1 740
Subscribers
+124 hours
+37 days
-530 days
Posts Archive
Repost from FDRE TVT Institute
በአገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ ያለው የአሰልጣኞች አቅም ግንባታ ስልጠና ምልከታ ተካሄደ፡፡
ከነሃሴ 15/ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተሰጠ የሚገኘው የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በተግባር ላይ የተመሰረተው በተለያዩ ማዕከላት ውስጥ በተዘጋጁ ወርክሾፖች በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
ስልጠናው የሚገኝበት ሁኔታ የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር፣ የድሬዳዋ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸውና የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ አመራሮች በጉብኘቱ ወቅት ተገኝተዋል፡፡
Website: http://www.ftveti.edu.et/
Youtube ; http://www.youtube.com/fdretvtinstitute
facebook https://www.facebook.com/TVTI.EDU.ET
Telegram; https://t.me/fdretvtinstitute
Tiktok; www.tiktok.com/@fdretvtistitute
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀት አመት የተቋሙ መሪ እቅድ ለኮሌጁ ፑል አመራር አባላት አስተዋወቀ::
ኮሌጁ የ2018 በጀት አመት እቅዱን ከዘርፉ አዳዲስ እሳቤዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማስቻል በትኩረት ሲዘጋጅ የቆየው መሪ እቅድ ተጠናቆ በኮሌጁ ለሚገኙ ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች ቀርቦ እቅዱን ማስተዋወቅ ተችሏል::
የእቅድ ትውውቅ መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ የተዘጋጀው የኮሌጁ የ2018 በጀት አመት መሪ እቅድ እዳለፉት ጊዜያት የውጤት አመላቾች ላይ ያተኮረ ሳይሆን ዋናው ውጤት ላይ ያተኮረና ተጠያቂነትም ያለበት እንደሆነ የገለፁ ሲሆን አክለውም እንደ ተቋም በተቻለ መጠን ከመንግስት የተሰጠንን ተልእኮ ሊያስፈፅም የሚያስችል እቅድ ማዘጋጀት ላይ ትኩረት ሰጥተን ሰርተናልም ብለዋል::
የኮሌጁ የ2018 በጀት አመት እቅዱን ለመድረኩ ተሳታፊዎች ያቀረቡት የኮሌጁ የእቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ስራ ክፍል ሀላፊ አቶ አለማየሁ ብርሃኑ ሲሆኑ ከአዲሱ የዘርፉ እሳቤ አንፃርና የተቋሙ ነባራዊ ሁኔታን መንሻ በማድረግ በእቅዱ የተካተቱ ተግባርና ሀላፊነቶችን በዝርዝር ገለፃ በማድረግ አስተዋውቀዋል::
በተጨማሪም ለኮሌጁ ዋና ስራ ሂደቶችና ደጋፊ ስራ ሂደቶች ካስኬድ ተደርጎ የሚወርደው እቅድ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎችም አጠቃላይ በቀረበው እቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ያሏቸውን ነጥቦች ለእቅዱ አዘጋጆች ምክረ ሀሳቦችን መስጠትም ችለዋል::
መድረኩ በቀጣይ ቀናትም የሚቀጥል ሲሆን በኮሌጁ የሚገኙ የስራ ሂደቶችና ክፍሎች ከዋናው የኮሌጁ እቅድ ላይ የራሳቸውን እቅድ ካስኬድ በማዘጋጀት የእቅድ ስምምነት የሚፈራረሙ መሆኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሀሴ 27.2017ዓ.ም
ድሬዳዋ
አድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት ለኮሌጁ የፑል አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት በGreen TVET እሳቤ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ::
የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት አድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) በኮሌጁ ትግበራውን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በGreen Energy ዙሪያ በርካታ ስራዎችን በኮሌጁ እንዲሁም በአስተዳደሩ ማከናወኑን አስታውሰው ፕሮጀክቱ ያስቀመጠውን ግብ ከማሳካት አንፃር ብዙ ተግዳሮቶችን አልፎ አሁን ላይ ከሌሎች የፕሮጀክት ሳይቶች አንፃር የተሻለ አፈፃፀም እያስመዘገብ እንደሚገኝም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ይህን በ Green TVET እሳቤ ላይ ያተኮረ የግብዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ያስፈለገው በቀጣይ ኮሌጁ በትኩረት ከሚሰራባቸው ተግባራት ውስጥ የGreen TVET አንዱ በመሆኑ ከወዲሁ በዘርፉ እሳቤ ላይ ሰፋ ያለ ግንዛቤ እንዲኖር ለማስቻል ያለመ እንደሆነው ገልፀዋል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ በቅድሚያ የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት ዋና አላማ ግብን አስመልክቶ በፕሮጀክቱ ዋና አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎ ገለፃ የተደረገ ሲሆን ዋና አስተባባሪው አያይዘውም ፕሮጀክቱ ከጅምሩ እንስቶ በኮሌጁ በቆየባቸው አመታት ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ያከናቸውን ዋና ዋና ቁልፍ ተግባራትና ያስመዘገባቸውን አመርቂ ውጤቶች በዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል::
የGreen TVET እሳቤ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ሰነድ በኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን Green Energy ከTVET ዘርፍ ጋር ያለውን ቁርኝትና ከቅርብ አመታት ወዲህም በዘርፉ ተቀዳሚ ትኩረት እያገኘ እንደሆነ በሚያመላክት ሁኔታ የግንዛቤ ስልጠናውን መስጠት ችለዋል::
የመድረኩ ተሳታፊዎች በተሰጣቸው የግንዛቤ ስልጠና መነሻነት ሀሳቦችን በማንሳት በግሩፕ የተወያዩ ሲሆን Green Energy ከትምህርትና ስልጠና አኳያ፣ ከቴክኖሎጂ አኳያ እንዲሁም አጠቃላይ ከኮሌጁ እንቅስቃሴ አኳያ በምን መልኩ አቀናጅቶ ለመተግበር ያስችላል የሚሉ ጉዳዮችን በዝርዝር አስቀምጠዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 19/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
በIOM የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም በEDI የስልጠና ሰጭነትና አስተባባሪነት ሲካሄድ የቆየው የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኞችና ምሩቃን የንግድ ሃሳብ pitching ስልጠና እና ውድድር ተጠናቀቀ።
በአስተዳደሩ ከሚገኙ ሁለቱ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የተመረጡና የንግድ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች ከነሀሴ 14/2017 ዓ.ም እስከ ነሀሴ 18/2017 ዓ.ም ለአምስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው ስልጠና እና የንግድ ሃሳብ ውድድር ፍፆሜውን አግኝቷል::
በእለቱ በነበረው የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የIOM ተወካይ አቶ ዘሪሁን እንደገለፁት ይህን መሰል ፕሮግራሞች ወጣቶች የተሻለ የንግድ ሃሳብ እንዲያጎለብቱ እና የንግድ ሃሳባቸውን እንዴት መግለፅ እንዳለባቸው የሚረዱበት እንዲሁም የቢዝነስ አጋር የሚያገኙበትን አጋጣሚን የሚፈጥር ነው ያሉ ሲሆን አክለው በውድድሩ ጥሩ ውጤት ያስመዘገቡትን ወጣቶች በሀገር አቀፍ ውድድር ላይ እንዲሳተፉ የሚደረግ ይሆናልም ብለዋል::
በተጨማሪም በውድድሩ አሸናፊ የሆኑት ወጣቶች የንግድ ሃሳባቸውን ወደ መሬት የሚያወርዱበትን እና ንግዳቸውን የሚያስፋፉበት መንገድ እንደሚመቻችላቸውም በመድረኩ ማወቅ ተችሏል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 19/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎፈቃድ ስራዎች ማስጀመሪያ እና የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በኮሌጁ ተካሄደ።
በዘንድሮ ክረምት "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የችግኝ ተከላ ንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን ይህን ምክንያት በማድረግም በተቋም ደረጃ በኮሌጁ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩን በዛሬው ዕለት ማከናወን ተችሏል::
በዛሬው ዕለት በኮሌጁ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የኮሌጁ አመራሮችና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን በተቋሙ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው ስፍራ ላይም አሻራቸውን እኑረዋል::
በቀጣይም በኮሌጁ የክረምት የበጎፍቃድ ስራዎች ላይ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የሚያከናውኑ ሲሆን በዚህም የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ፣ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግን ጨምሮ መሰል ማህበረሰብ ተኮር ንቅናቄዎች ላይ እንደሚሰራ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ለኮሌጁ የቦርድ አባላት አቀረበ፡፡
በበጀት አመቱ የተቋሙን አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለቦርዱ የቀረበ ሲሆን በዚህም ኮሌጁ ከዝግጅት ምእራፍ አንስቶ በበጀት አመቱ የነበረውን የእቅድ አፈፃፀምና አጠቃላይ በኮሌጁ የተሰሩ የለውጥ ስራዎችን እንዲሁም የተገኙ ውጤቶችን ለቦርዱ ሪፖርት አቅርበው ገለፃ ያደረጉ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ በተቋሙ ሊሰሩ በእቅድ የተያዙ ዘርፈ ብዙ ስራዎችንም ለቦርድ አባላቱ በዝርዝር አመላክተዋል፡:
በመድረኩ የቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግም የቦርድ አባላቱ ግብረ- መልሳቸውን የሰጡበት ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በቀጣይ በሚኖረው የስራ እንቅስቃሴ ላይ ምክረ-ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል::
በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በቀረበው የኮሌጁ አጠቃላይ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የቀጣይ ስራ አቅጣጫና መመሪያን በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ ለሚገኙ ወጣቶች የክረምት ወቅት የሙያ ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ተጀመረ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክረምት ወቅት አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ በሚል መርሃ-ግብር በአስተዳደሩ እረፍት ላይ ለሚገኙ የአጠቃላይ የ1ኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ ስልጠናዎችን መስጠት ጀምሯል::
ለወጣቶቹ በተዘጋጀ ኦረንቴሽን ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለወጣቶች ባስተላለፉት መልዕክትም የዚህ የክረምት ወቅት ስልጠና የተዘጋጀበት ዋና አላማ ወጣቶች እረፍታችሁን ቁምነገር ላይ በማዋል ቢያንስ በክረምቱ የአንድ ሙያ ባለቤት እንድትሆኑ ለማስቻል ነው ያሉ ሲሆን አክለውም የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ክረምቱን በኮሌጃችን በሚኖራችሁ ቆይታ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት የምትገነዘቡ በመሆኑ በቀጣይ ምዕራፋችሁ ለሙያ ተኮር ስልጠናዎች ቅድሚያ እንድሰጡ ያግዛችኃልም ብለዋል::
የአንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ የክረምት ስልጠና ላይ ለመሳተፍ ወደ ኮሌጁ የመጡ ወጣቶች በቅድሚያ የህይወት ክህሎት ስልጠና ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚወስዱ ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናው ወጣቶች የቀጣይ ህይወታቸውን የመምራት ክህሎት፣ችግሮችን የመፍታት ክህሎት እንዲሁም የውሳኔ አሰጣጥ ክህሎቶችን እንደሚያገኙበት የተገለፀ ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናውን እንዳጠናቀቁ በቀጣይ በመረጡት የሙያ ዘርፍ ላይ ስልጠናቸውን የሚጀምሩም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 7/12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት የ2017 ዓ.ም ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ አካሄደ::
በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የሁለተኛው ተርም መጠናቀቁን ተከትሎ በአመቱ የተከናወኑ ተግባራትን አፈፃፀም የሚገመግም ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ ተካሂዷል::
በሂደቱ ሀላፊና የኮሌጁ ም/ል ዲን አቶ ኢልያስ አህመድ የተመራው የማጠቃለያ መድረኩ በሂደቱ ስር ያሉ የክፍል ተጠሪዎች በተገኙበት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት በአመቱ የነበረውን የትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ፣ የትብብር ስልጠናዎች፣ የሰልጣኞች የተቋም ምዘናን ጨምሮ ለትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የተሰጡ ተጨማሪ ተልዕኮዎች አፈፃፀምን በዝርዝር መመልከት ተችሏል::
በተጨማሪም መድረኩ በከሰዓት ውሎው በዲፓርትመንቶች የቀረበውን የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ማቴሪያል የግዢ ፍላጎት ጥያቄዎች ላይ የአካዳሚክ አባላቱ በጥልቀጥ የተወያዩበት ሲሆን በቀረቡት የግዢ ፍላጎቶች ላይ አስፈላጊውን ማስተካከያ በማድረግ ለግዢና ፋይናንስ እንዲላክም ተደርጎል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 1/12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
+5
የሥራ ማስታወቂያ ለሥራ ፈላጊዎች!!!
ከትላንት ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን የሚቃኝ የልምድ ልውውጥ እና የተሞክሮ ሽግግር እያረጉ የሚገኙት ከሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች በዛሬው ዕለትም ቀጥለው በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ አድርገዋል።
በዚህም በኮሌጁ በመገኘት አጠቃላይ የክህሎት ልማቱ ከስራ ዕድል ፈጠራው ጋር ያለው መስተጋብር ምን እንደሚመስል በቢሮው አመራሮች እንዲሁም በኮሌጁ ዲን ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሀምሌ 25/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
