en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 313 subscribers, ranking 1 759 in the Transport category and 2 546 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 313 subscribers.

According to the latest data from 15 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 88 over the last 30 days and by 2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 40.23%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.41% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 352 views. Within the first day, a publication typically gains 2 050 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 16 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 313
Subscribers
+224 hours
+297 days
+8830 days
Posts Archive
ኔጌሌ ቦረና -ዶሎ አዶ-መልካ ሶፍቱ ሎት 1 የመንገድ  ፕሮጀክት 98 በመቶ ግንባታ ተጠናቋል አዲስ አበባ መስከረም 22፣ 2018 (ኢ .መ. አ) ሀገራችን በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን እና በሶማሌ ክልል ደግሞ ሊበን ዞንን የሚያገናኘው ኔጌሌ ቦረና ዶሎ አዶ መልካ ሶፍቱ  ሎት 1  የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 98 በመቶ  ተጠናቋል ፡፡ 64.5 ኪ ሎ ሜትር የሚረዝመው የዚህ መንገድ ግንባታ የቀድሞ ገፅታ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ የነበረ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ መሰራቱ የአካባቢውን የመንገድ ትራንስፖርት ዘርፍን ለማሳደግና በተለይም አላስፈላጊ የሆነ የጊዜ ብክነትን በማስቀረት ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ታምኖበታል፡፡ አለማየሁ  ከተማ  ጄኔራል ኮንትራክተር ኤምሲጂ ኮንስትራክሽን  ኃ.የተ.የግ.ማ. ከተሰኘ  የስራ ተቋራጭ ጋር በመቀናጀት ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን  ደግሞ ኤስጂ  አማካሪ መሀንዲሶች ኃ.የተ.የግ.ማ በማከናወን ላይ ነው፡፡ የመንገዱን ግንባታ ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የዋለው1, 371, 325, 369 ( አንድ ቢሊየን ሶስት መቶ ሰባ አንድ ሚሊየን ሶስት መቶ ሃያ አምስት ሺህ ሶስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ) ብር  በኢትዮጵያ መንግስት በጀት ተሸፍኗል፡፡ በ2013 በጀት ዓመት ግንባታው የተጀመረው ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በእስካሁኑ የስራ አፈጻጸም ከአጠቃላይ ስራው 64.32 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ስራው ተጠናቋል፡፡   ቀሪ ስራዎች  ማለትም የአደባባይ ስራ ፣ የእግረኛ መንገድ በዞን እና በወረዳ ከተሞች የመንገድ ዳር ምልክት ተከላ ፣ የእግረኛ ማቋረጫ ቀለም እና ሌሎች የመንገድ ቅብ ስራዎቹ ደግሞ በመጠናቀቅ ላይ ናችው ፡፡ መንገዱ በገጠር 10 ሜትር ፣ በቀበሌ 12  ሜትር ፣  በወረዳ 19 ሜትር  እንዲሁም  በዞን 21.5  ሜትር  ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ የመንገድ ግንባታ ስራው በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ ቦረና ዞን እና በሶማሌ ክልል የሊበን ዞን ዋና ከተማ ፊልቱን  ሚያገናኝ  መንገድ በመሆኑ በህብረተሰቡ ውስጥ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን እንደሚያጠናክር ይጠበቃል ፡፡ ፕሮጀክቱ የሁለቱን ክልሎች እንዲሁም ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖረውን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የንግድ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ በቂ የሆነ የመንገድ መሠረተ ልማት የሌለውን የአካባቢውን ሕብረተሰብ የመንገድ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል ፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው በስፋት የሚመረተውን የስንዴ ምርት ከእርሻ ቦታዎች ወደ ከተማ እና ወደ ገበያ ለሟጓጓዝ እንዲሁም ዘመናዊ የአስተራረስ ዘዴን  ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል  ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

መልካም በዓል !
መልካም በዓል !

በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በጋራ የአዳማ - አዋሽ የፈጣን መንገድ ሁለተኛው ክፍል፣ የመልካጂሎ - አዋሽ፣ ሎት 2 ፈጣን መንገድን በተመለከተ የፋይናንስ ድጋፍ ድርድር ተካሄደ በአፍሪካ ልማት ፈንድ የፋይናንስ ድጋፍ ለማካሄድ ግምገማና ውይይት ሲደረግበት የነበረው የአዳማ - አዋሽ የፈጣን መንገድ ሁለተኛው ክፍል፣ የመልካጂሎ - አዋሽ፣ ሎት 2 የፋይናንስ ድጋፍ ድርድር በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መካከል የመጨረሻ የፋይናንስ ድርድር ተካሄደ። ይህ ድርድር ባንኩ ፕሮጀክቱን ለማጸደቅ በቅርቡ ለባንኩ ቦርድ ከማቅረቡ በፊት የጋራ ግንዛቤ እና ስምምነት ለማድረግ እንዲያስችል የተደረገ ነው። የዚህ ፕሮጀክት ኣላማ በዋናነት የፍጥነት መንገድ መገንባት እንዲሁም ተጓዳኝ መሰረተ ልማቶችን ማሻሻል ያካትታል። የፍጥነት መንገድ ግንባታው በሁለት (2) ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን የመጀመሪው 48ኪ.ሜ በአፍሪካ ልማት ፈንድ ፋይናንስ የሚደረግ ሲሆን ቀሪው 19ኪ.ሜ በኮሪያ ኤግዚም ባንክ እንደሚሸፈን ይጠበቃል፡፡ ፕሮጀክቱ በዋናነት የሚያካትታቸው የመንገድ መሠረተ ልማት ግንባታ፣ የቴክኒክ ድጋፍ አገልግሎቶች፣ የሎጂስቲክስ፣ የትራንስፖርትና የንግድ፣ ተቋማዊ ድጋፍና አቅም ግንባታ፣ ለአካባቢው ህብረተሰብ የሚሰሩ ተጓዳኝ የልማት ስራዎች እና የካሳ ክፍያ እና የመልሶ ማቋቋም ይገኙበታል፡፡ ይህ መንገድ ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ እና ደቡብ ሱዳንን የሚያካትት ሁለገብ ፕሮጀክት ሲሆን ፕሮጀክቱ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የትራንስፖርት ትስስር ለማሻሻል ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በኮሪደሩ ላይ ቀልጣፋ እና ውጤታማ የትራንስፖርት ስርዓት እንዲኖር ማድረግ እና የንግድ እና በአካባቢው ያሉ አገራትን እርስ በእርስ ማስተሳሰር ነው። ፕሮጀክቱ ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ ለድህነት ቅነሳ ጥረቶች እና በፕሮጀክቱ አካባቢ ኢኮኖሚያዊ ዕድሎችን በማነቃቃት ድህነትን ለመቀነስ አስተዋፅኦ ያደርጋል። በአፍሪካ ልማት ባንክ በኩል 138.66 ሚሊዮን UA ወይም ባለው ወቅታዊ ምንዛሪ 181.5 ሚሊዮን ዶላር ፋይናንስ ለማድረግ ታሳቢ የተደረገ ሲሆን መንግስትም እስከ 26.12 ሚሊዮን UA (34.2 ሚሊዮን ዶላር) ፋይናንስ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ በኋላ የሚጠበቀው በአፍሪካ ልማት ባንክ በኩል በድርድሩ ውጤት መሰረት ፕሮጀክቱን ለባንኩ ቦርድ አቅርቦ ማጸደቅ ሲሆን እንደጸደቀም ቀጣዩ ስራ የፋይናንስ ስምምነት በመፈራም ወደ ትግበራ መግባት ሲሆን ይህም እ.ኤ.አ በ2026 መጀመሪያ ላይ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በሌላ በኩል ቀጣዩን 19ኪሜ የሚሆነውን የመንገድ ክፍል በተመለከተ ከኮሪያ ኤግዚም ባንክ ጋር የሚደረጉ ንግግሮች ትኩረት የሚሰጣቸው ይሆናል፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መልካም አዲስ ዓመት !
መልካም አዲስ ዓመት !

ጳጉሜ 4 ቀን "የከተሞቻችን ሁለንተናዊ ልማት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል ርዕስ ተከብሮ ዋለ ባቱ፣ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የዘንድሮ ጳጉሜ 4 ቀን  "የከተሞቻችን ሁለንተናዊ ልማት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት"  በሚል ርዕስ በባቱ ከተማ ተከብሮ ዋለ።  በዓሉ የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች  ምክር ቤት የመሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ  ፕሮፌሰር መሐመድ አብዶ ፣  የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ  ጫልቱ ሳኒ  ፣  የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን፣ የተጠሪ ተቋማት ዋና ዳይሬክተሮችና ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ፣ የክልል ቢሮ ኃላፊዎች እና በርካታ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተከብሯል። በፕሮግራሙ የመስክ ምልከታ እና ፓናል ውይይት የተደረገ ሲሆን በመስክ ምልከታው የሞጆ -ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ አካል የሆነውን ኮንትራት ሶስት ባቱ  - አርሲ  ነጌሌ የፍጥነት መንገድ የሥራ እንቅስቃሴን ተጎብኝቷል። በፕሮጀክቱ  መነሻ ቦታ እና በፍጥነት መንገዱ የክፍያ ጣቢያ ግንባታ ላይ የአፍታ ቆይታ በማድረግ  በፕሮጀክቱ መሃንዶሶች ለጎብኚዎች ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ በመቀጠልም ወደ ባቱ ከተማ አስተዳደር በማምራት በከተማው ውስጥ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን በከተማው አተዳደር ስለ ኮርደር ልማቱ ገለጻ ተደርጓል። በማጠቃለያው መርሐግብር   የፓናል ውይይት በካሄደ የዕለቱ መርሐግብር ተጠናቋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!

መልካመ በዓል!
መልካመ በዓል!

ስምንተኛው የመንገድ ጥናት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ):- ስምንተኛው የመንገድ ጥናት ኮንፈረንስ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ የትምጌታ አስራት ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን፣ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የመንገድ ዘርፍ ባለሙያዎች እንዲሁም ተመራማሪዎች በተገኙበት በቃሊቲ በሚገኘው የኢመአ የመንገድ ምርምር ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads የምርምር ማዕከሉ ባለፉት ሰባት ዓመታት የምርምርና ሥርፀት ኮንፈረንሶችን ሲያካሂድ የቆየ ሲሆን በተከታታይ በተከናነወኑ ጥናቶች ውጤታማ ለውጦችን ማምጣት ስለመቻሉ ተገልጿል። ኮንፈረንሱ አስራ አምስት ጥናታዊ ፅሁፎች እንደሚቀርቡ የታወቀ ሲሆን ፣ በዘርፉ ላይ ያተኮረ አውደርእይም በመካሄድ ላይ ይገኛል። በኮንፈረንሱ በሌሎች ሀገራት እና ፕሮጀክቶች ላይ የተሞከሩና ውጤታማ የሆኑ የመንገድ ግንባታና አስተዳደር ልምዶች በጥናት ተለይተው ለሀገራችን መልካም እድል ይዘው ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ። አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉ የመንገድ ዘርፍ ችግሮች ፣ ለአብነትም ለመንገድ ደህንነት ፣ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ፣ ለመንገድ መሸራተት እና መሰል ችግሮች የመፍትሄ ሃሳቦች በኮንፍረንሱ ላይ ቀርበዋል ። በመድረኩ የታደሙ ተሳታፊዎችም በመንገድ ግንባታ ፣ ዲዛይን ፣ ጥገና እና አስተዳደር አዳዲስ እውቀትንና ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም ፈጠራን በማከል ለሙያዊ ዕድገታቸው እና ለአገራቸው የመንገድ መሠረተ ልማት አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ሀገር አቀፍ የመንገድ ዘርፍ ጉባኤ ተጠናቀቀ ጅግጅጋ፣ ነሐሴ 21 ቀን 2017 ዓ/ም (ኢመአ) ከነሐሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጅግጅጋ ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ሀገር አቀፍ የመንገድ ዘርፍ ጉባኤ ተጠናቀቀ ፡፡ በጉባኤው የተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ኃላፊዎችና ተወካዮች እንዲሁም የፌዴራልና የክልል መንግስት የሥራ ሀላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በጉባኤው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፌ መሐመድ መንገድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ለማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው መንገድ የኢኮኖሚ ትስስርን የሚፈጥር እና ልማት የሚያፋጥን ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም “የመንገድ መሰረተ ልማት በሀገሪቷ ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው የመሠረተ ልማት ዘርፎች ቀዳሚና የሌሎች ልማቶች የጀርባ አጥንት ነው” ብለዋል፡፡ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው መንገድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ለማስቀጠል እና አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብን ለመገንባት አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልፀዋል። ባለፉት ዓመታት ለከተሞች በተሰጠው ትኩረት የከተማ መንገድ ለመኪኖች ብቻ ሳይሆን ለእግረኛ፣ ለብስክሌትና ለአካል ጉዳተኛ ዜጎቻቸን ያማከለና ሰው ተኮር እንዲሆን መደረጉ በመንገድ መሰረተ ልማት አዲስ ገጽታ ያጎናጸፈ መሆኑን ጠቁመው ከዚህ አኳያ የኮሪደር ልማት እየተጫወተ ያለው ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተለይ የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሞች ተቀርፀው ተግባራዊ በመደረጋቸው ውጤቶች መመዝገባቸውን እና የሀገራችን የመንገድ አውታር በከፍተኛ መጠን እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም በ10 ዓመቱ እቅድ እንደተመላከተው እንቅስቃሴን እና ተደራሽነትን ሚዛኑን በጠበቀ መልኩ ማስኬድን ዓላማ አድርጎ በመስራት ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ በመድረኩ የ2017 በጀት ዓመት የፌደራል መንገድ ዕቅድ አፈጻጸም እና ሌሎች የውይይት መነሻ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል ከ101 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የ1,048 ኪ.ሜ የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ፣ የነባር መንገዶች ማጠናከር፣ ደረጃ ማሻሻል እና የከባድ ጥገና እንዲሁም የ10,926 ኪ.ሜ ወቅታዊ እና መደበኛ ጥገና ማካሄድ መቻሉ ተገልጿል፡፡ የጀት ዓመቱ የፊዚካል እቅድ አፈጻጸምም 81 በመቶ ማሳካት መቻሉን የቀረበው የዘርፋ ሪፓርት ያሳያል ። በተጨማሪም በሀገሪቱ ያለው ጠቅላላ የመንገድ ርዝመት በፌዴራል፣ በክልል፣ በከተሞች እና በወረዳዎች የተሰሩ ክረምት ከበጋ የሚያስኬዱ መንገዶችን ጨምሮ አምና ከነበረበት 171,176 ኪሜ አሁን ላይ 180, 232 ሺ ኪ.ሜ መድረሱ ተገልጿል፡፡ ከዚህ ውስጥ 30,824 ኪ.ሜ የፌደራል፣ 36,395 ኪ.ሜ የክልል፣ 44,717 ኪ.ሜ የከተማ እንዲሁም 68,297 ኪ.ሜ የወረዳ መንገድ እንደሆነ ከቀረበው ሰነድ መገንዘብ ተችሏል። ይህን ተከትሎም በ1000 ስኩዌር ኪ.ሜ ውስጥ ያለው የመንገድ ርዝመት 157 ኪ.ሜ የደረሰ ሲሆን ክረምት ከበጋ የሚያገለግል መንገድ ላይ ለመድረስ ዜጎች በአማካይ እንዲጓዙ የሚጠበቀው ርቀት 4.3 ኪ.ሜ መድረሱ ተገልጿል። ከዚህም ባለፈ መንግሥት በክልሎች መካከል ፍትሃዊ የመንገድ ስርጭት እንዲኖር ትኩረት በመስጠት በተከታታይ ፍትሃዊነትን እንደ አንድ ዋና መመዘኛ ወስዶ እየሰራ እንደሆነም ተነስቷል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በመድረኩ ማጠቃለያ ባስተላለፉት መልዕክት ለቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል። ሚኒስትሯ ባሰትላለፉት መልዕክትም “መንገድ መገንባት ሀገር መገንባት ነው” በሚል መርህ ለዘርፉ ስኬት በመደመር መርህ በመቀናጀት፣ በመተባበርና በመናበብ በትኩረት መስራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸው በዘርረፉ ይስተዋሉ የነበሩ የአሰራር፣ የአደረጃጀትና የህግ ማዕቀፍ ችግሮችን ለመፍታት በርካታ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡ የመንገድ ዘርፉ እስካሁን እራሱን ችሎ አዋጅ ያልነበረው መሆኑንና በአሁኑ ወቅት ዘርፉን የሚመጥን አዋጅ ተዘጋጅቶ በመጽደቅ ላይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ዘርፉ በከፍተኛ ዕድገት ውስጥ ያለ ዘርፍ በመሆኑ በመንግስትም ትልቅ ትኩረት የተሰጠበት ነው ብለዋል፡፡ በ2017 በጀት አመት በመንገድ ዘርፍ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች በመድረኩ ላይ እውቅና የተሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ተሞክሯቸው እየተቀመረ አንዱ ከሌላው የሚማማርበት ይሆናል ተብሏል፡፡ በዚህም መሰረት የሶማሌ ክልል አንደኛ ደረጃ አፈጻጸም፣ የሲዳማ ክልል ሁለተኛ ደረጃ አፈጻጸም እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና የአፋር ክልል ሦስተኛ ደረጃ አፈጻጸም በማስመዝገብ የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ሀገር አቀፍ የመንገድ ዘርፍ ጉባኤ ተጠናቀቀ ጅግጅጋ፣ ነሐሴ 21 ቀን 2017 ዓ/ም (ከመልሚ) ከነሐሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጅግጅጋ ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የየዎየው 2ኛው ሀገር አቀፍ የመንገድ ዘርፍ ጉባኤ ተጠናቀቀ ፡፡ በጉባኤው የተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ታለፊዎችና ተወካዮች እንዲሁም የፌዴራልና የክልል የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በጉባኤው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፌ መሐመድ መንገድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ለማስቀጠል ወሳኝ መሆኑነን ገልጸው መንገድ የኢኮኖሚ ትስስርን የሚፈጥር እና ልማት የሚያፋጥን ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም “የመንገድ መሰረተ ልማት በሀገሪቷ ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው የመሠረተ ልማት ዘርፎች ቀዳሚና የሌሎች ልማቶች የጀርባ አጥንት ነው” ብለዋል፡፡ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው መንገድ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ለማስቀጠል እና አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብን ለመገንባት አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልፀዋል። ባለፉት ዓመታት ለከተሞች በተሰጠው ትኩረት የከተማ መንገድ ለመኪኖች ብቻ ሳይሆን ለእግረኛ፣ ለብስክሊተኛና ለአካል ጉዳተኛ ዜጎጎቻቸን ያማከለና ሰው ተኮር እንዲሆን መደረጉ በመንገድ መሰረተ ልማት አዲስ ገጽታ ያጎናጸፈ መሆኑን ጠቁመው ከዚህ አኳያ የኮሪደር ልማቶች እየተጫዉቱ ያለው ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተለይ የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሞች ተቀርፀው ተግባራዊ በመደረጋቸው ውጤቶች መመዝገባቸውን እና የሀገራችን የመንገድ አውታር በከፍተኛ መጠን ያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም በ10 ዓመቱ እቅድ እንደተመላከተው እንቅስቃሴን እና ተደራሽነትን ሚዛኑን በጠበቀ መልኩ ማስኬድን ዓላማ አድርጎ በመስራት ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ በመድረኩ የ2017 በጀት ዓመት የፌደራል መንገድ ዕቅድ አፈጻጸም እና ሌሎች የውይይት መነሻ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል ከ101 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የ1,048 ኪ.ሜ የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ፣ የነባር መንገዶች ማጠናከር፣ ደረጃ ማሻሻል እና የከባድ ጥገና እንዲሁም የ10,926 ኪ.ሜ ወቅታዊ እና መደበኛ ጥገና ማካሄድ መቻሉ ተገልጿል፡፡ የጀት ዓመቱ የፊዚካል እቅድ አፈጻጸምም 81 በመቶ ማሳካት መቻሉን የቀረበው የዘርፋ ሪፓርት ያሳያል ። በተጨማሪም በሀገሪቱ ያለው ጠቅላላ የመንገድ ርዝመት በፌደራል፣ በክልል፣ በከተሞች እና በወረዳዎች የተሰሩ ክረምት ከበጋ የሚያስኬዱ መንገዶችን ጨምሮ አምና ከነበረበት 171,176 ኪሜ አሁን ላይ 180, 232 ሺ ኪ.ሜ መድረሱ ተገልጿል፡፡ ከዚህ ውስጥ 30,824 ኪ.ሜ የፌደራል፣ 36,395 ኪ.ሜ የክልል፣ 44,717 ኪ.ሜ የከተማ እንዲሁም 68,297 ኪ.ሜ የወረዳ መንገድ እንደሆነ ከቀረበው ሰነድ መገንዘብ ተችሏል። ይህን ተከትሎም በ1000 ስኩዌር ኪ.ሜ ውስጥ ያለው የመንገድ ርዝመት 157 ኪ.ሜ የደረሰ ሲሆን ክረምት ከበጋ የሚያገለግል መንገድ ላይ ለመድረስ ዜጎች በአማካይ እንዲጓዙ የሚጠበቀው ርቀት 4.3 ኪ.ሜ መድረሱ ተገልጿል። ከዚህም ባለፈ መንግሥት በክልሎች መካከል ፍትሃዊ የመንገድ ስርጭት እንዲኖር ትኩረት በመስጠት በተከታታይ ፍትሃዊነትን እንደ አንድ ዋና መመዘኛ ወስዶ እየተሰራ እንደሆነም ተነስቷል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ሳኒ በመድረኩ ማጠቃለያ ባስተላለፉት መልዕክት ለቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል። ሚኒስትሯ ባሰትላለፉት መልዕክትም “መንገድ መገንባት ሀገር መገንባት ነው” በሚል መርህ ለዘርፉ ስኬት በመደመር መርህ በመቀናጀት፣ በመተባበርና በመናበብ በትኩረት መስራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸው በዘርረፉ ይስተዋሉ የነበሩ የአሰራር፣ የአደረጃጀትና የህግ ማዕቀፈ ችግሮችን ለመፍታት በርካታ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡ የመንገድ ዘርፉ እስካሁን እራሱን ችሎ አዋጅ ያልነበረ መሆኑንና በአሁኑ ወቅት ዘርፉን የሚመጥን አዋጅ ተዘጋጅቶ በመጽደቅ ላይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ዘርፉ በከፍተኛ ዕድገት ውስጥ ያለ ዘርፍ በመሆኑ በመንግስትም ትልቅ ትኩረት የተሰጠበት ነው ብለዋል፡፡ በ2017 በጀት አመት በመንገድ ዘርፍ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች በመድረኩ ላይ እውቅና የተሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ተሞክሯቸው እየተቀመረ አንዱ ከሌላው የሚማማርበት ይሆናል ተብሏል፡፡ በዚህም መሰረት የሶማሌ ክልል አንደኛ ደረጃ አፈጻጸም፣ የሲዳማ ክልል ሁለተኛ ደረጃ አፈጻጸም እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና የአፋር ክልል ሦስተኛ ደረጃ አፈጻጸም በማስመዝገብ የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት ሽዕማት ተበርክቶላቸዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ሀገር አቀፍ የመንገድ ዘርፍ ጉባኤ በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው ጅግጅጋ፣ ነሐሴ 19፣ 2017 ዓ.ም (ኢመአ): ሀገር አቀፍ የመንገድ ዘርፍ ጉባኤ " በጋራ ፣ ኢትዮጵያን እንገንባ" በሚል መሪ ቃል በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በጉባኤው የተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዘርፉ ቋሚ ኮሚቴና የክልል የዘርፉ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ የትምጌታ አሥራት ፣ ጉባኤው ለሃገራችን አይተኬ ሚና ባለው በመንገድ ልማት ላይ የሚካሄድ በመሆኑ ለሀገራችን ትልቅ ፋይዳ ያለው ጉባኤ እንደሆነ ገልጸዋል። አያይዘውም የሀገራችን የመንገድ ሽፋን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደመጣና በአሁኑ ወቅትም የሀገራችን የመንገድ ሽፋን ከ180ሺህ በላይ መድረሱ ገልጸዋል። ሀገራችን የምትከተለው የኢኮኖሚ ፓሊሲ ብዝሓ የኢኮኖሚ ዘርፍ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው ፣ በሕዝብ ቁጥርም ሆነ በቆዳ ስፋት ትልቅ ለሆነች ኢትዮጵያ ይህ በቂ እንዳልሆነና የመንገድ ተደራሽነት ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በቁርጠኝነት መሥራትን የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል። "መንገድ ስንገባ እየገነባን ያለነው ሀገር ነው" ያሉት አቶ የትምጌታ፣ በሂደቱ የሰው ሀይል ልማት በተለይም የአመራር እና ፈጻሚ አቅም ዘርፉ በሚፈልገው ደረጃ በቀጣይነት መገንባት ትኩረት የሚሰጠው እንደሆነ ገልጸዋል። አክለውም በፕሮጀክቶች ትግበራ ወቅት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ለመፍታት የሕዝብ፣ የባለድርሻ አካላት እና የመንግስት ቅንጅት እጅግ ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል። ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ ተገልጿል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads