en
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Open in Telegram
1 740
Subscribers
+124 hours
+37 days
-530 days
Posts Archive
እንኳን አደረሳችሁ!! "ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ አዲስ አመት በሰላም፣ በጤና አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ መጪው አዲስ አመትም ያቀድነው የምናሳካበት.. የእድገትና
+1
እንኳን አደረሳችሁ!! "ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ አዲስ አመት በሰላም፣ በጤና አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ መጪው አዲስ አመትም ያቀድነው የምናሳካበት.. የእድገትና የብልፅግና ዘመን ይሆንልን ዘንድ መልካም ምኞቴን ገልፃለው" #መልካም_አዲስ_አመት አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን

"እምርታና ማንሰራራት“ በሚል መሪ ሀሳብ ከሚከበሩ የጳጉሜ ቀናቶች አንዱ የሆነው ጳጉሜ 5 የነገው ቀን " ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ " በሚል መሪ ሃሳብ በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር በታላቅ ድምቀት ተከብሯል ።      በዚሁ መርሀ-ግብር ላይም በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር በድሬዳዋ አስተዳደር ዲጂታል ድሬን እውን በማድረግ ተቀዳሚ ድርሻችንን ለማበርከት በዲጂታል ቴክኖሎጂው መስክ በትኩረት በመንቀሳቀስ ተስፋን የሚያጭሩ የተለያዩ ፈጠራዎችንና ችግር ፈቺ አፖችን ማልማት መቻሉን ተናግረው ሌሎች በርካታ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎችን በትኩረት በማከናወን ላይ እንደሚገኙም ነው ክቡር ከንቲባው በዕለቱ ያስታወቁት ።      ጷግሜ 5 የነገው ቀንን ምክንያት በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር የለሙ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም ደግሞ በፈጠራ ስራዎች የበለፀጉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በስፋት እንደሚተዋወቁ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ለፕሮግራሙ መሳካትም ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።      በዕለቱም በቴክኖሎጂ የበለፀጉ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች ከድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፤ ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሁም ከኢንተርፕራይዞች ቀርበው ተጎብኝተዋል ።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ ለሆኑ ሠራተኞቹ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር በዛሬው እለት አካሄደ። በማዕድ ማጋራት መርሀ-ግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው "በቅድሚያ ይህን መርሃ-ግብር በምናካሂድበት እለት የዘመናት የኢትዮጵያውያን ህልም የሆነው የታላቁ የህዳሴ ግድባችን ተጠናቆ የሚመረቅበት በመሆኑ መርሃ-ግብሩን እጅግ ልዩ ያደርገዋል" ያሉ ሲሆን አክለውም "የታላቁ የህዳሴ ግድባችን በዛ ሁሉ ተጋድሎ ውስጥ አልፎ ዛሬ ለምረቃ መብቃቱ እኛ ኢትዮጵያውያን ተጋግዘን በአንድነት ከሰራን ሁሉን መለወጥና ማንሰራራት እንደምንችል ማሳያ ነው ያሉ ሲሆን የዚህ ታሪካዊ ቀን አንድ አካል በመሆናችንም ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን በማለት ደስታቸው አጋርተዋል:: በማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብሩ ላይ ከኮሌጁ ዲን በተጨማሪ የኮሌጁ ም/ል ዲኖች የተገኙ ሲሆን ለሠራተኞቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈው ከኮሌጁ የማኔጅመንት አባላት ጋር በመሆን የተዘጋጀውን መአድ አጋርተዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጷጉሜ 4 " የማሰራራት ቀን"

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ ስምምነት ፊርማ ሥነ-ስርዓት በዛሬው እለት አካሄደ:: በእቅድ ስምምነቱ ላይ የኮሌጁ ዲን የሆኑት አቶ ታደለ አሰፋ በስራቸው ከሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶች እና ደጋፊ ስራ ሂደቶች ጋር የ2018 በጀት አመት የእቅድ ስምምነትን ፊርማ በመፈራረም ርክክብ አድርገዋል:: በተጨማሪም በኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ ም/ዲን የሆኑት አቶ ኤሊያስ አህመድ በስራቸው ከሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች፣የስልጠና አስትባባሪዎች እና የክፍል ተጠሪዎች ጋር የ2018 የስልጠና ዘመን የእቅድ ስምምነትን ፊርማ በመፈራረም ርክክብ አድርገዋል:: እንዲሁም በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ ም/ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ በስራቸው ከሚገኙ የጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር አስተባባሪ እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ትግበራ አስተባባሪዎች ጋር የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ ስምምነትን ፊርማ በመፈራረም ርክክብ አድርገዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጷጉሜ 1/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ በተዋቀረው አዲስ የኢንተርፕራይዝ አደረጃጀት እና የኮሌጁ የምርት ሂደት አተገባበር ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ:: ተቋሙ በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ መሰረት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ከትምህርትና ስልጠናው ጎን ለጎን ምርትና ምርታማነት ላይ በሰፊው እንዲሰሩ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የራሱን ውስጠ ገቢ የሚያሳድግበትን አሰራር ዘርግቶ ወደ ትግበራ ለመግባት በሂደት ላይ ሲሆን በዛሬው እለትም በኮሌጁ ለሚገኙ የፑል አመራር አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተችሏል:: ኮሌጁ ከተለመደው የአሰራር ሂደት የተለየና በነፃነት ቢዝነሱ ላይ ትኩረት አድርጎ መንቀሳቀስ የሚችል አዲስ የኢተርፕራይዝ አደረጃጀት ማዋቀሩን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም ኢንተርፕራይዙ ከህግ አንፃር ማሙላት የሚገባውን ነገር በሙሉ አሟልቶ የተቋቋመ መሆኑንና በቀጣይ ኢንተርፕራይዙን ከኮሌጁ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛልም ብለዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም በቀጣይ በተቋሙ የሚኖረን የምርት ሂደት አሰራር ሁለት ጉዳዮችን ታሳቢ ያደርጋል ያሉ ሲሆን የመጀመርያው የተቋሙ ቀጣይነት ያለው ገቢ ሊያመንጭ የሚችል አቅም መፍጠር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በምርት ሂደት ውስጥ የሚሳተፉ አሰልጣኝ መምህራንን ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ማስቻል በመሆኑ ሁለቱንም እጣጥሞ ማስኬድ ከኛ ይጠበቃልም ብለዋል:: አዲስ የተዋቀረውን የኢንተርፕራይዝ አደረጃጀት ጨምሮ የኮሌጁ የምርት ሂደት አተገባበር ላይ ያተኮረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለመድረኩ ተሳታፊዎች የሰጡት የኮሌጁ የምርት ክፍል ሀላፊ አሰልጣኝ መምህር ነዋይ ይልማ ሲሆኑ ባቀረቡት ሰነድም ከዚህ ቀደም የነበረው የምርት ሂደት ተገቢውን የህግና የአስራር ሂደት የተከተለ ባለመሆኑ በሚፈለገው አግባብ ውጤት ማምጣት እንዳልቻለ ያመላከቱ ሲሆን አሁን ላይ ተሻሽሎ በፀደቀው የውስጥ አሰራር መመሪያ መሰረት ወደ ተቋሙ የሚመጡ ምርትና አገልግሎቶች በተቀመጠው የአሰራር ሂደት ውስጥ እንዲያልፉ የሚደረግበት አግባብ መዘርጋቱንም ገልፀዋል:: በአጠቃላይ በመድረኩ በቀጣይ ኢንተርፕራይዙን ለመማጠናከርና ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል ምን ማድረግ አለብን በሚል በመድረኩ በርካታ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለቀጣይ ስራዎች የጋራ መግባባት የተያዘበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጷጉሜ 1/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ የሚተገብራቸው ዋና ዋና ተግባራት ጥራት ላይ ያተኮረ ነፃ የውይይት መድረክ አካሄደ:: ኮሌጁ በ2018 በጀት ዓመት የትምህርትና ስልጠና እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ትግበራን በተሻለ ጥራት ለመተግበር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሀሳብ ለማሰባሰብ የሚያረዳ ነፃ የውይይት መድረክ ከተቋሙ አመራር አባላትና ከስልጠና ክፍሎች ከተወጣጡ ባለ ድርሻ አካላት ጋር ነፃ የውይይት መድረክ አካሂዷል:: የውይይት መድረኩ ዋና ዓላማ ኮሌጁ በ2018 ዓ.ም በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ የተቃኘ መሪ እቅድ ማዘጋጀቱን ታሳቢ በማድረግ በእቅዱ የተቀመጡ ተግባራትን በተሻለ መንገድ ለመፈፀም ችግሮችን በመለየትና አማራጭ የመፍትሄ ሃሳቦችን በማሰባሰብ ከመግባባት ላይ የተደረሰበትን ጭብጥ ይዞ በአዲሱ በጀት ዓመት ወደ ተግባር ለመግባት በማስፈለጉ እንደሆነም ተገልፇል:: በኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ እንዲሁም በኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ አማካኝነት የተመራው ነፃ የውይይት መድረክ በአራት ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የተካሄደ ሲሆን እነርሱም:- 1. የአሰራርና የአደረጃጀት ሁኔታዎች በምን መልኩ መሆን እንዳለባቸው... 2. በኮሌጁ የሚከናወኑ ተግባራት መነሻና መድረሻ የት ድረስ መሆን እንዳለበት.... 3. በኮሌጁ ከአመራር እስከ ፈፃሚ ያለው ሚና ምን ምን መሆን እንደሚገባው... 4. ከአሁናዊ ፖሊሲና ስትራቴጂካዊ ሁኔታዎች አኳያ(ከ11 ዘረመሎች አንፃር) እንደ ተቋም በምን አግባብ መንቀሳቀስ ይኖርብናል በሚሉ ነጥቦች ላይ ውይይት ማድረግም ተችሏል:: ለውይይት ይተቀመጡ የመወያያ አጀንዳዎችን መነሻ በማድረግም በመድረኩ ተሳታፊዎች በጥልቅ በነፃነት ሀሳቦች ተነስተው ውይይት የተካሄደ ሲሆን ኮሌጁ ለ2018 በጀት ዓመት የያዛቸውን ተግባራት በተሻለ መንገድ እንዲተገብር የሚያስችለውን በርካታ ግብዓቶችን ከመድረኩ ማግኘትም ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ነሃሴ 30/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል:: #መልካም_በዓል!!
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል:: #መልካም_በዓል!!