሁ BRIGHT PICTURE ☎️ 0975703821 ☎️ 0910100440 Tiktok 👉👉 @brightpictuer Instagram👉👉 @Bright Pictures https://t.me/Bright_Pictures

AD Efrata beauty mark የምንሰጣቸው አገልግሎት ጥፍር ሜካፕ አይላሽ ፀጉር ሂና Wax በተመጣጣኝ ዋጋ አድራሻ ጠባሴ መልእክት ኮንዶሚንየም birhan college fit lefit ስልክ 0984220655

ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.ethernet.edu.et @DBU11 @DBU111

የምርቃት ቀን ታውቋል
የምርቃት ቀን ታውቋል

የምርቃት ቀን ውድ ተመራቂዎች እንኳን ለ2018 ዓም የምርቃት ጊዜ አደረሳችሁ እያልን ለምርቃት ዝግጅት እንዲሆናችሁ ያህል ቻናላችን የምርቃት ቀንን መች እንደሚሆን ባጣራው መሰረት እስካሁን ያለው መረጃ ሰኔ 21 ነው። ነገር ግን እስካሁን በዩኒቨርሲቲው በኩል በማህተም ተረጋግጦ ለሚዲያ ይፋ አልተደረገም። @DBU11 @DBU111

Limited Stock እንኳን ለ2018 ዓም የምርቃት በዓላችሁ አደረሳችሁ በሽክረት ህትመት ያዘጋጀነውን የሪቫን ህትመት በMetalic Gold ውስን ማቴሪያል ብቻ ስለቀረ በገበያ ላይ ካለው እጥረት
+1
Limited Stock እንኳን ለ2018 ዓም የምርቃት በዓላችሁ አደረሳችሁ በሽክረት ህትመት ያዘጋጀነውን የሪቫን ህትመት በMetalic Gold ውስን ማቴሪያል ብቻ ስለቀረ በገበያ ላይ ካለው እጥረት አኳያ ቀድመው የሚመጡትን ደንበኞች ብቻ ማቴሪያል እስከቻለ ድረስ የምናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን። (ከጎልድ ሲዘር ውጭ ማንኛውንም አይነት ሪቫን በማግኘት ትችላላችሁ) ሽክረት ህትመት አድራሻ ሰማያዊ ፊትለፊት ኬብሮን ኮሌጅ ያለበት ህንፃ(እህል በረንዳ) 3ኛ ፎቅ ላይ ለበለጠ መረጃ 0940219376 0904238625

📦 በዩኒቨርሲቲ ቆይታዎ የዕቃዎችዎ አስተማማኝ ጠባቂ — Uni Storage! ለክረምት ዕረፍት ወደ ቤተሰብ ሲሄዱ የያዟቸውን ዕቃዎች የት እንደሚያስቀምጡ አሳስቦዎታል? ጭንቀትዎን ለኛ ይተውት! Uni
📦 በዩኒቨርሲቲ ቆይታዎ የዕቃዎችዎ አስተማማኝ ጠባቂ — Uni Storage! ለክረምት ዕረፍት ወደ ቤተሰብ ሲሄዱ የያዟቸውን ዕቃዎች የት እንደሚያስቀምጡ አሳስቦዎታል? ጭንቀትዎን ለኛ ይተውት! Uni Storage ዕቃዎችዎን በታማኝነት እና ሙሉ ዋስትና ባለው ቦታ ያከማችልዎታል። 📌 የ3 ወራት የማከማቻ የዋጋ ዝርዝር፦ 🧳 ትላልቅ ሻንጣዎች፦ 400 ብር 🎒 የጀርባ ቦርሳ / ዱፍል ባግ፦ 300 ብር 🧺 የልብስ ማጠቢያ ሳፋ፦100 ብር 🛏️ ብርድ ልብስ፦ 250 ብር 🧹 መጥረጊያ፣ መወልወያ እና የመሳሰሉት፦50 ብር 📚 መጻሕፍት እና ሌሎች ትናንሽ ዕቃዎች፦ 100 ብር 🎁 ልዩ ቅናሾች፦ ✅ ከ3 ዕቃዎች በላይ ለሚያስቀምጡ ደንበኞች ✅ በግሩፕ (በቡድን) ለሚመጡ ተማሪዎች ልዩ ቅናሽ አለን! 🔒 ደህንነቱ የተጠበቀ • 🤝 አስተማማኝ • 💰 ተመጣጣኝ 📲 አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 0962808077               ማሳሰብያ ዕቃ ለማስቀመጥ የዮኒቨርስቲው መታወቂያ ኮፒ ያስፈል  Uni Storage — ዕቃዎችዎን በአደራ የሚጠብቅ አገልግሎት! 📦✨

photo content

photo content

መልካም ፈተና- መልካም እድል @DBU11 @DBU111

Letter to All University 1.pdf7.01 KB