DBU Daily News
前往频道在 Telegram
Youtube https://youtu.be/_0l6c0I7ouM 👉ስለ ግቢው ወቅታዊ መረጃ 📌ዲፓርትመንቶች ፡⚽️ስፓርት፡🎤ኪነጥበብ ምሽቶች ፡📄የጊቢ ማስታወቂያ ፡ ምልከታወችና ታሪክ ወግ ፡📷📷አስገራሚ ፎቶወች ፡ እውነታዎች እና መረጃወች📃 መፀሀፍት ፡ ሳይኮሎጂ ሁሉም ይዳሰሱበታል:: Contact
显示更多📈 Telegram 频道 DBU Daily News 的分析概览
频道 DBU Daily News (@dbu11) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 507 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 14 413,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 337 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 507 名订阅者。
根据 06 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -63,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 21.24% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 823 次浏览,首日通常累积 3 082 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Youtube https://youtu.be/_0l6c0I7ouM
👉ስለ ግቢው ወቅታዊ መረጃ
📌ዲፓርትመንቶች ፡⚽️ስፓርት፡🎤ኪነጥበብ ምሽቶች ፡📄የጊቢ ማስታወቂያ ፡ ምልከታወችና ታሪክ ወግ ፡📷📷አስገራሚ ፎቶወች ፡ እውነታዎች እና መረጃወች📃 መፀሀፍት ፡ ሳይኮሎጂ ሁሉም ይዳሰሱበታል::
Contact”
凭借高频更新(最新数据采集于 07 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
14 507
订阅者
-224 小时
-247 天
-6330 天
帖子存档
14 507
+4
ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ከታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ጋር በመተባበር ለህፃናት ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና እየሰጠ ነው
===================
ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (አ/ወ/ጤ/ሳ/ካ) ፡፡ የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ከታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ጋር በመተባበር ለህፃናት ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ተገለጸ።
በሆስፒታሉ በመገኘት የቀዶ ሕክምና አገልግሎቱን እየሰጡ ያሉት የታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ.ር አንተነህ ይርጋለም እንደገለጹት የልብ ቀዶ ሕክምና ለሚያስፈልጋቸው ህፃናት ነፃ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን፣ ለቀዶ ህክምናው የሚያስፈልጉትን ዋና ዋና ማሽነሪዎች ከአዲስ አበባ ይዘው እንደመጡ አስታውቀዋል፡፡
ዶ.ር አንተነህ አክለውም መርሃ ግብሩ ሶስት ዋና ዋና ዓላማዎችን ያሳካል ብለዋል። የመጀመሪያው ውድ በሆነው የልብ ቀዶ ሕክምና ወጪ ምክንያት ለመታከም አቅም የሌላቸውን ህፃናት ተደራሽ ማድረግ፤ ሁለተኛው ከዩኒቨርሲቲና ከሌሎች ሆስፒታሎች ጋር የሙያ ልምድና እውቀት መለዋወጥ እና ሶስተኛው ደግሞ በመንግስት ሆስፒታሎች የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት እንዲስፋፋ የባለሙያ አቅም ግንባታን ማጠናከርና ድጋፍ ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።
በዕለቱ ከታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ሕክምና ማዕከል ከመጡ የሕክምና ባለሙያዎች እና ከሀኪም ግዛው ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች በተደረገ የጋራ ሥራ ለ3 ህፃናት ነፃ የልብ ቀዶ ሕክምና መደረጉንም ዶ/ር አንተነህ ተናግረዋል።
14 507
+1
የደብረብርሀን ዩንቨርስቲ 2018 ተመራቂዎች ሻምፒዮን የሆነው ብሩክ ደግነት ከ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ከፋርማሲ ትምህርት ክፍል በ 3.9741 የዩንቨርስቲውን ዋንጫ አንስቷል።
በጥቂት የሽርፍራፊ ነጥብ ልዩነት ብሩክን በመከተል የሴቶችን ዋንጫ ያነሳችው ታታሪዋ ዕንስት ደግሞ ከ ቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የ ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ምሩቋ ትርንጎ ገዛህኝ ናት።
የሜዳልያ አዋርድ አሸናፊዎች ከ Medical school pharmacy የዋንጫው ባለቤት ብሩክ ደግነት ፣ ከማኔጅመትንት የዋንጫ አሸናፊዋን ዕንስት ሜዳልያ የነጠቀው ብሩክ ደግነትን በጥቂት ነጥብ ልዩነት የሚከተለው ይኽነው አንሙት ነው ። ደመቀ መንገሻ በ 3.9 ፣ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መኳንንት አያሌው በ 3.918፣ ኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጅንጅነሪ 3.918 ፣ ከ ህግ ትምህርትቤት ትዕግስት ምህረት ታዬ በ3.92።
የ Graduated class of 2026 Gold cup አሸናፊዎች ብሩክ ደግነትን እና ትርንጎ ገዛህኝን interview ይዘን እንመለሳለን።
ውድ ተመራቂዎች በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ daily news መልካም ዕድል መልካም የስራ ዘመን ይመኝላችሗል።
@dbu11
@dbu111
14 507
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ (ሰኔ 23) ይጀምራል‼️
የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ኢትዮጵያ በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል::
ለፈተናው በድምሩ 563 ሺህ 501 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን ፣ 306 ሺህ 456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257 ሺህ 45 የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው::
@DBU11
@DBU111
14 507
+4
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን መቀበል ጀመረ
═══════ ❁✿❁ ═══════
ደብረ ብርሃን - ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ደ.ብ.ዩ)-
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል። ለፈተናው ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲው ግቢ መግባት የጀመሩ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው የተቋቋመው የፈተና አስተባባሪ ግብረ ኃይልም ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ እየተቀበለ ይገኛል።
በቀጣዮቹ ቀናት ከሰሜን ሸዋ ዞን እና ከደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ጣቢያቸው እንደሚገቡ ይጠበቃል።
እንደ መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናቸውን ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 03፤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ከሐምሌ 06 እስከ 16/2018 ዓ.ም የሚወስዱ ይሆናል።
ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በሰላማዊ ሁኔታ ፈተናቸውን እንዲያጠናቅቁ የሚያስችል አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
14 507
+3
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ20ኛው ዙር የተማሪዎች ምርቃት የዋንጫ ተሸላሚ ተማሪዎቻችን እንኳን ደሰ አላችሁ
═══════ ❁✿❁ ═══════
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሰኔ 21/2018። ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ20ኛው ዙር የተማሪዎች ምርቃት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገባችሁ የዋንጫ ተሸላሚ ተማሪዎቻችን ኮርተንባችኋል እንኳን ደስ አላችሁ፡፡
በምርቃት ስነ-ስርአቱ ከማኔጅመንት ትምህርት ክፍል አጠቃላይ ከሴቶች 3.9684 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት በማስበዝገብ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነችው ተማሪ ትርንጎ ገዛኸኝ አበራ የተለያዩ የአጠናን ዘዴዎችን በመጠቀም፤ ጠንክራ በማጥናቷ ለስኬት በመብቃቷ ከፍተኛ ደስታ የተሰማት መሆኑን ገልፃለች፡፡
አጠቃላይ ከዩኒቨርሲቲው 3.9741 የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫ ተሸላሚ ከፋርማሲ ትምህርት ክፍል ተማሪ ብሩክ ደግነት በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም ትምህርቱን በትኩረት ሲከታተልና ሲያጠና እንደነበር የገለፀ ሲሆን በሽልማቱ በጣም ደስተኛ እንደሆነና በቀጣይም በሚሰማራበት የስራ መስክ ያስተማረውን ማህበረሰብ በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
የትምህርት አመታትን ጽኑ አላማ ለማሣካት ለፍታችሁ በጥረታችሁ ይኸንን ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ በመቻላችሁና የዋንጫ ተሸላሚ በመሆናችሁ የዩኒቨርስቲያችን አምባሳደሮች ናችሁና እንኳን ደስ አላችሁ።
14 507
The graduate special vibe, special moment and special days
congratulations you graduate 🎉14 507
+4
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች እያስመረቀ ነው
═══════ ❁✿❁ ═══════
ዩኒቨርሲቲው ለ20ኛ ጊዜ በመደበኛ፣ በኤክስቴንሽን፣ በክረምት እና በርቀት መርኃ ግብሮች በቅድመ ምረቃ እና በድህረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን 807 ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የመመረቂያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል።
ተመራቂዎቹ በቅድመ ምረቃ መርኃ ግብር በ8 ኮሌጆች ሥር በሚገኙ 31 የትምህርት መስኮች እንዲሁም በድህረ ምረቃ መርኃ ግብር በ16 የትምህርት መስኮች የትምህርት ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ናቸው።
በታሪካዊው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ የኢትዮጽያ ደረጃዎች ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር፤ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባልና የእለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር መሰረት በቀለ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የሴኔት አባላት፣ የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
@DBU11
@DBU111
14 507
ይህ አዲስ የህይወት ምዕራፍ ነው ።
ምርቃት እልፎች የተመኙት ጥቂቶች ያሳኩት ህልም ነው ። እዚህ ግቢ ስትመጡ በእድል አይደለም የመጣችሁት ስለቻላችሁ :ለቦታው ስለምትመጥኑ ነው : ያሳለፋችሁት ጉዞ ውስጥ አንድም በጤና እንድም በውጤት ወደ ኃላ የቀሩ አሉ :እነሱ እንድ ቀን ይመጣሉ እናንተ ቀን ዛሬ ቀናችሁ ነው እንኳን ደስ አላችሁ ።
ዛሬ ተመርቃችሁ በምትጀምሩት አዲስ ህይወት ብዙ ደስ የሚሉ ግዜያቶችን ታሳልፋላችሁ ።
ግን አንድ ነገር ! ለሁሉም ግዜ እንዳለው እውቁ በምርቃት ማግስት ቤተሰብ ከእናንተ ተአምር አይጠበቅም : ስኬታማ በምትሆኑበት የስራ መስክ በንፁህ አእምሮ ጥሩ መመኘት ወደ ቦታው መቅረብ እንጂ ለአሉታዊ ስሜት መጋለጥ የለባችሁም ።
ምንም እንኳን ሚዲያው :አየሩ : ሰፈሩ ሁሉ ስለተስፋ መቁረጥ ቢያወራ : አንድ ነገር አትርሱ ለእናንተ ያለው የትም አይሄድም ።
ከመምህር ከተማራችሁት ትምህርት ቀጥሎ የምትማሩት የህይወት ትምህርት እጅግ ትዕግስት የሚጠይቅ ነው ማስታወሻችሁን ይዛችሁ ሰህተት ላለመድገም ሞክሩ ።
እንኳን ደስ አላችሁ መልካም የስራ ዘመን ።
wende abebe (መ'ኪያ )
@DBU11
@DBU111
14 507
ውድ ተመራቂዎች እንኳን ለ2018 ዓም የምርቃት ጊዜ አደረሳችሁ እያልን አሪፍ አሪፍ ፎቶ እናንተን ለማንሳት ዝግጅታችንን ጨርሰናል ከዚህ በፊት የሰራናቸውን ስራዎች ለመመልከት ቻናላችንን ይቀላቀሉ በድጋሚ እንኳን ለምርቃታችው ቀን በሰላም አደረሳችሁ BRIGHT PICTURE
☎️ 0975703821
☎️ 0910100440
Tiktok 👉👉 @brightpictuer
Instagram👉👉 @Bright Pictures
https://t.me/Bright_Pictures
14 507
AD
Efrata beauty mark
የምንሰጣቸው አገልግሎት
ጥፍር
ሜካፕ
አይላሽ
ፀጉር
ሂና
Wax
በተመጣጣኝ ዋጋ አድራሻ ጠባሴ መልእክት ኮንዶሚንየም birhan college fit lefit
ስልክ 0984220655
14 507
ውጤትዎን ይመልከቱ!
ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል።
ውጤትዎን ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et
@DBU11
@DBU111
14 507
14 507
+1
Limited Stock
እንኳን ለ2018 ዓም የምርቃት በዓላችሁ አደረሳችሁ
በሽክረት ህትመት ያዘጋጀነውን የሪቫን ህትመት በMetalic Gold ውስን ማቴሪያል ብቻ ስለቀረ በገበያ ላይ ካለው እጥረት አኳያ ቀድመው የሚመጡትን ደንበኞች ብቻ ማቴሪያል እስከቻለ ድረስ የምናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን። (ከጎልድ ሲዘር ውጭ ማንኛውንም አይነት ሪቫን በማግኘት ትችላላችሁ)
ሽክረት ህትመት
አድራሻ ሰማያዊ ፊትለፊት ኬብሮን ኮሌጅ ያለበት ህንፃ(እህል በረንዳ) 3ኛ ፎቅ ላይ
ለበለጠ መረጃ
0940219376
0904238625
14 507
📦 በዩኒቨርሲቲ ቆይታዎ የዕቃዎችዎ አስተማማኝ ጠባቂ — Uni Storage!
ለክረምት ዕረፍት ወደ ቤተሰብ ሲሄዱ የያዟቸውን ዕቃዎች የት እንደሚያስቀምጡ አሳስቦዎታል? ጭንቀትዎን ለኛ ይተውት! Uni Storage ዕቃዎችዎን በታማኝነት እና ሙሉ ዋስትና ባለው ቦታ ያከማችልዎታል።
📌 የ3 ወራት የማከማቻ የዋጋ ዝርዝር፦
🧳 ትላልቅ ሻንጣዎች፦ 400 ብር
🎒 የጀርባ ቦርሳ / ዱፍል ባግ፦ 300 ብር
🧺 የልብስ ማጠቢያ ሳፋ፦100 ብር
🛏️ ብርድ ልብስ፦ 250 ብር
🧹 መጥረጊያ፣ መወልወያ እና የመሳሰሉት፦50 ብር
📚 መጻሕፍት እና ሌሎች ትናንሽ ዕቃዎች፦ 100 ብር
🎁 ልዩ ቅናሾች፦
✅ ከ3 ዕቃዎች በላይ ለሚያስቀምጡ ደንበኞች
✅ በግሩፕ (በቡድን) ለሚመጡ ተማሪዎች ልዩ ቅናሽ አለን!
🔒 ደህንነቱ የተጠበቀ • 🤝 አስተማማኝ • 💰 ተመጣጣኝ
📲 አሁኑኑ ይመዝገቡ!
📞 0962808077
ማሳሰብያ
ዕቃ ለማስቀመጥ የዮኒቨርስቲው መታወቂያ ኮፒ ያስፈል
Uni Storage — ዕቃዎችዎን በአደራ የሚጠብቅ አገልግሎት! 📦✨
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
