ቅዱሳት መጻሕፍት
Open in Telegram
በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures
Show more7 842
Subscribers
+1024 hours
+417 days
+14330 days
Posts Archive
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
የጥንት ቤተክርስቲያን ጉባዔዎች
ክፍል-፪
የኤፌሶን ጉባኤ (431 ዓ.ም.)
የቤተ ክርስቲያን ሦስተኛው ጉባኤ ሲሆን በንጉሠ ነገሥት ቴዎዶስዮስ 2ኛ የተጠራው በነገረ ክርስቶስ ላይ ያሉ ውዝግቦችን፣ በዋነኛነት የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ ንስጥሮስን እና የእስክንድርያውን ቄርሎስን የሚመለከቱ ነገረ ክርስቶሳዊ ውዝግቦችን ለመፍታት ነው። ጉባኤው የተካሄደው በትንሿ እስያ (በአሁኗ ቱርክ) በምትገኝ ከተማ በኤፌሶን ሲሆን በክርስቲያናዊ አስተምህሮ ላይ ዘላቂ ተጽእኖ ነበረው።
የጉባዔው ዳራ እና አውድ
ወደ ኤፌሶን ጉባኤ ያደረሰው ዋናው የነገረ መለኮት ሙግት በክርስቶስ ተፈጥሮ እና በማርያም ስም "Theotokos" ቴዎቶኮስ (በግሪክኛ፡ "እግዚአብሔርን የተሸከመች" ወይም "የእግዚአብሔር እናት") በሚል ርዕስ ዙሪያ ያጠነጠነ ነበር። ንስጥሮስ፣ በአንጾኪያ ነገረ ክርስቶስ ተጽኖ፣ ማርያም በክርስቶስ መለኮታዊ እና ሰዋዊ ተፈጥሮዎች መካከል ያለውን ልዩነት በማጉላት ቴዎቶኮስ ከመባል ይልቅ "Christotokos" ክርስቶቶኮስ (“ክርስቶስ ተሸካሚ”) መባል እንዳለባት ተከራክሯል። ይህንን አመለካከት በአንድ አካል ውስጥ የክርስቶስን የሁለቱን ባሕርያት (መለኮትነትና ሰውነት) አንድነት በጠበቀው የእስክንድርያው ቄርሎስ ሙግት ገጠመው።
የጉባዔው ቁልፍ ክስተቶች
1. ጥሪ እና የመጀመሪያ ሂደቶች፡-
ጉባኤው በዳግማዊ አጼ ቴዎዶስዮስ ተጠርቶ ሰኔ 22 ቀን 431 በኤፌሶን ማርያም ቤተ ክርስቲያን በይፋ ተከፈተ። ሊቀ ጳጳስ ሰለስቲን ቀዳማዊ ወክሎ የአሌክሳንደሪያው ቄርሎስ ጉባኤውን ሲመራ ንስጥሮስ ግን ፈቃደኛ አልሆነም።
የአንጾኪያው ዮሐንስ እና የልዑካን ቡድኑ ከመድረሱ በፊት ቄርሎስ እና ደጋፊዎቹ ሂደቱን አካሂደዋል።
2. የንስጥሮስን ውግዘት፡-
የንስጥሮስ ትምህርት መናፍቅ ተብሎ ታውጆ ነበር፣ እናም ከቁስጥንጥንያ ፓትርያርክነታቸውም ተወገዱ። ጉባኤው የክርስቶስን መለኮታዊ እና ሰብአዊ ተፈጥሮዎች አንድነት በማረጋገጥ ማርያም ቴዎቶኮስ መባል እንዳለባት በድጋሚ አረጋግጧል።
3. የአንጾኪያን ልዑካን መምጣት፡-
የአንጾኪያው ዮሐንስ እና ጳጳሳቱ ዘግይተው መጡ እና የተለየ ጉባኤ አደረጉ፣ ቄርሎስን እና ተከታዮቹን አወገዙ። ንጉሠ ነገሥት ቴዎዶስዮስ 2ኛ መጀመሪያ ላይ ቢያቅማሙም በመጨረሻ ግን ከቄርሎስ አቋም ጎን ቆሙ።
4. በንጉሠ ነገሥቱ የተሰጠ ድጋፍ፡-
የምክር ቤቱ ውሳኔዎች በንጉሠ ነገሥቱ ባለሥልጣናት በይፋ እውቅና አግኝተዋል።
ንስጥሮስ በግዞት ወደ ግብጽ ገዳም ተወሰደ፣ ትምህርቱም ታፈነ።
ቁልፍ የአስተምህሮ ውጤቶች
ጉባዔው የሃይፖስታቲክ ህብረትን አስተምህሮ(በአንድ አካል ሁሉት ባህሪ ማለትም መለኮትነት እና ሰውነትን) አፅንቷል፣ እሱም በነገረ ክርስቶስ ውስጥ መሠረታዊ ፅንሰ-ሀሳብ ሆነ።
ንስጥሮስን በይፋ አውግዟል፤ ይህም ከጊዜ በኋላ ከምስራቃዊው ቤተክርስትያን (የኔስቶሪያን ቤተክርስቲያን) ጋር መከፋፈል አስከትሏል።
ጉባዔው የኒቂያን የሃይማኖት መግለጫ አጽንቷል እናም በእሱ ላይ ምንም አይነት ጭማሪ ወይም ለውጥ ውድቅ አድርጓል።
ከጉባዔው ማግስት እና የጉባዔው አስፈላጊነት
የኤፌሶን ጉባኤ በእስክንድርያ እና በአንጾኪያ በነገር ክርስቶስ ትምህርት ቤቶች መካከል ያለውን ልዩነት ጠንክሮ እንዲቀጥል ምክንያት ሆኗል።
የንስጥሮስ መለየት የንስጥሮስን አስተምህሮ በመከተል የምስራቅ ቤተክርስቲያን እንዲመሰረት አደረገ።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦
👉McGuckin, J. A. (2004). Saint Cyril of Alexandria and the Christological Controversy: Its History, Theology, and Texts. St. Vladimir's Seminary Press.
👉Tanner, N. P. (1990). Decrees of the Ecumenical Councils (Vol. 1). Sheed & Ward.
👉Chadwick, H. (1993). The Early Church. Penguin Books.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።”
ሉቃስ 17፥33
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
#እራሳችንን_እንመርምር
የመንፈሳችን ጤንነት እንዴት ነው?
“ባሪያዬ ካሌብ ግን ሌላ መንፈስ ከእርሱ ጋር ስለ ሆነ ፈጽሞም ስለተከተለኝ እርሱ ወደ ገባባት ምድር አገባዋለሁ፤ ዘሩም ይወርሳታል።”
ዘኍልቁ 14፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ታገሡ። እነሆ፥ ገበሬው የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ እስኪቀበል ድረስ እርሱን እየታገሠ የከበረውን የመሬት ፍሬ ይጠብቃል።”
ያዕቆብ 5፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
የጥንት ቤተክርስቲያን ጉባዔዎች
ክፍል-፩
ቤተክርስቲያን በየወቅቱ ለሚደርስባት ውስጣዊ ችግር ማለትም የአስተምህሮ ዝንፈት እና የሐሰት ትምህርትና አስተማሪዎች ሾልኮ መግባት በተደራጀ መልኩ መልስ ስትሰጥ ኖራለች። ምክንያቱንም አንድ ጊዜ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈጽሞ ለተሰጠን ሃይማኖት ጥንቃቄ ስለሚያስፈልግና አንዴ ከተዛነፈ ለመመለስ ስለሚያስቸግር ሳይቃጠል በቅጠል ስትል ኖራለች። ለዚህም ጥሩ ምሳሌ በሐዋርያት ሥራ ላይ ያለችዋ የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን ለተከሰተባት ችግር ምን አይነት መፍትሄ እንደሰጠች በምሳሌነት እንመልከት። ከዚያም የጥንት ቤተክርስቲያን አባቶች ይህን ፈለግ በመከተል የተሳበሰቡበትን ዋና ዋና ጉባኤዎች በተከታታይ ክፍል እንመለከታለን።
የሐዋርያት ሥራዋ ቤተክርስቲያን
ለምን ተሰበሰቡ?
“አንዳንዶችም ከይሁዳ ወረዱና፦ እንደ ሙሴ ሥርዓት ካልተገረዛችሁ ትድኑ ዘንድ አትችሉም ብለው ወንድሞችን ያስተምሩ ነበር።”
ሐዋርያት 15፥1
“ሐዋርያትና ሽማግሌዎችም ስለዚህ ነገር ለመማከር ተሰበሰቡ።”
ሐዋርያት 15፥6
ምን ወሰኑ?
"እንዲህም ጽፈው በእነርሱ እጅ ላኩ። ሐዋርያትና ሽማግሌዎች ወንድሞችም በአንጾኪያና በሶርያ በኪልቅያም ለሚኖሩ ከአሕዛብ ወገን ለሆኑ ወንድሞች ሰላምታ ያቀርባሉ። ያላዘዝናቸው ሰዎች ከእኛ ወጥተው፦ ትገረዙ ዘንድና ሕግን ትጠብቁ ዘንድ ይገባችኋል ብለው ልባችሁን እያወኩ በቃል እንዳናወጡአችሁ ስለ ሰማን፥ ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነፍሳቸውን ከሰጡት ከምንወዳቸው ከበርናባስና ከጳውሎስ ጋር የተመረጡትን ሰዎች ወደ እናንተ እንልክ ዘንድ በአንድ ልብ ሆነን ፈቀድን። ራሳቸውም ደግሞ በቃላቸው ያንኑ ይነግሩአችሁ ዘንድ ይሁዳንና ሲላስን ልከናል። ለጣዖት ከተሠዋ፥ ከደምም፥ ከታነቀም፥ ከዝሙትም ትርቁ ዘንድ ከዚህ ከሚያስፈልገው በቀር ሌላ ሸክም እንዳንጭንባችሁ እኛና መንፈስ ቅዱስ ፈቅደናልና፤ ከዚህም ሁሉ ራሳችሁን ብትጠብቁ በመልካም ትኖራላችሁ። ጤና ይስጣችሁ።"
ሐዋርያት 15፥23-29
የጥንት ቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች እነሆ፦
1. የኒቅያ የመጀመሪያው ጉባኤ (325 ዓ.ም.)
የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት ጥያቄ ያነሳውን የአርዮስን ምንፍቅና ለመፍታት በንጉሠ ነገሥት ቆስጠንጢኖስ ቀዳማዊ የኒቅያ ጉባኤ ተጀመረ።
ቁልፍ ውጤት፦ ጉባኤው የኒቅያን የሃይማኖት መግለጫ አወጣ፣ ኢየሱስም እንደ አብ “አንድ አካል” (ሆሞኡሲዮስ/ "homoousios") መሆኑን በማረጋገጥ አርዮሳዊነት ውድቅ አደረገ።
ጉባዔው ውሳኔ ለመስጠት እስከ ሁለት ወር የፈጀ ሲሆን እስከ 318 ጳጳሳት ተሳትፈውበታል።
2. የቁስጥንጥንያ ጉባኤ (381 ዓ.ም.)
ዓላማው የኒቂያን ጉባዔ ውሳኔ ለማጽናት እና የቀሩትን የአርዮስን ትምህርት ያመጣውን ተፅዕኖዎች ለመፍታት በአፄ ቴዎዶስዮስ ቀዳማዊ የተጠራ ጉባኤ ነበር።
ቁልፍ ውሳኔዎች፡-
የኒቅያን የሃይማኖት መግለጫ አስፋፍቷል። መንፈስ ቅዱስን እንደ መለኮት እና ከአብና ከወልድ ጋር እኩል መሆኑን አውጇል። አርዮሳዊነትን፣ አፖሊናሪያኒዝም እና መቄዶኒያኒዝምን አውግዟል።
ተፅዕኖው፦ የጠነከረ የሥላሴ ሥነ-መለኮት እና የኒቂያ ጉባኤ ውሳኔ አጠናክሯል።
ይቀጥላል...
ምንጭ፦
👉Stevenson, J., & Frend, W. H. C. (2013). A new Eusebius: Documents illustrating the history of the Church to AD 337. SPCK
👉Gonzalez, J. L. (2010). The Story of Christianity: Volume 1, The Early Church to the Reformation. HarperOne.
👉Schaff, P. (1885). History of the Christian Church, Volume III: Nicene and Post-Nicene Christianity. Charles Scribner’s Sons.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር (ያህዌ) ስለ እናንተ ይዋጋል፤ እናንተ ያለባችሁ መታገሥ ብቻ ነው።”
ዘጸአት 14፥14 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥3
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
#መሠረታዊ_አስተምህሮ
ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያንና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በሲመተ "ሐዋርያ" እና "ነቢያ" ላይ የያዙትን አቋም ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር እንዴት ይመለከቱታል? በጨዋነት አሳባችሁን በአስተያየት መስጫው ላይ ያስፍሩ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
#መሠረታዊ_አስተምህሮ
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ስለ ሲመተ-ሐዋርያ እና ሲመተ-ነቢይ ዙርያ በሚስዮንና ሥነ-መለኮት ቦርድ ጥናት ተጠንቶ ታኅሣሥ 2003 ዓ.ም ለቤተክርስቲያኒቱ 18ኛ መደበኛ ጉባዔ የቀረበ ጥናት። ቤተክርስቲያኒቱ ለምን ይህን ሹመት እንደማትቀበልና እንደምታወግዝ ከመጽሐፍ ቅዱስና ከታሪክ አመሳክራ የተነተነችውና ያቀረበቺው ሰፊ ጥናት ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እናንተ በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ፥ አሁን በሕይወት እንኖራለንና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 3፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?
ዮሐንስ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ፦ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤
³² እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው።
³³ እነርሱም መልሰው፦ የአብርሃም ዘር ነን ለአንድም ስንኳ ከቶ ባሪያዎች አልሆንም፤ አንተ፦ አርነት ትወጣላችሁ እንዴት ትላለህ? አሉት።
³⁴ ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው።
³⁵ ባርያም ለዘላለም በቤት አይኖርም፤ ልጁ ለዘላለም ይኖራል።
³⁶ እንግዲህ ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ በእውነት አርነት ትወጣላችሁ።
³⁷ የአብርሃም ዘር መሆናችሁንስ አውቃለሁ ነገር ግን ቃሌ በእናንተ አይኖርምና ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ።
³⁸ እኔ በአባቴ ዘንድ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ደግሞ በአባታችሁ ዘንድ ያያችሁትን ታደርጋላችሁ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔርም፦ እኔ መልካምነቴን ሁሉ በፊትህ አሳልፋለሁ፤ የእግዚአብሔርንም ስም በፊትህ አውጃለሁ፤ ይቅርም የምለውን ይቅር እላለሁ፥ የምምረውንም እምራለሁ አለ።”
ዘጸአት 33፥19
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል፤ የምሻውን ያደርጋል የላክሁትንም ይፈጽማል እንጂ ወደ እኔ በከንቱ አይመለስም።”
ኢሳይያስ 55፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት
#ቆሮንቶስ
ቆሮንቶስ የግሪክ ከተማ ናት፤ ከአቴናም 75 ኪ.ሜ. ያህል ትርቃለች። አቀማመጥዋ በሁለቱ የግሪክ አውራጃዎች በመቄዶንያና በአካይያ መካከል በሚገኘው ልሳነ ምድር ላይ ነበረ። ጳውሎስ በነበረበት ዘመን 250,000 ሰዎችና 400,000 ባሪያዎች በቆሮንቶስ ይኖሩ እንደ ነበር ይገመታል፡፡ ቆሮንቶስ ከሌሎቹ የግሪክ ከተሞች ይልቅ በአንዳንድ ነገሮች በልጣ ትታይ ነበር፤ ምክንያቶቹም የሚከተሉት ናቸው፦
1) ንግዷ፤ ከተማዋ በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር አጠገብ የምትገኝ የመንገደኞች መተላለፊያ የነጋዴዎች መናኸሪያ ነበረች፡፡ ከተማይቱ ሁለት ወደቦች አሏት፤ እነዚህም:-
ሀ) በስተ ምሥራቅ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በሰሮኖ ባሕረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የክንክራኦስ ወደብ፣
ለ) በስተ ምዕራብ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በቆሮንቶስ ባህረ ሰላጤ ላይ የምትገኘው የሌቻዶም ወደብ ናቸው፡፡
ልዩ ልዩ ዕቃዎች በቆሮንቶስ ልሳነ ምድር በዳዮልኮስ ጐዳና ላይ በትናንሽ መርከቦች ሞልተው እየተሳቡ ከወዲህ ማዶ ወዚያኛው ይሽጋገሩ ነበር፡፡ በትልልቅ መርከቦች የተጫኑ ዕቃዎችም በፉርጎ ሆነው እንደዚሁ ከአንዱ ዳር ወደ ሌላው ዳር ይጓጓዙ ነበር፡፡ በዚህ ዓይነት ሸቀጣ ሸቀጦች ከኢጣሊያ ከእስፓኝ ወደ ምዕራብ፣ እንዲሁም ከትንሹ እስያ፣ ከፊንቄና ከግብፅ ወደ ምሥራቁ ዓለም የሚጓጓዙበት በቆሮንቶስ ከተማ በኩል አድርገው ነበር።
2) ባህሏ፤ ቆሮንቶስ እንደ አቴንስ ሁሉ እስከዚህ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ባይኖራትም በሠለጠነው የግሪክ ባህል የመጠቀች ነበረች፤ ሕዝብዋም ለግሪክ ፍልስፍና ጥልቅ ፍቅር ስለነበረው ለጥበብ ከፍተኛ ወጪ ያደርግ ነበር።
3) ሃይማኖቷ፤ የቆሮንቶስ ከተማ በትንሹ አሥራ ሁለት ቤተ ጣዖቶች ነበሩባት፤ ጳውሎስ በነበረበት ዘመን እነዚህ ሁሉ ቤተ ጣዖቶች ለአገልግሎት ክፍት ይሁኑ አይሁኑ እስከዚህ የሚታወቅ ነገር የለም:: ከእነዚህ ቤተ ጣዖቶች መካከል አንዱ በግሪክ የተረታ ተረት ታሪክ ውስጥ የፍቅር አምላክ ተብላ የምትታወቀው የአፍሮዲጡስ ቤተ ጣዖት ሲሆን በቤተ ጣዖቱም ውስጥ ከሥርዓት አምልኮው ጋር በተያያዘ የዝሙት ሥራ መፈጸም የተለመደ ነበር፡፡ ከትያትር ቤቱ ሕንፃ በስተ ሰሜን ግማሽ ኪሎ ሜትር ያህል ርቆ የፈውስ አምላክ እያሉ ለሚጠሩት ለአስክሌፕደስ የተሠራ ቤተ ጣዖት አለ፡፡ በከተማይ ቱም መሃልም በ6ኛው ምዕተ ዓመት ቅድመ ልደት ክርስቶስ ላይ የተሠራ የአፖሎ ቤተ ጣዖት ቆሞአል፡፡ አይሁድ በከተማይቱ ውስጥ የሠሩትም ምኵራብ ነበር፡፡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ጽሑፍ የተቀረጸበት የመስኮት ጒበን በአሁኑ ጊዜ ተገኝቶ በጥንቲቱ የቆሮንቶስ ከተማ ቤተ መዘክር በክብር ተቀምጦአል፡፡
4) ምግባረ ብልሹነትዋ፤ ቆሮንቶስ እንደማንኛውም ትልቅ የንግድ ከተማ ሁሉ ለሥነ ምግባር ብልሹነት በሰፊው የተጋለጠች ነበረች፡፡ የአፍሮዲጡስ የጣዖት አምልኮ በሃይማኖት ስም ዝሙት እንዲ ስፋፋ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጎአል፡፡ በአንድ ዘመንማ ለዚሁ ሥራ የተለዩ አንድ ሺህ ዘማውያት በቤተ ጣዖቱ ውስጥ ያገለግሉ ነበር፡፡ ቆሮንቶስ ምግባረ ብልሹነትዋ የታወቀች ከመሆንዋ የተነሣ በግሪኩ የሰዋሰው ግሥ “መቆታንተስ” ማለት “በአሳፋሪ የዝሙት ተግባር መሰማራት” ማለት እንደሆነ የተቍጠረበት ወቅት ነበር፡፡ እንግዲህ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የነበረችው የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያንም ብዙ መከራ ችግር ውስጥ እንደምትገባ መገመት አያዳግትም፡፡
ቆሮንቶስ ጥንታዊት የግሪክ ከተማ ስትሆን፣ በጳውሎስ ዘመን በብዙ መንገድ ታዋቂ የነበረች የግሪክ መዲና ናት:: በአሁን ዘመን እንዳሉት ሀብታም ከተሞች ቆሮንቶስ በዕውቀት የታበየች፣ በሀብት የበለጠገችና በኢግብረገባዊ ሕይወት የረከሰች ነበረች፡፡ ማንኛውም ዐይነት ኀጢአት በዚህች በወጣላት ዓለማዊ ከተማ ተስፋፋ፡፡
ከጵርስቅላና ከአቂላ (1ቆሮ 16፥19) እንዲሁም ከራሱ ሐዋርያዊ ቡድን (ሐሥ 18፥5) ጋር በመጣመር፤ ሐዋርያው ጳውሎስ በሁለተኛው የወንጌል ጉዞው (ሐሥ 18፥1-17) ዐሥራ ስምንት ወር በቆሮንቶስ ከተማ ለአገልግሎት በቈየበት ጊዜ የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን መሠረተ፡፡ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ምእመናን ጥቂቶቹ አይሁድ ሲሆኑ፣ በአብዛኛው ጣዖት አምላኪዎች የነበሩ አሕዛብ ናቸው፡፡
ምንጭ፦ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር፤ ገጽ 1734፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 99፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1776
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ።”
ቆላስይስ 2፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 841
#እራሳችንን_እንመርምር
በሐዋርያት ትምህርት እየኖርን ነው? ለመሆኑ የሐዋርያት ትምህርት ምንድነው?
“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
ሐዋርያት 2፥42
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
