en
Feedback
ቅዱሳት መጻሕፍት

ቅዱሳት መጻሕፍት

Open in Telegram

በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures

Show more
7 833
Subscribers
+724 hours
+357 days
+15630 days
Posts Archive
. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ጥበቡ ጥልቅ፣ ኀይሉም ታላቅ ነውና፤ እርሱን ተቃውሞ ያለ አንዳች ጒዳት የሄደ ማን ነው?” ኢዮብ 9፥4 (አዲሱ መ.ት) ወደ ቻናሉ ለ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ጥበቡ ጥልቅ፣ ኀይሉም ታላቅ ነውና፤ እርሱን ተቃውሞ ያለ አንዳች ጒዳት የሄደ ማን ነው?” ኢዮብ 9፥4 (አዲሱ መ.ት) ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

#እራሳችንን_እንመርምር “ልቤን አነጻሁ፥ ከኃጢአትም ጠራሁ የሚል ማን ነው?” ምሳሌ 20፥9 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ይህን ሕዝብ ከግብፅ ምድር ካወጣህ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ይቅር እንዳልሃቸው፥ እባክህ፥ እንደ ምሕረትህ ብዛት የዚህን ሕዝብ ኃጢአት
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ይህን ሕዝብ ከግብፅ ምድር ካወጣህ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ይቅር እንዳልሃቸው፥ እባክህ፥ እንደ ምሕረትህ ብዛት የዚህን ሕዝብ ኃጢአት ይቅር በል።” ዘኍልቁ 14፥19 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ       ክፍል - ፰ የእግዚአብሔር ስም ሙሴም እግዚአብሔርን፦ እነሆ፥ እኔ ወደ እስራኤል ልጆች በመጣሁ ጊዜ። የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ላከኝ ባልሁም ጊዜ። ስሙስ ማን ነው? ባሉኝ ጊዜ፥ ምን እላቸዋለሁ? አለው። እግዚአብሔርም ሙሴን፦ «ያለና የሚኖር» እኔ ነኝ አለው እንዲህ ለእስራኤል ልጆች። «ያለና የሚኖር» ወደ እናንተ ላከኝ ትላለህ አለው። … ዘጸ ፫፣ ፲፫ - ፲፬ እግዚአብሔርም በደመናው ውስጥ ወረደ፥ በዚያም ከእርሱ ጋር ቆመ፥ የእግዚአብሔርንም ስም አወጀ። እግዚአብሔርም በፊቱ አልፎ። እግዚአብሔር፥ እግዚአብሔር መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት፥ እስከ ሺህ ትውልድም ቸርነትን የሚጠብቅ፥ አበሳንና መተላለፍን ኃጢአትንም ይቅር የሚል፥ በደለኛውንም ከቶ የማያነጻ፥ የአባቶችንም ኃጢአት በልጆች እስከ ሦስትና እስከ አራት ትውልድም በልጅ ልጆች የሚያመጣ አምላክ ነው ሲል አወጀ። .. ዘጸ ፴፬፣ ፭-፯ ስም፡- ምንድን ነው?  - መጠሪያ ነው። በምክንያት የሚወጣ። - ራስን መግለጫ /ማስተዋወቂያ/ ነው። ሰዎች ሲተዋወቁ መጀመሪያ የሚለዋወጡት ስም ነው። እገሌ እባላለሁ።… · አዳም በመጀመሪያ ለእንስሳት - በኋላም ለሚስቱ ስም አወጣ። - ባለቤትነትን ያሳያል። በመጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ስም በራሱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲተዋወቅ ፡- ለሙሴ- ማን ነው? ሲሉኝ…ማን ልበላቸው ባለው ጊዜ እንዲህ ብሎታል፡- "ያለና የሚኖር"  በእንግሊዝኛው - I AM that I AM’- ይላል። በቀጥታ እንዳለ ብንተረጉመው፡- « እኔ እኔው ነኝ፡- ማለት ነው። o ለእግዚአብሔር ማንም ስም አላወጣለትም፤ ራሱን ራሱ ገለጸ፣ ስሙን ተናገረ። o የሚገልጸው ነገር ስለሌለ "እኔ እኔው ነኝ" አለ። በአማርኛ "እግዚአብሔር"  ብለን የሰጠነው ስም የግዕዝ ቃል ነው። አባቶች በሁለት መልክ ይተረጉሙታል፡- ፩ኛ.  እግዚአ - ጌታ፣ ብሔር - ሃገር/ ዓለም/ - እግዚአ ብሔር፡- የዓለም ጌታ የሚል ነው። የዓለማት ሁሉ አስገኝ ባለቤት መሆኑን ያሳያል። ይህ ማንነቱን በሙሉ አይገልጸውም። ያንሳል። እርሱ ከጌታም በላይ ነውና።   ፪ኛ. እግዚእ- ወልድ፣ አብ - አብ፣ ሔር - መንፈስ ቅዱስ - ሥላሴነቱን ያሳያል። ይህ ስሙም ሦስትነቱን መግለጹ እንጂ መላ ማንነቱን ሊገልጽ አይችልም።  ስለዚህ ለሙሴ ራሱ እግዚአብሔር የተናገረው ስሙ የተሻለ ገላጭ ነው። እኔ እኔው ነኝ። የሚገልጸኝ፣ የሚመስለኝ የለም ሲል ነው። ለአብርሃም ዘፍ ፲፯፣ ፩ - እኔ ኤልሻዳይ ነኝ፡ ሲለው ከባሕርያቱ አንዱን ነው የሚገልጸው - ሁሉን ቻይነቱን።  ስለእርሱ ሁሉንም እኔ እንዲህ ነኝ በማለት መዘርዘር ስለማንችል፡- እኔ እኔው ነኝ፤ አለ። በኋላ ለሙሴ በድጋሜ ራሱ ያወጀው ስም፡-- የእግዚአብሔርንም ስም አወጀ። - አስር መግለጫዎችን የያዘ ነው። በየቁጥሮቹ እንያቸው፡-  ፩. እግዚአብሔር እግዚአብሔር - ሁለት ጊዜ - ለአጽንኦት፡  በእንግሊዝኛው ጌታ፣ ጌታ እግዚአብሔር ይላል። - የዓለም ጌታ፤ ባለቤትነቱን ያሳያል። ቀዳማዊ ነገር ይህ ነው። የእግዚአብሔር ስም- የፍጥረት ሁሉ ባለቤት /ጌታ/ እርሱ መሆኑን - በቅድሚያ ያውጃል።  ጌታ ያለን መሆናችንን ማወቅ፡ -  የማን መሆናችንን ማወቅ ማለት ነው። -የማን መሆናችንን ስናውቅ - ማንነታችንን እናውቃለን። ከዚያም ምን ማድረግ እንዳለብን እና እንደሌለብን እናውቃለን። ፪. መሐሪ፡- ቸር ነውና ምሕረቱ ለዘላለም ነውና  እንደተባለ። በኃጢአት ለወደቀው ሰው ቅድሚያ የሚያስፈልገው የእግዚአብሔር ነገር - ምሕረቱ ነው። ሰው ሲፈጠር የማን መሆኑን /ጌታ እንዳለው/ ካወቀ በኋላ በኃጢአት ስለወደቀ ምሕረቱን ይሻል። - ስለዚህ እግዚአብሔር መሐሪ ተባለ። ፫. ሞገስ ያለው፡-  ሞገስ ምን ማለት ነው? -- መልካም አመለካከት ያለው፤ ሀ. እግዚአብሔር ለሰዎች ያለው፡- -  ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ።  ዘፍ ፮፣፰ መልካም ተቀባይነትን አገኘ፡፡ ለኖኅ ሞገስን የሰጠው እግዚአብሔር ነው። - ሞገስ ያለው ስለሆነ፡፡  ፬. ታገሽ፡- ትዕግስቱን ፭. ቸርነቱ ብዙ የሆነ፡- ባለጸጋ፡- የሰጠ - - ተፈጥሮን፣ ሕይወትን የሰጠ። ፮. እውነቱ /ታማኝነቱ የበዛ፡- ማንም እውነትነቱን የማያረጋግጥለት፣ በራሱ እውነት የሆነ፡- ታማኝነቱን ለመግለጽ ነው። ፯. እስከ ሺ ትውልድ ቸርነትን የሚጠብቅ፡-  ሺ ሲባል በትክክል እየተቆጠረ አንድ ሺ ለማለት አይደለም። ቁጥሮች በውሳኔ እና ያለውሳኔ ይነገራሉ። ያለውሳኔ ሲነገሩ ቁጥርን ሳይሆን ታላቅነትን፣ ፍጹምነትን፣ ዘላቂነትን ያሳያሉ፡፡ ለምሳሌ፡- «አስር ጊዜ አትጨቅጭቀኝ፤ ሺ ጊዜ ብትለፋ አይሆንም።… » ሲባል ቁጥሮችን አይደለም። ፈጽሞ እንደማይሆን ለማሳየት ነው። ፰. ይቅር ባይ፡- አበሳን፣ መተላለፍን፡ ኃጢአትን… ይቅር የሚል።  ፱. በደለኛውን ከቶ የማያነጻ፡- በደለኛን ይቅር አይልም ማለት ነው? አይደለም። በእንግሊዝኛው that will by no means clear the guilty - ይላል። ጥፋተኛውን ነጻ ነህ / ንፁህ ነህ / ሊለው አይችልም። ያጠፋን ሳይቀጣ እንዳላጠፋ ዝም ብሎ አያልፍም። - ወይ በንስሐ ይቅር ይለዋል፤ ወይ ያጠፋዋል - ይበቀለዋል።  ፲. የአባቶችንም ኃጢአት በልጆች እስከ ሦስትና እስከ አራት ትውልድም በልጅ ልጆች የሚያመጣ አምላክ፡- በመጨረሻ የታወጀው የስሙ መገለጫ። የአባቶቹን ጥፋት / ኃጢአት/ እያየ ትውልዱ ንስሀ ካልገባ በዚያው ኃጢአት ይያዛል። ይጠየቃል።  - በአባቶች ኃጢአት ልጆች፣ የልጅ ልጆች ይቀጣሉ። ለምን? -እግዚአብሔር በኃጢአት ላይ ያለው ጭካኔ ከባድ እንደሆነ - እስከትውልድ እንደሚቀጥል እንጂ ዘመን በረዘመ ቁጥር ሳይቀጣ የሚተው፡ የሚረሳ እንዳልሆነ ያሳያል። -ልጆች ቅጣቱ ቢተርፋቸውም - ልጆች - እስከሆኑ ድረስ ንስሐ የመግባትና ምሕረት የማግኘት እድል አላቸው። -እስራኤላውያን በበረሀ በእግዚአብሔር ላይ በማመጻቸው የተቀጡት /፵ ዓመት የተንከራተቱት/ ያጠፉት አዋቂዎቹ ብቻ አይደሉም። አብረው የተወለዱት ሕጻናትም ተንከራትተዋል። -ልጆች፣ የልጅ ልጆች - እስከ ፫ ና ፬ ትውልድ - ይህ በውሳኔ የተነገረ ስለሆነ ቁጥሩን የሚያሳይ ነው። አንድ ሰው በዕድሜ ባለጸጋ ሲሆን የልጅ ልጆቹን ማየት የሚችለው እስከ ፬ ትውልድ ነው። -- ሲበድል ንስሐ ካልገባ ዓይኑ እያየ ልጆቹ የልጅ ልጆቹ ይቀጣሉ፣ ማለት ነው። ንስሐ መግባት አለበት። እንጂ ጥፋትን /በደልን/ ከእግዚአብሔር ጋር በዘመን ርዝመት ማረሳሳት አይቻልም። -ይህ ሲቀጥል - እኛ የምናጭደው የአባቶቻችንን በረከት/መርገም ሲሆን የእኛን በረከት/መርገም ልጆቻችን ያጫዳሉ የሚለውንም ያሳያል። -- ስለዚህ ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት - መልካም ከሆነ ውጤቱ፤ ክፉም ከሆነ ጦሱ እስከ ልጆቻችን እንደሚሆን አውቀን መጠንቀቅ አለብን። የእግዚአብሔር ስም በእግዚአብሔር ሲታወጅ ሙሴ የሰጠው ምላሽ - አምልኮ-ስግደት ነበር:: "ሙሴም ፈጥኖ ወደ መሬት ተጐነበሰና ሰገደ"፦  ዘጸ ፴፬፣ ፰ ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ።” 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥12-13 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ           ክፍል ፯ እግዚአብሔርን ፍለጋ - ቀጣይ ምኑን ነው የምንፈልገው? ባለፈው ክፍል  - እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚል - ስለእግዚአብሔር መኖር በተፈጥሮ፣ በሕሊና፣ በመሳሰሉት ማረጋገጥ እንደሚቻል አይተናል።  በአሁኑ ጊዜ የፈጣሪን /የእግዚአብሔርን መኖር የሚጠራጠር ብዙም ላይኖር ይችላል፤ ወይም በአሁኑ ጊዜ ለኛ ይህ ብዙም አሳሳቢ ጥያቄ አይደለም። ከላይ ከተጠቀሱት በአንዱ ወይም በሌላ በሆነ መንገድ - የእግዚአብሐየርን መኖር አረጋገጥን - እግዚአብሔርን አገኘነው።  ካገኘነው በኋላ ምኑን ነው ማየት የምንፈልገው? ስንል ዳዊት እንዲህ ይለናል፡- "ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።"  መዝ ፻፬/፻፭፣ ፬ - የእግዚአብሔር ሕልውና /መኖሩ/ የሚረጋገጠው አንድ ጊዜ ነው። ከተገኘ - አለ። አይጠፋም። ከዚያ በኋላ ግን ሁልጊዜ መፈለግ ያለብን "ፊቱን" ነው። - በምናያቸው ፍጥረታት የእግዚአብሔርን አስደቂ ኃያል እጅ  እናያለን። ቀጥሎ ግን ሁልጊዜ ፊቱን ማየት አለብን። ፊት ምንድን ነው? -የማንነት መለያ ነው። ሁላችንም የምንለየው በፊታችን ነው። መታወቂያ ላይ የሚደረገው ፎቶ - ጉርድ ፎቶ - የሚያሳየው ፊታችንን ነው። -  አንድን ሰው አየሁት ለማለት "ፊቱን" ማየት ግድ ነው። - ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ሕዝቡን ነጻ አውጥቶ ሲመራ፣ በተአምራት ብዙ ዘመን ከኖረ በኋላ፡- እግዚአብሔርን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡- o እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለ።…. - እግዚአብሔርም - o   …ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም......ፊቴ ግን አይታይም»   አለ።     ዘጸ ፴፫፡ ፲፯ - ፳፫። -  ፊቱን ማየት የማይቻል ከሆነ -ፊቱ የማይታይ ከሆነ -  ለምን ፊቱን ፈልጉ ተባለ? - ማየት የማይቻለው በዚህ በሥጋ ዓይን ነው። እግዚአብሔር መንፈስ ነውና። - በመንፈስ ግን ከእኛ ጋራ ሲሆን፣ ሲሠራ፣ ሕይወታችን ሲጠብቅ… እናየዋለን። "ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።"  (የሐዋ ፲፯፣ ፳፮) - መምህራን እንደሚያስተምሩት በርግጥ የሙሴ ጥያቄ ተመልሷል፤ ነገር ግን የተመለሰው ከ1400 ዓመት በኋላ- በኢየሱስ ክርስቶስ - በደብረ ታቦር ነው። o ሙሴ በጥየቄው መሰረት በዓይነ-ሥጋ በአካል እግዚአብሔርን ያየው - በኢየሱስ ክርስቶስ - ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነው አግዚአብሔር ነውና። "በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።" ማቴ ፲፯፣ ፪ - ፫ ዛሬም እኛ እግዚአብሔርን በመንፈስ ዓይን የምናየው - በኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ስለዚህ፡- ፭.  የፍለጋው ማብቂያ - ኢየሱስ ክርስቶስ o   በተሰጠን አእምሮ በምናደርገው ምርምር በተፈጥሮ፣ በኅሊና.. ፈጣሪ እንዳለ እናውቃለን። ፍጥረታትን ሁሉ እግዚአብሔር እንደፈጠራቸው እንዳስገኛቸው እንደሚቆጣጠራቸው እንረዳለን። o እግዚአብሔርን ፍለጋ የምናደርገው ጥረት እግዚአብሔር እንዳለ እንድናውቅ እንጂ ከእግዚአብሔር ጋር እንድንገናኝ አያደርገንም። o ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኘው በእኛ ፍለጋ ሳይሆን በእርሱ ፍለጋ ነው። እርሱ እኛን ስለፈለገን።  ስለዚህ የእኛ እግዚአብሔርን ፍለጋ የሚጠናቀቀው በራሱ በእግዚአብሔር ፍለጋ ነው። - የእግዚአብሔር ፍለጋ - ፍለጋው አያልቅም - እንደምንለው አይደለም። መድረሻ አለው።   የእግዚአብሔር ፍለጋ ማብቂያው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እኛ እርሱን ልንደርስበት ስለማንችል እርሱ እኛን ፈለገን። በሚገባን በምናውቀው ባሕርይ።  በሰው - ሰው ሆኖ ሊፈልገን መጣ። "የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው።"  ሉቃ ፲፱፣ ፲ "መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።"  ዮሐ ፩፣ ፲፰። "ተረከው" ማለት የቃል ትረካ አይደለም፤ በተግባር በኑሮ፣ በሕይወት፣ በሞት፡በትንሣኤ… ገለጠው ማለት ነው። ክርስቶስን ስናገኝ / ክርስቶስ ሲያገኘን/ ያን ጊዜ እግዚአብሔርን አገኘነው - አወቅነው፡ ማለት ነው። ማጠቃለያ፡- እግዚአብሔር አንዲህ አለ / ብሎ ተናገረ፣ ከማለታችን በፊት እግዚአብሔር አለ /መኖሩን/ እንበል። - እግዚአብሔር አለ/የለም በሚል ክርክር አንዱ ፈላስፋ የቆሎ ተማሪን ሲጠይቀው፣ እነዲህ መለሰለት፡ «እግዚአብሔርን አለ ብለኽው ባይኖር ችግር የለውም፤ የለም ብለኽው ካለ ግን ወዮልህ።» - አንዳንድ ወገኖች - ከባድ ችግር ሲገጥማቸው ወይም ያልሆነ መጥፎ ነገር ሲያዩ «እግዚአብሔርማ የለም፤ በእውነት ቢኖር እንደዚህ አይሆንም ነበር፤ » ይላሉ። -  እግዚአብሔር አንድን ነገር ለምን እንደሚያደርግ፣ እንዴት እንደሚሠራ ለእኛ ሁሉም ነገር ግልጽ ላይሆን ይችላል። ዝም ብለን በትዕግስት እንጠብቀው፤ እንደሚባለው አንዳንድ ነገሮች በጣም እንግዳ ይሆናሉ፤ ለምን እንዲህ ይሆናል አንበል፤ ቃሉ እንደሚል፡- "ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው።"  ዘዳ ፳፱፣ ፳፱ - ያለማቋረጥ ፀሐይን የሚያወጣት/የሚያገባት፣ ዝናቡን የሚያዘንብ፣ አዝመራውን የሚያበቅል፣ ለፍሬ የሚያደርስ፣ ሁሉን የሚመግበው ፣ የሚያስተዳድረው አምላክ - አለ። -  እኛንም ወደዚች ምድር ያመጣን፣ የፈጠረን ነው እርሱ የሚያኖረን ። አንጨነቅ። ሳለመድኃኔዓለም ምንም አንሆንም። አንፍራ። - በእውነት እግዚአብሔር አለ  ። ከሁሉም በላይ ትልቅ መጽናኛችን ነው። o   መኖሩን ያመንነውን  - ፈልገን ያገኘነውን ወይም በትክክል ለመናገር ፈልጎን ያገኘንን / እንድናገኘው የተፈለገውን/ መተዋወቅ  ቀጣዩ ተገቢ ጉዳይ  ነው ። ስንተዋወቅ የምንለዋወጠው ስምን ነው? -- እገሌ እባላለሁ።- - o  ስለዚህ ይህ ፈጣሪ ማን ይባላል?.... o  የእግዚአብሔር ስም ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ በእርሱ በኩል የኃጢአት ስርየት እንዲነገርላችሁ፥ በሙሴም ሕግ ትጸድቁበት ዘንድ ከማይቻላችሁ ሁሉ ያመነ ሁሉ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ በእርሱ በኩል የኃጢአት ስርየት እንዲነገርላችሁ፥ በሙሴም ሕግ ትጸድቁበት ዘንድ ከማይቻላችሁ ሁሉ ያመነ ሁሉ በእርሱ እንዲጸድቅ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን።” ሐዋርያት 13፥38-39 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ              ክፍል ፮ እግዚአብሔርን ፍለጋ ፫. የት ነው የምንፈልገው? ፫.፩ በተፈጥሮ፡-  ለእግዚአብሔር ሕልውና የመጀመሪያው ማስረጃ ሥነ ፍጥረት ነው። "የማይታየው ባሕርይ እርሱም የዘላለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ ከተሠሩት ታውቆ ግልጥ ሆኖ ይታያልና፤"   ሮሜ ፩፣ ፳ ሀ. ፍጥረታት ከምን ተገኙ? ከየት መጡ?  የሚታየው ነገር ሁሉ አስገኚ አለው። በራሱ የተገኘ ነገር የለም። o አንዳንድ ወገኖች ዓለሙ የተገኘው እንዲሁ ነው የሚሉ አሉ፤ - ተመራማሪዎች። በእግዚአብሔር መኖር የማያምን ጓደኛ የነበረው አንድ የእግዚአብሔር  ሰው  ያን ኢአማኒ ጓደኛውን «ዓለማት ከየት ተገኙ?» ሲለው የማያምነው ጓደኛም፡- «እንዲሁ ተገኙ» ይለው ነበር። አንድ ቀን አማኙ በካርቶን እና በወረቀት ቆንጆ ቤት ከሠራ በኋላ  ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው። በኋላ ከሃዲ ጓደኛው ሲመጣ የቤቱን ሞዴል አይቶ በጣም ተደነቀና ፡- « ከየት አገኘህው?» ሲለው - አማኙ  «እንዲሁ ተገኘ» አለው.. ይሄማ ሊሆን አይችልም  ሲል ያ አማኙ ጓደኛም፡- «አየህ እኔም ፍጥረታት ከየት ተገኙ? » ስልህ እንዲሁ ስትለኝ የነበረውም ሊሆን አይችልም ማለት ነው።  የምናየው ነገር ሁሉ ሠሪ ወይም አስገኚ አለው። በራሱ የተገኘ ነገር የለም። በአጠቃላይ የዚህ ውብ ተፈጥሮ አስገኝውስ ማን ነው?  ስንል -ፈጣሪ- እንዳለ /እንዳለው እንረዳለን። ለ. ፍጥረታት እንዴት ተገኙ? o አሁንም ተመራማሪዎች የመጀመሪያው ታላቅ ፍንዳታ (Big Bang) ከተከሰተ በኋላ- በሂደት ነገሮች ሁሉ ተገኙ፤ ይላሉ። ግን የመጀመሪያው የታላቅ ፍንዳታ ቁስ ከየት መጣ? ሲባል መልስ የለም። ከዚያም በኋላ በአዝጋሚ ለውጥ- አንዱ ከአንዱ እየተወጣ.. ተገኙ ይላል። o አንድ ጸሐፊ እንዲህ ብሏል፡-  ነገሮች አንዱ ከአንዱ ተገኘ ከተባለ ይህ ማለት እንግዲህ በከተማችን የምናያቸው ታላላቅ ፎቆች፣መንገዶች፣ ድልድዮች የተገኙት፡-  ጥሬ ዕቃዎቹ - ብረቱ፣ ሲሚንቶው ራሳቸውን አዘጋጅተው፣ እንጨቶች ራሳቸውን ጠርበው አስተካክልው፣ ጡቦች በራሳቸው እየተደረደሩ፣ ቆርቆሮው በራሱ እየተመታ፣ እየተጋጠመ ቤቱ ተሠራ የማለት ያህል ነው። ይህ ግን ፈጽሞ የማይሆን ነገር ነው። o  ይህ ዓለም የተፈጠረ ብቻ ሳይሆን በሥርዓት የተዋቀረ ዓለም ነው። Intelligent design - ግሩም ንድፍ ያረፈበት ድንቅ ተፈጥሮ ማለት ነው። ሐ. ፍጥረታት እንዴት ይኖራሉ? o ፍጥረት ሁሉ በእንቅስቃሴ ላይ ነው። የፀሐይ መውጣት/መግባት - የምድር መዞር- የፕላኔቶች - .. ሁሉም በእንቅስቃሴ ላይ ነው። ማን ነው የሚያንቀሳቅሰው? ወይም ይህንን እንቅስቃሴ የሚመራው/ የሚቆጣጠረው ማን ነው? ምድር፡- በፀሐይ ሥርዓት ውስጥ ፣ ወይም በሕዋ ውስጥ ያላት ሥፍራ ሕይወትን ሊያኖር በሚችል  መልኩ የተቀመጠች ናት። ምድር በፀሐይ ዙርያ ስትዞር ከምሕዋሯ  ትንሽ ራቅ ብትል - ሁሉም ነገር በረዶ ሆኖ በከፍተኛ ቅዝቃዜው ሕይወት በሙሉ ይሞታል፤  በተመሳሳይ ከምሕዋሯ ትንሽ ቀረብ ብትል በከፍተኛው ሙቀት የተነሳ ሁሉም ይቀልጥና ሕይወት አይኖርም፡። ፫.፪ በሕሊና፡- በተፈጥሮ ሁሉም ሰው ክፉና ደጉን የመለየት ሚዛናዊነት ተቀምጦለታል።  ሰው ቢማርም ባይማርም፣ እግዚአብሔርን ቢያምንም ባያምንም በተፈጥሮው በሕሊናው መልካምና መጥን የመለየት ችሎታ አለው። ይህ የሕሊና ዳኝነት - እንዴት በሁላችን ውስጥ ሊኖር ቻለ? ማን አስቀመጠው? - የጋራ ነገር እንዲኖረን ያደረገ አንድ አካል አለ?-- አዎ እርሱም የፈጠረን እግዚአብሔር ነው። ሰው ሥጋ /matter/ ብቻ አይደለም መንፈስ /Spirit/ አለው። ቁሳዊ ነገር ከቁሳዊ ነገር ሊገኝ ይችላል። ነገር ግን መንፈሳዊ ነገር ከቁሳዊ ነገር ሊገኝ አይችልም። መንፈሳዊ ነገር ከመንፈስ /ከረቂቅ አካል/ ብቻ ነው ሊገኝ የሚችለው። -- እርሱም እግዚአብሔር ነው። ስሜታዊ ነገሮች ፡ - ደስታ፣ ፍቅር፣ ሠላም፣ እምነት … የምንላቸው ማኅበራዊ እሴቶች ከቁሳዊ ነገር ሊገኙ አይችሉም። እነዚህን የማይዳሰሱ ረቂቅ ስሜቶችን ያስገኘ ስሜት ያለው / የሚሰማው/ ረቂቅ አካል ነው። -- እርሱም እግዚአብሔር ነው። ፫.፫ በጠፈር ምርምር o ስለከዋክብት ብዛት በሳይንሱ የሚሰጠውን መግለጫ ብናይ፡- በዘመናዊ ግዙፍ የርቀት ማሳያ /ቴሌስኮኘ/ ተመርምሮ እንደተገኘው ከኛ ፀሐይ አካባቢ የሚገኙ ከዋክብት ቁጥራቸው እስከ ሀያ ሚሊዮን ይጠጋል፡፡ ያለመሣርያ በባዶ ዓይን ሲመለከቷቸው ግን አምስት ሺህ ብቻ ያህላሉ ይላሉ፡፡ ተመራማሪዎቹ እንደሚሉት የከዋክብት ቁጥራቸው ሊወሰን የማይችል እልፍ አእላፍ /የብዙ ብዙ/ ስለሆነ የብዛታቸው ልክ እንኳንስ ተቆጥሮ ሊደረስበት ይቅርና ታይቶ የማያልቅ ነገር ሆኖባቸዋል፡፡ የርቀት መሣርያ መነጽሩን /ቴሌስኮኘ/ አሠራርና የማስተዋሉንም አኳኋን እያሻሻሉ በሄዱበት መጠን ቀድሞ ያልታዩ ሌሎች አዳዲስ ከዋክብት ይገኛሉ፡፡ የዚህን ሁኔታ ሲናገሩም መነጽሮቻችን ምንም ያህል ብናሻሽላቸው ከዋክብትን ጨርሰን ሙሉ በሙሉ ልናያቸው አንችልም፡፡ በጣም ዘልቀን ለማየት በቻልንበት መጠን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ሌሎች አዳዲስ ከዋክብት ይወጣሉ፡፡ የእኛ ዕውቀት ከቶ ሊዘልቀው የማይቻል ነው ይላሉ፡፡ /የዕውቀት ብልጭ ፤ ከበደ ሚካኤል፡ ገጽ 158/ o "ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።"  መዝ ፲፰/፲፱፣ ፩ የሰማይ ጥልቀት / የየከዋክብቱ ርቀት/፣-  አሁንም ለዚህ የሳይንሱን መግለጫዎች ብናይ፦ በፀሐይና በመሬት መካከል ያለው ርቀት ወደ 150 ሚሊዮን ኪ.ሜ ይጠጋል፡፡ የርቀቱን ግምት ለመገንዘብ በመድፍ ጥይት ጉዞ መስለው ይናገራሉ፡፡ የመድፍ ጥይት ፍጥነቱን ሳይቀንስ ከምድር ወደ ፀሐይ ቢተኮስ ከፀሐይ ለመድረስ 20 ዓመት ይፈጅበታል፡፡ ይህም ፀሐይ ከመሬት ምን ያህል በጣም የራቀች መሆኗን ያሳየናል፡፡ በማታ ከምናያቸው ስፍር ቁጥር ከሌላቸው በርካታ ከዋክብት ውስጥ ለመሬት ቅርብ የሆነችው ኮከብ  ከላይ በተቀመጠው ምሳሌ መሠረት ርቀቷ እጅግ በጣም ብዙ ከመሆኑ የተነሳ የመድፍ ጥይቱ ወደዚች ኮከብ ቢተኮስ ከርሷ ለመድረስ 7 ሺህ ዓመት ይወስድበታል፡፡ በዚህ ልኬታ የሌሎችን ከዋክብት ርቀት ብናስብ ምን ያህል የማይደረስበት እንደሚሆን መገመት እንችላለን፡፡ በየከዋክብቱ መሀል ያለው ርቀትም እጅግ በጣም ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ የሚለካው ብርሃን ከነርሱ ለመድረስ በሚፈጅበት ጊዜ ነው፡፡ ይህም የብርሃን ዓመት ይባላል። …. እግዚአብሔር በሰጠን አእምሮ - እየተመራመርን- ይሄን ሁሉ ስናይ /ስንሰማ/ የእነዚህ ሁሉ ፈጣሪ ምን ያህል ግሩም ድንቅ ነው እንድል ያደርገናል። ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ የሆኑ በሳይንስ ሊረጋገጡ /ሊመለሱ ያልቻሉ ብዙ ጉዳዮች /ክስተቶች አሉ። o የአጋንንት እና የመናፍስት አሠራር ፤ ተአምራት፣ ድንቆች…. o የነፍስ ምንነት፣ ሞት ምንድን ነው? ወዘተ… እነዚህ ሁሉ የሚያሳየን ሁሉን የፈጠረ፣ ሁሉን የሚቆጣጠር እና የሚመራ አምላክ እንዳለ ነው።   ታዲያ የእግዚአብሔርን መኖር በተፈጥሮ፣ በሕሊና ፣ በመሳሰሉት… ካረጋገጥን በኋላ የምንፈልገው ምኑን ነው? ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ያም ቀን እርሱም ከሳምንቱ ፊተኛው በመሸ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ያም ቀን እርሱም ከሳምንቱ ፊተኛው በመሸ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ፦ ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።” ዮሐንስ 20፥19 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ            ክፍል ፭ እግዚአብሔርን ፍለጋ "ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደ ሆነ፥ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ፥ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ስፍራ ዳርቻ መደበላቸው። ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም። ከእናንተ ከባለ ቅኔዎች አንዳንዶች ደግሞ። እኛ ደግሞ ዘመዶቹ ነንና ብለው እንደ ተናገሩ፥ በእርሱ ሕያዋን ነንና እንንቀሳቀሳለን እንኖርማለን።"   የሐዋ ፲፯፣ ፳፮ - ፳፰ ፩. እግዚአብሔርን መፈለግ ለምን አስፈለገ? ሀ. የተፈጠርንበት ዋና ዓላማ በመሆኑ-  እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ፡- ·የሰውን ወገኖች ከአንድ ፈጠረ - ከአዳምና ከሔዋን። አንድ ጊዜ ፈጠረ፣ በኋላ ብዙ ተባዙ ባለው አምላካዊ ቃል  በመዋለድ የሰው ዘር ይቀጥላል።   o "...እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፦ ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥"  ዘፍ ፩፡ ፳፯ - ፳፰ o "አዳምም ለሚስቱ ሔዋን ብሎ ስም አወጣ፥ የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና።" ዘፍ ፫፣ ፳ · የምንኖርበትን ዘመን - እና - ስፍራ /ቦታ/ መደበልን።  በየት ዘመን እስከ ስንት ጊዜ፣ በየት ሃገር ከየትኛው ቤተሰብ እንደምንወለድ እድሜና ሥፍራ የመደበልን እግዚአብሔር ነው። · እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረበት ዓላማ እንዲፈልገው  ነው። በሰጠው ነጻነት ተጠቅሞ ፈልጎ፣ አግኝቶ ፣ ወዶ እንዲከተለው እና አብሮት እንዲኖር። · እግዚአብሔርን ስለመፈለግ ዳዊት እንዲህ ብሏል፡- "በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ እግዚአብሔርን  የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።"  መዝ ፻፬/፻፭፣ ፩ - ፬ እግዚአብሔርን የምንፈልገው ለምንድን ነው? ከላይ በጥቅሱ እንዳየነው፡-   1.  ልብን ደስ ስለሚያሰኝ፣-እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው o ዘላቂ እና ከውስጥ - ከልብ - የሆነ እውነተኛ ደስታ ያለው እግዚአብሔርን በመፈለግ ነው። በሌላም ቦታ እንዲህ ተብሏል፡- "ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።" ፊልጵ ፬፣ ፬ 2. ለመጽናት፣-   እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም፡ o አንድ ሰው በተቸገረ ጊዜ - እገሌን ነው የምፈልግ እርሱ ይምጣልኝ - ይላል። በፈተና በሕይወት ውጣ ውረድ ለመጽናት የሚረዳን የሚያስፈልገን እግዚአብሔር ብቻ ነው። 3. ለሚፈልጉት ምላሽ ስለሚሰጥ፣- እግዚአብሔር እርሱን ለሚፈልጉት ምላሽ ይሰጣል እንጂ ተደብቆ አይቀመጥም። "ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና።"  ዕብ ፲፩፣ ፮ o በፍለጋ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ ሁለት ነገር ማመን አለበት፡- ፩. እግዚአብሔር እንዳለ - እግዚአብሔር አለ። ፪. ለሚፈልጉትም ዋጋ ይሰጣል። - ይመልሳል። ይገናኛል። - ፈልጉት ስንባል ሩቅ  ወይም ረቂቅ ስለሆነ ግን አይደለም። ምክንያቱም "ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።"  ተብሏልና፤ ስለዚህ  ቅርብ ነው። - በምናየው በተፈጥሮ፣ ዓለምን በማስተዳደሩ /በመግቦቱ/ ፣ በነፍሳችን ጥማት… እግዚአብሔርን መፈለግ ግድ ይላል። እግዚአብሔር የራቀ / ሩቅ/ የሚሆነው ዓይነ-ልቦናችን በኃጢአት ጨለማ ሲያዝ ብቻ ነው። - ማንም ሰው ከአምልኮ ውጪ አይደለም፤ ከእግዚአብሔር / ከአምላክ/ ፍለጋ ተለይቶ አያውቅም። ሁሉም ሰው የሚታመንበት፣ ተስፋ የሚያደርገው፣ አንድ አካል ይፈልጋል። እግዚአብሔርን የማያውቁና የማያምኑ ሰዎች እንኳን -ጨርሶ እምነት የለሽ- አይደሉም። የሚታመኑበት ይለያይ እንደሆነ እንጂ  የሆነ አንድ የሚታመኑበት ነገር አላቸው፤ - ጣኦት፣ ሃብት፣ …. - እግዚአብሔርን ፍለጋ አስፈላጊነቱ /አንገብጋቢነቱ/- በጨለማ ውስጥ መብራት የመፈለግ ያህል ነው። ካለዚያ የሚታይ ነገር አይኖርም፣ የሕይወት ጉዞው መደናበር ነው የሚሆነው። ሕይወት ያለእግዚአብሔር ጨለማ ናት። "እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም የምትል ይህች ናት።" ፩ ዮሐ ፩፣ ፭ ፪. እግዚአብሔርን እንዴት ነው የምንፈልገው? ሀ. በአእምሮ፡- /በዕውቀት/ -  ምናልባትም እየመረመሩ o ምናልባት ለምን ተባለ? በተሰጠን አእምሮና ነጻ ፈቃድ በምናደርገው ምርምር እግዚአብሔርን ላንደርስበት እንችላለን። በዓለማዊ ጥበብና ምርምር ብቻ እግዚአብሔርን ማግኘት አይቻልም። " በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች፥ በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአልና።"   ፩ ቆሮ ፩፣ ፳፩። o ሰው ከተፈጠረ በኋላ የሚያውቀው እግዘአብሔር የፈጠረውን መልካም ብቻ ነበር፤ የተከለከለችውን -በተለምዶ ዕጸ-በለስ - ዛፍን ከበላ በኋላ ክፉንም አወቀ፤ ለዚህ ነው ዛፊቱ፡- «፣መልካምና ክፉን የምታሳውቅ ዛፍ»  የተባለች። ከውድቀት በኋላ ሰው በተሰጠው አእምሮ በዘመናት ሁሉ እውቀቱን በማሳደጉ ወደ እነዚህ ሁለት ጎራዎች ሄዷል፡- ወደ መልካምና ወደ ክፉ። መልካም ውጤት - ምድርን ለኑሮ አመቺ ማደረጋችን - መጓጓዣ፣ መኖሪያ…ማሻሻላችን ክፉ ውጤት - ሰው ሰራሽ የጥፋት ስጋቶች መፈጠራቸው፡- ጠመንጃ፣ መርዝ….መሥራታችን ስለዚህ አዳም /ሰው/  መልካሙንና ክፉን  የምታስታውቀውን ዛፍ ስለበላ እና ስላወቀ - ያወቀውን መተግበር ጀመር። o   የተሰጠን አእምሮ ዋናው ዓላማ በተፈጠርንበት መልካምነት፣ መልካም የሆነውን ፍጥረት በማስተዳደር ፣መልካም የሆነውን እግዚአብሔርን በመፈለግና /በመምረጥ/ ለማምለክ ነበረ። o ፍለጋውን ማስቆም አይቻልም፤ ሰው ወደደም ጠላም በፍለጋ ውስጥ ነው። ዓይን እስካለ አላይም ማለት አይቻልም፤ እግርም እስካለ አልሄድም ማለት አይቻልም። o ፍለጋው ወደ እግዚአብሔር ሊያደርሰን ይችላል፣ ከእግዚአብሔር ሊያርቀንም ይችላል። እንደ ምንሄድበት አቅጣጫ ይወሰናል። o ስለዚህ በሕይወት ጉዞ ላይ- በነገሮች ፍለጋ ዋናው ቁምነገር  ዝምብሎ መሄዳችን /መኖራችን/ ሳይሆን ወዴት እየሄድን ነው?  የሚለው ነው። ዋናው አቅጣጫው ነው።  ግን እግዚአብሔርን የምንፈልገው የት ነው? ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤” ዮሐንስ 10፥4 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤” ዮሐንስ 10፥4 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ         ክፍል ፬ ችሎታዊ  መገለጫዎቹ፡- ፩. ሁሉን ቻይ / ኤልሻዳይ/፡- የሚሳነው ነገር የለም። ዘፍ ፲፰፣ ፲፬ o በእግዚአብሔር ዘንድ «አይቻልም» የሚባል ነገር  የለም። "ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፤" ፪ ነገ ፫፣ ፲፰ እንደተባለው። o እግዚአብሔር ነገሮችን የማያደርጋቸው ወይም የሚያዘገያቸው ስላልቻለ ሳይሆን ስላልፈለገ ወይም ጊዜያቸው ስላልሆነ ነው። o ስናጠፋ ወዲያው የማይቀጣን እንድንመለስ ጊዜ እየሰጠን ነው። "ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።"  ፪ ጴጥ ፫፣፱ ሁሉን ቻይ እና ታጋሽ የሆነውን የእግዚአብሔርን ነገር፡- -«...አላወቅህምን? አልሰማህምን? እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል።…»   ኢሳ ፵፣ ፳፯ - ፴፩ ፪. ሁሉን አዋቂ ፡- ከእርሱ እውቅናና ውጪ የሆነ/ሊሆን የሚችል ነገር ፈጽሞ የለም። "የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም። የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው? ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው?"  ሮሜ ፲፩፣ ፴፫ - ፴፭ - በሁሉም ቦታ ያለ ሁሉን ነገር በአንድ ጊዜ ነው የሚያውቀው፣ --  አማካሪ የለውም። ሞራላዊ መገለጫዎቹ፡  ከሰው ባሕርያት ጋር በሚነጻጸር መልኩ ስንገልጸው፡- እግዚአብሔር፡- ቅዱስ ነው፦  ልዩ ነው፤ የሚመስለው የለም ማለት ነው። - ከኃጢአት ጋር ሊስማማ/ሊኖር አይችልም። ለዘላለም ከኃጢአት የተለየ ነው፤ ጻድቅ ነው፡- ፍትሐዊ ባሕርይውን ያሳያል። ጥፋትን አይቶ አያልፍም፤ ይቀጣል። ፍቅር ነው፡-   ፍቅር የሚለውን ቃል አባቶች በየፊደሉ ሲተረጉሙት፡- ፍ፡- ፍጹም፣ ቅ፡- ቅዱስ፣ ር፡- ርህሩህ.. ስለዚህ ፍጹም፣ ቅዱስ፣ ርህሩህ የሆነ ፫ቱንም ያሟላ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ፡- እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፡- ፩ ዮሐ ፬፣ ፲፮ ጥበበኛ ነው፡-  የሚያደርገው ሁሉ እንከን/ ጉድለት የለበትም። ሁሉንም ነገር በጊዜው በጥሩ ሁኔታ ለተሻለ ዓላማ ያደርጋል።  « ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው»  መክ ፫፣ ፲፩ በዓለም ላይ ስንኖር እጅግ ጠቃሚና ወሳኙ ጉዳይ ምንድን ነው? ቢባል - እግዚአብሔርን ማወቅ, ነው፤ የሁሉም ነገር እና ጥያቄ መሠረታዊ መልስ ያለው በዚህ ውስጥ ነው። « አዎን፥ በእውነት ከሁሉ ይልቅ ስለሚበልጥ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ጌታዬ እውቀት ነገር ሁሉ ጉዳት እንዲሆን እቈጥራለሁ፤»  ፊልጵ ፫፣ ፰ እግዚአብሔርን / ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ -ለእርሱ ያለን ዕውቀት- ከሌላው ነገር ሁሉ ጋር ሲነጻጸር ጉዳት ማለት ነው። እግዚአብሔርን ለማወቅ እርሱ ራሱን በሰው - በሚገባን የራሳችን ባሕርይ - የገለጠልን በኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ስለዚህ ክርስቶስን ስናውቅ እግዚአብሔርን እናውቃለን ማለት ነው። ሙሉ በሙሉ አውቀን ባንጨርሰውም - እርሱን እያወቅን ፡ ስለእርሱ ያለን እውቀት እየጨመረ  ይሄዳል። ባወቅነው መጠንም ከእርሱ ጋር ያለን ቀረቤታ/ግንኙነት/ እየጨመረ ይሄዳል። ስለእርሱ ያለን እውቀት ሙሉ የሚሆነው በሰማያዊ መንግሥት በዘላለማዊ ሕይወት ከእርሱ ጋር ስንኖር ነው። o "በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው።  እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።…" መዝ ፻፬/፻፭፣ ፫-፬ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚሰጠው የዘላለም ሕይወት እግዚአብሔርን ማወቅ ስለሆነ ነው። "እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።"  ዮሐ ፲፯፣ ፫ የዘላለም ሕይወት እግዚአብሔርን ቀጥሎም ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ነው። የመረጃ ሳይሆን የሕይወት እውቀት፣ የግንኙነት፣ የልምምድ እውቀት… ማለት ነው፡ --ምን እንደምንፈልግ ሳናውቅ ወደ ፍለጋ አንገባም፡- የምንፈልገውን ነገር አውቀን ነው ወደ ፍለጋ የምንገባው። ስናገኘው እንድንረዳው። እግዚአብሔርን ማወቅ - እግዚአብሔርን እንድንፈልግ ያደርገናል። በቀጣይ - እግዚአብሔርን ፍለጋ / የፈጣሪ መኖር/ እናያለን። ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “የኃይላቸው ትምክሕት አንተ ነህና፥ በሞገስህም ቀንዳችን ከፍ ከፍ ይላልና።” መዝሙር 89፥17 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “የኃይላቸው ትምክሕት አንተ ነህና፥ በሞገስህም ቀንዳችን ከፍ ከፍ ይላልና።” መዝሙር 89፥17 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ      ክፍል ፫ የእግዚአብሔር ባሕርያት ስለእግዚአብሔር ለማወቅ ፍንጭ የሚሰጡን፣ የሚገልጡት ባሕርያቱ ናቸው። ተፈጥሯዊ መገለጫዎቹ፡-  ከሌላው ፍጥረት ጋር በሚነጻጸር መልኩ ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ-ቃላት በተቀመጠው መሠረት በ፬ መልኩ ይገለጻል። ፩. አይታይም፡-  እግዚአብሔር ረቂቅ - መንፈስ ነው። ደቃቅ ሆኖ በአጉሊ መነጽር /በማይክሮስኮፕ/ ወይም ሩቅ ሆኖ በርቀት - መነጽር /በቴሌስኮፕ/ የሚታይ አይደለም። - « ብቻውን አምላክ ለሚሆን ለማይጠፋው ለማይታየውም ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን።»  ፩ ጢሞ ፩፣ ፲፯ o በስሜት ሕዋሳቶቻችን ልንደርስበት አንችልም። o ከምናውቃቸው በመጀመር የርቀት /የመርቀቅ/ ቅደም ተከተል ሲቀመጥ ፡ ከግዙፍ ወደ ረቂቅ፡- መሬት - ውኃ- እሳት - ነፋስ - ነፍስ - መላእክት -የሥላሴ አካል። ይህ ማለት ከመሬት ውኃ ይረቃል፣ ከውሃ እሳት፣ ከእሳት ነፋስ፣ ከነፋስ ነፍስ፣ ከነፍስ መላእክት፣ ከመላእክት ደግሞ ሥላሴ ይረቃሉ። አባቶች አንደሚያስተምሩት የመላእክት እና የሥላሴ አካል ግን የአንዲት ጎመን ዘር እና የተራራ ያህል አይገናኝም፣ አይነጻጸርም። o እግዚአብሔር የማይታይ እንጂ የማያይ አይደለም። o በእምነት ግን በሕይወታችን እናየዋለን። ፪. አይወሰንም፡- በስፍራ/በቦታ የተወሰነ አይደለም። በዚያ አለ፤ በዚህ የለም፤ ይሄዳል/ይመጣል… አይባልም። «ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ አለህ። ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ። እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከባሕር መጨረሻም ብበርር፥ በዚያ እጅህ ትመራኛለች፥ ቀኝህም ትይዘኛለች።»  መዝ ፻፴፱/፻፵፣ ፯ - ፲ o ምሉእ በኰለሄ - በሁሉም ቦታ አለ።  ይህ ሲባል ግን በየቦታው ያሉት ነገሮች ሁሉ ግን የእርሱ አካል ናቸው ማለት አይደለም። ፫. አይለወጥም፡- በጊዜ ተጽእኖ ሥር አይደለም። ሁሉም ነገሮች በጊዜ ብዛት ይለወጣሉ፣  «…. ደግሞ። ጌታ ሆይ፥ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ፥ ሰማዮችም የእጆችህ ሥራ ናቸው፤   እነርሱም ይጠፋሉ አንተ ግን ጸንተህ ትኖራለህ፤ ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃሉ፤  እንደ መጎናጸፊያም ትጠቀልላቸዋለህ ይለወጡማል፤ አንተ ግን አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም»   ዕብ ፩፣ ፲ - ፲፪ o ጊዜ/ዘመን ሁሉንም ያስረጃል። እግዚአብሔር ግን ዘመንን ራሱን ያስረጀዋል። o እግዚአብሔር ብሉየ-መዋዕል፡- የተባለው በግዕዝ - ዘመናትን የሚያስረጅ ማለት ነው። o እግዚአብሔር የሚያልፍበት ወይም የሚጠብቀው ጊዜ የለም።  ትናንት/ነገ - የዛሬ ዓመት የሚቀጥለው ዓመት.. የሚባል የለም።  በእርሱ ዘንድ ሁልጊዜ ዛሬ ነው። «ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ። አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል።»  ራእ ፩፣ ፰ o ሰው ሊገዛ/ ሊቆጣጠር የሚችለው ያለውን /የአሁኑን/ ብቻ ነው። ለዚያውም የሚታየውን እና የቻለውን ያህል። o እግዚአብሔር ግን ያለውን፡ የነበረውን/ያለፈውን/ የሚመጣውንም ሁሉ ይገዛል፤ ይቆጣጠራል፣ ያስተዳድራል። o በእኛ ዘንድ ሺህ ዓመት በእግዚአብሔር ዘንድ እንደ አንድ ቀን ነው ሲባል እግዚአብሔር የሺ ዓመቱን ሥራ ዛሬ እንደተደረገ ያህል ነው - በዝርዝር የሚያውቀው። እኛ እንረሳለን። o እግዚአብሔር ስለማይለወጥ ስለእርሱ በትክክል የገባን ነገር አይለወጥም። ያው ነው ማለት ነው። ስለእርሱ በእርግጠኝነት መናገር እንችላለን። እንዲህ ነው ብለን።  ስለ ሰው ግን እገሌ እንዲህ ነው ብለን በእርግጠኝነት መናገር አንችልም ፣ ሰው ይለወጣልና። - እግዚአብሔር ስለማይለወጥ ዘላለማዊ  ነው፣ o የነበረ፣ ያለ ፣ የሚኖር ነው። ለሙሴ እንደተናገረው። - እግዚአብሔርም ሙሴን፦ «ያለና የሚኖር» እኔ ነኝ አለው፤ ዘፍ ፫፣ ፲፬ ፬. አይከፋፈልም o እግዚአብሔር ግን ከዚህ እና ከዚህ ነገሮች የተዋቀረ/የተገኘ ነው አይባልም። o እርሱ ሁሉን ያስገኘ እንጂ እርሱን የሚያስገኙ/ያስገኙ ነገሮች የሉም። ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “አቤቱ፥ እንዳንተ ያለ የለም፥ በጆሮአችንም እንደሰማን ሁሉ ከአንተ በቀር አምላክ የለም።” 1 ዜና 17፥20 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “አቤቱ፥ እንዳንተ ያለ የለም፥ በጆሮአችንም እንደሰማን ሁሉ ከአንተ በቀር አምላክ የለም።” 1 ዜና 17፥20 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

#እራሳችንን_እንመርምር ለእግዚአብሔር የምናቀርበው መሥዋዕት ምን አይነት ነው? በዋጋ፣ ያለዋጋ፣ በቸልተኝነት . . . “. . . ለአምላኬም ለእግዚአብሔር የሚቃጠል መሥዋዕት ያለ ዋጋ አላቀርብም አለው። ዳዊትም አውድማውንና በሬዎቹን በአምሳ ሰቅል ብር ገዛ።” 2ኛ ሳሙኤል 24፥24 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።” 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ         ክፍል ፪ ማወቅ ማለት ምን ማለት ነው?  o የእገሌን ቤት አውቀዋለሁ ማለት ውስጡን ክፍሎቹን፣ ዕቃዎቹን ወዘተ.. ማለት ነው።ቤቱን ማወቅ ግን ባለቤቱን ማወቅ ላይሆን ይችላል። ግዑዝ ነገሮችን በማየት፣ በመጎብኘት ማወቅ ይቻላል። o ሕይወት ያላቸውን ነገሮች ግን አውቃለሁ ለማለት ቀርበን የጠባይ ልውውጥ ማድረግን ይጠይቃል። ለምሳሌ አንድ ሰው «ይህን ውሻ አውቀዋለሁ፣» ቢል እንስሳው ውሻ መሆኑን እያለ አይደለም። ግን ካሁን ቀደም ከውሻው ጋር የተለየ ልምምድ አለው፡- ጠባዩን ስላየ - ኃይለኛ ስለሆነ/ ስለነከሰው ወዘተ ሊሆን ይችላል። o እንስሳን ለማወቅ ለማላመድ ጥቂት ቀናት/ ሳምንታት ሊጠይቅ ይችላል። ከዚህ በላይ ደግሞ ሰውን ማወቅ ቀላል አይደለም። ምክንያቱም ስለሰዎች የምናውቀው እኛ ባየናቸው፣ በሰማናቸው... መጠን ብቻ አይደለም፤ ሰዎቹ ስለራሳቸው ማንነት በለቀቁት መጠን ጭምር ነው። -- ዋናው ይህ ነው። ስላየናቸው አብረናቸው ስለኖርን ብቻ ላናውቃቸው እንችላለን። --- ሰዎችን ለማወቅ ወሳኙ ነገር ሰዎቹ ራሳቸውን የሚገልጡበት ሁኔታ ነው። ስለእግዚአብሔር ማወቅ ሰዎች ሁሉ ከእነዚህ ከ፫ቱ አይወጡም፡ ፩. ጭራሽ አለማወቅ- ሰምተው የማያውቁ… ጥቂት ሰዎች ፪. የተሳሳተ ማወቅ- ያወቁት መስሏቸው፣ ግን በደንብ አለማወቅ፡- አለመገናኘት።… አብዛኛው ሰው ፫. ትክክለኛ እውቀት፡- ማወቅ፣ ማናገር፣ እርሱም- መስማት፣ መመለስ። … የተወሰነ ሰው እኛ የትኛው ውስጥ ነን? በትክክል እናውቀዋለን ወይ? ያ ከሆነ ስናናግረው የሚሰማ እና የሚመልስ እንደሆነ ሊገባን ይገባል። እግዚአብሔርን ማወቅ ማለት በትክክል ካየነው በእግዚአብሔር ዘንድ መታወቅ ማለት ነው። ከእርሱ ጋር መስማማት ፣ በግል ሕይወት መለማመድ እና መቀራረብ፣ መገናኘትን... ያካትታል። ፪. እግዚአብሔርን እንዴት እናውቀዋለን? - እግዚአብሔርን ለማወቅ እኛ ምን ማድረግ አለብን ወይም  ምን ማድረግ እንችላለን? - እግዚአብሔርስ እንዲታወቅ እርሱ ምን ማድረግ አለበት/ ነበረበት? ወይም ምን አድርጓል? - እኛ ተምረን፣ ተመራምረን እንደርስበታለን? - አንችልም። እንኳን እርሱን የፈጠረውንም ተምረን አልጨረስነውም። - እግዚአብሔርን ሙሉ በሙሉ አውቅን መረዳት/ መጨረስ እንችላለን? -- አይቻልም፡- ምክንያቱም፡- o   ፩. የቋንቋ ውስንነት o   ፪. የአእምሮ ውስንነት - ስለእግዚአብሔር ልናውቅ የምንችለው o   ፩. እርሱ የገለጠልንን ያህል o   ፪. እኛም መረዳት የቻልነውን ያህል እግዚአብሔር የመገለጥ አምላክ - እርሱ ራሱን ገልጧል / እየገለጠም ነው። እነዚህ መገለጥ ሁለት ዓይነት ናቸው። ፩. አጠቃላይ መገለጥ፡-  በተፈጥሮ እና  በኅሊና ፪. ልዩ መገለጥ፡-  በመጽሐፍ ቅዱስ እና በኢየሱስ ክርስቶስ o በተፈጥሮ እና በመጽሐፍ ቅዱስ - ስለእግዚአብሔር እናውቃለን። o በኅሊና እና በኢየሱስ ክርስቶስ - እግዚአብሔርን እናውቃለን። - ስለእግዚአብሔር ማወቅ - እግዚአብሔርን ከማወቅ ፈጽሞ የራቀ እና የማይወዳደር ነው። አንዲት ዓሳ እናቷን - « ሁልጊዜ ሲወራለት የምንሰማው ውኃ ምን ዓይነት ነው? የት ነው ያለው?»  ብላ ስትጠይቅ፣ እናቲቱ ዓሳ ከውቅያኖሱ ሥር ልጇን አስቀምጣ፣ በፕሮጄክተር  ፎቶ፣ ፊልም እያሳየች - «ውኃ ይህን ይመስላል» ብላ ካስተማረቻት በኋላ -- «እንግዲህ ትንሽ ፍንጭ ካገኘሽ ራስሽ ሂጂና በዙርያሽ እንዲሄድ በውስጡ ሆነሽ ተለማመጂ»  ብላ ለቀቃቻት። o መጽሐፍ ቅዱስ መምህራን ተፈጥሮ፣-  ስለ እግዚአብሔር እንድናውቅ ያደርጉናል። ስለውኃ በሰሌዳ፣ በስዕል፣ በቤተሙከራ /በትንሽ ብርጭቆ/ መማር ማለት ነው። o በልባችን ክርስቶስን አምነን ወደ ሕይወታችን ስናስገባው  - ወደ ውቅያኖሱ ገባን - እግዚአብሔርን ማወቅ እንጀምራለን። ሕይወታችን እንዲመራ፣ እንዲገዛ እንዲቆጣጠር እንፈቅድለታን - በእርሱ ሙላት ውስጥ እንሆናለን። ያን ጊዜ የሕይወት የመኖር ትርጉም እየገባን ይሄዳል። ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።” ገላትያ 6፥9 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptu
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።” ገላትያ 6፥9 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ                ክፍል ፩ "....በሕይወትም ትኖራላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።" ሕዝ ፴፯፣፮ በሕይወት የመኖራችን ዓላማ እግዚአብሔርን ማወቅ ከሆነ እግዚአብሔርን እናውቀዋለን ወይ? "ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን፥ ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እወድዳለሁና።"  ሆሴዕ ፮፣ ፮ ፩. እግዚአብሔርን ማወቅ ያለብን ለምንድን ነው? ለሕይወት ስኬት - ለምድራዊ አስቤዛ ኑሮ መሟላት? ከኑሮ ጭንቀት ለመላቀቅ - ሰላምና እረፍት ለማግኘት? ለጠቅላላ ዕውቀት/ለመረጃ?  - አለ ወይስ የለም? እውነቱን ለማወቅ-  እግዚአብሔር ሲባል - ወደ አእምሮአችን / ወደ ምናባችን የሚመጣው ምስል ምንድን ነው? o በሩቅ በሰማይ ያለ- ቁልቁል የሚያይ ሽማግሌ መሰል…...? o በሥላሴ ስዕል እንዳሉት ፫ ተመሳሳይ የተቀመጡ ሽማግሌ መሰል.....? o ወይም ሌላ ምስል.......? እግዚአብሔርን ስናስብ ትዝ የሚለን ምንድን ነው? - እግዚአብሔርን ወይስ ከእግዚአብሔር የሆኑ ነገሮችን፤  - እግዚአብሔር በሕይወታችን በኃይሉ እየሠራ ነው? ወይስ በአእምሮአችን እንዲሁ የተቀመጠ ከብዙ ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው? - እግዚአብሔርን ነው ወይስ ስለእግዚአብሔር ነው የምናውቀው? ስለጃንሆይ ልናውቅ እንችላለን፤ ጃንሆይን ግን ላናውቃቸው እንችላለን፤ አላየናቸውም፣ አላገኘናቸውምና። - እግዚአብሔርን እናውቀዋለን? - እርሱስ ያውቀናል? - እንተዋወቃለን? - እናናግረዋለን?  - ከሆነስ -- ይሰማናል? -- ይመልስልናል? - እንደሚመልስልን ይሰማናል? ከእነዚህ ጥያቄዎች አንዱ መልሳችን «አይ» ከሆነ - እግዚአብሔርን አላወቅነውም። ወይም ስለእግዚአብሔር ያወቅነው አልገባንም። እግዚአብሔር ሊታወቅ ይችላል? ወይስ አይችልም? "የምታመልኩትን እየተመለከትሁ ሳልፍ። ለማይታወቅ አምላክ የሚል ጽሕፈት ያለበትን መሠዊያ ደግሞ አግኝቼአለሁና። እንግዲህ ይህን ሳታውቁ የምታመልኩትን እኔ እነግራችኋለሁ።"  የሐዋ ፲፯፣ ፳፫ "እናንተስ ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ፤ እኛ መዳን ከአይሁድ ነውና ለምናውቀው እንሰግዳለን።"      (ዮሐ ፬፣፳፪) እግዚአብሔርን የምናመልከው አውቀነው ነው? ወይስ ባይገባንም ማምለክ ስላለብን? ወይስ እንዲሁ በዘልማድ ሌሎች ስላደረጉት? እግዚአብሔርን ማወቅ/አለማወቅ ያለው ተጽእኖ - በሕይወታችን ለነገሮች ቅድሚያ የምንሰጠው ካለን የእግዚአብሔርን እውቀት አንጻር ነው። በደንብ ካወቅነው/ከገባን እንኖርለታለን። እንኖርበታለን። -- ካልሆነ እንደ ትርፍ/ተጨማሪ እናየዋለን። - በሕይወታችን በሚገጥሙን ፈተናና እና ችግሮች የምንወስዳቸው ውሳኔዎች እግዚአብሔርን ምን ያህል እንደምናውቀው ያሳያሉ። - ሕይወትን ለመኖር የሚያስመኘው ስኬቶቻችን ናቸው  - ወይስ በዓላማ መኖራችን? የዚህ ዓለም ስኬት መጨረሻው ምንድን ነው?.. ምን ስናገኝ ነው በቃ የምንለው? - በየዕለቱ/ በየጊዜው አእምሮአችን የሚይዘው ምንድን ነው? በልባችን እና በአእምሮአችን ሰፊውን ስፍራ የያዘው እግዚአብሔርን ከማወቅ / ካለማወቅ ጋር የሚያያዝ ነው። አንድ ባለሃብት ለአንድ አገልጋይ ያለውን ሰፊ የልማት/ የእርሻ ቦታ ሲያስጎበኘው ከስፋቱ የተነሳ በአንድ ቀን ተጎብኝቶ ሊያልቅ አልቻለም። ኋላ ባለሃብቱ «እንዴት ነው? ምን ተሰማህ?» ብሎ የሙገሳ ቃል ሲጠብቅ አገልጋዩ፡ «ይህንን ሁሉ ሃብት ለማስተዳደር ልብህ በዚህ ስለሚጠመድ ያሳዝነኛል» አለው።     የዚህ ባለሃብት ልብ አሁን እየኖረበት ካለ ዓለም ጋር የተቆራኘ ነው። ለአሁኑ እና ለዘላለሙ፣ ላለውና ለሚመጣው ነገር ሁሉ የምንሰጠው ዋጋ/ቦታ ባለን የእግዚአብሔር ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ነው። ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures