ቅዱሳት መጻሕፍት
Open in Telegram
በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures
Show more7 842
Subscribers
+1024 hours
+417 days
+14330 days
Posts Archive
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥5
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
ለዕረፍት ተጠርተናል
ጌታ በተለያየ በሚገባን መንገድ “ዕረፍት” እንዲህ ነው ብሎ ያሳየናል፣ይጠቁመናል፣ያቀምሰናል፡፡ቢሆንም ሙሉ የሆነ ዕረፍት የሚመጣው፣ በትጋት በፊቱ በመሆን የጌታ ጸጋ በሕይወታችን እየጨመረ ሲመጣ እንደ ሆነ ልብ ይሏል፡፡
ጌታችን የዕረፍት አምላክ ነውና ሊያሳርፈን ይፈልጋል፡፡ለእኛ ያለው ግልጽ የሆነው የልብ ሐሳቡም እንዲህ የሚል ነው፡-
“እኔ ሕይወት እንዲሆንላችሁ እንዲበዛላችሁ መጣሁ” (ዮሐንስ 10፡10)
ነገር ግን የብዙዎቻችን አኗኗር ሲታይ የዚህን አስደናቂ የተስፋ ቃል ምንነትና በውስጡ የያዘውን በረከት በሚገባ የተረዳነው አይመስልም፡፡ ዋናው ችግራችንም ልባችን ስቷል፡፡ ልባችን መሳቱን የሚያረጋግጥልን ደግሞ በማያሳርፉ ነገሮች ለማረፍ ሲቧጥጥና ሲያልም ማደሩ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ስለ እስራኤላውያን የምድረ በዳ ሕይወት ሲናገር “ሁል ጊዜ ልባቸው ይስታል፤ እነርሱም መንገዴን አላወቁም አልሁ፡፡ወደ ዕረፍቴም እንዳይገቡ በቁጣዬ ማልሁ” (መዝ 95 ፡10-11) ይላል፡፡ አዎ ልባችን ስቷል እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? የጌታ መንፈስ በተለያየ መንገድ“ ዕረፍት ይህች ናት የደከመውንም አሳርፉ ይህችም ማረፊያ ናት አላቸው እነርሱ መስማትን እንቢ አሉ” (ኢሳ 28፡12) እንደሚል ሆኖብናል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል “ይሳኮር አጥንተ ብርቱ አህያ ነው፤በበጎች ጉረኖም መካከል ያርፋል፡፡ዕረፍትም መልካም መሆንዋን አየ” (ዘፍጥረት 49፡14-15) ይለናል፡፡ የውስጣዊ ዕረፍት መልካምነት ምንም አያጠያይቅም፤ በሁሉም መልኩ ይጠቅማል፡፡መንፈሳችን ከእግዚአብሔር ለመስማት ይመቻቻል፤ የአእምሮአችንን የመሥራት እና የፈጠራ ችሎታ ይጨምረዋል፤ የእግዚአብሔርን ሥራ በቅጡ እንድሠራ ያስችለናል፤ ማኅበራዊ ሕይወታችንን እንዲስተካከል አመቺ ሁኔታን ይፈጥራል፤ዕረፍቱ በራሱ ለሰዎች የሚታይ ጠንካራ መልዕክት ነው (በተለይ ለማያምኑ ሰዎች) ፡፡
ከጌታቸው የተማሩ እና ያረፉ ሰዎች ከሕይወት ምልልሳቸው ይታወቃሉ፡፡ሲቅበጠበጡና ሲባዝኑ አይታዩም፡፡እንዳውም ሕይወታቸው ከሩቅ ይናገራል፡፡በጌታቸው ያረፉ ሰዎች በቃሉ ጉልበት ውስጣቸው ስለተለወጠ ከማንኛውም ቀንበር ነጻ ናቸው፡፡ቅድሚያ የሚሰጡትን የሚያውቁ ሲሆን፣ምርጫዎቻቸውም ውሱን ይሆናሉ፡፡መረጋጋትና ሰላም የሚታይባቸው እና የምሥጋና ሕይወት ያላቸው (የማይነጫነጩ፣ የማያጉረመርሙ) ስለሆነ፣የምድር ጨው ወይም የዓለም ብርሃን ናቸው፡፡ሰው እነርሱን አይቶ ልቡ ይነካል፡፡ሰው እነርሱን አይቶ የተለወጡበትን ምንጭ ያስተውላል፡፡ሰው እነርሱን አይቶ ወደ እዚህ ድንቅ የዕረፍት አምላክም ይመጣል፡፡
ስለዚህ ከመባከን ወጥተን በዕረፍት ለመመላለስ እና የዕረፍትን በረከቶች ለማፈስ ምን እናድርግ የሚለው ላይ ጥቂት ብዬ ጽሑፌን ልደምድም፡፡
#ነጥብ_አንድ ፡-በትጋት የጌታን ቃል እያሰላሰልንና እያጠናን ብሎም በጸጋው ዙፋን ፊት በቂ ጊዜን በጸሎት ስናሳልፍ፣ የጌታን ድምጽ ለመስማት ዕድል ይኖረናል፡፡እምነት ከመስማት (ሮሜ 10፡17) ስለሆነ፣የእግዚአብሔርን ድምፅ ስንሰማ ደግሞ እምነታችን በሚገባ ይጠነክራል፡፡ ቃሉ “የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል” (ምሳ 1፡33) ይላልና፣ ከመቅበዝበዝ፣ከመባከንና ከሥጋት እንድናለን፡፡
#ነጥብ_ሁለት፡-ጌታን በሚገባ ማወቃችንና የእሱ በሕይወታችን እየተገለጠ መሄዱ፣ዕረፍታችንን እየጨመረው ይሄዳል፡፡በማቴዎስ 11፡25-30 ያለው ክፍል ይህንን ሐሳብ በሚገባ ያብራራዋልና፣ነጥብ አንድ ላይ ያለውንም ሐሳብ ይደግፈዋልና ልጥቀሰው፡፡ እንዲህ ይላል፡-
‹‹በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ። አባት ሆይ የሰማይና የምድር ጌታ፤ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግንሃለሁ፤አዎን፤አባት ሆይ፤ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና። ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፤ከወልድም በቀር ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር አብን የሚያውቅ የለም።እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፣ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ።ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፤እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፣ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና››
ይህንን ቃል ብዙ ጊዜ ያነበብነው ቢሆንም፣በተግባር በሕይወታችን ያልተተረጐመ ቃል ነው ብዬ አምናለሁ፡፡የእርሱ ለእኛ መገለጥ እና የነፍሳችን ዕረፍት ማግኘት ትልቅ ትስስር እንዳለው ማየት ይቻላል፡፡ ማለትም ወደ እርሱ የመቅረባችንና የመማራችን መጠን፣ለእኛ የመገለጡን መጠንና የዕረፍታችንን መጠን ይወስነዋል፡፡ለዚህ ነው “ከኔም ተማሩ ለነፍሳችሁ ዕረፍትን ታገኛላችሁ” ብሎ በትሕትና የሚጋብዘን፡፡ቃሉ “ለአሕዛብ የታወቀው ምሥጢር እንደ ተገለጠ መጠን ሊያበረታችሁ ለሚችለው” (ሮሜ 16፡26) የሚለውም ለዚህ ነው፤በተገለጠልን መጠን ዕረፍቱ እየበዛልን፣እየበረታን እንሄዳለንና፡፡ጌታ ሆይ፣የማሳረፍህን ብቃትና ችሎታ እንድናየው ዓይናችህን ግለጥልን!!
ምንጭ:- bekedesa7.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የተስፋን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ፤”
ዕብራውያን 10፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
ብዙ ተስፋ
ተስፋ የሚለው ቃል ሲጠራ በራሱ ተስፋ ይለመልማል። ልብ በሐሤት ይሞላል። የሰው እግር በድል የሚራመደው ልቡ በተስፋ ሲሞላ ነው። ተስፋ ከሌለ እግር ሽባ ይሆናል። ተስፋ ግን ሽባውን እግር የሚያረታ፥ ከተጠበቀው በላይ የሚያራምድ ነው። ተስፋ ያጣ ሰው ምንም ሳይሆን ብዙ የሆነ ይመስለዋል። ገና ቀን ሳለ ሌሊት መስሎት ይተክዛል። ትጥቁና ስንቁ እያለ ጦርነቱን በሽንፈት /በበቃኝ/ ይደመድማል። ተስፋ መዳረሻ ነው። ከምሳ ሰዓት በኋላ እስከ እራት ያለው ጊዜ ረጅም ነው። ሠርክ ላይ ትንሽ ምግብ ይቀመሳል። ያ መክሰስ ወይም መዳረሻ ነው። ተስፋም እንዲሁ ነው። እግዚአብሔር ያሰበልን ነገር ላይ ለመድረስ መዳረሻ /መቈያ/ ነው።
ተስፋ በመጀመሪያ በፅንሰቱ ኋላም በልደቱ ደስ ያሰኛል። ተስፋ ያደረጉት ነገር ሲፈጸም ልብ ሙሉ ይሆናል፤ መኖርም ምክንያታዊ ይመስላል። እግዚአብሔር የተስፋ አምላክ፥ የተስፋ መሠረት፥ የተስፋ ፍጻሜ ነው። እግዚአብሔር ተስፋን የሚሰጠው ከራሱ የፍቅርና የቸርነት ባሕርይ በመነሣት ነው። ይህ ሁለት ነገሮችን ያስተምረናል።
1. ተስፋን የሰጠን በራሱ ፈቃድ ስለ ሆነ ለመፈጸም አይቸገርም።
2. የተስፋ መነሻ ፍቅር ነው፤ ፍቅር ሲኖረን ቸሮች ብቻ ሳይሆን ባለተስፋም እንሆናለን።
ተስፋን በሚመለከት የሰው ልጅ አመለካከት ከዚህ ተቃራኒ ይመስላል። ይኸውም፡- ሰው ተስፋ የሚሰጠው በስሜት፥ በጉባኤ ሞቅታ ሊሆን ይችላል፤ ሲረጋጋና አጢኖ ሲያስበው ይቆማል። እግዚአብሔር ግን በመጥራቱና በመስጠቱ የማይጸጸት አምላክ ነው። የሰው ልጅ ብዙ ጊዜ ከጥላቻና ከመሰልቸት ጋር ስለሚሆን ተስፋ ማድረግና ተስፋ መስጠት ያቅተዋል። እግዚአብሔር ግን ሳይለወጥና ሳይናወጥ ፍቅር ሆኖ ይኖራል። የእግዚአብሔር ተስፋ ጨቅጫቃ ልጆችን ማባረሪያ አይደለም፤ የፍቅሩ መግለጫ ነው።
የእግዚአብሔር ቃል ትንቢትን፥ ተግሣጽን ብቻ ሳይሆን ተስፋንም የተሞላ ነው። ተስፋ የቃሉ አካል ነው። ተስፋ ክርስቲያኖች የሚራመዱበት ኀይል ነው። የእስትንፋስን ያህል ሊቋረጥ የማይገባው የመጀመሪያው ነገር ቢኖር ተስፋ ነው። ተስፋ ከሌለ ማቀድ፥ ማገልገል፥ … ሊኖር አይችልም፤ ወደ ትልቅ ፈተና ውስጥ የምንገባው ተስፋችን የተነቃነቀ ቀን ነው።
ስለ ተስፋ ይህን ያህል ያልነው ከትንቢተ ሐጌ ምዕራፍ 1፥9 ላይ፥ “እናንተ ብዙ ነገርን ተስፋ አደረጋችሁ፥ እነሆም፥ ጥቂት ሆነ፤” የሚለውን ቃል ለማንሣት ነው፤ ሰዎች ተስፋ ይሰጡናል። የሰዎች ተስፋ ግን ርግጠኛነት የሌለው፥ ሊሆንም ላይሆንም የሚችል እንጥልጥል በረከት ነው። እንዲህ መሆኑንም በጥርጣሬ እንጂ በልበ ሙሉነት አንይዘውም። የእግዚአብሔር ተስፋ ግን ርግጥና ጽኑ ነው። እግዚአብሔር ተስፋ ከሰጠን የሆነ ያህል ነው፤ ርግጠኛም ነው። በራሳችንም ብዙ ተስፋ እናደርጋለን። ከፖለቲካው ዙረት፥ ከአባቶች ጉባኤ፥ ከክርስቲያኖች አንድነት፥ ከአገልጋዮች መቀራረብ፥ ከትዳር ጓደኛችን፥ ከልጆቻችን፥ ከጀመርነው ዕቅድ፥ … የምንጠብቀው ነገር አለ። እግዚአብሔር ግን ለእነዚያ ከምርኮ ተመላሾች፥ “እናንተ ብዙ ነገርን ተስፋ አደረጋችሁ፤ እነሆም ጥቂት ሆነ” አላቸው (ሐጌ 1፥9)።
ብዙ ተስፋ አድርጎ ጥቂት እንኳ አለማግኘት የጨነገፈ ምኞት ነው። እግዚአብሔር ለምን እንዲህ አለ? በቃሉ ውስጥ “በውኑ ይህ ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን?” ተብሎ ተጽፏል (ሐጌ 1፥)። የተሸለሙ ቤቶች መሥራት፥ ስለ ተሻለ ኑሮ ማሰብ፥ እግዚአብሔርን አያስከፋውም። ነገር ግን ሁሉም ነገር ውብ የሚሆነው በጊዜው ነው። ጊዜው የእግዚአብሔር ቤት የፈረሰበት፥ ቅጥሩ የወደቀበት፥ መሥዋዕት የማይቀርብበት፥ ንጹሕ አምልኮ የሌለበት ነበር። በዚህ ጊዜ በተሸለሙ ቤቶች ውስጥ መኖር፥ ስለ ጌጠኛ ዕቃዎች ማሰብ ተገቢ አይደለም። በዚህ ሁኔታ ብዙ ተስፋ ማድረግ፥ ምርቱን ዕፍኝ የማይሞላ ያደርገዋል።
በየአብያተ ክርስቲያናቱ ያለው የልማት ዕቅድ ድንቅ ነው። ስለ ትልልቅ ተቋማት ማሰብ፥ ጫና በሚያሳድር የተፈሪነት ቦታ መቀመጥ፥ የክርስቲያን መሪዎች ጥማት እየሆነ መጥቷል። ክርስቲያኖችም እኛ ቦታውን ብንይዘው ምድሪቱ ትባረካለች በማለት ሥጋዊ ዝግጅታቸውን እያጧጧፉት ነው። የእግዚአብሔር ቤት ግን ፈርሷል። ንጹሕ አምልኮት፥ እግዚአብሔርን የሚያከብር መሥዋዕት ጠፍቷል። ሕዝቡ ቅር እንዳይለው የልማዱ ዝማሬና ቅዳሴ ይቀርብለታል እንጂ በንስሓና በይቅርታ መቅረብ አልቻልንም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ብዙ ተስፋዎችና ዕቅዶች በዝተዋል። እግዚአብሔር ከሌለበት ዕቅድ ሁሉ ከንቱ መሆኑን ግን አላስተዋልንም። የቤተ ክርስቲያን ግርማዋ ቅድስና እንጂ ሥጋዊ ሥልጣን አይደለም። የሚያስፈልገንም ምድራዊ በረከት ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ይሁንታ ነው። - “ብዙ ተስፋ”
ምንጭ :- www.chorra.net
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አምላክህ እግዚአብሔር የእጅህን ሥራ ሁሉ ባርኮልሃልና፤ በዚህ በታላቅ ምድረ በዳ መሄድህን አውቆአል፤ በዚህ አርባ ዓመት ውስጥ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነበረ፥ አንዳችም አላጣህም።”
ዘዳግም 2፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
አንተ የምትተኛ ንቃ! ኤፌ.5፡14
እንቅልፍ አራት ደረጃዎች እንዳሉት ሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ እነዚህን ደረጃዎች ከመንፈሳዊ እንቅልፍ አንጻር በማየት የቤተክርስቲያን ሁኔታ ለማየት እንሞክራለን፡፡
#ደረጃ_1፡- አይን መጨፈን የሚጀመርበት- ንቁ ሆነን ስናከናውናቸው የነበሩ ነገሮችን ማከናወን የምናቆምበት ወቅት ነው፡፡ ይህ ጊዜ በቀላሉ ለመንቃት የሚቻልበት ደረጃ የመሆኑን ያህል በፍጥነት ወደ ቀጣዩ እንቅልፍ ደረጃ የሚታለፍበት በመሆኑ ብዙ በዚህ ደረጃ የመቆየት እድል የለውም፡፡
ይህን ከመንፈሳዊ እንቅልፍ አንጻር ስናየው በዚህ ደረጃ ላይ የሚገኝ አማኝ ቀደም ሲል በንቃት የሚጸልየውን ጸሎት በፍቅር ለእግዚአብሄር የሚያቀርበውን አምልኮ እንዲሁም በመሰጠት ያነበው የነበረውን የእግዚአብሄር ቃል ለማንበብ ሃይል የሚያጣበት እና በሃጢያት ላይ ማመቻመች የሚጀምርበት ደረጃ ነው፡፡
"የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?" (ገላ.3፡1)
#ደረጃ_2፡- ቀላል እንቅልፍ – በዚህ ደረጃ አይንን ከመጨፈን ባለፈ ወደ ቀላል እንቅልፍ የሚገባበት ደረጃ ሲሆን በዚህም የልብ ምት እና ሰውነት ሙቀት የሚቀንስበት ወቅት ሲሆን በዚህም ሰውነታችን ወደ ጥልቅ እንቅልፍ ለመግባት ዝግጅት የሚያደርግበት ወቅት ነው፡፡
በዚህ የመንፈሳዊ የእንቅልፍ ደረጃ ላይ ልባችን ለክርስቶስ የነበረውን መቃጠል (ፍቅር) የሚያጣበት እና ያለን መንፈሳዊ መነቃቃት የሚቀዘቅዝበት ደረጃ ነው፡፡
"…የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና። እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፡፡" (ራእ.2፡4-5)
#ደረጃ_3_እና_4፡- ከባድ እንቅልፍ- በዚህ ወቅት ሰውነታችን ጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ የሚገባበት በመሆኑ በዙሪችን እየተከናወኑ ያሉ ነገሮችን ማስተዋል አንችልም፡፡ ንቁ በሆንበት ጊዜ የሚታዘዙን ጡንቻዎቻችን ፓራላይዝድ የሚሆኑበት የእንቅልፍ ደረጃ ነው፡፡
በዚህ የመንፈሳዊ የእንቅልፍ ደረጃ ላይ ከመንፈሳዊ አለም ያለን ቁርኝት የሚቋረጥበት እና ለመንፈሳዊ ነገር ባዳ የምንሆንበት ይልቁንም ስንጸየፋቸው የነበሩ አለማዊ ልምምዶች ምንም እንዳለሆኑ ተቆጥረው በቤተ ክርስቲያን ስፍራ የሚይዙበት ፣ ከአለም ጋር መዳቀልና መቀላቀል የተለመደ የሚሆንበት ደረጃ ነው፡፡
ወገኞች ሆይ በየትኛውም የመንፈሳዊ የእንቅልፍ ደረጃ ላይ እንገኝ ያው እንቅልፍ ላይ በመሆናችን እንንቃ እንመለስ!
"ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤" (ሮሜ.13፡11)
ምንጭ :- virtuousinchristministry
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አቤቱ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ እነሆ፥ አንተ ሰማይንና ምድርን በታላቅ ኃይልህና በተዘረጋች ክንድህ ፈጥረሃል፥ ከአንተም የሚያቅት ነገር የለም።”
ኤርምያስ 32፥17
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
መንፈሳዊ ዲሲፕሊንና በረከቱ
ጽሑፌ የሚያተኩረው ምሳ 2፡1-2 ላይ ሲሆን እናንተ ጊዜ ሲኖራችሁ ሙሉ ምእራፉን በቂ ጊዜ ሰጥታችሁ አጥኑት፡፡በዚህ ምእራፍ ላይ ምሳ 2፡6 እንደ መግቢያ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል ብዬ አስባለሁ፡፡ቃሉ አንዲህ ይነበባል፡- ‹‹እግዚአብሄር ጥበብን ይሰጣልና ከአፉም እውቀትና ማስተዋል ይወጣሉ›› ከዚህ ቃል ጋር ኢሳ 55፡10-11 ተመሳሳይነት አለውና ያንቡት፡፡እጅግ መልካም የሆነ የተስፋ ቃል ነው ነገር ግን መጠየቅ ያለብን እንዴት ነው ጥበብንና ማስተዋልን የምንቀበለው የሚለውን ነው፡፡ ለኔ መንገዶቹ በጥቅሉ ሶስት ይመስሉኛል፡-
👉ከቃሉ ጋር ጠበቅ ያለ ህብረትና ግንኙነት ሲኖረን
👉የጌታን ፊት በጸሎት አጥብቀን ስንፈልግ
👉ቃሉን በህይወታችን በተግባር ስንፈጽም
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትን ሶስት መንገዶች በሚገባ ደጋግመን ስናደርግ መንፈሳዊ ማስተዋላችንና መረዳታችን እየጨመረ ስለሚሄድ ወደ ህይወታችን የሚመጣው እድገትና ለውጥ ቀላል አይሆንም፡፡
ምሳ 2፡1-4 ላይ ቃሉ በህይወታችን መውሰድ ስለሚገባን ወሳኝ እርምጃዎችና የምንከፍላቸውን ዋጋዎች ያሳየናል፡፡እነዚህንም በዝርዝር አሰቀምጫቸዋለሁ፡-
👉ቃሉን ብትቀበል
👉ጆሮህ ጥበብን ብታደምጥ
👉ልብህን ወደ ማስተዋል ብታዘነብል
👉በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት
👉ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት
👉ለማስተዋል ድምጽህን ብታነሳ
👉እንደ ብር ብትፈላልጋት
👉እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት
እነዚህ ከላ ያሉት ስምንት ትእዛዞች በሁለት ሊጠቃለሉ ይችላሉ፡-
1ኛ፡-ከቃሉ ጋር የጠበቀ ቁርኝትና ጥናት
2ኛ፡-ከቃል ጥናቱ ጋር አብሮ የሚሄድ የጠበቀ ጸሎት
የእግዚአብሄር ቃል መርህ እንደሚያስተምረን ፡-ትእዛዝ -------------------------›በረከት
የእግዚአብሄር ቃል ትእዛዝንና በረከትን አጣምሮ የያዘ ነው፤ስለዚህ ትእዛዞቹን ሳናደርግ የቃሉ በረከት ወደ ህይወታችን አይመጣም፡፡ከላይ ያሉትን ስምንት ተግባሮች በህይወታችን ስንለማመድ ወደ ህይወታችን የሚመጡትን በረከቶች እንይ፡-
በዚያን ጊዜ እግዚአብሄርን መፍራት ታውቃለህ
የአምላክህን እውቀት ታገኛለህ/አምላክን በግል በሚገባ ታውቀዋለህ(በእንግሊዝኛው ‹‹you will gain knowledge of God>>)
መለኮታዊ ጥበቃው በህይወትህ ይበዛል
ነፍስህ በመንፈሳዊ ደስታ ትጥለቀለቃለች
ጽድቅንና ፍርድን መልካም መንገድን ታስተውላለህ (discernment)
በደጋግ ሰዎች መንገድ ትሄዳለህ(success)
በተግባር ደረጃ የቃሉ ብርሀን በህይወታችን ሲበዛና እንደ ቃሉ ስንኖር ከሶስት ትልልቅ ጥፋቶች እንድናለን፡-
1ኛ፡-ከክፉ መንገድ እናመልጣለን (ወደ ስድስት ጥፋቶች ከቁጥር 12 እስከ 15 ተዘርዝረዋል)
2ኛ፡-በቀጥታ ከዝሙት (sexual sins) እና ከሚያመጣብን ጥፋት እንድናለን
3ኛ፡-ክፉ ከሆነውና ወደ ጥፋት ከሚወስደው የአለም አሰራር እናመልጣለን
ስለዚህ ለቃሉ ያልተከፋፈለ ልብን እንስጥ፤ ፊቱን ሳናሰልስ እንፈልግ፤ አድርጉ የሚለንም ለማድረግ እንጨክን !
ምንጭ :- belacheb6.blogspot.com
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እንደ ዛሬው ቀን በሥርዓቱ ትሄዱ ዘንድ፥ ትእዛዙንም ትጠብቁ ዘንድ፥ ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ጋር ልባችሁ ፍጹም ይሁን።”
1ኛ ነገሥት 8፥61
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
#እራሳችንን_እንመርምር
“እናንተ ስሜን የምታቃልሉ ካህናት ሆይ፥ ልጅ አባቱን፥ ባሪያም ጌታውን ያከብራል፤ እኔስ አባት ከሆንሁ ክብሬ ወዴት አለ? ጌታስ ከሆንሁ መፈራቴ ወዴት አለ? ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። እናንተም፦ ስምህን ያቃለልን በምንድር ነው? ብላችኋል።”
ሚልክያስ 1፥6
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“የላከኝም ከእኔ ጋር ነው፤ እኔ ደስ የሚያሰኘውን ዘወትር አደርጋለሁና አብ ብቻዬን አይተወኝም አላቸው።”
ዮሐንስ 8፥29
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ዛፍ ቢቈረጥ ደግሞ ያቈጠቍጥ ዘንድ፥ ቅርንጫፉም እንዳያልቅ ተስፋ አለው።”
ኢዮብ 14፥7
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
የቀጠለ...
እውነተኛ አምልኮተ ሕይወት
ንጉሥ ዳዊት ይህንን ሲል ነፍሱ ተጨማሪ ነገር ሳትፈልግ ቀርታ አልነበረም፤ ነገር ግን የነፍሱን የውስጥ ጩኸት ዝም ማሰኘት ስለቻለ ነው እንጂ፡፡ በቁጥር 2 ላይ “ነፍሴን አሳረፍኳት” በማለት ይናገራል፡፡ እንደው ቆም ብለን ብንጠይቅ፡- ዳዊት ነፍሱን ያሳረፋት ከምን ነበር? ከብልጥግናና ክብር፣ በአጠቃላይም እግዚአብሔር ከሌለበት የተጨማሪ ነገሮች ፍለጋ … ወዘተ ነበር፡፡ ነፍሱ እነዚህን ነገሮች አጥብቃ ትፈልግ እንጂ እርሱ ግን በጭራሽ አልፈቀደላትም፤ እንደውም የነፍሱን ፍቃድ ዝም ማሰኘትን ነበር የመረጠው፡፡
ዘማሪው ነፍሱን እንዴት አድርጎ ዝም እንዳሰኛት በምሳሌ ሲያስረዳ፣ ለእናቱ ጡት ጽኑ የሆነ ፍቅር ያለው ሕፃን የሚወደውን ጡት ትቶ በእናቱ ጭን ላይ ዐርፎ እንደሚቀመጥ ሁሉ፣ ነፍሱ በውስጡ ጸጥ ብላ የተቀመጠች መሆኑን ይገልጻል፡፡ ዳዊት በምንም ዐይነት ሁኔታ ለነፍሱ ፈቃዷን እንድታደርግ ዕድል እንደማይሰጣት ይናገራል፡፡
ዛሬ ባለን ነገር ረክተን ብንኖርና ልባችንን ከቁሳቁስ ይልቅ እግዚአብሔር ላይ ብናሳርፍ፣ ምን ያህል እርሱን ደስ ማሰኘት በቻልን ነበር?! ነገር ግን ዛሬ ከጌታ ይልቅ ልባችን ምንጥቅ የሚልለት ነገር ከልክ በላይ መብዛቱ እጅግ የሚያስገርም ነው፡፡ አንዳንዴማ ጌታ ትዝ የሚለን በዕለተ ሰንበት ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመሄድ ስንነሣ ብቻ ነው፡፡ በሌላው ቀን በጌታ አልረካ ያለው ልባችን በቀንና በሌሊት ሲንቀዋለል የሚከርመው አላፊና ጠፊ የሆነውን ቁሳቁስ በመፈለግ ላይ ነው፡፡ በጌታ ላይ ልባችን ይረፍ፤ ሌላውን ሁሉ ትተን ባለን ነገር እንደሰትና እንርካ፡፡ ዘማሪው እንዳለው ዛሬም እኛ ነፍሳችንን እናሳርፋት፡፡ የጌታን እንጂ የነፍሳችንን ፍቃድ ለመፈጸም አንድከም፡፡ አሜን ይሁንልን!
ጌታን በመታመን መኖር
እውነተኛ የአምልኮ ሕይወት ያለው ሰው ሁልጊዜ ኑሮው በእምነት ነው፡፡ ሕይወቱ ሰልፍና ውጣ ውረድ የበዛበት ቢሆንም እንኳን፣ በጌታው ላይ ያለው እምነቱ ፈጽሞ አይላላም፡፡ ከጌታው ጋር መልካም የአምልኮ ሕይወት ያለው ዘማሪው በዚህ ክፍል ላይ የሚናገረው፣ “ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እስራኤል ሁሉ በእግዚአብሔር ይታመን” በማለት ነው፡፡ በጌታው የሚታመን ሰው ጌታውን ከሁሉ አብልጦ የሚወድድ ነው፡፡ በጌታው በመታመኑም ነፍሱ ከክስረት ይልቅ ወደ መንፈሳዊ ብልጽግና ትገባለች፡፡ ስለዚህም የተለማመደውን ይህንን መለኮታዊ በረከት ሌሎችም ይካፈሉት ዘንድ መግቢያ በሩ በጌታ ላይ መታመን እንደ ሆነ እየተናገረ ይጋብዛቸዋል፡፡
ጻድቅ ሕይወቱ ብርቱ ውጊያ የበዛበት ቢሆንም፣ ዘወትር በጌታው እየታመነ ወደ ፊት መገስገሱን አያቆምም፡፡ በእምነት የጌታውን ፊት እየተመለከተ በየዕለቱ ማለቂያ ከማይገኝለት የአምላኩ የበረከት ሙላት እየጨለፈ ይጎነጫል፡፡ በዚህ ስፍራ ላይ ዘማሪው መላው እስራኤልን ወደዚህ የመታመን ሕይወት ይጋብዛቸዋል፡፡ “ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ” የሚለው አባባሉ አማኝ ምንጊዜም ቢሆን መኖር ያለበት በእምነት መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ሰው ከአምላኩ ሌላ የሚታመንበትና የሚመካበት ነገር ካለው ፈጽሞ ጤነኛ የሆነ የአምልኮ ሕይወት ሊኖረው አይችልም፡፡ ዘማሪው በዚህ ክፍል ላይ ዘመኑን ሁሉ በእምነት ለመኖር መወሰኑን ያውጃል፡፡ ውሳኔውም ሆነ ጽኑ አቋሙ ጠንካራና የማይበገር ነው፡፡ ይሄ ሰው በጭራሽ እምነት አልባ ኑሮ ለመኖር የማይሻ ነው፡፡
ዛሬ በአምልኮ ሕይወታችን ውስጥ በጌታ መታመን ዋነኛ ተግባር እንጂ ዐልፎ ዐልፎ እየከረምን እንደ መረቅ የምናጣቅሰው ልምምዳችን ሊሆን አይገባም፡፡ የእግዚአብሔር እጅም በኀይል ለሥራ የሚንቀሳቀሰው በስሙ ለሚታመኑ ቅዱሳን ነው፡፡ ዛሬ ከጌታ ሌላ የተመረኮዝነውንና የተንጠለጠልንበትን ነገራችንን ትተን ራሳችንን ሙሉ በሙሉ በጌታ ላይ እንጣል፡፡ በፍጹም ልባችንም በእርሱ እንታመን፡፡ የዚያን ጊዜ በእውነትም ጌታን በሕይወታችን ማየትና ተኣምራቱንም ማጣጣም እንጀምራለን፡፡
ምንጭ:- hintset.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በደስታ ቅን ነገር የሚያደርጉትን፣ መንገድህን የሚያስቡትንም ትረዳለህ፤ ”
ኢሳይያስ 64፥5 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
እውነተኛ አምልኮተ ሕይወት
አምልኮን በአንድ ቃል ለመግልጽ አስቸጋሪ ቢሆንም፣ ከራስ ለሚበልጥ አንድ አካል የሚሰጥ ታላቅ አክብሮትና ስግደት፣ ወይም በፍርሀትና መንቀጥቀጥ ራስን ለሌላው ማስገዛት ወይም መስጠት የሚለውን ሐሳብ ይገልጻል፡፡ አምልኮ በዕለተ ሰንበት በጋራ ተከማችተን የምናሰማው የዝማሬ ድምፅ ወይም የምናከናውነው ሃይማኖታዊ ሥርዐትና ልማድ ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን መላው ሕይወታችንን በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ ለጌታ ማስገዛትና መኖርን ያካተተ ልምምድ ነው፡፡
ሰው የተፈጠረበት ተቀዳሚ ዓላማ እግዚአብሔርን እንዲያመልክና ከእርሱ ጋር ሕያው ኅብረት እንዲኖረው ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍጹም ጻድቅና ቅዱስ፣ ከክፋትም የራቀ ሕያው አምላክ ነው፡፡ ሰው ደግሞ ከኀጢአት ውድቀት የተነሣ ከጽድቅ ይልቅ ዐመፃን የሚሻ፣ ራስ ወዳድና ስግብግብ ፍጥረት ነው፡፡ ታዲያ ይህ ዐይነቱ ሰው እንዴት ሆኖ ለአምላኩ ፈቃድ የሚመች አምልኮ ሊያቀርብ ይችላል? በእውነቱ ይሄ ወሳኝ የሆነ ጥያቄ ነው፡፡
ምንም እንኳን በልጁ የቤዛነት ሥራ አምነንና ድነትን አግኝተን የምንመላለስ ብንሆንም፣ የምንኖረው ግን ከኀጢአት ጋር እየታገልን ነው፡፡ በፍጹም ልባችን ጨክነን ለአምላካችን ፈቃድ ብቻ ለመኖር ስንውተረተር በድንገት በሥጋችን ምኞት ተስበንና በኀጢአት ማጥ ውስጥ ተዘፍቀን ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ የሚገርም ነው!
በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረው ሰው አምላኩን ለማምለክ ሲቀርብ፣ ለአምላኩ የሚመቸው ነገር ምን እንደ ሆነ አስቀድሞ ማወቅ ይኖርበታል፡፡ በዛሬው አጭር መልእክቴ እውነተኛ የሆነ አምልኮተ ሕይወት ምን ዐይነት እንደ ሆነ ማሳየት ይሆናል፡፡ ይህንንም ከመዝሙር መጽሐፍ 131፥1-3 ሁለት ሐሳቦችን በመመልከት እንጀምራለን፡፡
አቤቱ ልቤ አይታበይብኝ፥
ዐይኖቼም ክፍ ከፍ አይበሉብኝ፤
ከትልልቆች ጋር ከእኔም ይበልጥ ከሚከበሩ ጋር አልሄድሁም፡፡
ነፍሴን አሳረፍኋት፥
የእናቱንም ጡት እንዳስተዉት ዝም አሰኘኋት
ነፍሴ የእናቱን ጡት እንዳስተዉት በእኔ ውስጥ ናት
ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እስራኤል በእግዚአብሔር ይታመን፡፡
ባለው ነገር ረክቶ እና ደስተኛ ሆኖ መኖር
በእጃችን ያለውና የእኛ ነው የምንለው ነገር በሙሉ በራሳችን ብርታት ያገኘነው ሳይሆን፣ በአምላክ ቸርነት የተጎናጸፍነው መሆኑ ከገባን ባለን ነገር መርካትና መደሰት አይሳነንም፡፡ ያለኝ ይበቃኛል ብሎ የሚኖር ሰው ርካታው በጌታው ብቻ እንጂ ዙሪያውን በሰበሰበው ቁሳቁስ እንዳልሆነ ጠንቅቆ የተገነዘበ ሰው ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ተጨማሪ ነገሮችን ለማግኘት ሲደክም ከጌታው ጋር ያለውን መለኮታዊ ቁርኝት በቁሳቁስና ጠፊና አላፊ በሆኑ ነገሮች ይለውጠዋል፡፡ ይህንን የዘመረው ዳዊት በእስራኤል ላይ ንጉሥ የነበረ፣ በጊዜው ትልቅ ስምና ዝና የነበረው፤ ሀብትና ባለጠግነት ያላነሰው፣ ሚስቶችና ልጆች ያሉት፣ በሀገሪቱ ላይ የመጨረሻውን ውሳኔ መወሰን የሚችል ገናና ሰው ነበር፡፡ ይህ ሰው ከየት እንደተነሣና ማን እዚህ እንዳዳደረሰው በደንብ የገባው ስለ ነበር ከጌታው ጋር ያለውን ኅብረት በምንም ነገር ሊተካው አይፈልግም፡፡ ስለዚህ “ልቤ አልታበየም፤ ሐሳቤም ለአጉል ትልቅነት አልተነሳሳም፤ እንዲሁም አሁን ካለኝ የበለጠ ነገር ለመያዝ ከአቅሜ በላይ አልተንጠራራሁም” (ከአ.መ.ት. የተወሰደ) በማለት ባለው ነገር መርካቱን በግልጽ ተናገረ፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ:- hintset.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው፤ የእስራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል፤ እግዚአብሔርም ይመስገን።”
መዝሙር 68፥35
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
የጥንት ቤተክርስቲያን ጉባዔዎች
ክፍል-፬
ከኬልቄዶን ጉባኤ (451 ዓ.ም.) ከተካሄደ በኋላ፣ በርካታ ዋና ዋና የቤተክርስቲያን ጉባዔዎች ተካሂደዋል። ነገር ግን፣ እነዚህ ሁሉ ጉባኤዎች በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት አላገኙም። ለዚህም ዋናው ምክንያት በተለይም ከኬልቄዶን በኋላ በተፈጠሩ ጥልቅ ሥነ-መለኮታዊ አለመግባባቶች እና ፖለቲካዊ ልዩነቶች የተነሳ ነው።
ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ያሉ ቁልፍ ክስተቶች፡-
1. የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በኬልቄዶን ጉባዔ ውሳኔ አለመስማማት
ይህ ጉባዔ በብዙ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ውድቅ ተደርጓል፣ በተለይም በግብፅ፣ በሶሪያ እና በአርሜኒያ። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ከጊዜ በኋላ የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በመባል ይታወቃሉ። ይህም ጉልህ እና ዘላቂ የሆነ መከፋፈል አስከትሏል።
2. የኬልቄዶንያ እና የኬልቄዶንያ ያልሆኑ ካምፖች ምስረታ፡-
የኬልቄዶን ጉባዔ ውሳኔ በምዕራቡ ቤተ ክርስቲያን (ሮምን ጨምሮ) እና በባይዛንታይን (ምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ) ቤተ ክርስቲያን ጸንቷል። ሆኖም፣ የኬልቄዶንያ ያልሆኑ አብያተ ክርስቲያናት ራሳቸውን ችለው ቀጥለዋል፣ እያንዳንዱም የየራሱን ወጎች፣ ተዋረዶች እና ሥነ-መለኮታዊ ማዕቀፎችን እያዳበረ ቀጥለዋል።
3. የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መነሳት እና ሌሎች፦
የአሌክሳንደሪያ ኮፕቲክ(የግብፅ) ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፣ የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና የአርመን ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ኬልቄዶንን ያልተቀበሉት ዋና ዋና አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። በአካባቢያቸውም ሀይማኖታዊ እና ሀገራዊ ተቋማት ሆኑ።
4. በምስራቅ-ምእራብ ቤተክርስቲያን ላይ ያመጣው ተጽእኖ፦
በኬልቄዶን የተጀመረው መከፋፈል በክርስትና ውስጥ የአስተምህሮ፣ የፖለቲካ እና የባህል መለያየት እንዲጨምር አስተዋጽኦ አድርጓል፣ ይህም ከጊዜ በኋላ በ1054 ዓ.ም በምስራቅ ኦርቶዶክስ እና በሮማ ካቶሊካዊነት መካከል በተከሰተው መለያየት ተጠናቀቀ።
ምንጭ፦ Chadwick, H. (1993). The early Church (Revised ed.). Penguin Books.
Pelikan, J. (1971). The Christian tradition: A history of the development of doctrine, Volume 1: The emergence of the Catholic tradition (100-600). University of Chicago Press.
Meyendorff, J. (1989). Imperial unity and Christian divisions: The Church 450–680 A.D. St. Vladimir's Seminary Press.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እርሱም በዘገየ ጊዜ እግዚአብሔር ስላዘነለት እነዚያ ሰዎች የእርሱን እጅ የሚስቱንም እጅ የሁለቱን የሴቶች ልጆቹንም እጅ ይዘው አወጡትና በከተማይቱ ውጭ አስቀመጡት።”
ዘፍጥረት 19፥16
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
የጥንት ቤተክርስቲያን ጉባዔዎች
ክፍል-፫
የኬልቄዶን ጉባዔ 451
በ451 ዓ.ም የተካሄደው የኬልቄዶን ጉባኤ የቤተክርስቲያን አራተኛው ጉባኤ ሲሆን በክርስትና ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ከሚሰጣቸው ጉባኤዎች አንዱ ተደርጎ ይወሰዳል። ነገረ ክርስቶሳዊ አስተምህሮ በመቅረጽ እና የጥንቷ ቤተክርስቲያንን ያከፋፈሉትን ስነ-መለኮታዊ አለመግባባቶችን ለመፍታት ማዕከላዊ ሚና ተጫውቷል።
ታሪካዊ ዳራ
የኬልቄዶን ጉባኤ በንጉሠ ነገሥት ማርሲያን በኬልቄዶን፣ በቁስጥንጥንያ አቅራቢያ (በአሁኑ ኢስታንቡል፣ ቱርክ) አቅራቢያ፣ በዋነኛነት በክርስቶስ ማንነት ላይ ያለውን ውዝግብ ለመፍታት ነበር።
ሥነ-መለኮታዊ ዳራ
የኬልቄዶን ማዕከላዊ ሥነ-መለኮታዊ ክርክር የሚያጠነጥነው መለኮታዊ እና ሰብዓዊ ተፈጥሮዎች በኢየሱስ ክርስቶስ አካል ውስጥ እንዴት አብረው እንደሚኖሩ ነው። ሶስት ዋና ዋና አመለካከቶች ነበሩ፡-
ንስጥሮሳዊነት፡- ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ አካላት፣ አንድ መለኮት እና አንድ ሰው እንዳሉት አስተምሯል። ይህ በኤፌሶን ጉባኤ (431 ዓ.ም.) ተወግዟል።
Monophysitism ሞኖፊዚቲዝም (ከግሪክ ሞኖስ = አንድ፣ ፊዚስ = ተፈጥሮ)፡- ክርስቶስ አንድ ባሕርይ ብቻ ነበረው፣ በዋናነት መለኮት የሆነ፣ የሰውን ተፈጥሮ ተውጦ ነው በማለት ተሟገተ።
Dyophysitism ዳይኦፊዚቲዝም፡- ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ መለኮት እና ሰዋዊ ተፈጥሮዎች እንዳሉት በአንድ አካል የተዋሃዱ መሆናቸውን አስረግጦ ተናግሯል።
የኬልቄዶን ጉባዔ መግለጫ
የጉባዔው ውሳኔ እንደሚከተለው በኢንግሊዝኛ(በኢንግሊዝኛ የቀረበበት ምክንያት በትርጉም ወቅት የሚያሻማ ቃል ላለመጠቅም ነው) ቀርቧል።
"[...] one and the same Christ, Son, Lord, Only-begotten, acknowledged in two natures, without confusion, without change, without division, without separation; the difference of the natures being by no means removed because of the union, but rather the properties of each nature being preserved and concurring into one person and one subsistence."
ይቀጥላል. . .
ምንጭ፦ Pelikan, J. (1974). The Christian Tradition: A History of the Development of Doctrine, Vol. 1: The Emergence of the Catholic Tradition (100–600). University of Chicago Press.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 842
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
