📚የአንብብ ትውልድ📚
Open in Telegram
☞ይህ ቻናል የተከፈተው የሰዎችን የማንበብ ልምድ ለማሳደግና አንባቢ የሆኑ ትውልዶችን ለመፍጠር ነው!! ✔አስተማሪ የሆኑ ታሪኮች ✔ግጥሞች ✔ምክር አዘል ቁም ነገሮች ✔እንዲሁም የተለያዩ መፅሀፎች በ pdf ይቀርብበታል አንባቢ ከሆኑ ይቀላቀሉን💝አንባቢ መሆን ብልህነት ነው💝 for any comment☞ @Anbabyan2bot
Show more1 146
Subscribers
-224 hours
-107 days
-330 days
Posts Archive
1 147
ረሱል (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በእውነተኛ እምነት እና በፍቅር ህይወታቸው ውስጥ ብዙ አስደናቂ ነገሮች አሉ 😍😍
ከእነዚህ አንዱ የሰው ልጆች ሁሉ አንድ እንደሆኑና ምንም እንኳን የቆዳ ቀለም የቋንቋ የሃገር ....ልዩነት ቢኖራራቸዉ ሁላችንም በአላህ ፊት እኩል እንደሆንን ያስተማሩት ነው።
በተጨማሪም ስለ ጁምአ ቀን ታላቅነት ነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦
«خَيْرُ يَوْمٍ طَلَعَتْ عَلَيْهِ الشَّمْسُ يَوْمُ الْجُمُعَةِ»
(«ፀሐይ ከወጣችባቸው የሳምንቱ ቀናቶች ሁሉ በላጩ የጁምአ ቀን ነው») — [ሶሒሕ ሙስሊም]
እኛም እንደ ረሱል (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) 😍😍😍እውነተኛ እምነትና ፍቅር በህይወታችን ውስጥ እንዲኖር እንሞክር
ሀጃችን የሚወጣበት የጨነቀዉ የታመመ የታሠረ የታረዘዉ ነፃ የሚሆንበት ያላገባዉም የሚታጭበት😍 የዱዐ ቀን እንዲሆን ተመኘሁ 🤲🤲🤲🤲
መልካም ጁምዐ😍😍😍😍
1 147
#ፉአድ_ሙና ከልቡ ደራሲ ነው📚🎉
አላህ ከዚህ በላይ ብዙ መፅሀፎችን የሚፅፍበት ብርታት እንዲሰጠው እመኛለው😍
አላህ ባነበብነው የምንጠቀም ያድርገን🥺🤲
1 147
+1
Alhamdulillah #ሲማ ን አስጀምሮ ላስጨረሰኝ ጌታዬ🥰🥰
ይህን መፅሀፍ ሁላችሁም ብታነቡት ብዙ የምትጠቀሙበት ነገር ይኖራል ወላህ😍
መፅሀፉን @Sima_book ላይ ታገኙታላችሁ🎉🎉
1 147
ጠንካራ ሆኖ ለመቆየት ዲስፕሊን ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። ሁሌ ማንበብ አሰልች ይሆናል ግን ለስራችንና ለራሳችን እድገት ስንል የምንከፍለው ዋጋ መሆኑን ስናስብ የግድ እናደርገዋለን። አለማድረጋችን የሚያስከፍለን ዋጋ ምን እንደሆነ ስናውቅ ደግሞ ይበልጥ ጠንከራ እንሆናለን።
ለዚህ መርህ ራስን ማስገዛት መቻል ትልቅ አቅም ይጠይቃል። በተለይ በጣም በተጣበበ ሰዓት ለቤተሰብ፣ ለስራ፣ ለማህበራዊ ህይወትና community service መስጠት ትልቅ አቅም ይፈልጋል።
@Anbabiwoch
1 147
#ወደ_ከፍታ
#ክፍል_19
" ደስታን ከአበባ፣ ገርነትን ከእርግብ፣ መታዘዝን ከንብ፣ ስራን ከጉንዳን፣ እና ቀድሞ መነሳትን ከዶሮ ተማሩ። " " የሰው ልጅ ከአንድ በላይ ሕይወት የለውም፣ ሕይወቱን ካበላሸው ምድራዊውም ሰማያዊውንም ዓለም ያጣል፣ ስለዚህንም የንሰሐ (ተውበት) በር ክፍት ነው፣ የአላህ ጸጋም ተሰጥቶሀል፣ ቸርነቱም ይመጣል፣ ይሄዳል ። "
ከዚህ ክፍል የተወሰደ@ANBABIWOCH📖
1 147
“ለነፍስህ የምትሰጣት ትልቁ
የጁሙዓ ስጦታ በነቢዩ (ﷺ)ላይ
የምታደርገው ሰለዋት ነው”
صَلُّوا عَلَى النَّبِيِّ
اللهُم صلِّ وسلِم وبَارك على نبينَا محمدﷺ🤍
1 147
لَقَدْ مَنَّ اللَّهُ عَلَى الْمُؤْمِنِينَ إِذْ بَعَثَ فِيهِمْ رَسُولًا مِّنْ أَنفُسِهِمْ يَتْلُو عَلَيْهِمْ آيَاتِهِ وَيُزَكِّيهِمْ وَيُعَلِّمُهُمُ الْكِتَابَ وَالْحِكْمَةَ وَإِن كَانُوا مِن قَبْلُ لَفِي ضَلَالٍ مُّبِينٍ
አላህ በምእምናን ላይ ከጎሳቸው የኾነን፤ በእነርሱ ላይ አንቀጾቹን የሚያነብ፣ የሚጠራቸውም፣ መጽሐፍንና ጥበብን የሚያስተምራቸውም የኾነን መልእክተኛ በውስጣቸው በላከ ጊዜ፤ በእርግጥ ለገሰላቸው፡፡ እነርሱም ከዚያ በፊት በግልጽ ስህተት ውስጥ ነበሩ፡፡(አል- ኢምራን 164)
ረቢዕ ይህ ወር የአላህን መልዕክተኛ የታደልንበት ነው
ምንኛ ብንታደል ይሆን የእርሶ ኡመት ያደረገን 🥰🥰🥰
አውሺ ባወሳቸው ረሺም በረሳቸው ቁጥር የአላህ ሰላት እና ሰላም በአሽረፈል ኸልቅ ላይ ይሁን
❣صلُّوا على خير العباد وسلِّـموا
فصلاتنا ذُخـــــرٌ لنا ووسَـــامُ
يا ربُّ صَـلِّ على النَّبيِّ محـمَّدٍ
مَــا لاحَ برقٌ وأسـتهلَّ غَمـــامُ
اللهم صلِّ وسلم على نبينا محمدﷺ❤
🩵 በሀቢባችን ላይ የበዛ ሰለዋት የምናወርድበት በሩቋ ሀገር ያሉትም የሰላሙን አየር የሚያስተነትኑበት፣ የድል ሰላት የሚሰግዱበት፣ ለተጨነቁት ወንድሞቻችን ድልን ለታመመ መዳንን፣ ለሞቱት ሸሂድነትን የሚወፈቁበት፣ በካህፍ እና በዱዓ የደመቀ እና የተዋበ ጁምዓ ይሁንልን💚💚💚
1 147
Repost from Usmanic Islamic psychology/ ስለ ሰው ልቡና
"የፊታቸው ሰማይ ላይ ፈገግታ የማትጠልቅ የዘውትር ፀሀይ ነበረች ፥ ገፃቸው ለተመለከታቸው በሙሉ ደስታን የሚያጋባ የሀሴት ድግስ ነው። በትህትና የተቀመረ የማማር አክሊልል ደፍተዋል ፣ በነቢይነት ስክነት ሞገስ እና በሰውነት ጨዋ ማንነት ገፃቸው የረጋ ነው...።"
(መሰል ውብ አንቀፆችን ስለ ውዱ ነብይ (ﷺ) የሚያገኙበትን 'ፍፁም ሰው ፍፁም ነብይ' መፅሐፍ በመግዛት ከመልእክተኛው ጋር በጥልቀት እና በውበት ይተዋወቁ።)
የኢስላማዊ ሳይኮሎጂ መፅሀፌ እስኪደርስ እቺ ስለ ውዱ ነቢይ (ﷺ) በውብ ቋንቋ እና በጥልቅ ሀሳብ የከተብኳትን መፅሀፍ ውሰዱ።
ርእስ= ፍፁም ሰው ፍፁም ነብይ
ፀሀፊ = ኡስማን ሙስጠፋ
የህትመት ጊዜ= ነሀሴ 2017 ዓ.ል
መፅሐፉን ለማግኘት በቴሌግራም ዩዘርኔም @usmanoman ወይም በስልክ 0921390122/ 0912027023 ላይ ያናግሩን
1 147
#ወደ_ከፍታ
#ክፍል_18
" ስኬታማ ሰዎች ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ትውልዱ ከንግግራቸው ሊጠቀም ይገባል፣ መሐመድ ቢን ራሺድ አል-መኽቱም ተስፋ መቁረጥን ስለማሸነፍ እና የማይቻለውን ስለመታገል ይነግራችኋል፣ ስለዚህ ጆሯችሁን ስጡት። ..."
ከዚህ ክፍል የተወሰደ📚 @Anbabiwoch 📚
1 147
ልጅ አያቱ በእርሳስ ደብዳቤ ስትፅፍ ይመለከታል "አያቴ የምትፅፊው ስለ እኔና አንቺ ነው ወይስ ስለ እኔ ብቻ ነው?
"
አያቱም መፃፏን አቁማ "በእርግጥ የምፅፈው ስለ አንተ ነው ከምፅፋቸው ቃላቶች ይልቅ ትልቁ ነገር የምፅፍበት እርሳስ ነው።ስታድግ ይህን እርሳስ እንደምትወደው እርግጠኛ ነኝ።"
ልጁም እርሳሱን በንቀት እየተመለከተ "ይህ እርሳስ እኮ ተራ ነው እስካሁን ካየኋቸው እርሳሶች በምን ይለያል?"
"እሱ የሚወሰነው ነገሮችን በምታይበት መንገድ ነው።ይህ እርሳስ 5 ጥበቦች አሉት
አንደኛው ጥበብ :ብዙ መልካም ነገሮችን መከወን ትችላለህ ነግር ግን እኔ ይህን እርሳስ እርምጃውን እየመራሁ እንደምፅፍበት ሁሉ አንተንም በእያንዳንዷ እርምጃህ የሚመራህ አምላክ እንዳለ ሁሌም አስታውስ።
ሁለተኛው ጥበብ: መፃፌን ለአፍታ አቁሜ መቀረጫ አውጥቼ እርሳሱን እቀርፀዋለሁ፤እርሳሱ በመጠኑም ቢሆን ሊጎዳ ይችላል ነገር ግን ከበፊቱ ይበልጥ የሰላ ይሆናል።አንተም ሀዘንና መከራ ሲገጥሙህ ይበልጥ ህይወትህን እንደሚቀርፁትና የተሻለ ሰው እንደሚያደርጉህ አስብ።
ሶስተኛው ጥበብ፣እርሳስ ስህተቶችን እንድናስተካክል ማጥፊያ እንድንጠቀም ይፈቅድልናል።ይህ ማለት ችግርን ማረም ስህተት አይደለም፣በፍትህ መንገድ እንድንሄድ ያደርገናልና።
አራተኛው ጥበብ:የእርሳስ ትልቁ ነገር ከውጭ የሚታየው እንጨት ሳይሆን ከውስጥ ያለው ግራፋይት ነው።አንተም ከውጫዊው ማንነትህ ይልቅ ውስጥህ ስለሚሆነው ነገር ልትጨነቅ ይገባሀል።
አምስተኛውና የመጨረሻው ጥበብ እርሳስ ምልክትን ትቶ ያልፋል።እንተም በእያንዳንዷ ቀን የምታደርገው ነገር ሁሉ ምልክትን ትቶ ማለፉ አይቀርምና የምታደርጋቸውን ነግሮች ሁሉ አመዛዝነህ አድርግ"
story of apencil by paulo coehlo
@Anbabiwoch
1 147
ለማንበብ ስትዘጋጅ ማድረግ ያለብህ ነገሮች ፦
**
፨ ስኬታማ መሆን እንደምትችል ወስነህ ግባ ከዚያም ‹‹ቢስሚላሂ›› ብለህ ጀምር፤
፨ ከኮምፒውተር ስክሪን ላይ የምታነብ ከሆነ ተጨማሪ ጥንቃቄ ውሰድ፤
፨ ለእንቅልፍ የሚጋብዙና ስሜትን ሊሰርቁ የሚችሉ ነገሮችን በአከባቢህ ካሉ አስወግድ ፤
፨ ዐይንህ ከአእምሮህ ጋር በተቀናጀ ቁጥር ስኬታማ እንደምትሆን አትርሳ፤
፨ በቂ ብርሃን ባለበት ቦታ ላይ ሆነህ አንብብ፤
፨ ስታነብ እረፍት እየወስድክ አንብብ፤
፨ ስለምትፈልገው ነገር በቂና አስፈላጊ አገልግሎት የሚሰጥህ መጽሐፍ መሆኑን ለይ፤
፨ በጣም ትኩረትን የሚሻና ውስብስብነት ያለውን መጽሐፍ በድካምና በእንቅልፍ ስሜት ወይም በሁኔታዎች የመረበሽ አጋጣሚ ላይ ስትሆን አታንብብ፡፡
፨ በንባብ ዙሪያ ጥናት ያደረጉ ሙያተኞች ከቀን ንባብ የሌሊት ንባብ ተመራጭ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ (ሌሎች ምሁራን ደግሞ የቀን እንደሚበልጥ ተናግረዋል፡፡ አንተ የግል ልምድህን አጥንተህ የራስህን ምርጫ ያዝ)
፨ ለማንበብ ፍላጎትና ጉጉት ባሳደረብህ መጽሐፍ በመጀመር ልምድህን አዳብር ።
📚📚@Anbabiwoch📚📚
