1 740
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-630 days
Posts Archive
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ሰልጣኝ ተማሪዎች በጋራ በመሆን "ደም በመለገስ ህይወት እንታደግ" በሚል መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሃ-ግብር አካሄዱ፡፡
በደም ልገሳው መርሃ-ግብር ወቅት ደማቸውን የለገሱ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ሰልጣኝ ተማሪዎች በሚተካ ደም የማይተካውን የሰው ሕይወት መታደግ የሚያስችል ተግባር ላይ መሳተፋቸው ደስታ እንደፈጠረላቸው ገልፀው በቀጣይ ዙር በሚኖረው የደም ልገሳ መርሃ-ግብር ተሳታፊ እንደሚሆኑም ገልፀዋል፡፡
የደም ባንክ አገልግሎት ሰራተኞችም በደም ልገሳ ፕሮግራሙ ደማቸውን ለለገሱት የኮሌጁ ሰራተኞችና ተማሪዎች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን በቀጣ እንዲህ አይነት መርሃ ግብሮችን በጋራ ከኮሌጁ ጋር እንደሚሰሩም ገልጸዋል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ሀምሌ 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#ጥቆማ
ኢትዮጵያ 5 ሚሊዮን #ኮደሮችን ለማሰልጠን ያለመ ፕሮጀክት አስጀምራለች።
ለ3 ዓመታት ያህል የሚቆየው ይሄ ፕሮጀክት ከተባበሩት አረብ ኤሜሪትስ (UAE) ጋር በመተባባር የሚተገበር ነው ተብሏል።
ምን መማር ይቻላል ?
- Android Kotlin Development Fundamentals
- Data Science Fundamentals
- Programming Fundamentals
ትምህርቱን እንዴት ማግኘት ይቻላል ?
ስልጠናዎቹ በዩዳሲቲ (Udacity) በተሰኘው ኦላይን የትምህርት ፕላትፎርም ተዘጋጅተው የቀረቡ ናቸው።
ሰልጣኞች ያለ አንዳች ክፍያ በነጻ ኮምፒውተራቸውን ወይም ስልካቸውን በመጠቀም መሰልጠን ይችላሉ።
ስልጠናዎቹ 6-7 የሚሆኑ ሳምንታትን የሚፈጁ ሲሆን በማጠቃለያው ላይ ሞያዊ ሰርተፊኬት ይሰጣል።
የስልጠናዎቹን ይዘት እንዲሁም ተጨማሪ መረጃዎች በተዘጋጀው ድረ-ገጽ ( https://ethiocoders.et/ ) ላይ መመልከት ይችላሉ።
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
በማዕድናት፣ በፈጠራዎች፣ ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አይ ሲ ቲ ዘርፍ ላይ እየሰራችሁ ላላችሁ ኢንተርፕራይዞች በ3ኛው ዓመታዊ የመካከለኛ አነስተኛ እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ/MSME/ መድረክ ላይ በመገኘት ልምድና ተሞክሮአችሁን እንዲሁም ሥራችሁን ለማጋራት ትልቅ ዕድል ተመቻችቶላችኋል ፡፡
በማዕድናት፣ በፈጠራዎች፣ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ እና አይ ሲቲ ዘርፍ የተለያዩ ሥራዎችን በመስራት ሁለት ዓመትና በላይ የቆያችሁ ኢንተርፕራይዞች ይህ ዕድል እንዳያመልጣችሁ፡፡
ፎረሙ የሚካሄደው በአፍሪካ ናሚቢያ ሲሆን መስፈርቱን የምታሟሉ ኢንተርፕራይዞች በፍጥነት ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት መመዝገብ ትችላላችሁ ፡፡
ሊንክ https://msmeforum.africa/
የዚህ የአፍሪካ ኢንተርፕራይዞች አውታረ መረብ ስብስብ ፕሮግራም አባል መሆንም ትልቅ ዕድል ነው፡፡
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካንፓስ፥ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ሠልጣኝ ተማሪዎችን በዛሬው እለት በጋራ በመሆን አስመረቁ።
በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ሃርቢ ቡህ እንደገለጹት የአንድ አገር ኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት የሚወሰነው በትምህርት የሰለጠነ የሰው ሃይል የዳበረ እውቀትና ክህሎት ባላቸው ዜጓቿ በመሆኑ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።
ምክትል ከንቲባው አክለውም ድሬዳዋ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት በምታደርገው ጥረት ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ተመርቀው የሚወጡ ተማሪዎች ያልተቆጠበ ተሣትፎ ቀዳሚውን ድርሻ የሚይዝ ብለዋል።
በዚህ የምርቃት ስነ -ስርአት ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ሃርቢ ቡህ፣ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ፣ የሁለቱም ኮሌጆች ዲኖችና ም/ዲኖች እንዲሁም መምህራን እና ተመራቂዎችና የተመራቂ ቤተሠቦች ተገኝተዋል ።
በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ ከኢትዮ ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካንፓስ ተማሪ ኤርሚያስ ከፍያለው 3.95 በማምጣት አጠቃላይ የወርቅ ሜዳሊያና የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን ከድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካንፓስ ጋርመንት ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆኑት ሲሳይ ዘውዱ እና በእምነት ጠብቀው 3.91 እኩል ነጥብ በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ በመሆን አጠናቋል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ሀምሌ 6/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+1
የሥራ ማስታወቂያ
****
Ethiopian Airlines
መረጃውን ሼር በማድረግ ለወጣቶቻችን ተደራሽ እናድርግ!!
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
ለኮሌጅና ዩኒቨርስቲ ምሩቃን በሙሉ
****
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚቢሽን(Job Fair)" የፊታችን አርብ ሰኔ 28/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ሁለገብ ሜዳ የሚካሄድ ይሆናል።
በዚህም ስራ ፈላጊ ምሩቃን የተለያዩ ድርጅቶች በቅጥር ሥራ የምታገኙበትን ሁኔታ ሊያመቻቹ እናንተን ስለሚጠብቁ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በመያዝና በአካል በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች "ከተረጂነት አስተሳሰብ ለመላቀቅና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት አደረጉ።
በመድረኩም ከተረጂነት ለመላቀቅና በምግብ እራስን ለመቻል አገራዊ መግባባትን መፍጠር አስፈላጊ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በተረጂነት ተጨባጭ ለውጥ ባለመመዝገቡ የዜጎችን አመለካከት በመቀየር፣ አቅምን በማቀናጀትና እንዲሁም የዘርፉን ተጨባጭ ሁኔታ በመረዳት የሥራ ዕድል ፈጠራን ማጠናከር እንደሚገባም በሰነዱ ቀርቧል።
ተሳታፊዎች በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት ያደጉበት ሲሆን አገራዊ እሳቤውና አቅጣጫውን እንደ አስተዳደሩ ተጨባጭ ሁኔታ በማዘጋጀት ወደ ስራ ለመግባት ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት እንዲሰጠውም አስተያየታቸውን ሰተዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
