en
Feedback
Addis News

Addis News

Open in Telegram
405
Subscribers
-124 hours
No data7 days
-230 days
Posts Archive
🛑🛑🛑ዜናዎች 🛑የፌደራሉ መንግስት እና ሕወሃት አደራዳሪ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፣ በፌደራል መንግሥቱና በሕወሃት መካከል ለማደርገው የሽምግልና ጥረት ከፌደራል መንግሥቱ ትዕዛዝ አልቀበልም ሲሉ ሕወሃት ሰሞኑን ላቀረበባቸው ወቀሳ ምላሽ ሠጡ። ኦባሳንጆ፣ ትኩረት ለማግኘት ሲባል ጥንቃቄ የሚያሻቸውን ሚሥጢራዊ መረጃዎች ይፋ ማድረግ ኃላፊነት የጎደለው ድርጊት ነው በማለት ጽሕፈት ቤታቸው ባወጣው መግለጫ ተችተዋል። አንዳንድ የሕወሓት አመራሮች የሽምግልና ጥረቱን ለማጣጣል ሲሞክሩ የአሁኑ የመጀመሪያቸው አይደለም ያሉት ኦባሳንጆ፣ በቅርቡ አዲስ የሽምግልና ጥረት የጀመሩት ፖለቲካዊና ወታደራዊ ጠብ ጫሪ ክስተቶች በመፈጠራቸው መኾኑን ገልጸዋል። ላንድ ወገን ያደላሉ መባሉን ኦባሳንጆ ያጣጣሉ ሲሆን፣ በአገሪቱ ሌላ ዙር ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የሁሉንም ወገኖች ርምጃ በቅርበት እንዲከታተልም ጥሪ አድርገዋል። 🛑የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የመንግሥት ሠራተኞችን የማኅበር ቤት ግንባታ መነሻ ዋጋ በካሬ ከ35 ሺሕ ብር ወደ 50 ሺሕ ብር ከፍ ማድረጉን ዋዜማ ሠምታለች። በግንባታው የመነሻ ዋጋ መሠረት የ25 በመቶ ቅድመ ክፍያ ከፈጸሙ በኋላ ያልተጠበቀ የዋጋ ጭማሪ እንዳጋጠማቸው የመምህራን ማኅበራት ኮሚቴዎች ለዋዜማ ተናግረዋል፡፡ በ25 በመቶ ቅድመ ክፍያ ግንባታ ያስጀመሩ አንዳንድ ማኅበራት፤ በጭማሪው ምክንያት ግንባታ አቋርጠዋል። አስተዳደሩ ክፍያውን መቀጠል ላልቻሉ መምህራን ገንዘቡን እንደማይመልስ ገልጧል፡፡ ዋዜማ ያነጋገረቻቸው ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የከተማ አስተዳደሩ አንድ ኃላፊ በበኩላቸው፤ አስተዳደሩ የግንባታ መነሻ ዋጋውን እንጂ አጠቃላይ የግንባታውን ዋጋ መወሠን አይችልም ብለዋል። 🛑በትግራይ ደቡባዊ ምሥራቅ ዞን ሕንጣሎ ወረዳ "ማይ ሹመት" በተባለ ቦታ ትናንት ምሽት በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንድ ቤተሰብ አባላት የኾኑ ሦስት ሰዎች ሕይወት አልፏል ሲል ሥልጣን በኃይል የያዘው ሕወሃት-መራሹ የክልሉ አስተዳደር ፌደራል መንግሥቱን ከሠሠ፡፡ በጥቃቱ ሕይወታቸውን ካጡት መካከል የአራት ዓመት ሕጻን እንደሚገኝበት አስተዳደሩ ገልጧል። በጥቃቱ፣ ቁጥራቸው ባልተገለጸ ሌሎች ሰዎች ላይ የመቁሠል ጉዳት ደርሷል ተብሏል። ሒዋነ በተባለ ቦታ ደሞ፤ እኩለ ሌሊት ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት በሰላማዊያን ሰዎች መኖሪያ ላይ ጉዳት መድረሡን አስተዳደሩ ጠቅሷል፡፡ ፌደራል መንግሥቱ በክልሉ ውስጥ ተፈጸመ ስለተባለው የድሮን ጥቃት ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ያለው ነገር የለም። 🛑ፌዴራል ፖሊስ፣ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባለፈው ሳምንት ለኢሕአፓ አባላት ይስሃቅ ወልዳይ እና አበበ አካሉ እንዲሁም ለጠበቃ አበራ ንጉስ በፈቀደው ዋስትና ላይ ይግባኝ ጠየቀ፡፡ የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች ትናንት ሰኞ ለእያንዳንዳቸው የተጠየቀውን የ50 ሺሕ ብር ዋስትና ቢያስይዙም፣ ፌደራል ፖሊስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሠሚ ችሎት ይግባኝ በማለቱ ተጠርጣሪዎቹ ከእስር እንዳልወጡ ዋዜማ ከጠበቆቻቸው ሠምታለች፡፡ ፖሊስ ይግባኝ የጠየቀው፣ ተጠርጣሪዎቹ "ጽምዶ" ከተባለው ጥምረት ጋር ግንኙነት ስላላቸው በዋስትና ቢወጡ ከቡድኑ ጋር ሊቀላቀሉ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳለው በመግለጽ ነው። ችሎቱ፣ በይግባኝ አቤቱታው ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለመስከረም 5 ቀን፣ 2019 ዓ፣ም ቀጠሮ ሠጥቷል። 🛑በኖርዌይ ባለሀብቶች የተያዘው አኮቦ ሚኒራልስ የወርቅ አውጪ ኩባንያ፣ በነሃሴ ወር ጋምቤላ ከሚገኘው የማዕድን ማውጫ ጣቢያው 16 ኪሎ ግራም ወርቅ ማግኘቱን አስታወቀ። ኩባንያው ከሠገሌ ጣቢያ በተጠቀሠው ወር ከአንድ ቶን አፈር ውስጥ 26 ኪሎ ግራም ወርቅ ማምረቱንና ይህም ምርት ከጀመረ ወዲህ ሁለተኛው ከፍተኛው ምርቱ መኾኑን ገልጧል። ኩባንያው ከሁለት ዓመታት በፊት ሥራ ከጀመረ ወዲህ ያመረተው ወርቅ መጠን 158 ኪሎ ግራም ደርሷል። ኩባንያው፣ ዲማ ወረዳ ውስጥ ወርቅ እንዲፈልግ የተፈቀደለት ቦታ 182 ኪሎ ሜትር ሲኾን፣ ወርቅ እንዲያለማ የተፈቀደለት ቦታ ስፋት ደሞ 16 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ነው። 🛑የኬንያ መንግሥት በአነስተኛ የንግድ ዘርፎች የተሠማሩ የውጭ ዜጎች ሠነዳቸውን ሕጋዊ እንዲያደርጉ የሦስት ወራት ጊዜ ሠጠ። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ በአነስተኛ ንግድ ሥራዎች የተሠማሩ የውጭ ዜጎች በተለይ ቡሩንዲያዊያን ንግዳቸውን ትናንት ሰኞ እንዲዘጉ ባለፈው ሳምንት ትዕዛዝ ሠጥተው ነበር። መንግሥት በአነስተኛ የንግድ ሥራዎች የተሠማሩ የውጭ ዜጎች ሥራ እንዲያቆሙ እስከ ትናንት ቀነ ገደብ መስጠቱን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ስደተኞችም በበርካታ አካባቢዎች የንግድ መደብሮቻቸውን ካለፈው ሳምንት ዓርብ ጀምሮ ዘግተዋል። ፕሬዝዳንቱ አነስተኛ የንግድ ሥራዎች ለዜጎች ብቻ የተተው መኾን እንዳለባቸው ገልጸዋል። የአገሪቱ የስደተኛ ሕግ፣ ስደተኞች በአነስተኛ የንግድ ሥራዎች ላይ እንዲሠማሩ ይፈቅዳል።

የተከሳሽ ንብረት ከሆነ ስልክ ላይ የተገኘው ቪዲዮ ላይ የሚታየው የእገታና የማሰቃየት ወንጀል የተፈጸመው በ2021 ነው ። በዚህ ቪዲዮ ላይ አንድ የታገተ ሰው ሲደበደብ እና ሲሰቃይ ፡ እንዲሁም እርቃኑን በማድረግ ክብሩን የሚነኩ እና አዋራጅ ድርጊቶችን እንዲፈጽም ሲያስገድዱት ይታያል ። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለም ከአሁን በኋላ ይህንን የተፈጸመበትን እገታና ድብደባ እንዲሁም ከዚህ በፊት የሚያውቃቸውን ሚስጥሮች ለፖሊስ ቢናገር ፡ ይህንን ራቁቱን ሆኖ የሚታይበትን ቪዲዮ በሶሻል ሚዲያ ፖስት እንደሚያደርጉት ሲያስጠነቅቁት ይሰማል ። ይህንን ጉዳይ እዚህ ላይ ፖዝ አድርገን አሁን ስለሳራ ካሊፋ እናውራ ። ........ ሳራ ከሊፋ ትባላለች ፡ ግብጻዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ ፡ እና የተለያዩ ካምፓኒዎችን የምታስተዳድር ሴት ናት ። ሳራ 2.5 ሚሊየን ፎሎወር ባለው የኢንስታግራም አካውንቷ በየጊዜው በምትለቀው ፎቶና ቪዲዮ ፡ ቅንጦት ማለት ፡ ሀብት ማለት ፡ ምን ማለት እንደሆነ የሚያሳዩ ናቸው ። ...በቻኔል ጉቺ እና ቪቶን ውድ አልባሳት ዘንጣ ውድ ዋጋ በሚከፈልባቸው የፓሪስ ሬስቶራንቶች ሺህ ዶላር የሚያወጣ በሻማና በሻምፓኝ የታጀበ ራት እየተመገበች ፡ ቀን በሉቭር ሙዚየም ስለተመለከተችው የሞናሊዛ ስእል የምትናገር ። ...... በማያሚ ቢች ላይ እየተንሳፈፈች ባለች የቅንጦት ጀልባ በረንዳ ላይ ነጭ የሀር ጋዋን ለብሳ ፡ በትልቅ ስስ ብርጭቆ ብርማ ቀለም ያለው አንጸባራቂ ነገር እየጠጣች ስለቀን ውሎዋ የምትተርክ ሴት ናት ። ..... ይህች ዝነኛ እና ሀብታም ሴት በሀገሯ ግብጽ ውስጥም ፡ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ የስፖርት መኪናዋን እያጓራች በካይሮ ጎዳናዎች ላይ የምትታይ ። እኔ ነኝ ባለው ቅንጡ ህይወቷ የምትታወቅ ፡ በዋና ከተማዋ ምርጥ ምርጥ በሚባሉ የግል ቪላዎቿ የምትኖር ፡ ሀብት ብቻ ሳይሆን ግብጽን ከዳር እስከዳር ያዳረሰ ዝና ያላት ታዋቁ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ ፡ የቀድሞ ሞዴልና ኢንቨስተር ናት ። ... ሆኖም ...... በኤፕሪል 2025 ባላት ሀብትና ዝና እንዲሁም ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር ባላት ቅርርብ የምትታወቀው የሳራ ካሊፋ ትልቅ ቪላ በር ላይ ከቆመው የፖሊስ መኪና የወረዱ የግብፅ ፖሊስ አባላት የዝነኛዋን መኖሪያ ቤት አንኳኩተው ሳራ ካሊፋን ለጥያቄ እንደሚፈልጓት ተናገሩ ። ...... ፖሊስ ጣቢያ እንደደረሱም ታዋቂዋ ዝነኛዋና ሚሊየነሯ ሳራ ከሊፋ አደንዛዥ ዕፅ በማምረት በማከፋፈል እና የወንጀል ቡድኖችን በመምራት እንደምትፈልግ ተነግሯት ክስ ተመሰረተባት ። ...... ፖሊስ ሳራን በቁጥጥር ስር አውሎ በግብጽ ውስጥ ያሏትን ዘመናዊ ቪላዎች መፈተሽ ጀመረ ። በዚህ ፍተሻ ወቅትም ፡ 750 ኪሎ ግራም የሚመዝን አደንዛዥ እፅ እና የእጽ ማቀነባበሪያ ላቦራቶሪ አገኘ ። ይህ ብቻ አይደለም ሳራ ከሌሎች ተባባሪዎቿ ጋር በመሆን የወንጀልና የእገታ ድርጊት እንደምትፈፅም የሚያስረዱ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችና ፡ ድርጊቱን የሚያረጋግጡ የተለያዩ ቪዲዮዎችን ከራሷ ስልክ ላይ አግኝቷል ። ከነዚህ መሀከል ቅድም ከላይ በመግቢያችን ላይ ያነሳነው ሰው ጉዳይ ነው ። ..... ይህ የእገታና ድብደባ ወንጀል የተፈጸመበት ሰው የቀድሞ የሳራ ሾፌር የነበረ ሲሆን ፡ ከፖሊስ ጋር ግንኙነት አለህ በሚል ጥርጣሬ ወደሳራ ቪላ እንዲመጣ ከተደረገ በኋላ ስለትን ያካተተ አደገኛ ድብደባና እንግልት እና ሌሎች አዋራጅ ነገሮች እንደተፈጸሙበት ፡ ራቁቱን አድርገው ቪዲዮ ከቀረጹት በኋላ ፡ ከንግዲህ አንዳች ሚስጥር ቢያወጣ ቪዲዮውን በሶሻል ሚዲያ ፖስት እንደሚያደርጉት አስጠንቅቀው ስለለቀቁት ከማፍያው ቡድን ሊደርስበት የሚችለውን ጉዳት በመስጋት ፡ በነሳራ ከሊፋ ወንጀል እንደተፈጸመበት ሳይናገር ለአመታት ቆይቷል ... ፖሊስ ይህንን ቪዲዮ ከሳራ ስልክ ላይ ካገኘ በኋላ ግን አደንዛዥ እፅ ከማምረትና ማሰራጨት ወንጀል በተጨማሪ የእገታና ውንብድና ተግባር መፈጸም የሚል ሌላ ተጨማሪ ክስ ተመስርቶባት ላለፉት 14 ወራት በእስር ቤት ሆና ክሷን ስትከታተል ቆይታ ነበር ። ........... በግብጽና በዱባይ ራሱ ግዙፍ ቪላዎች ያሏት ፡ ከአሜሪካና እስከ አውሮፓ ፡ ከኤዥያ እስከ አፍሪካ ፡ የቅንጦት ኑሮዋን በኢንንስታግራም ፖስት እያረገች ብዙዎች እሷን መሆን እንዲመኙ ያደረገችው ፡ በአደንዛዥ እጽ የብዙዎችን ህይወት ያመሰቃቀለች ፡ ሚስጥራዊ የወንጀል ቡድን መሪ ትሆናለች ብሎ ማንም አስቦ አያውቅም ነበርና በዚህ ወንጀል ተጠርጥራ ስትያዝ በተለይ ለግብጻውያን አስደንጋጭ ዜና ነበር ። ....... በዚህ መልኩ ላይዋን አሳምራ ለአመታት የኖረችው ሳራ ካሊፋ መጥፎ ስራዋ ጊዜው ደርሶ ተገለጠና ለወራት ሲካሄድ የቆየው የክስ ሂደት ተጠናቆ ትናንት 11 ከሚሆኑ የቡድን አጋሮቿ ጋር በግብጽ ፍርድ ቤት ሞት ተፈርዶባታል ..... አሁን ያ ሁሉ የቅንጦት ህይወት ተረት ሆኗል ። ሚሊዮኖች የፈሰሰባቸው ቪላዎቿን ከንግዲህ አትኖርባቸውም ። በወንጀል እና በሰው dm የተገኘው ሀብት ፡ ውድ አልባሳቶቿ ፡ አስር ሺህ ዶላሮችን የሚያወጡ ሽቶዎች ከንግዲህ የሉም ። አደለም እነዚህ ትርፍ ነገሮች ከንግዲህ በነጻ የሚገኘውንም አየር ትቀማለች ። ሳራ ካሊፋ በድብቅ ለሰራችው የአመታት ወንጀል ፡ በግልፅ ሊከፈላት ቀናት ብቻ ይቀራሉ ።

photo content
+6

🛑🛑🛑 🛑ገዥው ብልጽግና ፓርቲ አዲስ በሚመሠርተው መንግሥት ውስጥ ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚኾኑ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎችን ለአዲስ ተሿሚዎች ለመስጠት መወሠኑን ዋዜማ ሠምታለች። የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ ረዘም ላሉ ዓመታት በአመራርነት ያገለገሉ ተሿሚዎች ራሳቸውን ለሌላ ተልዕኮ እንዲያዘጋጁ እንደነገሯቸው ምንጮች ገልጸዋል። በሥራ ላይ ከሚገኙ አመራሮች መካከል ባለፈው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት በቂ ሥራ አልሠሩም በሚል ከሥራቸው የታገዱ ሹሞች መኖራቸውንም ምንጮች ተናግረዋል። በካቢኔ ምርጫ የሚንስትርነት ሹመት የሚሠጣቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የሚኖሩበት ዕድል አለ ያሉት ምንጮች፣ አዲስ በሚዋቀሩ የካቢኔ ድልድሎች ውስጥ ሹመት ማግኘት እንፈልጋለን የሚል ጥያቄ ያቀረቡ የፓርቲ አመራሮች መኖራቸውን ጭምር ሠምተናል። Link - https://cutt.ly/ZykaokpG 🛑የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ የሽብር ወንጀል ተጠርጣሪዎቹ የኢሕአፓ አመራር ይስሃቅ ወልዳይ፣ የፓርቲው አባል አበበ አካሉ እና የቀድሞው የሰላም ሚንስትር የዴኤታ ታዬ ደንደዓ ጠበቃ አበራ ንጉሥ እያንዳንዳቸው በ50 ሺሕ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ፈቀደ። ችሎት፤ የፖሊስን ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ፤ ተጠርጣሪዎቹ ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ መወሠኑን ዋዜማ ሠምታለች። ፖሊስ ምርመራውን እንዳላጠናቀቀ በመግለጽ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት የተጠየቀው ትናንት በዋለው ችሎት ነበር። 🛑ጣሊያን፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ በናይል ወንዝ ውዝግባቸው ዙሪያ እንዲነጋገሩ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ዝግጁ መሆኗን መግለጧ ተሠማ። የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒዮ ታጃኒ ሰሞኑን ከግብጹ አቻቸው ባደር አብደላቲ ጋር ግብጽ ውስጥ በሠጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ ፍላጎቱ ካላቸው ጣሊያን ድርድሩን ለማመቻቸት ዝግጁ መኾኗን መናገራቸውን ሚድል ኢስት ሞኒተር ጋዜጣ ዘግቧል። ሚንስትሩ፣ ግብጽ በዓለማቀፍ ሕግ መሠረት ከወንዙ ውሃ የድርሻዋን እንድታገኝ የሚያስችል ስምምነት ያስፈልጋል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም ግብጽ ለጣሊያን የአደራዳሪነት ሀሳብ ምን ምላሽ እንደሠጠች ዘገባው አልጠቀሠም። 🛑የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞች ብዛት ከ15 ሚሊዮን አለፈ። ኩባንያው ከተመሠረተ ጀምሮ ከ3 ሺሕ 500 በላይ የኔትዎርክ ጣቢያዎችን በአገሪቱ ውስጥ ማቋቋሙንና ኔትዎርኩ ለ60 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተደራሽ መኾኑን ሃላፊዎቹ መናገራቸውን የኬንያው ዘ ስታር ጋዜጣ ዘግቧል። የኩባንያው እድገት ከአዲስ መሠረት ላይ ለሚጀምር ኩባንያ በዓለም ላይ ፈጣኑ እድገት መሆኑን ሃላፊዎቹ ጠቅሠዋል ተብሏል። ባለፉት አራት ዓመታት ለማኅበረሰብ ልማትና ድጋፍ 139 ወጪ ማድረጉን የጠቀሠው ኩባንያው፣ ባለድርሻ አካላትና አጋሮች ደሞ 545 ሚሊዮን ብር ለዚሁ ዓላማ ማዋጣታቸውን መግለጡን ዘገባው አመልክቷል። 🛑የአማራ ክልል ፖሊስ፣ በባሕርዳር ከተማ በመንግሥት ተሽከርካሪ በመታገዝ ሰዎችን ያገቱ ግለሰቦችን ከነተሽከርካሪው ነሃሴ 29 ቀን ባሕርዳር ውስጥ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ። ተጠርጣሪዎቹ ታጋቾቹን አፍነው በመውሠድ ለ11 ቀናት አግተው እንዳቆዩዋቸው የገለጸው ፖሊስ፣ ታጋቾቹን ለመልቀቅ ሦስት ሚሊዮን 370 ሺሕ ብር ጠይቀው ገንዘቡን ከቤተሰቦቻቸው መቀበላቸውን ገልጧል። የእገታ ወንጀሉ የተፈጸመው በክልሉ የከተሞች ልማትና ፕላን ኢንስቲትዩት ቢሮ ተሽከርካሪ አማካኝነት መሆኑን ፖሊስ የጠቀሠ ሲሆን፣ የመንግሥት ተቋማት ለሥራ በተመደቡላቸው ተሽከርካሪዎችና አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እንዲያደርጉም አሳስቧል። 🛑በሱዳን የተመድ ዓለማቀፍ አጣሪ ቡድን፣ ኢትዮጵያዊያን ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር ወግነው ከሚዋጉ የውጭ ዜጎች መካከል እንደሚገኙበት አረጋግጫለሁ አለ። ቡድኑ፣ የኢትዮጵያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ቻድ ዜጎች ዳርፉርን ጨምሮ በተለያዩ ግንባሮች በውጊያ መሳተፋቸውን መለየት እንደተቻለ ገልጧል። ኾኖም የቡድኑ ምርመራ ከፈጥኖ ደራሹ ኃይል ጋር የተሠለፉ ኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ግንኙነት ያላቸው ስለመኾኑ አላመለከተም። ለሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ድጋፍ ያደርጋሉ የሚል ውንጀላ የሚቀርብባቸው የተለያዩ አገራት መረጃ እንዲሠጡኝ ጠይቄያለሁ ያለው ቡድኑ፣ ከኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሊቢያ ምላሽ እንዳላገኘ ገልጧል። 🛑የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ፣ አፍሪካ "ሜርካተር" በተባለው ለበርካታ ክፍለ ዘመናት ሥራ ላይ ባለው የዓለም ካርታ ላይ ባነሳችው ቅሬታ ላይ ዛሬ ድምጽ ይሠጣል። በአፍሪካ ኅብረት ድጋፍ የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ፣ መንግሥታት፣ ትምህርት ቤቶች፣ ዓለማቀፍ ድርጅቶችና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ከነባሩ "ሜርካተር" ካርታ ይልቅ አዲሱን "ኢኳል ኧርዝ" የተሠኘውን ካርታ እንዲጠቀሙ ይጠይቃል። በአፍሪካ የውሳኔ ሀሳብ ላይ የተነሳው ዋነኛ ቅሬታ፣ ካርታው አሕጉሪቱን ከትክክለኛ ስፋቷ እርጅጉ አሳንሶ ያቀርባል የሚል ነው። በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተሠራው ይሄው ካርታ፣ በምድር ወገብ አካባቢ የሚገኙትን አሕጉራት ስፋት በእጅጉ ያሳንሳል፤ በሰሜን ዋልታ አካባቢ ያሉትን ደሞ አግዝፎ ያቀርባል የሚል ትችት የካርታ ባለሙያዎች ያቀርቡበታል።

🛑🛑🛑ዜናዎች 🛑የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር አካባቢዎችንና መንደሮችን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ጉዳት እያደረሠ ይገኛል በማለት ለአልጀዚራ በሠጡት ቃል ከሰሱ። ጌታቸው፣ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች ይረዳል በማለት ጭምር መወንጀላቸውን ዜና አውታሩ ማምሻውን ዘግቧል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከኢትዮጵያ ግዛት እየተነሳ በሱዳን ጦር ሠራዊት ላይ ጥቃት ይፈጽማል የሚለውን የሱዳን ባለሥልጣናት ውንጀላ ያስተባበሉት ጌታቸው፣ ኢትዮጵያ የሱዳንን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንደምታከብር ተናግረዋል ተብሏል። ሱዳን ጦሯን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር ወደሚዋሠነው ብሉናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ በብዛት እያንቀሳቀሰች መኾኗንም ዘገባው የሱዳን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። 🛑የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩት የኢሕአፓ አባላት ይስሃቅ ወልዳይ እና አበበ አካሉ እንዲሁም የቀድሞው የሰላም ሚንስትር ደዔታ ታዬ ደንደአ ጠበቃ አበራ ንጉስ ላይ መርማሪ ፖሊስ በሰባት ቀናት ውስጥ ምርመራውን አጠናቆ ለነሃሴ 28 እንዲያቀርብ አዘዘ። ፖሊስ ትናንት በዋለው ችሎት ላይ ምርመራውን ለማጠናቀቅ 14 ቀናት ተጨማሪ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቆ ነበር። ችሎቱ ዛሬ ለመርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ ሰባት ቀናት የፈቀደው፣ መርማሪ ፖሊስ የሚያቀርባቸውን ምስክሮች ቃል ለመስማት መኾኑን ገልጧል። ችሎቱ፣ ተጠርጣሪዎቹ ካኹን ቀደም ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ነሃሴ 28 ውሳኔ እሠጣለሁ ብሏል። 🛑ጎጎት ፓርቲ፣ ከኦሮሚያ ክልል የተነሱ ታጣቂዎች በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ሱተን ቀበሌ ነሃሴ 19 ቀን በፈጸሙት ጥቃት ሦስት የሚሊሺያ አባላትን ጨምሮ ሰባት ነዋሪዎች ተገድለዋል አለ። ፓርቲው፣ ታጣቂዎቹ ሌሎች አምስት ሰዎችን አፍነው እንደወሠዱ ገልጧል። በታጣቂዎቹ ጥቃት በርካታ የመንግሥትና የግል ተሽከርካሪዎች፣ መኖሪያ ቤቶችና የግል ንግድ ቤቶች መቃጠላቸውን ጭምር ፓርቲው ጠቅሷል። ታጣቂዎች በአካባቢው በተደጋጋሚ በሚፈጽሙት ጥቃት ላይ ግልጽ ምርመራ እንዲደረግና የምርመራ ውጤቱ ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ እንዲኹም የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ተጨማሪ የፌደራል የጸጥታ ኃይል ባስቸኳይ እንዲሠማራ ፓርቲው ጠይቋል። 🛑በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ፣ "በሕገወጥ መንገድ" ሲዘዋወሩ ነበር ያላቸውን 32 ኤርትራዊያን በቁጥጥር ሥር አዋለ። በቁጥጥር ሥር የዋሉት ኤርትራዊያን፣ 14ቱ ሴቶች፣ 11ዱ ወንዶች እንዲኹም ሰባቱ ሕጻናት መኾናቸውን ፖሊስ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሠራጨው መረጃ ገልጧል። ሁለት የኤርትራዊያኑ አዘዋዋሪዎችና አንድ ሹፌር ጭምር በቁጥጥር ሥር ውለዋል ተብሏል። ኤርትራዊያኑና አዘዋዋሪዎቻቸው ከተማዋ ውስጥ የተያዙት፣ ሲያትል ከሚባል አልቤርጎ ምድር ቤት ላይ በሚገኝ አዳራሽ ተሸሽገው መኾኑን ፖሊስ ጠቅሷል። በርካታ ኤርትራዊያን ስደተኞች በደቡብ ኢትዮጵያ በኩል ድንበር አቋርጠው ኬንያ እንደሚገቡ የአገሪቱ ፖሊስ በተደጋጋሚ ገልጧል። 🛑በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ፍራንክ ጋርሺያ ወደ ኢትዮጵያ ሊጓዙ ነው። ጋርሺያ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙት፣ የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እና የጋራ የጸጥታ እና ኢኮኖሚ አጋርነቶችን ለማጎልበት እንደኾነ መስሪያ ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጧል። ኾኖም ጋርሺያ መቼ ኢትዮጵያ እንደሚገቡና ከየትኞቹ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር እንደሚወያዩ የመስሪያ ቤቱ መረጃ አላመለከትም። ጋርሺያ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለተመሳሳይ ዓላማ ወደ ኬንያ እና ዛምቢያ ጭምር ያቀናሉ ተብሏል። 🛑ኡጋንዳ በፍልስጤሟ ጋዛ ሠርጥ እንዲሠማራ ለሚቋቋመው ዓለማቀፍ የማረጋጊያ ተልዕኮ 1 ሺሕ 200 ወታደሮች እንደምታዋጣ የአሜሪካ ባለሥልጣናት ማረጋገጣቸውን ዘ ኢስት አፍሪካ ጋዜጣ ዘገበ። የኡጋንዳ ወታደሮች በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት በሠርጧ ይሠማራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዘገባው ጠቅሷል። ቡሩንዲም ለተልዕኮው ወታደሮች ለማውጣት እየተነጋገረች መኾኑን ዘገባው ጠቅሷል። ሞሮኮ፣ በተልዕኮው ትሳተፋለች ተብላ የምትጠበቅ ሌላኛው አፍሪካዊት አገር ናት። በአሜሪካ ሀሳብ አመንጪነት የሚቋቋመው ዓለማቀፍ የማረጋጊያ ኃይል፣ ጋዛን የማረጋጋትና ለሰብዓዊ ዕርዳታ ሥራዎች ድጋፍ የመስጠት ሃላፊነት ይኖረዋል።

🛑🛑🛑ዜናዎች 🛑በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ሸዋ ዞን ኢልፈታ ወረዳ ዛሬ ዓርብ ማለዳ ላይ የአማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት፣ የወረዳው የሚሊሺያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሌሊሳ ወርቁን ጨምሮ ሌሎች የአካባቢው የአስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች መገደላቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በጥቃቱ፣ በወረዳው የሃሩ ሲናኒ ቀበሌ ዋና አሥተዳዳሪ ጊቲማ አያንሳ፣ የጉቴ ቀበሌ የሠላምና ጸጥታ ጉዳዮች ኃላፊ ግርማ ጨዋቃ እና ሁለት የክልሉ ሚሊሺያ አባላት ሕይወታቸው ማለፉን ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። የአማጺ ቡድኑ አባላት ጥቃቱን ከፈጸሙ በኋላ ወደ ወረዳው አሥተዳደር ጽሕፈት ቤት አምርተው እንደነበርና ኾኖም የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከስፍራው ሲደርሱ ታጣቂዎቹ ከተማዋን ለቅቀው እንደወጡ ምንጮች ነግረውናል። 🛑በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መደበኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ተማሪዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሠጠው ዕድል መሠረት በከተማዋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ለመቀጠል ቢያመለክቱም ማመልከቻቸው ውድቅ እንደተደረገ ዋዜማ ሠምታለች። የከተማዋ አስተዳደር ከ1 እስከ 8ኛ ክፍል በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ያልተማሩ አመልካቾችን አልቀበልም ማለቱን የተማሪዎች ቤተሰቦች ተናግረዋል። በእቴጌ መነን እና ገላን ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለመማር ያመለከቱ ተማሪዎች ቤተሰቦች፣ ልጆቻቸው እስከ 8ኛ ክፍል ያለውን ትምህርት በአማርኛ ቋንቋ በመማራቸው ብቻ ማመልከቻቸው ተቀባይነት እንዳላገኘ ገልጸዋል። የከተማዋ አስተዳደር በእቴጌ መነን ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ሴት ተማሪዎችን የሚቀበል ሲኾን፣ በገላን ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ደሞ ወንዶችን ተቀብሎ ያስተምራል። 🛑ብሄራዊ ባንክ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ በሕገወጥ የሃዋላ ገንዘብ መላኪያ ዘዴዎች አማካኝነት ገንዘብ ከመላክ እንዲታቀቡ በድጋሚ አሳሰበ። ባንኩ ይህን ማሳሰቢያ በድጋሚ ያወጣው፣ ባሁኑ ወቅት በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገር ውስጥ የሚልኩት ገንዘብ በመጨመሩ መኾኑን ገልጧል። ባንኩ ፍቃድ የላቸውም በማለት ከዘረዘራቸው የሃዋላ ገንዘብ አስተላላፊዎች መካከል፣ አዲስ መኒ ትራንስፈር፣ አማና ኤክስፕረስ፣ ባካል መኒ ትራንስፈር፣ ወርልድ ዳይሬክት ሊንክ፣ ጁባ ኤክስፕረስ፣ አዋሽ ዳይራክት እና ታጅ ፋይናንሻል ሠርቪስስ ይገኙበታል። ደንበኞች የገንዘባቸውን ደኅንነት ለመጠበቅና ገንዘባቸው አስተማማኝ በሆነ መንገድ ወደ አገር ቤት መድረሱን ለማረጋገጥ ሕጋዊ ፍቃድ የተሠጣቸውን የገንዘብ ማስተላለፊያ ወኪሎች ብቻ እንዲጠቀሙ ባንኩ መክሯል። 🛑ትናንት በትግራይ ክልል ምሥራቅ ዞን ክልተ አውላሎ ወረዳ ሁለት የድሮን ጥቃቶች እንደተፈጸሙ የክልሉ ቴሌቪዥን ዘገበ። በአብርሃ ወአጽብሃ ቀበሌ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ባንድ ትምህርት ቤቱ ሕንጻና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም በጥቃቱ ወቅት በትምህርት ቤቱ ውስጥ ወይም በትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ይኑር አይኑር ዘገባው አይመለከተም። ከትናንት በስቲያም፣ በክልሉ ምሥራቃዊ ዞን ሰሃርቲ ጊጀት ከተማ ዓለም ባንክ ድጋፍ ያደረገለት አንድ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በድሮን ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሠበት የክልሉ ባለሥልጣናት ገልጠው ነበር። 🛑የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት የአገሪቱን የኃይል ማመንጨት አቅም ወደ 9 ሺሕ 770 ሜጋ ዋት ለማድረስ ማቀዱን አስታወቀ። በበጀት ዓመቱ እንዲመረት ከታቀደው ኃይል ውስጥ፣ ከ29 ሺሕ 884 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ለአገር ውስጥ ፍጆታ እንዲሁም ከ2 ሺሕ 249 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ የሚኾነውን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን የኩባንያው ሥራ እስፈጻሚ አሸብር ባልቻ ዛሬ በሠጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ኩባንያው በዚሁ በጀት ዓመት በውጭ ምንዛሬ ከሚሸጠው ኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ 278 ነጥብ 63 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ማቀዱን አሸብር ገልጸዋል። ኩባንያው የውጭ ምንዛሬ የሚያገኘው፣ በአገር ውስጥ በመረጃ ማቀነባበር ሥራ ለተሠማሩ የውጭ ኩባንያዎች እና ለጎረቤት አገራት ከሚሸጠው ኃይል ነው። ኾኖም የኤልኒኖ የአየር ንብረት ለውጥ በኩባንያው የኃይል ማመንጨት ሥራዎችና ከኃይል ሽያጭ በሚያገኘው ገቢ ላይ አሉታዊ ጫና ሊያሳድር እንደሚችል አሸብር ጠቁመዋል። 🛑የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን፣ ላለፉት ስድስት ወራት በሦስት የሮይተርስ የዜና ወኪል ዘጋቢዎች ላይ ጥሎት የቆየውን የሥራ ፍቃድ እገዳ አነሳ። ባለሥልጣኑ የሦስቱን የሮይተርስ ዘጋቢዎች የሥራ ፍቃድ የመለሠው፣ ከዜና ወኪሉ ኃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኋላ መኾኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጧል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ፣ ሮይተርስ "የሚዛናዊነት"፣ "የትክክለኛነት"፣ "የተዓማኒነት" እና "የተጨባጭነት' ችግር ያለባቸውና ላንድ ወገን ያደሉ ዘገባዎችን ይሠራ ነበር በማለት በውይይቱ ወቅት መናገራቸውን ባለሥልጣኑ ጠቅሷል። ባለሥልጣኑ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሮይተርስ ቋሚ የዜና ወኪሎች ፍቃድ እንደታደሠላቸው አውቀው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቋል። ሮይተርስ በበኩሉ፣ በኢትዮጵያ ላይ "ነጻ"፣ "ገለልተኛ" እና "ተዓማኒ" ዘገባዎችን መስራት እንደሚቀጥል አረጋግጧል። የሮይተርስ የዘጋቢዎች ፍቃድ የታገደው፣ ሮይተርስ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ኢትዮጵያው ውስጥ ወታደራዊ ማሠልጠኛ አቋቁሟል የሚል ዘገባ መስራቱን ተከትሎ ነበር። 🛑የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቻይናዋ ቸንጉ ግዛት እና አዲስ አበባ መካከል በዛሬው ዕለት በቀጥታ ጭነት የማጓጓዝ አገልግሎት ጀመረ። አዲሱ የጭነት ማጓጓዣ አገልግሎት፣ በምዕራባዊ የቻይና ግዛቶች እና በአፍሪካ መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ይበልጥ እንደሚያሳድገው አየር መንገዱ ባሠራጨው መረጃ ገልጧል። የአየር መንገዱ የጭነት አገልግሎት በተለይ እንደ ሌጎስ፣ አክራ፣ ዳካር፣ ኢንቴቤ እና ሉቡምባሺ ያሉ የአፍሪካ ከተሞች ከቻይና ጋር ያላቸው የንግድ ትስስር እንዲጠናከር ያስችላል ሲል የቻይናው ዥንዋ የዜና ወኪል ዘግቧል። አየር መንገዱ ይህንኑ የጭነት አገልግሎት በቦይንግ 777 አውሮፕላኖቹ በሳምንት ሁለት ቀናት እንደሚሠጥ ዘገባው አመልክቷል። የአየር መንገዱ የጭነት ማጓጓዝ አገልግሎት ወደፊት በሳምንት ወደ አራት ቀናት ሊያድግ ይችላል ተብሏል። አየር መንገዱ ባሁኑ ወቅት 12 ቦይንግ 777 የጭነት ማጓጓዣ አውሮፕላኖች አሉት።

🛑🛑🛑ዜናዎች 🛑ዛሬ ረፋዱ ላይ በደቡባዊ እና ሰሜን ምዕራብ የትግራይ አካባቢዎች የድሮን ጥቃቶች እንደተፈጸሙ የክልሉ የዜና ምንጮች ዘገቡ። በደቡብ ትግራይ ዞን ራያ አዘቦ ወረዳ ሁለት የድሮን ጥቃቶች እንደተፈጸሙ የዞኑ ባለሥልጣናት መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በጥቃቱ በሲቪሎች ንብረትና በመስኖ እርሻ ልማት ላይ ጉዳት መድረሱን ዘገባው ጠቅሷል። በሰሜን ምዕራብ ዞን እንዳባጉና ወረዳ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ደሞ፣ በሲቪሎች መኖሪያዎች ላይ ጉዳት አድርሷል መባሉን ዘገባው አመልክቷል። ባለሥልጣናቱ ለጥቃቱ ፌደራል መንግሥቱን ተጠያቂ አድርገዋል ተብሏል። ጥቃቶቹ በተፈጸሙባቸው አካባቢዎች በሰዓቱ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ይኑር አይኑር ለጊዜው አልታወቀም። 🛑በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የደገም ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ ተፈራ ደሴ ትናንት እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው አማጺ ቡድን በፈጸመው ጥቃት መገደላቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በጥቃቱ ለጊዜው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የመከላከያ ሠራዊት፣ የኦሮሚያ ፖሊስ እና የክልሉ ሚሊሺያ አባላትም ሕይወታቸው ማለፉን ምንጮች ነግረውናል። ተፈራ የተገደሉት፣ ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከክልሉ ፖሊስና ሚሊሺያ አባላት ጋር "ጋር ኢሌ" በተባለ ቦታ የጸጥታ ሥራ በማከናወን ላይ ሳሉ እንደኾነ ዋዜማ ተረድታለች። 🛑በጋምቤላ ክልል አቦል ወረዳ ማነታቸ ያልታወቁ ታጣቂዎች ትናንት ጧት ባንድ የሕዝብ ማጓጓዣ አውቶቡስ ላይ በፈጸሙት ጥቃት አንድ ሰው ተገድሎ አራቱ መቁሠላቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በክልሉ በተለይ በኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ በሕዝብ ትራንስፖርት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች በተደጋጋሚ ይፈጸማሉ። ባለፈው ወር አጋማሽ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ወደ ኢታንግ ከተማ በተሽከርካሪ በመጓዝ ላይ የነበሩ የመንግሥት ሠራተኞች ላይ በፈጸሙት ጥቃት፣ እንድ የአካባቢውን ሹመኛ ገድለው ሁለቱን ማቁሠላቸውን ዋዜማ መዘገቧ ይታወሳል። 🛑በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ፣ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሐይማኖት አባቶችና በ"ቅባት" እምነት አራማጆች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በእርቅ ተፈትቷል ተባለ። የ"ቅባት" እምነት አራማጅ አባቶች ያለ ቤተክርስቲያኗ ቤተ-ክህነት ፍቃድ ያሳተሟቸውን ማኅተሞችና የገቢ መሰብሰቢያ ደረሠኞች ለመመለስና አስተምህሯቸውንና ለመተው እንደተስማሙ የወረዳው አስተዳደር ገልጧል። ቤተክርስቲያኗ በእምነቱ አራማጆች ላይ የጣለቻቸው እግዶችም እንደተነሱ ተገልጧል። የ"ጸጋ" እና የ"ቅባት" እምነት ልዩነት፣ እየሱስ ክርስቶስ ቅዱስን ከተቀባበት ጊዜ ጋር የተያያዘ እንደኾነ ይታወቃል። 🛑የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት፣ "ከኢትዮጵያ ግዛት የተነሳ" ድሮን ትናንት ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ መትቼ ጥያለሁ አለ። የሱዳን መከላከያ ሚንስቴር፣ ድሮኑ ተመትቶ የወደቀው የድንበር ከተማ በሆነችው ኩርሙክ አካባቢ መኾኑን ገልጧል። የድሮኑ ዒላማ ምን እንደነበር፣ የድሮኑ ባለቤት ወይም የድሮኑ ሥሪት የት አገር እንደኾነ መረጃ ይኑረው አይኑረው ሚንስቴሩ አልጠቀሠም። የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት በዚሁ ውንጀላ ዙሪያ ለጊዜው ያለው ነገር የለም። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል፣ ኩርሙክ ከተማን ከሱዳን ጦር ሠራዊት በከሳምንት በፊት በማስለቀቅ መልሶ መቆጣጠሩ ይታወሳል። 🛑የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባድር አብደላቲ፣ በአፍሪካ ቀንድ ከዓለማቀፍ ሕግጋት ጋ በተጻረረ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት ይደረጋሉ ያሏቸውን ጥረቶች አገራቸው እንደምትቃወም ለፕሬዝዳንት ትራምፕ የዓረብና የአፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ተናገሩ። እነዚህ በኃይል የሚካሄዱ ጥረቶች መቆም አለባቸው ያሉት አብደላቲ፣ የቀጠናው አገራት "አንድነት"፣ "ሉዓላዊነት" እና "የግዛት አንድነት" ሊከበር ይገባል በማለት ከቡሎስ ጋር ትናንት በስልክ ባደረጉት ውይይት አጽንዖት እንደሠጡ የግብጽ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የባሕር በር በኃይል ለማግኘት ይደረጋሉ ያሏቸው ጥረቶች የየትኛው አገር ጥረቶች እንደኾኑ አብደላቲ ባይጠቅሱም፣ ኢትዮጵያ ግን ቀይ ባሕር ላይ የባሕር በር ማግኘት የኅልውና ጉዳይ መኾኑን ደጋግማ ስትገልጥ ቆይታለች። 🛑በደቡብ ሱዳን ጆንገሌ ግዛት በተመድ ሰላም አስከሪዎች ተሽከርካሪ ላይ የታጠቁ አካላት በዛሬው ዕለት በፈጸሙት ጥቃት ሁለት ሰላም አስከባሪዎች ተገደሉ። በጥቃቱ ሌሎች ሰባት ቆስለዋል ተብሏል። አሜሪካ፣ ጥቃቱን የፈጸሙት የታጠቁ ወጣቶች ናቸው በማለት ጁባ በሚገኘው ኢምባሲዋ በኩል ባወጣችው መግለጫ ድርጊቱን ክፉኛ አውግዛለች። በጥቃቱ ላይ ሙሉ እና ግልጽ ምርመራ እንዲደረግ ያሳሰበችው አሜሪካ፣ ለጥቃቱ ተጠያቂ የኾኑ አካላት ለፍርድ እንዲቀርቡም ጠይቃለች።

🛑🛑🛑የአብይ አህመድ በዛሬው የምክክር ኮሚሽን የማጠቃለያ መርሃግብር ላይ አለመገኘት እንደተራ ክስተት ማየት የሚገባ አይመስለኝም። ባኞ ቤት ተሰራ፥ ሽንት ቤት ተገነባ ብሎ ለምርቃቱ ጀሌውን አንጋግቶ የሚሄደውና ለቴሌቪዥንና ፎቶግራፍ ቀረጻ ጥንቅቅ ብሎ የሚቀርበው አብይ አህመድ በዚህ የአገዛዙ ትልቅ ድግስ ላይ አለመገኘቱ በሌላ ጉዳይ ተጠምዶ ነው የሚለው ሰብብ ምክንያት ማንንም የሚያሳምን አይደለም። ከእሱና ከሚስቱ በስተቀር ሁሉም ጀሌዎቹ አዳራሹ ውስጥ ነበሩ። ደግሞ መርቆ የከፈተው መድረክን መዝጋት የነበረበት እሱ መሆን ነበረበት። እንደሰማሁት በመርሃ ግብሩ ላይ የእሱ መገኘት ተጠቅሶ ነበር። ግን አብይ አህመድ የለም። የት ሄዶ? እሱን የበላ ጅብ ካለስ ለምን አልጮኸም? አንዳንድ ሹክሹክታዎች የሰውዬውን መታመም የሚያሳዩ ናቸው። ቢሮው ከታየም 10 ቀናት እንዳለፉትም ይነገራል። ያለወትሮውም በቴሌቪዥን ስክሪን ላይ የማይጠፋው አብይ አህመድ በዚህ የአገዛዙ ትልቅ መድረክ ላይ አለመታየቱ ጥርጣሬዎችን እንድናጤናቸው ያደርጉናል። አብይ ታማሚ እንደሆነ ከግምት በላይ መረጃዎች ያመለክታሉ። ከጭንቅላቱ የኋላ ክፍል ጋር በተያያዘ በየጊዜው ለህክምና ውጭ ሀገር እንደሚመላለስ በቅርበት የማውቀው መረጃ አለኝ። ታዬ ደንደአ ከመታሰሩ በፊት በነበረን የስልክ ቆይታ አንድ ቀን የገጠመውን አጫውቶኛል። አብይ አህመድ ውጭ ሀገር ለህክምና ቆይቶ ሲመለስ ከሽመልስ አብዲሳ ጋር በተፈጠረ የክረረ አለመግባባት የተነሳ ሊያናግረው ቤተመንግስት ጠርቶት ነበር። አብይ የሰውን አእምሮ ለመቆጣጠር የሚጠቀማቸው ስልቶችን ታዬ ደንደአ ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ገለጸልኛና በቤተመንግስት ቆይታውም አብይ አህመድ ኮቱን አውልቆ ሸሚዙንም ቁልፉን ፈትቶ ጀርባውን ለታዬ ያሳየዋል። ከወገቡ ጀምሮ እስከ ኋለኛ የጭንቅላቱ ክፍል ድረስ በፋሻ ተጠቅልሏል። ከበድ ያለ ህክምና አደርጎ እንደተመለሰ ለታዬ ነገረው። ጭንቅላቱን ለመስለብና ታዬ አርፎ እንዲቀመጥ ለማድረግ እንዲህ ዓይነቱን ታክቲክ እንደሚጠቀም ታዬ አውቆ ነበርና ብዙም አልደነገጠም። ለማንኛውም አብይ አህመድ ጽኑ በሆነና ከአንጎል ጋር በተያያዘ የጤና ችግር ውስጥ እንዳለ ታዬ በወቅቱ አጫውቶኝ ነበር። በቅርቡም ዶ/ር ሚልኬሳ ሚደጋ ባጋራን መረጃ አብይ አህመድ በየጊዜው ከኋላው የጭንቅላቱ ክፍል ደም የሚቀዳ እንደሆነ በዚህም ከአንድ ወር በፊት ለዚሁ ህክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ እንደነበር ገልጾልናል። በአንድ ወር ልዩነት አብይ አህመድ ወደዚያ ህክምና ሄዶ ሊሆን እንደሚችል ከጥርጣሬም በላይ መግለጽ ይቻላል። ይህ ሁኔታ የመለስ ዜናዊን የመጨረሻ ሳምንታት አስታወሰኝ። መልስ ዜናዊ በጭንቅላት ካንሰር ይታመም ነበርና ኢሳት ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች የአቶ መለስ ዜናዊን የጤና ሁኔታ በየጊዜው እየተከታተለ ለተመልካቹ ያቀርብ ነበር። ሀምሌ 21 በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2004 ዓመተ ምህረት መለስ ዜናዊ ህይወቱ አለፈ። መረጃው ለኢሳት ደርሶት ከማንም አስቀድሞ የመለስ ዜናዊ ህልፈት ይፋ አደረገ። በወቅቱ የህወሀት/ኢህ አዴግ መንግስት መለስ ዜናዊ ለስራ ጉዳይ በውጭ ሀገር እንደሚገኝ በመግለጽ ከፍተኛ የመረጃ ማዛባት ዘመቻ ላይ ተጠምዶ ነበር። በረከት ስምዖን እንደውም ለእንቁጣጣሽ ጠብቁት ይመጣል የሚል መግለጫ ሰጠ። መለስ ዜናዊ በዚያን ጊዜ በብራስልስ የአስክሬን ማረፊያ ሞርግ ውስጥ ነበር። በዚያን ሰሞን የአፍሪካ ህበረት ወሳኝ ስብሰባ በአዲስ አበባ ይካሄድ ነበርና የወቅቱ የህብረቱ ሊቀመንበር የሴኔጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ''ወንድማችን መለስ ዜናዊ ከአጠጋባችን ባለመኖሩ እናዝናለን'' ሲሉ ተናገሩ። ህወሀት/ኢህ አዴግ የደበቀውን ሚስጢር ማኪ ሳል አፍረጠረጡት። ይህን የማኪ ሳልን መግለጫ ለማስተባበል በወቅቱ የህወሀት/ኢህ አዴግ አገዛዝ መጠነ ሰፊ የመግለጫ ጋጋት ሲያቀርብ እንደነበረ አስታውሳለሁ። ከአንድ ወር በኋላ የመልስ ዜናዊ ህለፈት በብሄራዊ ቴሌቪዥን ይፋ ተደረገ። የሰሞኑ የአብይ አህመድ ከሚዲያና ከመድረኮች መጥፋት ያን ወቅት አስታወሰኝ። ለምን እንደሆነ አላውቅም። ግን አብይ አህመድ የት ነው? መደበኛውን የጤና ህክምና ክትትል ሊያደርግ ወይስ ከዚያ የከፋ ነገር ይኖር ይሆን? መጠርጠራችን ስህተት አይደለም። የሀገር መሪ ነውና ከዛሬው ዓይነት መድረክ ሲጠፋብን ጊዜ አሳሰበንና ነው ይህቺ የለቀለቅነው😜😀😋 Messy Mekonnen

ሰበር! "ከብልፅግና ጋር ተስማምተን ወስነናል" ኮምሽኑ የምክክሩ ተሳታፊዎች ስብሰባ ረግጠው ወጥተዋል ምክክር ኮምሽኑ ከምክክር ሂደቱ ውጭ ከብልፅግና ጋር ተስማምቶ አዲስ አበባ የኦሮሚያ መቀመጫ እንድትሆን ወስኛለሁ ብሏል። ከደቂቃዎች በፊት የአዲስ አበባ ጉዳይ እንዲነበብ የተደረገ ሲሆን የምክክር ኮምሽኑ ከፍተኛ አመራር ዮናስ አዳዬ የአዲስ አበባን ጉዳይ የሚያቀርቡትን በማቋረጥ ኮምሽኑ አዲስ አበባ ጉዳይ ከብልፅግና አመራሮች ጋር ተነጋግሮ የኦሮሚያ መቀመጫ እንድትሆን መወሰኑን ለተመካካሪዎች ገልፆአል። የአዲስ አበባ ጉዳይ በተመካካሪዎቹ ተወካይ ዮሃንስ መኮንን በኩል እየቀረበ የነበር ሲሆን የተመካካሪዎቹ ውሳኔ አዲስ አበባ ኦህዴድ አልቀበለውም ያለው አማራጭ ነበር ተብሏል። በዚህ ወቅት ታዲያ የኮምሽኑ አመራር ዮናስ አዳዬ ወደ መድረክ በመውጣት በዚህ ጉዳይ ከብልፅግና አመራሮች ጋር ተስማምተው ለኦህዴድ መወሰናቸውን ገልፆአል። ዮናስ አዳዬ የተመካካሪዎቹን ውሳኔ በማቋረጥ ከብልፅግና ጋር ተስማምተን የኦሮሚያ መቀመጫ እንድትሆን ወስነናል ብሎ ሲገልፅ የአማራ ክልል፣ የአዲስ አበባና ሌሎች ተወካዮች አቋርጠው ጥለው መውጣታቸው ታውቋል Via Getachew Shiferaw

photo content

🛑🛑የአዲስ አበባን ህዝብ እወክላለሁ ብለው የተቀመጡት ከንቲባ፣ አዲስ አበባ የኦሮምያ መሆን አለባት እያሉ ሽንጣቸውን ገትረው ሲከራከሩ ስትሰማ፣ እርሳቸው ከንቲባ ከሆኑበት ጊዜ ጀምሮ ከተማዋን “ኦሮማይዝድ” ለማድረግ የተኬደበት እርቀት ውል ብሎ ይታይሃል። እንዲሁም ለምን በየመስሪያ ቤቱ የአንድ አካባቢ ሰዎች ያለ ብቃታቸው እየተመረጡ እንዲሰገሰጉ እንደተደረገ፣ መሬት ለእነማን ይሰጥ እንደነበር ሁሉ ፍንትው ብሎ ይታይሃል። ሽመልስ አብዲሳ “አዲስ አበባ የኦሮምያ ካልሆነ ነገ ኦሮሞ ከከተማ ይውጣ ቢባል ምን ዋስትና አለው?” ብሎ መጠየቁንም ሰምቻለሁ። እናንተስ ነገ አዲስ አበባን የግላችሁ ካደረጋችኋት በኋላ፣ ከኦሮሞ ውጭ ያለው ህዝብ ሁሉ ይውጣ ብትሉ ነዋሪው ምን ዋስትና አለው? አታደርጉትም እንዳይባል በአርሲ፣ በወለጋ ወዘተ አሳይታችሁናል። የማፈናቀል፣ መሬትና ህንፃ የመቀማት ልምዱም አላችሁ። በነገራችን ላይ በኢትዮጵያ ህዝብ ሃብት ደብረዘይት አካባቢ የሚገነባው አዲሱ አየር ማረፊያም፣ ነገ የኦሮምያ ነው ቢባል፣ ህዝቤ ምንም ዋስትና የለውም። አዲስ አበባ ላይ ይህ ሁሉ ኢንቨስትመንት ይፈስ የነበረው ከተማዋ የኦሮምያ መሆኗ አይቀርም በሚል ሂሳብ ነበር ማለት ነው። ማን ያውቃል ከተማዋ የኦሮምያ ካልሆነች ቀሪው የፕሮጀክት ብር ወደ ሸገር ሊዞር ይችል ይሆናል። ስስታም ሰው በፍቅር አብሮ መኖር አያውቅም ይባላል። እናም አሸንፎ ከመውጣት ውጭ ኢትዮጵያን የማዳኛ መንገድ ያለ አይመስለኝም። Via Fasil Y

🛑🛑🛑ዜናዎች 🛑በአገራዊ ምክክር ጉባኤው 300 ያህል የኦሮሚያ ክልል ተመካካሪዎች፣ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ መኾኗን የሚያረጋግጥ ድንጋጌ በሕገመንግሥቱ ይካተት የሚለው ጥያቄያችን አማራጭ የሌለው ምክረ ሀሳብ ኾኖ ካልተያዘ ከጉባኤው እንወጣለን በማለት ማስጠንቀቃቸውን ዋዜማ ሠምታለች። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንም፣ የጋራ ማረጋገጫ ቡድኑ ያመሳከራቸውን ምክረ ሀሳቦች ከማቅረቡ በፊት ስብሰባ ያልጠራውን የክልል ተወካዮች ጉባኤ ትናንት ሰብስቦ የኦሮሚያ ተመካካሪዎችን ቅሬታ አቅርቧል። የክልል ተወካዮች ጉባኤ፣ ቅሬታውን መርምሮ የመፍትሄ ሀሳብ የሚያቀርብ የ11 ክልሎች ፕሬዝዳንቶች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ ሦስት የትግራይ ተወካዮች፣ አምስት የሃይማኖቶች ተወካዮች፣ ሦስት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁለት የወጣቶች ተወካዮች የተካተቱበት ኮሚቴ አቋቁሟል። ኾኖም በርካታ ተመካካሪዎች፣ የኦሮሚያ ተመካካሪዎች ቅሬታ ከምክክር ሂደቱ የወጣና ሂደቱን ወደ ኋላ የሚመልስ ነው የሚል ተቃውሞ አሠምተዋል ተብሏል። ለሥራ ቡድኖች ከቀረቡት 476 ምክረ ሀሳቦች ውጭ አዲስ የሚጨመር ወይም የሚቀነስ ምክረ ሀሳብ ካለ፣ ራሳቸውን ከጉባኤው ለማግለል የወሠኑ ተመካካሪዎች መኖራቸውም ታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን፣ የምክክር ጉባኤው በእያንዳንዱ አጀንዳ ላይ የተጠናቀሩትን የመጨረሻ ምክረ ሀሳቦች በማዳመጥ ላይ መኾኑን ዛሬ ማምሻውን ገልጧል። የምክክር ጉባኤው የተጠራው፣ የኦሮሚያ ተወካዮችን ቅሬታ ይመረምራል የተባለው የክልል ተወካዮች ገባኤ ምን መፍትሄ አቅርቦ እንደኾነ ግን ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ማወቅ አልተቻለም። 🛑ሥልጣን በኃይል የተቆጣጠረው ሕወሃት-መራሹ የትግራይ አስተዳደር፣ ትግራይ ሕዝቧንና ግዛቷን ከጥቃት ለመከላከል በቂ አቅም አላት አለ። የክልሉ አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ እስካሁን ያሳየው ትዕግስት እንደ ድክመት ወይም የትግራይ ሕዝብ ራሱን መከላከል እንደማይችል ተደርጎ መቆጠር የለበትም በማለት አጽንዖት ሠጥቷል። በትግራይ ላይ የሚፈጸሙ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ እንዲያወግዝና ሁኔታው ተባብሶ ወደለየለት ጦርነት እንዳያመራ ጣልቃ እንዲገባም አስተዳደሩ ጠይቋል። አስተዳደሩ፣ ፖለቲካዊ ልዩነቶችን በንግግር ለመፍታት አሁንም ዝግጁ መኾኑን ገልጧል። በሌላ በኩል፣ የትግራይ ትምህርት ቢሮ፣ ትናንት መቀሌ ውስጥ የድሮን ጥቃት የተፈጸመው በመምህራን መኖሪያ ላይ ነው በማለት ከሷል። ቢሮው፣ በጥቃቱ 14 መምህራን እና ቤተሰቦቻቸው የመቁሰል ጉዳት እና በመምህራን ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ጠቅሷል። የክልሉ መምህራን ማኅበርም፣ የድሮን ጥቃቱ በመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ እንደተፈጸመ በመግለጽ አውግዟል። 🛑በኢትዮጵያ የወባ በሽታ አስተላላፊ ተሕዋሲያን ዘረ መላቸውን በመቀያየር መድሃኒት የመቋቋም አቅማቸው በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ጤና ሚንስቴርና የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከአሜሪካ ተመራማሪዎች ጋር ባደረጉት ጥናት አረጋገጡ። በአገሪቱ ከስድስት ዓመት በፊት 1 ሚሊዮን የነበረው በወባ የተያዙ ሰዎች ቁጥር በአውሮፓዊያኑ 2024 ወደ 10 ሚሊዮን አሻቅቧል። መድሃኒቶችን የሚቋቋሙ በርካታ የወባ ተኅዋሲያን ዝርያዎች በስፋት መሠራጨታቸውን ጥናቱ አሳይቷል። ኾኖም መድሃኒቶችን የሚቋቋሙ ተሕዋሲያን መበራከት በአገሪቱ ውስጥ የወባ በሽታ ለመጨመሩ ዋነኛ ምክንያት አይደለም ያለው ጥናቱ፣ የወባ መቆጣጠሪያ ፕሮግራሞች መቋረጥና የአየር ንብረት ለውጥ አስተዋጽዖ እንዳደረጉ ገልጧል። በሽታውን በመከላከል ላይ ትልቅ ትኩረት ማድረግና የበሽታ ምርመራን ማስፋፋት ከፍተኛ ትኩረት እንዲሠጠው ጥናቱ አሳስቧል። 🛑የኢትዮጵያና ቻይና ኩባንያዎች የ330 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያላቸው 33 የትብብር ስምምነቶች ሰሞኑን ተፈራረሙ። አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው የሁለቱን አገራት የወጪ ንግድ ለማሳደግ ባለመ መድረክ ላይ ከ200 በላይ የኢትዮጵያ እና ቻይና ኩባንያዎች ተሳትፈዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልከው የወጪ ምርት 369 ሚሊዮን ዶላር መድረሱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስትር ካሳሁን ጎፌ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል። ካሳሁን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ኢትዮጵያ ወደ ቻይና ገበያ የምትልከው ምርት በ92 በመቶ ማደጉንም ገልጸዋል። ቻይና ያለ ታሪፍ በርካታ ምርቶቻቸውን እንዲልኩ ከፈቀደችላቸው የአፍሪካ አገራት አንዷ ናት። 🛑ነገ ቅዳሜ በመቀሌ እንዲካሄድ ታቅዶ የነበረው የአሽንዳ ዓመታዊ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሠረዘ። የአሸንዳ በዓል ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት የተሠረዘው፣ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በሚካሄደው የድሮን ጥቃት ሳቢያ መኾኑን የትግራይ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ገልጧል። የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች አንቂዎች፣ በክልሉ በሴቶች ላይ የሚፈጸመሙ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን በመቃወም ሴቶች በዓሉን ጥቁር በመልበስና "ጥቁር አሸንዳ" በሚል መሪ ቃል እንዲያከብሩት ቅስቀሳ ሲያደርጉ ነበር። ይህንኑ ተከትሎ፣ የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ከመደበኛው ባሕላዊ ስነ ሥርዓት ውጪ ሌላ እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም ሲል ሰሞኑን ማስጠንቀቂያ አውጥቶ እንደነበር አይዘነጋም። 🛑የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች፣ በተለያዩ የሙያ መደቦች ለሚቀጠሩ የውጭ ዜጎች ዝቅተኛው ወርሃዊ ደመወዝ አራት ሺሕ ድርሃም ወይም 1 ሺሕ 80 ዶላር ገደማ እንዲኾን ወሠነች። የአገሪቱ መንግሥት የውጭ ዜጎች የሚሠማሩባቸውን ሁሉንም የሙያ መስኮች በዘጠኝ መደቦች ደልድሏቸዋል። የውጭ ዜጎች የሚቀጠሩባቸው የሙያ ዘርፎች በዘጠኝ መደቦች የተከፈሉት፣ የዓለም የሥራ ድርጅትን የሙያ ደረጃ መስፈርቶች መሠረት በማድረግ መሆኑን የአገሪቱ መንግሥት ገልጧል። ከዘጠኙ የሙያ መደቦች መካከል፣ ከድርጅት ማናጀርነት፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከግብርና፣ ከአገልግሎትና ሽያጭ እና ከማዕድን ዘርፍ ጋር የተያያዙ ምድቦች ይገኙበታል። ኢትዮጵያ ከቤት ሠራተኞች በተጨማሪ በቅርቡ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የሠለጠኑ ባለሙያዎችን ወደ ኢምሬቶች መላክ መጀመሯ ይታወሳል።

የአማራ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ የጋምቤላ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ የደቡብ ምዕራብ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ አማርኛ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ ሀረሪ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ በተግባር አማርኛ ፤ በወረቀት ግን አደሬ፣ ኦሮምኛና አማርኛ የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ አማርኛ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ የፌድራል ተቋማት የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ የፌድርሽን ምክር ቤት ስብሰባ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ የምክክር ኮሚሽኑ ጉባኤ የተካሄደው ~ ~ ~ ~ በአማርኛ የብልጽግና ጽ/ቤት እና ምክር ቤት ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ የታላቁ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሥራ ቋንቋ ~ ~ አማርኛ ሌላው ቀርቶ TPLF እና OLA የሚመክሩት ~ ~ ~ ~ አማርኛ መሬት ላይ ያለው የአማርኛ ሚና በዚህ ደረጃ ሆኖ እያለ ቋንቋውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ አድርጎ ለመሰየም አለመቻል አስገራሚ ነው። የዚህ ምክንያቱ ደግሞ የሀገራችን ኋላቀር የብሽሽቅ ፖለቲካና የተቃርኖ ትርክት ነው። በእርግጥ አማርኛ ብሄራዊ ቋንቋ ተብሎ ተሰየመም አልተሰየመም የሚቀይረው ነገር የለም። ይሁንና ባለመሰየሙ በኋላቀር የተቃርኖ ትርክት አይምሯቸው የተበረዘ ወገኖች ግን የደስታና የእርካታ ስሜት ይሰማቸዋል። እነሱ እርካታ ይሰማቸው ዘንድም አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተብሎ አይሰየምም። የሆነ ሆኖ አብዝሀኛው ህዝባችንን የሚያግባባ ቢያንስ አንድ ሀገራዊ ቋንቋ መኖሩ መልካም አጋጣሚ ቢሆንም ፤ በጥላቻ እና ኋላቀር የተቃርኖ ትርክት ምክንያት ይሄን በረከት ወደ እርግማን እና ልዩነት ቀይረነዋል። @highlight

photo content

የአማራ ክልል ተወካዮች በተለያዩ ጊዜያት በምክክሩ ሂደት ተስተውለዋል ያሏቸውን ክፍተቶች በሚመለከት ለኮሚሽኑ ቅሬታ ማቅረባቸውን መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ለቀረቡ ቅሬታዎች ምላሽ አለመሰጠቱንና በአሁናዊ የምክክር ሂደቱ ዙሪያ ያላቸውን ቅሬታ አስመልክቶ የኮሚሽኑን ኮሚሽነሮች ማነጋገራቸውን ሰምተናል። ተወካዮቹ “የምክክር ሂደቱ ተጥሶ ወደ ኋላ እንዲመለስ መደረግ የለበትም፣ የክልል ተወካዮች ጉባኤ የሚጠራበት አሠራር የለም፣ ኮሚሽኑ በዘረጋው አሠራር መሰረት በሥራ ቡድን የጸደቀ ምክረ ሀሳብ ዳግም የሚታይበት ምክንያት የለም፣ ኮሚሽኑ ወደ መደበኛ የምክክር ሂደቱ ተመልሶ ጠቅላላ ጉባኤ የማያካሂድ ከሆነ ራሳችንን ከምክክሩ እናገላለን” የሚሉና ሌሎች የቅሬታ ሀሳቦችን ማቅረባቸውን ምንጮች ነግረውናል። የኮሚሽነሮች ምላሽ የአማራ ክልል ተወካዮችን ያነጋገሩት ኮሚሽነሮች፤ ኮሚሽኑ የምክክር ሂደቱን የጣሰ ተግባር አላደረገም የሚል ምላሽ መስጠታቸውን ሰምተናል። ከኦሮሚያ ክልል ተወካዮች የቀረበውን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩ በሽምግልና እንዲታይ ውሳኔ ማሳለፋቸውን ለአማራ ተወካዮች እንደገለጡና የክልል ተወካዮች ጉባኤ እንዲጠራ የተደረገው ለዚሁ አላማ መሆኑን ማስረዳታቸውን ምንጮች ነግረውናል። በዚህም ከክልል ተወካዮች ጉባኤ ተውጣጥቶ የተቋቋመው ኮሚቴም ሁለቱ ወገኖች በጠቅላላ ጉባኤው ተሳትፈው የምክክር ሂደቱን በአግባቡ እንዲያጠናቅቁ የሚያደርግ ምክረ ሀሳብ እንዲያመነጩ መጠየቃቸውን፤ ከዚህ ባለፈ የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች ያነሱትና የአዲስ አበባአ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫነት ጉዳይን የሚመለከተው ምክረ ሀሳብ ላይ በኮሚቴው አማካኝነት የሚደረግ ለውጥ አይኖርም ሲሉ ኮሚሽነሮች መናገራቸውን ምንጮች ነግረውናል። የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገብረ ሥላሴ፤ “በጠቅላላ ጉባኤ የሚነበብ ምክረ ሀሳብ ለሁሉም የሥራ ቡድኖች ቀደም ሲል የቀረበው እንጂ፣ አዲስ ምክረ ሀሳብ አይካተተም” በሚል ለአማራ ክልል ተወካዮች ንግግር ማድረጋቸውን ሰምተናል። ከምክክር ሂደቱ ለመውጣት ያቆበቆቡ ተመካካሪዎች ኮሚሽኑ ለተመካካሪዎች ባዘጋጃቸው የማረፊያ ቦታዎች ከሌሎች ጊዜያት የተለየ ድባብ መኖሩን ተረድተናል። ለሥራ ቡድኖች ከቀረቡት ከ476 ምክረ ሀሳቦች የሚጨመር አልያም የሚቀነስ ምክረ ሀሳብ ካለ ራሳቸውን ከምክክር ሂደቱ ለማግለል የወሰኑ ተመካካሪዎች ወደየመጡበት አካባቢ ለመመለስ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውንም ምንጮች ነግረውናል። እነዚህ ተመካካሪዎች ኮሚሽነሮች የአማራ ክልል ተወካዮችን ካነጋገሩ በኋላ፣ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የሚቀርበውን ምክረ ሀሳብ ሰምተን ውሳኔያችንን እናሳልፋለን ብለው እየተጠባበቁ እንደሚገኙም ተረድተናል። ለነሐሴ 15 ቀን የተቀጠረው ጠቅላላ ጉባኤ ኮሚሽኑ ያቋቋመው ኮሚቴ የሚያቀርበውን ምክረ ሀሳብ መሰረት በማድረግ ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚመለከት ስብሰባ ሰኔ 15 ጠዋት እንደሚደረግ የነገሩን ምንጮች፤ ጠቅላላ ጉባኤው ነሐሴ 15 ከሰዓት በኋላ ይደረጋል በሚል ለተመካካሪዎች እንደተነገራቸው ጠቁመዋል። ኮሚሽነሮች ለኦሮሚያ ክልል ተወካዮች፣ ለክልል ተወካዮች ጉባኤ አባላት እና ለአማራ ክልል ተወካዮች የሰጧቸው ማብራሪያዎችና ምላሾች የተለያየ ይዘት ያላቸው መሆናቸውን ተረድተናል ያሉት ምንጮቻችን፤ ሁለቱም ወገኖች በጠቅላላ ጉባኤ ተገኝተው የምክክር ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ የማድረግ ትልቅ የቤት ሥራ እንደሚጠብቃቸው ነግረውናል።[ዋዜማ] ዘገባው የዋዜማ ነው ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዝርዝር መረጃና ትንተና ከስር በኮመንት መስጫው ሊንክ ላይ ተቀምጧል፤ ይከታተሉ…

♦ 300 የሚደርሱ ኦሮሚያ ክልልን መወከላቸውን የገለጡ ተመካካሪዎች . . . ዋዜማ- ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በ37ኛ ቀን ውሎው ሊያካሂድ የነበረው ጠቅላላ ጉባኤ ሳይካሄድ ቀርቷል። ኮሚሽኑ በተመካካሪዎች የቀረቡ 476 ምክር ሀሳቦች ነሐሴ 14 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በጠቅላላ ጉባኤ እንደሚጸድቁ አስታውቆ የነበረ ቢሆንም፤ ኦሮሚያ ክልልን የወከሉ ተመካካሪዎች ባቀረቡት ቅሬታ ምክንያት ጉባኤው ሳይካሄድ መቅረቱን ምንጮች ነግረውናል። ነሐሴ 13 ቀን ምን ተፈጠረ በስምንቱም አጀንዳዎች ዙሪያ የተጠናቀሩና የተመሳከሩ 476 ምክረ ሀሳቦች ነሐሴ 13 ቀን በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ በሥራ ቡድን ደረጃ ለሁሉም ተመካካሪዎች ቀርበዋል። ኮሚሽኑ ምክረ ሀሳቦች ውሳኔ የሚያገኙበትን አሠራር ቀደም ብሎ አሳውቆ የነበረ ቢሆንም፤ አሠራሩን ተግባራዊ ሳያደርገው ቀርቷል። በሰነድ ተዘጋጅቶ በቀረበው አሠራር ምትክም፤ ምክረ ሀሳቦች ከነ አማራጮቻቸው በሥራ ቡድን ደረጃ ጸድቀው በቀጥታ ወደ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲቀርቡና በጭብጨባ እንዲጸድቁ መወሰኑን የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በተለያዩ ጊዜያት በሰጧቸው መግለጫዎችና፤ ለተመካካሪዎች ባቀረቧቸው ማብራሪያዎች ገልጠዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገብረሥላሴ ነሐሴ 13 ቀን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫም፤ በሥራ ቡድን ደረጃ የቀረቡት ምክረ ሀሳቦች ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርበው እንደሚጸድቁ ገልጠው ነበር። በሁሉም የሥራ ቡድኖች ሁሉም ምክረ ሀሳቦች ከተነበቡ በኋላ፤ ነሐሴ 14 ቀን በጠቅላላ ጉባኤ “በጭብጨባ” እንደሚጸድቁ በኮሚሽኑ ባለሙያዎች መነገሩን የገለጡት የዋዜማ ምንጮች፤ ከዚህ ሂደት በኋላ አብዛኞቹ ተመካካሪዎች ወደ ማረፊያቸው ማቅናታቸውን ነግረውናል። ይሁንና 300 የሚደርሱ ኦሮሚያ ክልልን መወከላቸውን የገለጡ ተመካካሪዎች ቅሬታ አለን ሲሉ ኮሚሽነሮች እንዲያነጋግሯቸው መጠየቃቸውን የገለጡልን ምንጮች፤ ሦስት ኮሚሽነሮች የተመካካሪዎችን ቅሬታ መቀበላቸውን ነግረውናል። ተመካካሪዎቹ በአዲስ አበባ ጉዳይ በቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ዙሪያ ቅሬታ እንዳላቸው፤ “አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ መሆኗን” የሚያረጋግጥ ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ አማራጭ የሌለው ምክረ ሀሳብ ሆኖ ካልተካተተ ከምክክር ሂደቱ እንደሚወጡ ለኮሚሽነሮች መናገራቸውን ሰምተናል። ኮሚሽነሮችን ያነጋገሩት ተመካካሪዎች በአዲስ ኮንቬንሽን ማዕከል እስከ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ እርስ በእርስ ሲመካከሩ ማምሸታቸውን የገለጡል ምንጮች፤ ኮሚሽነሮች ደግሞ ስብሰባ ሳያካሂድ የቆየው የክልል ተወካዮች ጉባኤ ቀደም ብሎ ዕቅድ ባይያዝለትም ነሐሴ 14 ቀን እንዲሰበሰብ ለጉባኤው አባላት መልዕክት ማስተላለፋቸውን ነግረውናል። ነሐሴ 14 ቀን ጠዋት ነሐሴ 13 ቀን ለተመካካሪዎች በተላለፈው መልዕክት መሠረት ተመካካሪዎች በጠቅላላ ጉባኤው ለመሳተፍ ወደ ምክክር አዳራሽ ቢያቀኑም፤ የክልል ተወካዮች ጉባኤ ስብሰባ ቀደም ብሎ እንዲካሄድ መወሰኑ ተነገራቸው ። በኮሚሽኑ ውሳኔ ግራ የተጋቡ ተመካካሪዎች፤ ኮሚሽኑ ከምክረ ሀሳብ የውሳኔ አሰጣጥ ሥርዓት ጋር የተገናኙ አካሄዶችን ሳይከተል መቅረቱን በማንሳት የክልል ተወካዮች ጉባኤ እንዲካሄድ የተወሰነበትን ምክንያት ጠይቀዋል። የኮሚሽኑ ባለደረቦችም ጉባኤው እንዲሰበሰብ የተደረገው ከኦሮሚያ ክልል ተመካካሪዎች የቀረበውን ቅሬታ መሠረት በማድረግ ኮሚሽኑ ባስተላለፈው ውሳኔ ምክንያት መሆኑን የሚያመላክት ምላሽ መስጠታቸውን ሰምተናል። የጉዳዩን አሳሳቢነት የተመለከቱ ተመካካሪዎች በተለያዩ ቡድኖች ተከፋፍለው እርስ በእርስ ሲነጋገሩና ሲመካከሩ እንደነበር ያስተዋሉ ምንጮች ለዋዜማ እንደገለጡት፤ ቀጥዩን ሂደት የተመለከቱ መደበኛ ያልሆኑ ውይይቶች ተካሂደዋል። ለስብሰባ የተጠሩት የክልል ተወካዮች ጉባኤ አባላት ስብሰባ ከመጀመራቸው በፊትም ጉባኤው የተጠራበትን ምክንያት በተለያየ መንገድ መጠየቃቸውን ሰምተናል። ሙሉ የጉባኤው አባላት ባልተገኙበትና ውጥረት በነገሰበት ስብሰባም፤ የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች የኦሮሚያ ክልል ተወካይ ተመካካሪዎች ያቀረቡትን ቅሬታ ለጉባኤው አባላት ማቅረባቸውን ገልጠዋል። የጉባኤው አባል የሆኑት የሁሉም ክልሎች ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የሁለቱ ከተሞች ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በተካሄደው ስብሰባ፤ “አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ መሆኗን የሚያረጋግጥ ድንጋጌ በሕገ መንግስቱ እንዲካተት” የሚል አማራጭ የሌለው ምክረ ሀሳብ በመጨረሻው የምክረ ሀሳብ ሰነድ እንዲካተት መጠየቁን ሰምተናል። በፌደራል ከተሞች ጉዳይ የተጠናቀረው የምክረ ሀሳብ ሰነድ ኮሚሽኑ ተግባራዊ ባደረገው አሠራር መሠረት በሥራ ቡድን ደረጃ ጸድቆ የጠቅላላ ጉባኤውን መካሄድ እየተጠባበቀ የሚገኘው የምክረ ሀሳብ ሰነድ፤ በአዲስ አበባና የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ጉዳይ ሁለት አማራጭ ምክረ ሀሳቦችን መያዙን መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ምክረ ሀሳብ ክልሎች ርዕሰ ከተማቸውን ራሳቸው መምረጥ እንደሚችሉ የሚያስቀምጥ “የመርህ ድንጋጌ” በሕገ መንግስቱ እንዲካተት የሚጠይቅ ነው። ሁለተኛው ምክረ ሀሳብ ደግሞ በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 5 ላይ፤ “አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ከመሆኗ ጋር በተያያዘ ከተማዋንና ክልሉን የሚመለከቱ ጉዳዮች በሕግ ይወሰናሉ” የሚል ድንጋጌ እንዲካተት የሚጠይቅ ነው። ይህ ምክረ ሀሳብ ኮሚሽኑ ተግባራዊ ባደረገው አሠራር መሠረት በጋራ ማረጋገጫ ቡድን ተረጋግጦና በአጀንዳው ዙሪያ በተመካከረው የሥራ ቡድን የጸደቀ ሲሆን፤ ኦሮሚያ ክልልን መወከላችውን የገለጡት ተመካካሪዎች ያቀረቡት ቅሬታ ከምክክር ሂደቱ የወጣና፣ የምክክር ሂደቱን ወደ ኋላ የሚመልስ ነው የሚል ተቃውሞ ማስነሳቱን ሰምተናል። የአማራ ክልል ተወካዮች ምን አሉ? በክልል ተወካዮች ጉባኤ ስብሰባ ላይ የተገኙ የአማራ ክልል ተወካዮች፤ “ጉባኤው ለስብሰባ መጠራቱ የምክክር ሂደቱን ያልተከተለና ከአሠራር ውጭ የተደረገ ነው” ሲሉ መናገራቸውን ሰምተናል። የምክረ ሀሳብ ውሳኔ አሰጣጥ ተግባራዊ አለመደረጉን ተከትሎ የክልል ተወካዮች ጉባኤ እንዲሰበሰብ የሚያደርግ ምክንያት የለም፣ ጉባኤው ይጠራ ቢባል እንኳን የጋራ ማረጋገጫ ቡድን ሥራውን ከማከናወኑ በፊት እንጂ ቡድኑ ሥራውን ካጠናቀቀና ያደራጀውን ምክረ ሀሳብ ለሥራ ቡድኖች አቅርቦ እንዲጸድቅ ካደረገ በኋላ መሆን የለበትም በሚል የኮሚሽኑ ውሳኔ ላይ የመረረ ቅሬታ አሰምተዋል። የክልል ተወካዮች ጉባኤ ጉዳይ የተገቢነት ጥያቄ የተነሳበት የክልል ተወካዮች ጉባኤ ስብሰባ ኮሚቴ በማቋቋም ተጠናቅቋል። በጉባኤው የተገኙ የክልል ፕሬዝዳንቶችና ሌሎች ተመካካሪዎች የተለያዩ አስተያየቶችን ከሰነዘሩ በኋላ፤ ጉዳዩን በጥልቀት የሚመለከትና መፍትሄ ያፈላልጋል የተባለለትን ኮሚቴ ያቋቋመ ሲሆን፤ በኮሚቴው የ11ዱ ክልሎች ፕሬዝዳንቶች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ ሶስት የትግራይ ክልል ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤው አባል የሆኑ አምስት የሃይማኖቶች ተወካዮች፣ 3 የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራሮች፣ ሁለት የወጣቶች ተወካዮች ተካትተዋል። ኮሚቴው በከተሞች አጀንዳ ዙሪያ ከጥቃቅን ቡድን ጀምሮ የተካሄደውን የምክክር ሂደት ተመልክቶ የውሳኔ ሀሳብ እንዲያቀርብ መጠየቁን የነገሩን ምንጮች፤ ስለቀጣዩ ሂደት ግልጽ አቅጣጫ አለመቀመጡን ነግረውናል። የአማራ ክልል ተወካዮች ያቀረቡት ቅሬታ

photo content

🛑🛑🛑ዜናዎች 🛑ለአገራዊ ምክክር ጉባኤ የቀረበው አዲስ አበባ ራሷን በራሷ የምታስተዳድር ተጠሪነቷ ለፌደራሉ መንግስት የሆነች ከተማ ትሁን የሚለው ምክረ ሀሳብ ያለ ተጨማሪ አማራጭ ስምምነት ላይ ተደርሶበታል ተብሏል። ክልሎች ርዕሰ ከተማቸውን ራሳቸው እንዲመርጡ የሚፈቅድ ድንጋጌ በሕገመንግሥቱ እንዲካተት የሚጠይቅ ምክረ ሀሳብም ቀርቧል። “ርዕሰ ከተማ” እና “መቀመጫ” የሚሉት ቃላትም ባሕግ እንዲደነገጉ ተጠይቋል። “ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ያላትን ልዩ ጥቅም የሚመለከተው የሕገመንግሥቱ ድንጋጌ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ ድንጋጌ እንዲተካ አማራጭ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል። አዲስ አበባና ድሬዳዋ ባፌደሬሽን ምክር ቤት ውክልና እንዲኖራቸውና ድሬዳዋም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጭምር ውክልና እንዲኖራት ምክረ ሀሳብ መቅረቡን ምንጮች ገልጸዋል። 🛑በአገራዊ የምክክር ጉባኤው በአገር ግንባታ ላይ የተወያየው የሥራ ቡድን፣ “እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች” የሚለው የሕገመንግሥቱ መግቢያ፣ “እኛ የሕብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያ ሕዝብ” በሚል እንዲተካ ምክረ ሀሳብ አቀረበ። አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ፣ ሶማሊኛና አፋርኛ የፌደራል ቋንቋ እንዲኾኑና በክልሎች መዝሙሮች ላይ ያሉ አሉታዊ ይዘቶች እንዲስተካከሉ፣ ራሳቸውን በብሔር ማንነት መግለጽ የማይፈልጉ ዜጎች እንደ ኢትዮጵያዊ ብቻ እንዲታዩና ከብሄረሰቦች የራስን እድል በራስ የመወሠን መብት ውስጥ የመገንጠል መብትን እንዲወጣ የሚጠይቁ ምክረ ሀሳቦችም መቅረባቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በክልሎች ውስጥ የሚከሠቱ ግጭቶች አስገዳጅ ሁኔታ ከፈጠሩ ያለ ክልሉ መንግሥት ጥያቄ ፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ እንዲገባ፣ በአካባቢው ያሉ ማንነቶች በአስተዳደር መዋቅሮች እንዲወከሉ፣ የሕገ መንግስት ፍርድ ቤት እንዲቋቋምና የኢትዮጵያ ሕጋዊና ታሪካዊ ደንበር ቀይ ባሕር መሆኑ እንዲታወቅ የሚጠይቁ ምክረ ሀሳቦችም መቅረባቸው ታውቋል። 🛑ዛሬ ረፋዱ ላይ በመቀለ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች በተፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች 13 ሰዎች ከባድ እና ቀላል የመቁሠል አደጋ እንደደረሠባቸው የሕወሃት-መራሹ የክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ አስታወቀ። አንደኛው ጥቃት በሐወልቲ ክፍለ ከተማ እዳማርያም በተባለ አካባቢ በሚገኙ መኖሪያ ቤቶች ላይ እንደተፈጸመ የጠቀሰው ቢሮው፣ ሁለተኛው ኩይሓ በተባለ ቦታ እንደተፈጸመ ጠቅሷል። በጥቃቱ ከቆሠሉት መካከል፣ አንድ የሁለት ዓመት ሕጻን ይገኝበታል ተብሏል። ቢሮው፣ ለጥቃቱ ፌዴራል መንግሥቱን ተጠያቂ አድርጓል። ከግጭት ማቆም ስምምነቱ ወዲህ መቀለ ላይ የድሮን ጥቃት እንደተፈጸመ ሲገለጥ የዛሬው የመጀመሪያ ነው። 🛑ብሄራዊ ባንክ ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ባካሄደው የ500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የብር ዋጋ ከዶላር አንጻር መሻሻል አሳየ። በዛሬው ጨረታ የተጫራች ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት ከ710 ሚሊዮን ዶላር በላይ መድረሱን ባንኩ ገልጧል። ባንኩ በዛሬው ጨረታ አንድን ዶላር በ160 ብር ከ21 ሳንቲም እንደሸጠ ገልጧል። ባንኩ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ባካሄደው የ125 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ አንድ ዶላር የተሸጠው 161 ብር ከ80 ሳንቲም ሲሆን፣ ተጫራች ባንኮች ያቀረቡት ከፍተኛው ዋጋ 163 ብር ከ99 ሳንቲም ነበር። በዛሬው ጨረታ 22 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ በጨረታው የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የቻሉት ባንኮች 21 ባንኮች ናቸው። በጨረታው ላንድ ዶላር የቀረበው ከፍተኛው ዋጋ 160 ብር ከ25 ሳንቲም ገዳማ መኾኑን የጠቀሠው ባንኩ፣ ዝቅተኛው ዋጋ ደሞ 159 ብር ከ50 ሳንቲም መኾኑን ገልጧል። 🛑ኢትዮጵያ ስደተኞችን ከማኅበረሰቡ ጋር ለመቀላቀል የነደፈችውን የ"ማካተት"ብሄራዊ ፍኖተ ካርታ ወደ ተግባር ለማስገባት ብሄራዊ ኮሚቴ ሰሞኑን አቋቋመች። ኮሚቴው በፌዴራልና ክልሎች ደረጃ ጽሕፈት ቤቶችን እንደሚያቋቁም የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ገልጧል። ኮሚቴው፣ በተያዘው ዓመት ቅድሚያ የሚሠጣቸውን ተግባራት የያዘ የአፈጻጸም እቅድ አጽድቋል። "ማካተት"፣ በተለያዩ ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ ስደተኞች ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ከዜጎች ጋር እኩል እንዲያገኙ እና ሥራ በመስራት ራሳቸውን እንዲችሉ ሁኔታዎችን የሚያመቻች ብሄራዊ ፍኖተ ካርታ ነው። 🛑በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ትላንት ረቡዕ ከሰዓት በኋላ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ዋና ሥራ አሥኪያጅ እና የአዋሽ ባንክ ዋና ኦዲተርን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቀ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ዋዜማ ሠምታለች። በጥቃቱ የአዋሽ ባንክ ጊዳ አያና ቅርንጫፍ ዋና ኦዲተር ለሚ መንግሥቱ፣ የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ጊዳ አያና ቅርንጫፍ ዋና ሥራ አሥኪያጅ ማሙሽ ማሩን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ጥቃቱ የተፈጸመው፣ በወረዳው ቱሉ ሌንጫ ቀበሌ ልዩ ስሙ "መቀ ለሊ" በተባለ ሥፍራ ጸጥታ ኃይሎች ከባንኮቹ የተሠበሠበ ጥሬ ብር በተሽከርካሪ አጅበው በመጓዝ ላይ ሳሉ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። ታጣቂዎቹ ሰሞኑን በዞኑ አንገር ጉቴ ከተማ ተፈጽሞ የነበረውን ጥቃት በመሸሽ ነቀምት ከተማ ቆይተው ወደ ቀያቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ነዋሪዎችን ጭምር ከመኪና በማስውረድ መግደላቸውንና ቀሪዎችን አፍነው መውሠዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል። 🛑የኦሮሚያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እስካሁን ላላወጡ የመንግሥት ሠራተኞች ከተያዘው ወር ጀምሮ ደመወዝ እንዳይከፈላቸው ማገዱን ዋዜማ ሠምታለች። ቢሮው የሠራተኞችን ቆጠራ ለማካሄድ ሠራተኞች ፋይዳ መታወቂያ እንዲያወጡ ለበታች ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት መዋቅሮች ባለፈው ዓመት ማሳሰቢያ አሠራጭቶ የነበረ ቢሆንም፣ እስካሁን መታወቂያውን ያላወጡ ሠራተኞች መኖራቸውን ቢሮው ከጻፈው ደብዳቤ ላይ ተመልክተናል። ሠራተኞች መታወቂያውን እስከ ነሐሴ 18 ድረስ ካላወጡ በደመወዝ ክፍያ ላይ ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂ እንደማይኾን ቢሮው አስጠንቅቋል። 🛑ከተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ጋር ግንኙነት ያለው የቻይናው ዚጂን ጎልድ ኢንተርናሽናል ኩባንያ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሱዳን ድንበር አቅራቢያ የኩርሙክ የወርቅ ማውጫን ከያዘው የካናዳው አላይድ ጎልድ ኩባንያ የ9 ነጥብ 2 በመቶ የአክሲዮን ድርሻ ገዛ። ዚጂድ ከረጅም ጊዜ ድርድር በኋላ የአክሲዮን ድርሻውን የገዛው በ300 ሚሊዮን ዶላር ነው። አላይድ ኩባንያ ከማዕድን ማውጫው በተያዘው ወር ወርቅ ማውጣት እንደሚጀምር ገልጦ ነበር። ዚጂን ኢንተርናሽናል አላይድ ጎልድ ኩባንያን ካሁን ቀደም በ4 ቢሊዮን ዶላር ለመግዛት ያደረገው ጥረት ሳይሳካ መቅረቱ ይታወሳል።

የመቀሌ ከተማ በድሮን ጥቃት መመታቷ ተሰማ የትግራይ ክልል ርዕሰ ከተማ መትቀሌ ዛሬ ጠዋት በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) መመታቷን ህወሓት አስታወቀ። ጥቃቱ በቀጥታ በሰዎች መኖሪያ አካባቢ ላይ ያነ
የመቀሌ ከተማ በድሮን ጥቃት መመታቷ ተሰማ የትግራይ ክልል ርዕሰ ከተማ መትቀሌ ዛሬ ጠዋት በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) መመታቷን ህወሓት አስታወቀ። ጥቃቱ በቀጥታ በሰዎች መኖሪያ አካባቢ ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ባለሥልጣናቱ ገልጸዋል። በሰው እና በንብረት ላይ ስላደረሰው ጉዳት እስካሁን የታወቀ ነገር የለም። የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አማኑኤል አሰፋ «ስለደረሰው ጉዳት ዝርዝር መረጃ የለኝም» ብለዋል። ባለፈው ማክሰኞም ከመቀሌ 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በነበረ ጥቃት አንድ ታጣቂ መገደሉና ሁለት መቁሰላቸው ይታወሳል። በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል ያለው ውጥረት እየጨመረ በመምጣቱ ድንበሮች ላይ ተጨማሪ ጦር እየሰፈረ ይገኛል። የኢትዮጵያ መንግሥት ስለዚሁ ጥቃት እስካሁን በይፋ የሰጠው ምላሽ የለም። DW

🛑🛑🛑ዜናዎች 1🛑የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ዛሬ የምክክር ጉባኤው ያጸድቀዋል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የምክክሩ የመጨረሻ የምክረ ሀሳቦችን የያዘ ሠነድ በመጪው ሐሙስ እንደሚጸድቅ አስታወቀ። ኮሚሽኑ፣ የሁሉም አጀንዳዎች ምክረ ሀሳቦች ለስምንቱም የሥራ ቡድኖች መቅረባቸውን ዛሬ በሠጠው መግለጫ ገልጧል። የምክክሩ የተጠቃለለ የምክረ ሀሳቦች ሠነድ አራት ሺሕ አባላት ላሉት ጉባኤ በዛሬው ዕለት ሳይቀርብ የቀረው፣ ምክረ ሀሳቦችን የሚያጣጥመውና የሚያመሳክረው 120 አባላት ያሉት ቡድን የሚያከናውነው ሥራ ከፍተኛ ጥንቃቄና ተጨማሪ ጊዜ በመፈለጉ ነው ተብሏል። 🛑የአገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ በምክክር ጉባኤው ተፈጥረዋል ላሏቸው መስተጓጎሎች ተመካካሪዎችን ሰብስበው ይቅርታ መጠየቃቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በሌላ በኩል፣ በምክክር ጉባኤው ሂደት ዙሪያ ተሳታፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች መግለጫ ማውጣት ያልቻሉት፣ በውስጣቸው በተፈጠረ የሀሳብ ልዩነት ምክንያት መኾኑን ምንጮች ነግረውናል። ገዥው ፓርቲ አዲስ በሚመሠርተው መንግሥት ሥልጣን እንደሚሠጣቸው ቃል የገባላቸው አንዳንድ የፓርቲ አመራሮች፣ መግለጫ አናወጣም የሚል አቋም ይዘው መቆየታቸውን ከሦስት ፓርቲዎች አመራሮች ሠምተናል። በሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች የመከረው የምክክር ጉባኤው የሥራ ቡድን፤ ለሁሉም ዜጎች እኩል መብት የማይሠጡ የክልል ሕገ መንግሥቶች ለሰብዓዊ መብት ጥሠቶች ምክንያት በመሆናቸው መሻሻል አለባቸው የሚል ምክረ ሀሳብ ማቅረቡን ዋዜማ ተረድታለች። በሙስናና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ የመከረው የሥራ ቡድን በበኩሉ፣ የመንግሥት ሠራተኞች ግብር እንዲቀንስ ምክረ ሀሳብ አቅርቧል ተብሏል። 🛑የኢትዮጵያ መንግሥት የብር ማሽቆልቆልን ለመግታት በተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት ያወጣው 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ውጤት ሳያመጣ መቅረቱን ብሉምበርግ ዘገበ። የብር ዋጋ ኢትዮጵያ የውጭ እዳዋ እንደገና እንዲዋቀርላት ከምታደርገው ጥረት ጋር እንደሚያያዝ ዘገባው ጠቅሷል። የብር ዋጋ በተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት በ3 ነጥብ 2 በመቶ ማሽቆልቆሉንና አንድ ዶላር ከመደበኛው ምንዛሬ በ15 በመቶ ጭማሪ በትይዩ ገበያ በ180 ብር እየተመነዘረ መኾኑን ዘገባው አመልክቷል። አንዳንድ ዓለማቀፍ የፋይናንስ ባለሙያዎች እስከ ቀጣዩ ዓመት ታኅሳስ አንድ ዶላር ከ185 እስከ 195 ብር ሊመነዘር እንደሚችል ሲገምቱ፣ ሌሎች ግን ምንዛሬው 163 ብር ገደማ ላይ ሊረጋ እንደሚችል ግምታቸውን ሠጥተዋል ተብሏል። ብር እንዲዳከም ያደረጉት ዋና ምክንያቶች፣ የመካከለኛው ምሥራቅ ግጭትና የነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋ ማሻቀብ መኾናቸውን ብሉምበርግ ጠቅሷል። 🛑የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ችሎት፣ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀድሞው የሠላም ሚንስትር ዴኤታ ታዬ ደንደአ ላይ የጣለውን የእስር ቅጣት ውሳኔ ዛሬ ማጽናቱን ዋዜማ ሠምታለች። ታዬ ነሐሴ 6 ቀን በዋለው ችሎት አምስት ነጥብ የያዘ ቅሬታ አቅርበው እንደነበር የታዬ ባለቤት ስንታየሁ አለማየሁ ነግረውናል። ኾኖም ይግባኝ ችሎቱ ታዬ የእስካሁኑ የእስር ቅጣት በቂ ኾኖ ተቆጥሮ ከእስር ልፈታ በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ ቅጣቱን እንዳጸና ስንታየሁ ገልጸዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ ከመገኘት ወንጀል ጋር በተያያዘ የሰባት ዓመት እስር ፈርዶባቸው የነበረ ሲሆን፣ ታዬ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ይግባኝ መሠረት ቅጣቱ ወደ አራት ዓመት ዝቅ እንደተደረገላቸው ይታወሳል። 🛑በቢሾፍቱ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለውድድር ከመረጣቸው የውጭ ኩባንያዎች መካከል የቻይና ኩባንያዎች ቀዳሚዎቹ ኾኑ። የቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽንን ጨምሮ 10 ያህል የቻይና ወይም ከቻይና ኩባንያዎች ጋር አጋርነት የፈጠሩ ኩባንያዎች የአውሮፕላን ማረፊያውን ቁልፍ ሥራዎች ለመስራት ለመጨረሻው ውድድር ተመርጠዋል። አሜሪካ፣ ቱርክ፣ ኳታር እና ሕንድን ጨምሮ የበርካታ አገራት አንዳንድ ኩባንያዎችም በዝርዝሩ ተካተዋል። አየር መንገዱ የመጨረሻዎቹን ኩባንያዎች የሚመርጥበትን ጊዜ ወደ ቀጣዩ ዓመት ጥር አራዝሞታል። 🛑የአሜሪካዋ ቦስተን የፌደራል ፍርድ ቤት፣ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር ለአምስት ሺሕ ያህል ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የተሠጠውን ጊዜያዊ ከለላ ማቋረጥ ይችላል ሲል ትናንት ወሠነ። የአገር ውስጥ ደኅንነት መስሪያ ቤቱ ለኢትዮጵያዊያን የተሠጠውን ጊዜያዊ ከለላ እንዳያቋርጥ አንድ የፌደራሉ ፍርድ ቤት ባለፈው ሚያዝያ ጊዜያዊ እገዳ ጥሎ ነበር። የአገር ውስጥ ደኅንነት መስሪያ ቤቱ ጊዜያዊ ከለላቸው የተቋረጠባቸው ስደተኞች ወዲያውኑ በፍቃዳቸው ከአገሪቱ እንዲወጡ ያሳሰበ ሲሆን፣ ካልኾነ ግን ታስረው ወደ አገራቸው ይባረራሉ ሲል አስጠንቅቋል። ለኢትዮጵያዊያኑ ጊዜያዊ ከለላ የተሠጠው፣ ከአምስት ዓመት በፊት በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ወቅት እንደነበር ይታወሳል።