en
Feedback
ቅዱሳት መጻሕፍት

ቅዱሳት መጻሕፍት

Open in Telegram

በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures

Show more
7 833
Subscribers
+724 hours
+357 days
+15630 days
Posts Archive
የቀጠለ... የበሰለ ክርስቲያን ምልክቶች                  5. የበሰለ ክርስቲያን አንደበቱን/ንግግሩን ይጠብቃል - አንዳንድ ጊዜ ሃኪሞች ሊመረምሩን ሲሉ እስቲ ምላስህ ጎልጉል ይሉናል፤ እግዚአብሔርም አንደበታችን ያለውን ኀይል ያውቃል (ያዕ.3፡2)። ራስን መግዛት የሚጀምረው አንደበትን በመግዛት ነው። ያልተገሩ አንደበቶች በአብያተ ክርስቲያናት የሚፈሥሠውን ንጹህ ውሃ ሲያደፈርሱ ይስተዋላሉ። የተጀመሩ ታላላቅ መዋቅሮች በኀሜት፣በአሉባልታና በከንቱ ወሬ ሳይተገበሩ ንድፍ ብቻ ሆነው ቀርተዋል።  ሃሜት ገዳይ ነው፤ ስም አጥፊነት ከነፍሰ ገዳይነት እኩል ነው። መንፈሳዊ ሰው የሚለየውም ከአንደበቱ ስለሌላው ክርስቲያን በሚናገረው ነገር ነው (ያዕ.1፡26)።    በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አሉባልታን፣ኀሜትንና ወሬን የሚያመላልሱትን የሰይጣን ወኪሎችን ማስተናገድ የለብንም። በአገራችን “ወገንህ ሲታማ ለኔ ብለህ ስማ” ይባል የለ፤ ሌላውን የሚያማልን ሰው ነገ እኛን እንደማያማ ምንም ማስተማመኛ የለንም። በቤተ ክርስቲያን የወሬ ቋትና የአሉባልታ ሉካንዳ ነጋዴዎችን በጽድቅ ጅራፍ ከመቅደሱ ገፍታ ልታስወጣ ይገባታል። ስውር የአጋንንት ወኪሎች ናቸውና ነጻ ይውጡ ወይ ለቅቀው ይውጡ! የበሰለ ክርስቲያን አንደበቱን የጠበቀ፣ንግግሩ በጨው እንደተቀመመ በጸጋ የሆነና በሚናገረውም የሚያንጽ እንጂ የሚያፈርስ አይደለም።  6. የበሰለ ክርስቲያን አስታራቂና የሰላም ሰው ነው - በአማራው አገር ልጅ ሲወለድ ባልና ሚስት ከተለያዩ “አደፍርስ” ብለው ይጠሩታል፤ ልጅ ሲወለድ ባልና ሚስት ከታረቁ ግን “አንዳርጌ” ይሉታል። መቼም ጥሪያችን ለአንዳርጌነት እንጂ ለአደፍርስነት አይደለም (ያዕ.3፡18)። ጠብና መለያየት የመንፈሳዊ ብስለት ምልክቶች አይደሉም ይልቁንም የአለመብሰል እንጂ። በቆርንጦስ ቤተ ክርስቲያን የነበረውን “መደፍረስ” ተመልክቶ ጳውሎስ “ገና ህጻናቶች” ናችሁ አላቸው (1ቆሮ.3፡1-13)። “ኸረ እነ እከሌ የበሰሉ ናቸው ታዲያ እነርሱ እንኳን ይጣላሉ” የሚል ቢኖር የብስለትን መለኪያ በትክክል እንዳልተረዳ እንዲያስተውል እመክራለሁ። የበሰለ ክርስቲያን የሰዎችን ሰላም መጠበቅ፣ማስታረቅና ልዩነቶችን ማጥበብ አንዱ ምልክቱ ሲሆን በአካሄዱም ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ለመኖር የሚተጋ ነው።  ማጠቃለያ፦ እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው መንፈሳዊ ብስለትን የምንለካባቸው ጥቂቶች መስፈርቶች ናቸው። ታዲያስ አንተስ በትህትና እያደግህ ነው? ጌታንስ በትዕግስት በተግዳሮት ወቅቶች በጸሎት ትጠብቀዋለህ ወይስ የራስህን መንገድ ትሄዳለህ? ለእግዚአብሔር ቃል ያለህ መታዘዝ ምን ያህል ነው? ለድኆች ግድ ይለሃልን? ከአንደበትህ ለሚወጣው ትጠነቀቃለህ? አደፍርስ ነህ ወይስ አንዳርጌ?   ህይወትህን መዝን! ምንጭ:- amharicgospel.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ጳውሎስ በነበረበት ዘመን ቆሮንቶስ የምን አውራጃ ዋና ከተማ ነበረች?
Anonymous voting

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “በዚያ ጭልጥ ባለና አስፈሪ ምድረ በዳ፣ በዚያ በሚያስጠማና ውሃ በማይገኝበት ደረቅ መሬት፣ መርዘኛ እባብና ጊንጥ ባለበት ምድረ በዳ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “በዚያ ጭልጥ ባለና አስፈሪ ምድረ በዳ፣ በዚያ በሚያስጠማና ውሃ በማይገኝበት ደረቅ መሬት፣ መርዘኛ እባብና ጊንጥ ባለበት ምድረ በዳ መራህ፤ ከጽኑ ዐለትም ውሃ አፈለቀልህ።” ዘዳግም 8፥15 (አዲሱ መ.ት) ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

የበሰለ ክርስቲያን ምልክቶች               የፍራፍሬዎች  መብሰል የሚታወቅበት አይነተኛው መንገድ ቅምሻ ነው። የበሰለ ሙዝ በቆዳው ቢያስታውቅም ሲቀመስ ግን የብስለቱ መጠን ምን ያህል እንደሆነ ይታወቃል። በውጪ ገጽታ ታቶ መታወቅ ከማይችሉ ነገሮች አንዱ የሰው የውስጥ መንፈሳዊ ይዘትና ጥልቀት እንዲሁም ብስለት ነው። መንፈሳዊ ብስለት በተለምዶ ከአፋችን በሚወጥ “ክርስቲያናዊ አባባሎች” የሚለካም አይደለም።  እንደ ክርስቲያን የራሳችንንም ሆነ የሌሎች “ክርስቲያን ነን የሚሉትን” ሰዎች ብስለት የምንለካባት አይነተኛ ሚዛን ምን ይሆን? በተለምዶ ሳቂታና  ተግባቢ፤ ድምጻቸውን ከፍ አድረገው የሚስቁ መንፈሳዊ ሰዎች አይመስሉንም፤ አንዳንዴም መጽሐፍ ቅዱሳቸው በየንግግራቸው መካከል የማይጠቃቅሱ መንፈሳዊ ነገር የገባቸውም አይመስለንም። የስነ መለኮት ዲግሪ ቢኖረን መልካም ባይኖረን ደግሞ እንዲኖረን መትጋቱ  ክፋት ባይኖረውም፤ የዲግሪ መኖርና አለመኖር በመንፈሳዊ ህይወት የመብሰልና ያለመብሰል ምልክት ሊሆን አይችልም። እና ታዲያ የክርስቲያንን መንፈሳዊ ብስለት በምን ይለካል?  1. የበሰለ ክርስቲያን ትሁት ሰው ነው::   ሐዋርያው ያዕቆብ በያዕቆብ መልዕክቱ 1፡1 ላይ “… የእግዚአብሔርና የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ … “ ብሎ ራሱን ይጠራል።  በመጽሐፍ ቅዱሳችን ከስድስት የማያንሱ ሰዎች “ያዕቆብ” ተብለው ተጠርተዋል። የኢየሱስ ክርስቶስ ወንድም የነበረው ያዕቆብ ከትንሳዔው በፊት ኢየሱስን ይከተል እንደነበር የሚጠቁም ምንም ማስረጃ የለም (ዮሐ.7፡5)። በህይወቱ ከተከሰተው አስደናቂ ለውጥም የተነሳ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን አዕማድ ተብለው ከሚጠሩት አንዱ እንደነበር ጳውሎስ ይመሰክርለታል  (ገላ.1፡9፤2፡9፤ ሐዋ.12፡17)። ለ15 አመታትም በመጀመሪያይቱ ቤተ ክርስቲያን ስመጥር አገልጋይ ነበረ (ገላ.1፡18)።  ያዕቆብ ሩጫውን ሲጨርስም በሰማዕትነት ነበር የሞተው።     ለቤተ ክርስቲያን በጻፈው መልዕክቱ ግን ራሱ ባሪይ (ዱሎስ) ብሎ ይጠራል። ዱሎስ ማለት ከባርነት የተለቀቀ ግን በራሱ ፈቃድ ከአሳዳሪ ጌታው ጋር የሚኖር ማለት ነው። በብሉይ ኪዳን ነጻ መውጣት ሲችል በፈቃዱ ከጌታው ጋር ለመኖር የሚፈልግ ባሪያ በከተማይቱ በር ጆሮውን ተበስቶ ከጌታው ጋር መኖሩን ይቀጥላል። ምልክትነቱም በፈቃዱ መገዛቱን ያሳያል። ሐዋርያው ጳውሎስ በገላ.6፡17 የኢየሱስ ክርስቶስን ማህተም በስጋው እንደተሸከመ የሚናገረውም ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ነው። ምልክቱም በፈቃድ ራስን ዝቅ አድርጎ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ (ባሪያ) መሆን ነው። ባርነት የራስን ክብር ጥሎ በትህትና የጌታን ፈቃድ ማድረግ ነው። አማኝ ይህ ሲገባውና እርምጃ የጌታው ፈቃድ አድራጊ፤ ራሱንም እንደጌታ ባሪያ አድርጎ መቁጠር ሲጀምር መንፈሳዊ ህይወቱ መብሰሉን የምንመዝንበት አይነተኛ መለኪያ ነው።  2. የበሰለ ክርስቲያን በተግዳሮት ሰዓታት የጸሎት ህይወትና ታጋሽነት ይታይበታል:: የጸሎት ህይወት ማለት አካል በስጋ ተላብሶ በውስጡ እንዲቆም የሚያደርገው የውስጥ አጥንቶቹ (ስኬለተን) እንደሆነ እንዲሁ  የጸሎት ህይወት የአማኝ የውስጥ ጥንካሬ ሰጪ ክፍሉ ነው። በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ሦስት እንደምንመለከተው ታሪክ ሲድራቅ ሚሳቅና አብድናጎም ንጉሱ እንዲሰግዱ ላቀረበላቸው ትዕዛዝ እንቢ ያሉት ቀደም ብለው ሌሊት ከዳንኤል ጋር መጸለይን የተለማመዱ ስለሆነ ነው። ንጉሱንም ያስቆጠው ይኸው ጥንካሬያቸው ነው። በተግዳሮት ሰዓት አማኝ የራሱን ወይንም የሰይጣንን ፈቃድ እንዲያደርግ ግፊ የሚመጣበት ጊዜ ስለሆነ በጸሎትና በትዕግስት በመቆም ማዕበሉን ማሳለፍ ይችላል። የበሰለ ክርስቲያን በነገሮችን ግፊት ከእግዚአብሔር ፈቃድ አያፈነግጥም፤ በጊዜውም አለጊዜውም ይታገሳል፤ ይጸናልም (ያዕ.1፡2፤ 5፡13፤ 7-12)። እውነተኛ ባህርያችን ደግሞ የሚገለጠው በተግዳሮትና ጨለማ በሚመስሉ ጊዜያቶች ነው። በተግዳሮት ጊዜያት በትዕግስትና በጸሎት ጌታን መጠበቅ ከቻለ አማኝ መንፈሳዊ ብስለት አለው ማለት ነው። 3. የበሰለ ክርስቲያን ቃሉን  ይታዘዛል:: ቅዱሳት መጽሐፍት የእግዚአብሔርን ቃል እንድንታዘዝ ይመክሩናል (ያዕ.1፡22፤ 2፡14፣ 18)። የእግዚአብሔር ቃል ልንኖርበትና ልንታዘዘው የተሰጠን የህይወት መምሪያች ነው። በሌላ አነጋገርም የመተዳደሪያ ደንባችን ነው። ደንብ የተሰጠው እግዚአብሔርን በሚያከብር ህይወት መስመርን ጠብቀን እንድንራመድ እንጂ ልንታሰርበት አይደለም። ቃሉን በመጠበቅ እውነተኛ መንፈሳዊ አርነትን  እንለማመዳለን። ቃሉን የማያከብር እግዚአብሔርን አያከብርም፤ ለቃሉ የማይገዛ ለእግዚአብሔር የማይገዛ ነው። ለቃሉ ከመታዘዝ አሻፈረኝ ብለን እግዚአብሔርን ማምለክም ሆነ ማገልገል አንችልም። የበሰለ ክርስቲያን ግን የእግዚአብሔር ቃል በህይወቱ የመጀመሪያውን ስፍራ ይዟል፤ይታዘዘዋል እንዲሁም ፍሬን ያፈራበታል። 4. የበሰለ ክርስቲያን ለድሆች ይራራል:: ያዕቆብ በመልዕክቱ ጨምሮ የሚያሳየው ሌላው የበሰለ ክርስቲያን ከራሱ ባሻገር የሌሎችን ጉዳትና ማጣት የሚሰማው መሆኑን ነው (ያዕ.1፡27፤2፡2-6)። እውነኛ የበሰለ ክርስቲያን እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው አህያ አይሆንም። እግዚአብሔር የድኅ አደጎች አባት ነው ተብሎ በብሉይ ኪዳን (አሞጽ 4፡1፤ 5፡11-12፡14፤ መዝ.69፡33) መጠቀሱ የሚያመለክተን እግዚአብሔር ለድሆች የሚራራ መሆኑን ነው። በጥንቱ አለም 90% ህዝብ ድሃ ነበር።  በዚህም ዘመን በአለም ውስጥ ያለው ህዝብ 100 ነው ብለን ብንወስድ፤ 57ቱ የሚኖሩት በእስያ ሲኖሩ፤ 21 በአውሮጳ፤ 14 በሰሜንና በደቡብ አሜሪካ እንዲሁም 8ቱ በአፍሪካ ይኖራሉ። በየአመቱ የእስያና የአፍሪካ ህዝብ በቁጥር እየጨመረ ሲሄድ የሰሜን አሜሪካና የአውሮጳ ህዝቦች ግን ቁጥራቸው 50% እየቀነሰ ይሄዳል። የሚገርመው ግን 50% የአለም ኀብት ያለው ከመቶው በ6ቱ ሰዎች እጅ መሆኑ ነው። ስድስቱም ደግሞ አሜሪካኖች ናቸው ነው። ከመቶ የአለም ህዝብ 70% ማንበብና መጻፍ አይችሉም፤ ከመቶ 50 ሰዎች ከምግብ ማጣት ጋር የተያያዘ በሽታ አለባቸው። 35ቱ ንጹህ የሚጠጣ ውሃ የላቸውም፤ 80ዎቹ ሰው ሊኖርበት በማይገባና በማይመጥን ስፍራ ይኖራሉ። ከመቶው አንድ ሰው ብቻ ዩንቨርሲቲ ወይንም ኮሌጅ ይማራል።     በምድራችን ድኅነት ምንድነው ተብሎ የምንነጋገርበት ጉዳይ አይደለም። ዙሪያ ገባው ድኅነት ፍጥጥ ብሎ በመንገድ እየተጋፋን በቤተ ክርስቲያናችን በሁሉ ስፍራ የምናየው ጉዳይ ነው። ቤተ ክርስቲያን ብዙ ማከናወን ያለባት ራዕዮች አሏት፤ ከሌሎቹ ባልተናነሰ ሁኔታም የረድዔትን አገልግሎት ልታከናውን ይገባታል። የበሰለ ክርስቲያንም ለድኆች የሚራራና በሚችለው ሁሉ ችግራቸውን በሚችለው አቅሙ ለመቅረፍ የሚያግዝ ነው እንጂ ድሎቱ አስከባሪ ብቻ ሊሆን አይገባውም።  ይቀጥላል...    ምንጭ:- amharicgospel.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ለአክሪጳም፦ በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ።” ቆላስይስ 4፥17 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Ho
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ለአክሪጳም፦ በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ።” ቆላስይስ 4፥17 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ዕለት ዕለት ማዳኑን አውሩ።” 1 ዜና 16፥23 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scrip
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ዕለት ዕለት ማዳኑን አውሩ።” 1 ዜና 16፥23 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ዓለምን የሚያሸንፈው እምነታችን ነው!! “ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና the lust of the flesh, የዓይን አምሮት the lust of the eyes, ስለ ገንዘብም መመካት the pride of life, ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም።” 1ዮሐ.2፡15-16 የሰው ልጅ በእግዚአብሔር እጅ ተበጅቶ በዔደን ገነት ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የሚፈትኑትና ከእግዚአብሔር ፈቃድና ሃሳብ እንዲጎድል እየጠለፉ የሚጥሉት ሦስት ጣምራ ጠላቶች አሉት። እነርሱም ከላይ በምናነበው መልእክት ውስጥ የተገለጡት፤ #የሥጋ ምኞት፣ #የዓይን አእምሮትና #እኔነት ናቸው። “እኔነት” ወይም በአማርኛው መጽሐፍ ቅዱሳችን “ስለገንዘብ መመካት” ተብሎ የተተረጎመውን ሃሳብ ስናብራራው፤ በዚህ ሕይወት ባለን ነገር ወይም በራስ የመተማመን፣ የመኮፈስና ከፍ-ከፍ የማለት፣ ገደብ የለሽ ሃብትና ክብር፣ ከዚህ ዓለም የሆነውን ጥበብና እውቀት የማግኘትና ሁልጊዜም ለማግኘት የመጓጓት ፍላጎት እንደሆነ እንረዳለን። “ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው።” ሮሜ.8፡6   እግዚአብሔር የመጀመሪያውን ሰው በራሱ መልክና ምሳሌ ፈጥሮና አበጃጅቶ በዔደን ገነት ሲያስቀምጠው ሁለት መንገዶችን በፊቱ አኑሮ ነው። (በምድር ከሚኖሩ አሕዛብ ሁሉ መካከል ለይቶ ርስት የሰጣቸውን እሥራኤላውያንን ወደርስታቸው ለማስገባት በምድረ በዳ በመራቸውም ጊዜ የእሥራኤል አምላክ እነዚህን ሁለት መንገዶች በፊታቸው አኑሮ እንደነበር በዘዳ.30፡19-20 ላይ ተጽፎ እናገኛለን) በዔደን ገነት መካከል በነበረው የሕይወት ዛፍ ተምሳሌትነት የተገለጠውና እግዚአብሔርን የሕይወትና የህልውና ማዕከል በማድረግ፣ ለቃሉም በመኖርና በመታዘዝ፣ ወይም በመንፈስ በመመላለስ ወደሚገኘው የማይጠፋ ሕይወት የሚወስደውና፤ መልካሙንና ክፉውን በሚያስታውቀው ዛፍ ተምሳሌትነት የተገለጠውና ራስን የህልውና ማዕከል በማድረግ፣ በራስ ፈቃድና ሃሳብ ወይም እንደ ሥጋ ፈቃድና ሃሳብ እንደወደዱ በመመላለስ ከእግዚአብሔር ወደመለየትና ወደሞት የሚወስደው መንገዶች ናቸው። በሴቲቱና በእባቡ መካከል በተደረገው ‘ውይይት’ የተቀሰቀሰውና ኋላም አሸንፎ የወጣው ሁለተኛው መንገድ ነው። “ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ (የሥጋ ምኞት)፣ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ (የዓይን አምሮት)፣ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ (እኔነት) አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።” (ዘፍ.3፡6) የሰው ልጅ በፊተኛው ሰው አዳም አለመታዘዝ ወይም በእነዚህ ሦስቱ ጣምራ ጠላቶቹ አማካኝነት ከእግዚአብሔር ሕይወት ተለይቶ ወድቆበት ከነበረው የሞትና የጨለማ ጉድጓድ የወጣው፤ በኋለኛው (በመጨረሻው) አዳም መታዘዝ ነው። የኋለኛው አዳም መታዘዝ በይፋ መታየትና መገለጥ የጀመረው ደግሞ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው” የተባለው የቀደመው እባብ በዔደን ገነት የፊተኛውን ሰው ፈትኖ ከሕይወት መንገድ እንዳሳተው፣ ለአርባ ቀንና ሌሊት በጾምና በጸሎት በደከመበት ምድረ በዳ ኢየሱስ ክርስቶስንም ፈትኖ ለመጣል ያደረገው ሙከራ በከሸፈበት ወቅት ነው። በዚህ የምድረበዳ ፈተናም ወቅት በፈታኙ በኩል ለኢየሱስ ክርስቶስ ቀርቦለት የነበረው ፈተና፤ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር እጅ ተበጅቶ በዔደን ገነት ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የሚፈትኑትና ከእግዚአብሔር ፈቃድና ሃሳብ እንዲጎድል እየጠለፉ የሚጥሉት ሦስቱ ጣምራ ጠላቶቹ ማለትም የስጋ ምኞት፣ የዓይን ዓምሮትና እኔነት ነበሩ። (ማቴ.4፡1-11 ይነበብ) “በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።” (ዮሐ.16፡33) እውነተኛው ክርስትና ሲገባን በእነዚህ ሦስቱ ጣምራ ጠላቶቻችን የሚደርስብንን ፈተና የሚያህል ሌላ ታላቅ መከራ በዚህ ዓለም ላይ እንደሌለ እንረዳለን። በራዕይ መጽሐፍ ውስጥ “እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው” የተባሉት፣ ልብሳቸውን በበጉ ደም አጥበው ያነጹት ናቸው። በበጉ ደም ታጥቦ የሚነጻው ልብሳችን ደግሞ በዚህ ዓለም በሚገኝ ነውርና እድፍ፣ ማለትም በሥጋ ምኞት፣ በዓይን አምሮትና በእኔነት ያደፈው ማንነታችን ነው። በበጉ ደም ታጥቦ መንጻት ማለትም፣ በድካማችንና በኃጢአታችን ከምንወነጀልበት የዲያብሎስ ክስ ነጻ ከመውጣት ጀምሮ፣ የሥጋችንን ድካም ምክንያት አድርጎ በእኛ የሚሰራውን የኃጢአት ኃይልና ሕግ ፈጽመን ድል እስከምናደርግበትና እስከምናሸንፍበት፣ በዚህም የሥጋ ሥራ ከተባሉት የሞት አገልጋዮች አርነት ወጥተን በመንፈስ ፍሬ ወይም በክርስቶስ ሕይወት ሙላት እስከምንሞላበት የሕይወት ከፍታ የሚደርስ ነው። ዓለምን ማሸነፍና “ድል ነሺ” የመባል ትርጉሙም ይኸው ነው። (ገላ.6፡14 ይመልከቱ) እኛ ለዓለም - ዓለምም ለእኛ የተሰቀለበት የክርስቶስ መስቀል፣ ዓለምንና በዓለም ያሉትን ማለትም የሥጋ ምኞት፣ የዓይን ዓምሮትንና እኔነትን ከእኛ ፈጽሞ ያስወገደና የሚያስወግድ የእግዚአብሔር ጥበብ ነው። አንድ ክርስቲያን የክርስቶስ የመስቀል ላይ ሞት ከእርሱ ሕይወት ጋር የተያያዘበትን ሙሉውን እውነት ካላየ፣ እግዚአብሔር በሕይወቱ ሊፈጽመው ያሰበውን የከበረ ዓላማ መገንዘብ ካለመቻሉም በላይ፣ በክርስቶስ ኢየሱስ የሰጠውን የከበረ ሕይወት በሙላት ሊያጣጥም አይችልም። ክርስቶስ በመስቀል ላይ የከፈለው ቤዛነታችን እርሱም የበደላችን ስርየት ከእግዚአብሔር ጋር የታረቅንበት ብቸኛው መንገድ እንደመሆኑ፣ እኛም ከክርስቶስ ሞት ጋር መተባበራችን ወይም አሮጌው ሰዋችን ከክርስቶስ ጋር መሰቀሉን መረዳታችን ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ የምናሸንፍበት የድላችን ዋስትና ነው። የክርስቶስ ሕይወት ሕይወታችን የሚሆነው ሞቱም ሞታችን ከሆነ ብቻ ነው። ለዚህም ነው የተወደደው ወንድማችን ጳውሎስ፡- “ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው” ያለው። (ገላ.2፡20) ክርስትና የምንለው የከበረ ኑሮና ሕይወት በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምንኖረው ኑሮ ነው። ወይም በሌላ አገላለጥ ክርስትና እኛ የምንኖረው ሳይሆን የእግዚአብሔር ልጅ በእኛ የሚኖረው ኑሮ ነው!! ይህም እግዚአብሔር ከዘላለም ዘመናት በፊት ሰውሮት የነበረው፣ ልጁ በሥጋ በመምጣቱ ለቅዱሳኑ ሁሉ የገለጠው የከበረ ምሥጢር ነው። ምሥጢሩም የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ በእኛ ዘንድ  መሆኑ ነው። ዓለምንም የሚያሸንፈው፤ ማለትም የሥጋ ምኞት፣ የዓይን አምሮትና እኔነት ከተባሉት ክፉ ጠላቶቻችን አርነት የሚያወጣን በእኛ ያለው ክርስቶስ እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የሚመሰክረው እምነታችን ነው።   “ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንምየሚያሸንፈው እምነታችን ነው። ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው?”     1ዮሐ.5፡4-5 ምንጭ:- tibebe-belay.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “በእርሱም እናንተ ደግሞ ለእግዚአብሔር መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ አብራችሁ ትሠራላችሁ።” ኤፌሶን 2፥22 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “በእርሱም እናንተ ደግሞ ለእግዚአብሔር መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ አብራችሁ ትሠራላችሁ።” ኤፌሶን 2፥22 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

The Confessions of Saint Augustine ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study

እግዚአብሔርን ማወቅ           ክፍል ፲፪      (የመጨረሻ ክፍል) የእግዚአብሔር ሥራ "ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና። እንግዲህ። የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? አሉት። ኢየሱስ መልሶ፦ ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው።"    (ዮሐ 6፣ 27 – 29) - ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሕዝቡ እንጀራና አሳ አበርክቶ ስለሰጣቸው - ለዚያ ሲሉ ነበር የተከተሉት። ለዚህ መልስ ሲሰጣቸው - ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፡፡ የምትከተሉኝ ለምን ዓላማ ነው? እንደ ክርስቲያን /የክርስቶስ ተከታዮች/ በዚች ምድር የመኖራችን ዓላማ ምንድን ነው? ብንል መልሱ የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ነው። -  እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታል፡- ወልድ የአብ ልጅ ነው። አብን መስሎ፣ አብን አክሎ የተገኘ፣ - ማኅተም፡- ሲደረግ ቅርጹ በወረቀቱ ላይ በትክክል ያርፋል። የአብን ማንነት በሥጋ /በሰው/ ታትሞ ያየነው በክርስቶስ ነው። - ወልድ ሰው ሲሆን አብ አትሞታል። የምወደው ልጄ ይህ ነው ብሎ ማረጋገጫ /ማኅተም/ አድርጎበታል። - ስለዚህ በክርስቶስ የሆነውን ማንኛውም መንፈሳዊ ሥራ እግዚአብሔር ከእኔ ነው ብሎ እውቅና /ማረጋገጫ / ይሰጠዋል- ማለት ነው። የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ነው። -ይህ የእግዚአብሔር ሥራ ምንድን ነው? የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? - የሚለው ተገቢ ጥያቄ ነው። - በራሳችን እንደሚመስለን - እርሱን ደስ የሚያሰኙ ጥሩ ጥሩ ነገሮችን ማድረግ። ጾም፣ ጸሎት፣ መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ፣ ጥሩ ሰው መሆን፣….የእኛ ድርጊቶች። ክርስቶስ ግን ለዚህ ጥያቄ የሰጠው መልስ፡- አጭር፣ ግልጽ፣ ቀላል ነው። -  እርሱ በላከው እንድታምኑ። - በክርስቶስ ማመን። --- ምንም ጥረት አይጠይቅም። ድርጊት/እንቅስቃሴ /ውጣ ውረድ የለበትም። - በቃ፤ በልብ ማመን- መቀበል። - ማመን፡- ለመዳን ከዚያም ለማዳን።  የሚሠራው እርሱ ነው።…… የእግዚአብሔር ሥራ ከመጀመሪያው፡-  ዓለምን መፍጠር። እግዚአብሔር ዓለምን የመፍጠር ስራውን ጨርሶ - አረፈ- ተብሏል።  ከዛ በኋላ ምን ይሠራል? ቦዘኔ ነው? ምን እያደረገ ነው ያለው በአሁኑ ሰአት?. ከሠራው ሥራ ሁሉ አረፈ…ይላል፤ ያረፈው ከመፍጠር ነው፤ /ዘፍ ፪፣ ፪-፫/ ይህም ማለት አዲስ ነገርን ከማስገኘት። እንጂ ሥራ ፈታ ማለት አይደለም። በመላው ፍጥረት ላይ ያለው ቀጣይ ሥራው ማስተዳደር፣ መጠበቅ፣ መመገብ ነው። - እግዚአብሔር ፍጥረታትን ለመመገብ ምን ይሠራል? - ወዲያ- ወዲህ ሽር ጉድ .. ይላል? በዚህ ዘመን የሚኖሩትን 7 ቢሊየን ሕዝብ እንደ አንድ ሰው ይመግባል፣ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን እንስሳት፣ አራዊት፣ አእዋፋት… ይመግባል፣ ያስተዳድራል። እንዴት? - ሥርዓት /ሲስተም/ በመዘርጋት ነው። አንዱ አንዱን እንዲመግብ - የዝናብ፣ የፀሐይ፣ የነፋስ… ሥርዓት። የእጽዋት፣ የእንስሳት አመጋገብ ሥርዓት..ወዘተ… በሰዎች ላይ ያለው ዋናው ስራ ማዳን ነው። በዚህ ጉዳይ እስከዛሬ ይሠራል። ምክንያቱም o ሰዎች ከመበደል ስላላረፉ፣ እርሱም ከማዳን አላረፈም። o በአሁኑ ሰአት የእግዚአብሔር ዋና የማያቋርጥ ሥራ ምንድን ነው? - ማዳን ነው። ፩. እግዚአብሔር በምን? - በቃሉ ይሠራል። - መፍጠር፡- እግዚአብሔር ዓለምን በቃሉ ፈጠረ፣ እግዚአብሔር ይህን ግዙፍ/ረቂቅ ድንቅ ዓለም ለመፍጠር ቃሉ በቂ ነበርና "በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ፤"   መዝ ፴፫፣፮ - ማዳን፡- በአካላዊ ቃሉ በወልድ - በኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን አዳነ። - የጠፋውን የሰውን ልጅ ቃሉ ሥጋን ለብሶ - ሰው ሆኖ - ተሰቅሎ አዳነን፤ "ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥"    ዮሐ ፩፣ ፲፬ ቃል - ወልድ ሥጋን ከለበሰ በኋላ - የእግዚአብሔርን ሥራ ሲሠራ ኖረ፤ "ኢየሱስ ግን፦ አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለሁ ብሎ መለሰላቸው።"  ዮሐ ፭፣ ፲፯ ይህን የተናገረው ፴፰ ዓመት በአልጋ ተኝቶ የነበረውን ሰው ከፈወሰ /ካዳነ በኋላ ነው። አባቴ ይሠራል፣ እኔም እሠራለሁ - ያለው ማዳንን ነው። - ሥጋዊ ደኅንነት። ዋናው ትልቁ ሥራው - ስለእኛ በመስቀል ላይ ቤዛ ሆኖ መሞት ነው። "እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤"  ዮሐ ፲፯፣ ፬ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሰውን የማዳን ሥራውን አጠናቋል። ጨርሷል። ሁሉ ተፈጸመ። - ሥራው ያለቀ ነው። ሰዎች ይህን የተፈጸመ ሥራ እንዲቀበሉ /እንዲያምኑ/ መናገር ማወጅ ብቻ ነው የሚጠበቀው፤ ይህም በሐዋርያት ተጀምሮ - ዛሬም በአገልጋዮች /በእኛ/ ይቀጥላል። በእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ውስጥ የሰው ድርሻ ምንድን ነው?/ ስንት % ነው? ማመን ብቻ። በክርስቶስ የተሠራውን / የተፈጸመውን የመስቀል ሥራ መቀበል። ስለዚህ የሰው ድርሻ ስንት % ነው? -- ምንም።  0 %. :: መፈጠራችን / መወለዳችን ያለእኛ አንዳች አስተዋጽኦ ሙሉ በሙሉ እንደተከናወነ፡- መዳናችንም እንዲሁ ሙሉ በሙሉ በእርሱ የተፈጸመ ነው። የማዳኑን ስራ መቀበል - በእርሱ የማዳን ሥራ ውስጥ ድርሻ ማስቀመጥ አይደለም። መቀበሉ፣ ማመኑ ለራሳችን መዳን ነው። "ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥"  መዝ ፫፣ ፰ ፤   "…..የሰውም ማዳን ከንቱ ነው።" መዝ ፻፰፣ ፲፪ ስለዚህ፡- "ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆች አትታመኑ።" መዝ ፻፵፮፣ ፫ ይልቅስ፡- "ሰው ዝም ብሎ የእግዚአብሔርን ማዳን ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው።"   ሰቆ ፫፣ ፳፮ ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ስምዖንም መልሶ፦ አቤቱ፥ ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም፤ ነገር ግን በቃልህ መረቦቹን እጥላለሁ አለው።” ሉቃስ 5፥
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ስምዖንም መልሶ፦ አቤቱ፥ ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም፤ ነገር ግን በቃልህ መረቦቹን እጥላለሁ አለው።” ሉቃስ 5፥5 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

አቂላ እና ጵርስቅላ ከሮም ወጥተው ወደ ቆሮንቶስ ከተማ የመጡት ለምን ነበር?
Anonymous voting

እግዚአብሔርን ማወቅ         ክፍል ፲፩ የእግዚአብሔር መልክ መታየት - ለውስን ፍጡር - ፊት ለፊት በብሉይ ኪዳን - ለሙሴ "እኔ አፍ ለአፍ በግልጥ እናገረዋለሁ፥ በምሳሌ አይደለም የእግዚአብሔርንም መልክ ያያል በባሪያዬ በሙሴ ላይ ትናገሩ ዘንድ ስለ ምን አልፈራችሁም? አለ።"    ዘኁ ፲፪፡ ፰ ሙሴ ክብርህን አሳየኝ ባለው ጊዜ፡- "እግዚአብሔርም አለ፦ እነሆ ስፍራ በእኔ ዘንድ አለ፥ በዓለቱም ላይ ትቆማለህ ክብሬም ባለፈ ጊዜ በሰንጣቃው ዓለት አኖርሃለሁ፥ እስካልፍ ድረስ እጄን በላይህ እጋርዳለሁ እጄንም ፈቀቅ አደርጋለሁ፥ ጀርባዬንም ታያለህ ፊቴ ግን አይታይም።"    ዘጸ ፴፫፣ ፲፰ - ፳፫፡ - በኋላ ከሲና ተራራ ሲወርድ ፊቱ አንጸባረቀ፡- ጨርቅ ሸፈነው። "አሮንና የእስራኤልም ልጆች ሁሉ ሙሴን ባዩ ጊዜ፥ እነሆ የፊቱ ቁርበት አንጸባረቀ ወደ እርሱም ይቀርቡ ዘንድ ፈሩ።"  ዘጸ ፴፬፣ ፳፱ - ፴፭ - በትክክል ከእግዚአብሔር ጋር በመንፈስ ከተገናኘን የእግዚአብሔር መልክ ይሳልብናል። እርሱን እናንጸባርቃለን። ለእኛ ላይታወቀን ይችላል። የሚያዩን ግን ያውቃሉ። በአዲስ ኪዳን፡- ፫ ቱ ሐዋርያት- በደብረ ታቦር "በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።…."  ማቴ ፲፯፣ ፩ - ፰ - በእግዚአብሔር መልክ - በእርሱ ፊት መኖርን የመሰለ መልካም ነገር የለም። ለአሕዛብ ሐዋርያ ሳውል - ጳውሎስ "ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤ በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ። ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ።…" የሐዋ ፱፣ ፩ - ፰ - ጌታን ፊት ለፊት በብርሃን መልክ አየው። በቀን በቀትር ስለሆነ ያየው ጌታ ከፀሐይ ብርሃን ይበልጥ አብርቷል ማለት ነው። /የሐዋ ፳፪፣፮/ ፬.የእግዚአብሔር መልክ - በክርስቶስ ተመለሰልን። "እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።"  ፪ ቆሮ ፫፣ ፲፰። አዳም ከበደለ በኋላ በራሱ መልክ ልጅን ሲወልድ ይሄ በኃጢአት ማንነት የወደቀ የሰው ዘር በመጽሐፍ ቅዱስ - አሮጌ ሰው ተብሏል። አስወግዱት ተብለናል። ዕውቀት "እርስ በርሳችሁ ውሸት አትነጋገሩ፥ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥ የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል።"   ቆላ ፫፣ ፱ - ፲ ጽድቅ ቅድስና "ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።"  ኤፌ ፬፣ ፳ - ፳፬ የተፈጥሮ መልካችን የሚመለሰው - እግዚአብሔርን መምሰል የምንችለው - በክርስቶስ - ነው። "ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኵር ይሆን ዘንድ፥ አስቀድሞ ያወቃቸው የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና፤"   ሮሜ ፰፣ ፳፱ - እግዚአብሔር ዓለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የወሰነው - በመልኩ የፈጠረው/የሚፈጥረው/ ሰው ያን መልክ በኃጢአት እንደሚያጣው ስላወቀ- በልጁ መልኩ /የሰው/ እንዲመለስለት ማቀዱ ነው። በተፈጥሮ /በመፈጠር/ ያገኘነውን እና በኃጢአት ያጣነውን መልክ የሚመለስልን በጥረታችን ሳይሆን በመወለድ ነው። - በመንፈስ ዳግም በመወለድ። - ልጅ አባቱን ይመስላል፣ ይህም በሌላ ነገር፡ በሥራ…ሳይሆን በመወለድ ነው። - እኛም በክርስቶስ ስናምን ከመንፈስ ቅዱስ ዳግም እንወለዳልን። እግዚአብሔርንም እንመስላለን። - እግዚአብሔርን መምሰል ከእኛ ከልጅ ይጠበቃል። - እግዚአብሔርን መምሰል - በሕይወታችን በኑሯችን ይንጸባረቃል። o   ዕውቀት፡- እግዚአብሔርን ማወቅ፡- ዮሐ ፲፯፣ ፬ እግዚአብሔር በልጁ የሰጠን የዘላለም ሕይወት እርሱን ማወቅ ነው።- መገናኘት o ጽድቅ፡- ኃጢአታችን በክርስቶስ የመስቀል ዋጋ ስለተከፈለ እኛ ነጻ ነን። አሁንም ለምንሠራው ኃጢአት ንስሐ ስንገባ -በደሙ ስርየት እናገኛለን። o ቅድስና፡- ከኃጢአት የተለየ ሕይወት መለማመድ። ከክፉ ሥራ ለመራቅ በመልካም ሥራ መጠመድ፡፡ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ፍሬዎቹን ያፈራል። ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ጠላቶቻችንም ይህ ነገር እንደ ደረሰልን፥ እግዚአብሔርም ምክራቸውን ከንቱ እንዳደረገው ሰሙ፤ እኛም ሁላችን ወደ ቅጥሩ እያንዳንዳችን
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ጠላቶቻችንም ይህ ነገር እንደ ደረሰልን፥ እግዚአብሔርም ምክራቸውን ከንቱ እንዳደረገው ሰሙ፤ እኛም ሁላችን ወደ ቅጥሩ እያንዳንዳችን ወደ ሥራችን ተመለስን።” ነህምያ 4፥15 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ        ክፍል ፲ ፬. የእግዚአብሔር መልክ "እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው።"  ዘፍ ፩፣ ፳፯ መልክ፡- ሲባል የማይታየውን የሰውን ረቂቅ ማንነት /መንፈስ/ ለማመልከት ነው። የእግዚአብሔር መልክ በሰው፡ በ፫ መልክ ይታያል፤ ፩. በነፍሱ፡  እግዚአብሔር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ ሲፈጥረው ማንኛችንን ነው የሚመስለው? የሰው መልክ የተለያየ ነው። ጥቁሮች፣ ነጮች፣ ቀዮች፣….  በሰው ላይ ያረፈው መልክ በሥጋ ሳይሆን በነፍስ። ሥጋ ከአፈር ነው። ነፍስ ከእግዚአብሔር እስትንፋስ ናት። የእርሱን ነገሮች በተመጠነ ሁኔታ ወደ እኛ አሳርፏል። o የነፍስ ባሕርያት፡፫ - አሳቢነት፣ ተናጋሪነት፣ ዘላለማዊነት:: o ስለዚህ ነፍስ፡- ከእንስሳት የምንለይበት፣ እግዚአብሔርን የምንመስልበት ነው። ፪. በኑሮ/በአኗኗሩ፡  ሰው ዘላለማዊ ሆኖ ሲኖር - ፫ መገለጫዎች አሉት።  ፩. ዕውቀት፡- ከራሱ ጋር ያለውን ግንኙነት ያሳያል፣ በዚህ ውስጥ፡- የመምረጥ የመወሰን፣ የማድረግ/መሥራት/ ነጻነት አለን፤…ባወቅነው/በገባን ጉዳይ ላይ ምላሽ እንሰጣለን ይህም ስሜት ይባላል፤ በመጨረሻ ባወቅነው ነገር ተንተርሰን በጉዳዩ ላይ ፈቃዳችን እንገልጻለን። ይህም ውሳኔ ይባላል። ፪. ቅድስና፡- ከሌላው ጋር ያለውን ግንኙነት ያሳያል።- በዚህ ውስጥ፣ ያለኃጢአት / ያለበደል/ በሰላም መኖር፣ ኅብረት፣ሌላውን የመፈለግ /የመርዳት/ ነገሮች ይገለጻሉ። ፫. ጽድቅ፡- ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት ያሳያል፡- በዚህ ውስጥ ያለኃጢአት ከአምላክ ጋር የመኖር፣ አምላክን የመፈለግ፣ የመታመን /ተስፋ የማድረግ ሁኔታዎች አሉ። በሥልጣን፡-  መግዛት ፣ ማስተዳደር - በሁለት ጉዳዮች፡ ራሱን እንዲገዛ  ዓለምን / ተፈጥሮን እንዲገዛ የእግዚአብሔር መልክ ሲባል መንፈሳዊ /ረቂቅ / የሆነ ጉዳይ ነው፡ እግዚአብሔርን መምሰል ነው። ሰው በነፍሱ በተሰጠው ነጻነት በእግዚአብሔት ላይ በማመጹ - መልካም ብቻ የሚያውቅ እና የሚኖር የነበረው ክፉንም አወቀ። - በውስጡ የነበረውን የእግዚአብሔር መልክ አጣ። ስለዚህ የራሱን መልክ ያዘ፣ ክፉና ደግ ያለበት። ይህንም ለትውልድ አስተላለፈ፡፡ በእግዚአብሔር መልክ ተፈጥሮ ሲኖር የነበረው አዳም ከበደለ በኋላ ልጅን በመልኩ ወለደ። "አዳምም ሁለት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ልጅንም በምሳሌው እንደ መልኩ ወለደ" ዘፍ ፭፣ ፫። ስለዚህ የአዳም በኃጢአት የወደቀ ማንነት /መልክ/ በሰው ዘር ሲተላለፍ ኖረ። ይህን በአዳም በኃጢአት ያጣናቸውን ኋላ በክርስቶስ ተመልሰውልናል። - እግዚአብሔርን መምሰል። ፪. ከውድቀት በኋላ የእንስሳት መልክ "የማይጠፋውንም የእግዚአብሔር ክብር በሚጠፋ ሰውና በወፎች አራት እግር ባላቸውም በሚንቀሳቀሱትም መልክ መስለው ለወጡ።"   ሮሜ ፩፣ ፳፫ - ሰው ከውድቀት በኋላ የእግዚአብሔርን መልክ /ክብር/ ሲያጣ የራሱን መልክ ያዘ - በሚጠፋ ሰው። -  ከዚህ የሚብሰው ግን የእንስሳትን መልክ መያዛችን ነው።  አራት እግር ባላቸው በሚንቀሳቀሱትም.. o እንስሳዊ ባሕርይ፡- ገደብ ማጣት፣ ልቅ መሆን፣ መብላት-መብላት፣ መተኛት፣ ብቻ…. ፫. ከውድቀትም በኋላ ያልጠፉ የእግዚአብሔር መልክ መገለጫዎች- ሦስቱ የነፍስ ባሕርያት፡-  ፩. አሳቢነት- በነፍሳችን ከሌሎች ሕይወት ካላቸው የምንለይበት - አሳቢነት- ነው። ፪. ተናጋሪነት፡- ቋንቋ፣ መግባባት፣ ከመሰሎቻችን ጋር በውይይት መገናኘት… ፫. ሕያውነት፡- ዘላለማዊ ነን። ከነዚህ በተጨማሪ፡- ፬. አቅዶ - መሥራት፡- እግዚአብሔር ፈጣሪ ነው። ሁሉን አስገኝቷል። ሰውም በተሰጠው አሳቢ አእምሮ ካሉት ፍጥረታት - ብዙ ነገሮችን አስገኝቷል። - የምናየው ቁሳቁስ፣ ተክኖሎጂ፣ ኮምፒውተር… ፭. መንፈስ - ሰው የምንለው ሥጋ /ቁሳዊ/ ብቻ አይደለም። ከዚያ ያለፈ ማንነት አለን። መንፈሳዊነት። ይህም መንፈስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተካፈልነው ተፈጥሯዊ መልክ ነው። ፮. ማመዛዘን፡- ክፉና ደጉን መለየት- ሰው ቢማርም ባይማርም፣ እግዚአብሔርን ቢያውቅም ባያውቅም፣ በውስጡ የሕሊና ሚዛን /ዳኝነት/ ተቀምጦለታል፤ የዚህ መገለጫው ክፉ ስንሰራ የሕሊና ወቀሳ፣ መልካም ስንሠራ የሕሊና እርካታ አለ፤ ሕሊና የእግዚአብሔር ወኪል ነውና፤ እነዚህ ሰው በኃጢአት ከወደቀ ባኋላ ጨርሰው ያልጠፉ የእግዚአብሔር መልክ ናቸው፤ ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ታላቅነትህን የጸናችውንም እጅህን ለእኔ ለባሪያህ ማሳየት ጀምረሃል፤ በሰማይና በምድርም እንደ ሥራህ እንደ ኃ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ታላቅነትህን የጸናችውንም እጅህን ለእኔ ለባሪያህ ማሳየት ጀምረሃል፤ በሰማይና በምድርም እንደ ሥራህ እንደ ኃይልህም ይሠራ ዘንድ የሚችል አምላክ ማን ነው?” ዘዳግም 3፥24 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

እግዚአብሔርን ማወቅ            ክፍል ፱ የእግዚአብሔር ወዳጆች እግዚአብሔር ካደረገላቸው ነገር ጋር በማያያዝ ለልጆቻቸው ስም ያወጡ ነበር። ምናሴ - ማስረሻ፡- አባቱ ዮሴፍ መከራየን የአባቴን ቤት አስረሳኝ ሲል። ዘፍ ፵፩፣፶፩ ሳሙኤል - እግዚአብሔር ሰማ - መካኒቱ ሐና ጸሎቷን ስለሰማ ልጅ ስለሰጣት፡      ፩ ሳሙ ፩፣ ፳ o ዛሬ የእኛ ስም አወጣጥ ምን ይመስላል? - የእግዚአብሔር ወገን መሆናችንን የሚያሳይ ነው?.. ስሞቻችንን ብንፈትሻቸው፡ - ቦግ አለ፣ ዱብ አለ።  - ኩራባቸው፣ ሰጥአርጋቸው፣ ቦታዎችንም ከእግዚአብሔር ጋር በማያያዝ ይሰይሙ ነበር። "አጋር ከሣራ ተሰዳ ስትወጣ እግዚአብሔር አገኛት - በመልአኩ፡ እርስዋም ይናገራት የነበረውን የእግዚአብሔርን ስም ኤልሮኢ ብላ ጠራች የሚያየኝን በውኑ እዚህ ደግሞ አየሁትን? ብላለችና። ስለዚህም የዚያ ጕድጓድ ስም ብኤርለሃይሮኢ ተብሎ ተጠራ"፡  ዘፍ ፲፮፣ ፲፫ - ፲፬ እግዚአብሔር የወዳጆቹን ስም ይለውጣል። - አብራም /ታላቅ አባት/ - አብርሃም /የብዙዎች አባት/… - ያዕቆብ /አሰናካይ -ተረከዝ የሚይዝ (ሲወለዱ የኤሳውን እግር ይዞ ስለነበር ወላጆቹ ያወጡለት እግዚአብሔር ግን - እስራኤል - አለው፡- እግዚአብሔር ያሸንፋል ማለት ነው። ወዳጆቹ ወደፊት የሚሆኑትን በማየት ሕይወታቸውን ለመለወጥ ስማቸውን ከመለወጥ ይጀምራል። እኛም ዛሬ በወል ስም -በክርስቶስ - ክርስቲያን የተባልነው- ከስማችን ጀምሮ ሕይወታችን እንዲለወጥ የክርስቶስን ፈለግ በመከተል እርሱን ወደ መምሰል እንድናድግ ነው። የእግዚአብሔር ስም ለእኛ ምን ያስተምረናል? ይመልስልናል፡-  በስማችን ስንጠራ - አቤት- ብለን መልስ እንሰጣለን። በስም መጥራት የግንኙነቶች መጀመሪያ /ትውውቅ/ ፣ የሥራ መጀመሪያ ነው። ከጠራን በኋላ ወደ ጉዳያችን እንገባለን። o እግዚአብሔር ስም ያለው መሆኑ እንድንጠራው ያስችለናል። እርሱም  እንደሚመልስልን ማረጋገጫ ነው። ግንኙነትን ያመለክታል አጠራራችን ግንኙነታችንን ያመለክታል። ከስሞቹ የትኛውን እንደምንጠቀም የሚያሳየው ቅርበታችንን ነው፤ o ለምሳሌ እኔ ስጠራ፡- አቶ አብርሃም / ጋሼ አብርሃም ብሎ የሚጠራኝ - የሥራ ግንኙነትን ያሳያል፤ በክብር በሩቁ የምጠራበት ነው ፡፡  አብርሽ - የወዳጅ መጥሪያ ነው- ቅርበትን ያሳያል፤ ባባ - የአባትና የልጅ..የበለጠ ቅርበትን ያሳያል። o እግዚአብሔርን ስንጠራው የትኛውን እንጠቀማለን። እግዚአብሔር  የሚለው በተፈጥሮ ሁሉም እርሱን የሚጠራበት - የአክብሮት -የጌትነቱ-የፈጣሪነቱ ነው። ለእኛ ግን ከዚያም በላይ ነው። በሩቁ የምናከብረው ብቻ አይደለም። ቅርብ ነው- አባታችን ስለሆነ፤ ጌታ ስትጸልዩ፡- አባታችን ሆይ - በሉ  አለ "አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።"  ሮሜ ፰፣ ፲፭። አባ፣ አባት፡- የልጅነት - የቅርበት ስለሆነ- በዚህ እንድንጠራው ይፈልጋል። በከንቱ አይጠራም፡ -  ስም መጠሪያ ቢሆንም በትንሹ በትልቁ መጥራት የለብንም። ከ፲ቱ ትዕዛዛት አንዱ ሆኖ መሰጠቱ ይገርማል። ለስሙ ምን ያህል እንደሚጠነቀቅ/ እኛም እንድንጠነቀቅ በቋሚነት በ፲ቱ ትእዛዛት ተካተተ። "የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና።"   ዘጸ ፳፣ ፯ፀ ስሙን በከንቱ መጥራት -ማለት o ያለቦታው መጥራት - እግዚአብሔርን ለጥፋት ተባባሪ ማድረግ o ስሙን ማሰደብ፡- የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን በማይሆን ቦታ/ በኃጢአት/ ብንገኝ የሚሰደበው እግዚአብሔር ነው።  መጠጊያ - የጸና ግንብ ተብሏል። - "የእግዚአብሔር ስም የጸና ግምብ ነው ጻድቅ ወደ እርሱ ሮጦ ከፍ ከፍ ይላል።"  ምሳ ፲፰፣ ፲ መድኃኒት - "እንዲህም ይሆናል የእግዚአብሔር ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል እግዚአብሔርም እንደ ተናገረ፥ በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም መድኃኒት ይገኛል።"   ኢዩ ፪፣ ፴፪ "የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።"   ሮሜ ፲፣ ፲፫ o ስሙን መጥራት ማለት - ግንኙነትን የሚያሳይ ነው። ስላወቀን/ስላወቅነው ነው። በአጠቃላይ የእግዚአብሔር ስም፡- o ስለ እግዚአብሔር ማንነት እንድናውቅ ያደርገናል። o እንደስሙ እንደሚሠራ ያረጋግጥልናል። ሰዎች እንደስማቸው ላይሆኑ ይችላሉ። ትዕግስት - ተብለው ትዕግስት የሌላቸው ሊሆኑ ይችላሉ። እግዚአብሔር ግን እንደስሙ ይሠራል።/ ያደርጋል። o እንድንታመንበት ይረዳናል። የስሙ ኃይል ተግባራዊ መገለጫ - ኢየሱስ o ጌታ ሲወለድ መጠሪያው፡- ኢየሱስ - አዳኝ - በኃጢአት ስለጠፋን ያዳነን መድኃኒት /ማቴ ፩፣ ፳፩/  አማኑኤል - እግዚአብሔር ከእኛ ጋር - በኃጢአት ከእርሱ ርቀን ስለነበር እርሱ እኛን ፈልጎ መጣ፣ - ከእኛ ጋር ሆነ።  /ማቴ ፩፣ ፳፫/ ክርስቲያን የሚለው የወል ስማችን የክርስቶስ መሆናችንን ያመለክታል፡፡ በእኛ ላይ ባለቤት ነውና፣ በመፍጠርና በማዳን። ስለዚህ ባለቤት ካለን በእርሱ እና ለእርሱ ልንኖር ይገባል። o ከስም ሁሉ በላይ የሆነ - ሁሉ የሚንበረከክለት ስም "ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥… ነው።"  ፊልጵ ፪፣ ፱ - ፲ በሰዎች ምስጋና እና ልመና፣ ለአጋንንት ውጊያ የሚጠራ፣ "እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኋል። እስከ አሁን በስሜ ምንም አልለመናችሁም፤ ደስታችሁ ፍጹም እንዲሆን ለምኑ ትቀበሉማላችሁ።"   ዮሐ ፲፮፣  ፳፫ - ፳፬። o ምስጋና ወደ እግዚአብሔር የሚደርስበት "ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።"   ኤፌ ፭፣ ፳ o ሁሉ የሚደረግበት "እግዚአብሔር አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት።"  ቆላ ፫፣ ፲፯ o  ስለስሙ መነቀፍ ደስታ ነው። "እነርሱም ስለ ስሙ ይናቁ ዘንድ የተገባቸው ሆነው ስለ ተቈጠሩ ከሸንጎው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ፤"   የሐዋ ፭፣ ፵፩ ስሙ ለጠላት ቁጣን ፣ ለእኛ ለልጆቹ ግን ደስታን ያመጣል። o በስሙ አለማመን ፍርድን ያስከትላል። "በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።"   ፩ ዮሐ ፫፣ ፲፰ o ስሙ ከፍተኛ ኃይል ስላለው አጋንንትን የምንዋጋበት ብቸኛው መንገድ ነው። ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥ ….. ወዘተ…. ከስሙ ጋር የተያያዙ ብዙ ነገሮች ናቸው። o ስምህ ይቀደስ፣ ስለስሙ መመስከር፣ ….. የጌታ መሆናችን ዋናው መገለጫው ይህ ነውና- "ጌታ ለእርሱ የሆኑትን ያውቃል፥ ደግሞም፦ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ከዓመፅ ይራቅ የሚለው ማኅተም ያለበት የተደላደለ የእግዚአብሔር መሠረት ቆሞአል።"  ፪ ጢሞ ፪፣ ፲፱። ዋናው ከአመፅ መራቅ ነው እንጂ "የጌታ ነኝ!" ብሎ መፎከር አይደለም። ይቀጥላል . . . ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “እርሱም ደግሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትሆኑ እስከ ፍጻሜ ድረስ ያጸናችኋል።” 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥8 ወደ ቻና
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “እርሱም ደግሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትሆኑ እስከ ፍጻሜ ድረስ ያጸናችኋል።” 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥8 ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የትኛውን መልእክት ሲጽፍ ነው ከሶስቴንስ ጋር አብሮ እንደነበረ የተናገረው?
Anonymous voting

. ──•◈•─────•◈•─ የዕለቱ ጥቅስ ──•◈•─────•◈•─ “ጥበቡ ጥልቅ፣ ኀይሉም ታላቅ ነውና፤ እርሱን ተቃውሞ ያለ አንዳች ጒዳት የሄደ ማን ነው?” ኢዮብ 9፥4 (አዲሱ መ.ት) ወደ ቻናሉ ለ
.       ──•◈•─────•◈•─                  የዕለቱ ጥቅስ          ──•◈•─────•◈•─ “ጥበቡ ጥልቅ፣ ኀይሉም ታላቅ ነውና፤ እርሱን ተቃውሞ ያለ አንዳች ጒዳት የሄደ ማን ነው?” ኢዮብ 9፥4 (አዲሱ መ.ት) ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures