en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 342 subscribers, ranking 1 756 in the Transport category and 2 537 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 342 subscribers.

According to the latest data from 17 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 95 over the last 30 days and by 18 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 41.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 485 views. Within the first day, a publication typically gains 2 032 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 16.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 342
Subscribers
+1824 hours
+417 days
+9530 days
Posts Archive
የቱሉቦሎ-ኬላ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) 80 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ቱሉቦሎ-ኬላ ዲዛይን እና ግንባታ የመንገድ ፕሮጀክት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል፡፡ አሁን ላይ 46.2 በመቶ የውሃ ማፋሰሻ ፣ 96.4 በመቶ የአፈር ሙሌት እና ቆረጣ ፣ 76.5 ኪሎ ሜትር ሰብ ቤዝ ፣ 71.3 ኪሎ ሜትር ቤዝ ኮርስ ፣ 95.7 በመቶ የስትራክቸር ፣ 71.3 ኪሎ ሜትር አስፋልት ንጣፍ ስራዎችን በማከናወን አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም 92.54 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ የመንገዱን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ ኮርፖሬሽን የተባለ የስራ ተቋራጭ ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥሩን ስራውን ደግሞ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች ኃ.የተ.የግ. ኩባንያ በማከናወን ላይ ነው:: የመንገድ ፕሮጀክቱ ትከሻን ሳይጨምር በወረዳ የእግረኛ እና አካፋይ መንገድን አካቶ 20 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው:: ለመንገዱ ግንባታ የሚውለውን 1,317,686,548 (አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ አስራ ሰባት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሰማንያ ስድስት ሺህ አምስት መቶ አርባ ስምንት ብር) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው:: መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ-ቡታጅራ -ሆሳና እና ከአዲስ አበባ - ወልቂጤ - ጅማ መስመር ያሉትን ዋና መንገዶች ያገናኛል፡፡ በተጨማሪም የአካባቢው ህብረተሰብ ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆን በማድረግ በስፋት የሚመረቱ ጤፍ እና የመሳሰሉ የሰብል ምርቶችን እንዲሁም የእንሰት ውጤቶችን ወደ መሃል ከተማ ለማጓጓዝ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው የጎላ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

Specific Procurement Notice Invitation for Initial Selection Works (Design and Build)

የዲንኬ-ሣውላ-ሽፍቴ እና ቱርጋ-ያላ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ቀሪ ሥራዎች በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ የካቲት 07፣ 2016 (ኢ መ አ) ፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጋሞ እና ጎፋ ዞኖችን የሚያስተሳስረው የዲንኬ-ሣውላ-ሽፍቴ እና ቱርጋ-ያላ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ቀሪ ሥራዎች በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ 85 ነጥብ 68 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው፡፡ የመንገድ ግንባታው ከአፈጻጸም ውስንነቶች ጋር በተያያዘ ችግር የቀድሞው የኮንትራት ዉል እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወሳል፡፡ አሁን ላይ የፕሮጀክቱን ቀሪ ሥራዎች በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ለማጠናቀቅ ግንባታው በዓለም አቀፉ ቻይና ውይ የሥራ ተቋራጭ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚውለው 3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በአፍሪካ ልማት ባንክ ይሸፈናል፡፡ በእስከ አሁኑ የግንባታ ሥራ፤ የመንገድ ጠረጋ፣ ጊዜያዊ የመንገድ ጥገና እንዲሁም የ 34 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተሠርቷል፡፡ በተጨማሪም የ12 ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ ድልድዮች ግንባታ ሥራ በፕሮጀክቱ ተካትቷል፡፡ ከዚህ ቀደም በኅብረተሰቡ በተደጋጋሚ ሲነሱ የነበሩ የዲዛይን ይሻሻልን ጥያቄ መሠረት ከቱርጋ እስከ ያላ ያለው የ 9 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ተለዋጭ መንገድ በፕሮጀክቱ እንዲካተት ተደርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ እንደመሆኑ መንገዱን ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ በኩል ግንባር ቀደም ሚና ይጫወታል፡፡ የኹለቱን የጋሞ እና ጎፍ ወንድማማች ሕዝቦች ይበልጥ በማቀራረብ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን በእጅጉ ያሳልጣል፡፡ የማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መሰል ተቋማት ተደራሽነት በማስፋት የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት ኑሮ ያቀላል፡፡ ፕሮጀክቱ በታለመለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የየአካባቢው ነዋሪ እና በየመዋቅሩ የሚገኙ የመስተዳድር አካላት በመንገድ ወሰን ውስጥ የሚገኙ ንብረቶችን በወቅቱ በማንሳት አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርጉ ኢ መ አ ይጠይቃል፡፡ የዚህ ፕሮጀክት አካል የኾነው የሶዶ-ዲንኬ ክፍል-1 አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በቅርቡ ይጠናቀቃል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የደብረብርሃን - አንኮበር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናቀቁ አዲስ አበባ, የካቲት 4፣ 2016 (ኢመአ) ፡- የደብረብርሃን - አንኮበር 42 ኪሎሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ዋና ዋና ሥራዎች የተጠናቀቁ ሲኾን፣ ቀሪ ውስን ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው፡፡ አሁን ላይ ከግንባታው አጠቃላይ ሥራ 98 በመቶው ተጠናቋል። ከግንባታ ሥራዎች መካከል የ39 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ፣ ሰብቤዝ ፣ የመንገድ ዳር የአደጋ መከላከያ አጥር እንዲሁም የትራፊክ ጠቋሚ ምልክቶች የማቅለም ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ ሀገር በቀሉ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘ ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱን ለማካሄድ የተመደበው 1,623,194,217.85(አንድ ቢልዮን ስድስት መቶ ሃያ ሶስት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አራት) ብር በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው ይህ መንገድ በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ ላለፉት በርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ነው፡፡ ሆኖም ግን ከአገልግሎት ብዛት አኳያ መጎዳቱ ፤ የቦታው አስቸጋሪ ተፈጥሮአዊ አቀማመጥ በጠጠር ደረጃ ለነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት አመቺ አለመሆኑ እንዲሁም ያለው በርካታ ሀገራዊ እና ማኅበራዊ ጠቀሜታ ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ ከዚሁ የደብረብርሃን-አንኮበር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተጨማሪ የአንኮበር-ዱለቻ እና የዱለቻ-አዋሽ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ሶስት ፕሮጀክቶች ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቁ ከዚህ ቀደም ወደ አፋር ለመሄድ ይወስድ የነበረውን ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ ለማስቀረት እንደ አማራጭ ሆነው ያገለግላሉ፡፡ የአንኮበር ከተማ የተለያዩ ታሪካዊ ቅርሶችን በውስጡ የያዘው የአጼ ምኒሊክ ቤተመንግስት መገኛ በመሆኑ ፣ መንገዱን ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ በኩል ግንባር-ቀደም ሚና ይጫወታል፡፡ በተጨማሪም ምቹ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር በማስቻል የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በእጅጉ የሚያቃልል ከመሆኑም ባሻገር ምርት በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲደርስ በማስቻል የአርሶ-አደሩን ተጠቃሚነት ይጨምራል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

"በኢትዮጵያ አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት የሰራተኛው ሚና" በሚል ርዕስ ውይይት ተካሄደ። አዲስ አበባ ፣ ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) "በኢትዮጵያ አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት የሰራተኛው ሚና" በሚል ርዕስ ሰራተኞች እና የስራ ኃላፊዎች የተሳተፉበት ውይይት ተካሄደ። በውይይቱም ስልጡን ሲቪል ሰርቪስ መገንባት በሚኖረው ሚና ዙሪያ እና ሀብትን በመፍጠር ጉዞና ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ የውይይት ሰነድ ቀርቧል፡፡ በገለፃውም ኢትዮጵያ ያሏትን ያልተነኩ የተፈጥሮ ሀብቶች በአግባቡ ለመጠቀም የመንገድ ዘርፍ ወሳኝ ሚና እንዳለው ተመልክቷል፡፡ በዚህም ረገድ እንደተቋም የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመፍታት የላቀ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ነፃ፣ገለልተኛ እና አካታች የሆነ ሲቪል ሰርቫንትን ለመፍጠር የሚያስችል የአሰራር ስርዓትን መዘርጋት እንዳለበት ተገልጿል፡፡ በቀጣይም ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በጋራ በመወያየትና በመመካከር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚገባው ተገልጿል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የባሕር ዳር አባይ ወንዝ ድልድይ መዳረሻ መንገድ ፕሮጀክት አስፓልት ንጣፍ ስራ ተጀመረ አዲስ አበባ ፣ ጥር 25 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) በባሕር ዳር ከተማ ውስጥ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው ግዙፉ የአባይ ወንዝ ድልድይ መዳረሻ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አስፓልት ንጣፍ ስራ ተጀመረ፡፡ ከሄኒ ጋርደን አደባባይ እስከ ዘንዘልማ መገንጠያ ድረስ የሚዘልቀው 4.7 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የባሕር ዳር አባይ ወንዝ ድልድይ መዳረሻ መንገድ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም የመፋሰሻ ቱቦ ዋና ዋና ስራዎች በአብዛኛው ተጠናቀዋል፡፡ በተጨማሪም የሰብቤዝ ንጣፍ ፣ የቤስ ኮርስ ንጣፍ ፣ የቤዛዊት መንገድ መሿለኪያ እና መወጣጫዎች ሙሌት እንዲሁም የከርብስቶን ስራዎች በሰፊው ሲከናወን ቆይቶ ወደ አስፓልት ንጣፍ ስራ ተሸጋግሯል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ያለበት የአፈፃፀም ደረጃ 38.2% ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የአስፋልት እና የትራፊክ ምልክቶች ተከላ ፤ የቀለም ቅብ ስራዎች ፤ የመንገድ ላይ መብራቶች ተከላ እንዲሁም የእግረኛ መንገድ ንጣፍ በስፋት ለመጀመር ከፍተኛ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን የተመደበውን 825,659,857 ብር ሙሉ ለሙሉ የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። መንገዱ የእግረኛ እና አካፋይን ጨምሮ መደበኛ ቦታዎች ላይ 51 ሜትር እንዲሁም የህዝብ ማጓጓዣ ማቆሚያ ቦታዎች ላይ 59 ሜትር ስፋት አለው፡፡ ከዚህም ባሻገር በአንድ ጊዜ በግራ እና በቀኝ 6 መኪናዎችን ማስተናገድ እንዲችል ተደርጎ በመገንባት ላይ የሚገኝ ሲሆን ፤ የመኪና ማቆሚያ ቦታንም ጭምር አካቶ በባህር ዳር ከተማ ፍኖተ ካርታ መሰረት የሚገነባ ሰፊ የመንገድ ፕሮጀክት ነው፡፡ ግንባታው ሃፍኮን ኮንስትራክሽን እና ክሮስ ላንድ ኮንስትራክሽን በተባሉ ሀገር በቀል የስራ ተቋራጮች በጥምረት በመካሄድ ላይ ነው፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ቦቴክ ቦስፈረስ የተባለ የውጭ ሀገር አማካሪ ድርጅት ከሀገር በቀሉ ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ስራዎች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ንዑስ አማካሪ መሃንዲስ ጋር በጋራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ መንገዱ የኢትዮ ሱዳን ዋና መስመር የሆነው የአዲስ አበባ - ባህርዳር - ጎንደር-መተማ መንገድ አንዱ ክፍል ነው፡፡ ግንባታው ተጠናቆ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ሲሆን ፤ በአገልግሎት ብዛት የተጎዳውን ነባር የባህር ዳር አባይ ወንዝ ድልድይ የትራፊክ ጫና ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ያስተነፍሳል ተብሎ እንደሚታመን በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የፕሮጀክቱ አስተዳዳሪ ኢንጅነር አዲስሕይወት ታደሰ ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የሥልጣኔ በር

የአሳይታ- አፋምቦ-ጅቡቲ ድንበር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ ወደ ጅቡቲ ለመጓዝ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኘው የጋላፊ መስመር በተጨማሪ ለወደፊቱ ሌላ አማራጭ ሆኖ የሚያገለግለው የአሳይታ-አፋምቦ-ጅቡቲ ድንበር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡ የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ስራዎች ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን፣ የትራፊክ ምልክቶች ተከላ ፤ የቀልም ቅብ ስራዎች እና ሌሎች ጥቃቅን ስራዎች ተገባደዋል፡፡ የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን የተመደበው 1,600,901,379 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ አንድ ሺህ ሶስት መቶ ሰባ ዘጠኝ ብር) ሙሉ ለሙሉ የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገዱ ርዝማኔ 50.34 ኪሎ ሜትር ሲሆን ፣ የጎን ስፋቱ ትከሻን ጨምሮ በገጠራማ ሥፍራዎች 10 ሜትር ፣ በወረዳ ከተሞች 19 ሜትር እና በዞን 21.5 ሜትር ስፋት አለዉ። ፕሮጀክቱ የሶስት ድልድዮች ግንባታንም ባካተተ መልኩ ነው ሲካሄድ የቆየው፡፡ ግንባታውን ሲያካሂድ የቆየው ሀገር በቀሉ የስራ ተቋራጭ አሰር ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ይዲዲያ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንትስ ሲያከናውን ቆይቷል። በአካባቢው ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረ በመሆኑ ህብረተሰቡ በትራንስፖርት እጦት ምክንያት በእግር እና በግመል ከመጓዝ ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበረውም። መንገዱ በዋናነት ኢትዮጵያን በአሳይታ በኩል ከጅቡቲ ጋር በቅርበት ያስተሳስራል። የሀገራችንን የገቢ እና ወጪ ንግድ በማቀላጠፍ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አሳይታ ከተማን ከአፋምቦ ወረዳ ብሎም በርካታ ቀበሌዎችን በማገናኘት የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን ይበልጥ ያጠናክራል። ይህ አካባቢ የአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ የሚገኝበት በመሆኑ በርካታ ምርቶች የሚመረትበት መስመር ነው። ከእነዚህ ምርቶች መካከል ከፍተኛ የጨው ምርት፣ ጥጥ፣ ቴምር፣ ሰሊጥ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ ብርቱካን፣ ሃባብ እና በርካታ ፍራፍሬዎች ይጠቀሳሉ። የመንገዱ መገንባት እነዚህን ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ብሎም ወደ ጀቡቲ ለማድረስ ይበልጥ ያግዛል። ከዚህም ባሻገር በመስመሩ የትምህርት ፣ ጤና እና መሰል ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግልጋሎቶችን በአፋጣኝ አንዲስፋፉ ያደርጋል። በተጨማሪም ይህ መስመር አሁን ላይ ያለውን ሚሌ - ዲቼ ኦቶ-ጋላፊ-ጅቡቲ ወደብ ያለውን መንገድ በ 30 ኪሎ ሜትር ያሳጥረዋል። ወደፊት በአካባቢው ሊመረቱ የሚችሉ የፋብሪካ ውጤቶችን (ስኳር ፣ የስንዴ ዱቄት) ወደ ውጪ ገበያ ለማቅረብ ፋይዳው የጎላ ነዉ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጎሬ-ማሻ-ቴፒ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ ጥር 15 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልልን ከኦሮሚያና ጋምቤላ ክልሎች ጋር በአቋራጭ የሚያገናኘው የጎሬ - ማሻ - ቴፒ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ የመንገዱ ግንባታ ሲጠናቀቅ ኦሮሚያን እና ጋምቤላን በኢሉ አባቦር በኩል እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን በሸካ ዞን በኩል በቅርበት ያስተሳስራል፡፡ አሁናዊ የግንባታው አፈጻጸም 44 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ ይህ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ 631 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘዉ ጎሬ ከተማ መነሻዉን በማድረግ ቴፒ ከተማ ላይ ያበቃል፡፡ ፕሮጀክቱ የሚካሄድበት አካባቢ ከፍተኛ እና የተራዘመ ዝናብ የሚዘንብበት በመሆኑ የግንባታ ሂደቱ በታሰበለት ፍጥነት እንዳይሄድ አድርጎት ቆይቷል፡፡ በተጨማሪም የወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ፣ የዋጋ ንረትና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግሮች በግንባታ ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን አሳድረዋል፡፡ ሆኖም ግን አሁን ላይ በአካባቢው የሚስተዋለው የዝናብ ሁኔታ በመቀነሱ እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሚዛን እና አካባቢው ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እና በኢመአ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ በመሆኑ ችግሮቹ ከሞላ ጎደል ተቀርፈዉ አሁን ላይ አፈፃፀሙ እየተፋጠነ ይገኛል፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 7 ሜትር ፤ በከተማ 14 ሜትር ፤ በወረዳ 19 ሜትር እና በዞን 21 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ ነዉ እየተገነባ የሚገኘዉ፡፡ የአካባቢውን የአየር ፀባይ መነሻ በማድረግ የመንገዱ ትክሻ ክፍል በከፍተኛ ጥራት በአስፋልት ደረጃ የሚሰራ እና የአስፋልት አይነቱም (super paved) መሆኑ ይህን ፕሮጀክት ከሌሎች ፕሮጀክቶች ለየት ያደርገዋል፡፡ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሃዩንዳይ ዴቭሎፕመንት ካምፓኒ ሲሆን ፣ ሱሶንግ ኢንጅነሪንግ ፤ ኮርያ ኮንሰልታንትስ ኢንተርናሽናል ፤ ዳሳን ኮንሰልታንተስ በንዑስ አማካሪነት ከኔት ኮንሰልቲንግ ጋር በጣምራ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ ፡፡ 141 ኪሎ ሜትር ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን ይህ ፕሮጀክት ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው የገንዘብ መጠን 4,468,211,740.75 (አራት ቢሊዮን አራት መቶ ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ሁለት መቶ አስራ አንድ ሺህ ሰባት መቶ አርባ ብር ከሰባ አምስት ሳንቲም) ሲሆን ፤ የሚሸፈነውም ከኮሪያ ኤግዚም ባንክ በተገኘ ብድር ነው ፡፡ ነባሩ የጎሬ-ማሻ-ቴፒ መንገድ በጠጠር ደረጃ የነበረና እጅግ የተጎዳ በመሆኑ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ አልነበረም፡፡ በዚህም ምክንያት ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት ፤ አሽከርካሪዎችን ደግሞ ለአላስፈላጊ የጊዜ ብክነትና ወጪ ሲዳርግ የቆየ ሲሆን ፣ ካለው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። መንገዱ ስድስት ወረዳዎች እና ከ15 በላይ ቀበሌዎችን በቅርበት ያስተሳስራል፡፡ ከእነዚህም ዉስጥ (አሊ ፣ ዲዱ ፣ ማሻ ፣ አንደራቻ ፣ የኪ እና ጎደሬ) የሚባሉ የወረዳ ከተሞች ተጠቃሾች ናቸዉ፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳዉ የጎላ ነዉ፡፡ አካባቢው እንደ ቡና ፣ ማር ፣ የሻይ ቅጠልና የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች እንዲሁም ፍራፍሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ የሚመረትበት በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ከፍተኛ የሆነ የገበያ ትስስር እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

መልካም በዓል!

የፌዴራልና ክልል መንገድ ኤጄንሲዎች የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የልምድ ልውውጥ ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ጥር 8 ቀን 2016 ዓም (ኢመአ)፡ በመንገድ ፈንድ በጀት የሚመደብላቸው 71 የፌዴራልና የክልል እንዲሁም የከተማ መስተዳድሮች መንገድ ኤጀንሲዎች የ2016 በጀት ዓመት ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማና የልምድ ልውውጥ ተካዷል፡፡ በመድረኩ ከክልሎች እና ከከተማ መስተዳደሮች የተውጣጡ የመንገድ ኤጀንሲዎች የስድስት ወራት መደበኛና ወቅታዊ የመንገድ ጥገና አፈፃፀማቸውን ያቀረቡ ሲሆን ፣ በዕቅድ ትግበራው ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስመልክቶም የጋራ ምክክር ተደርጓል። የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በሀገሪቱ የተከሰቱ የፀጥታና አለመረጋጋት ችግሮች ፣ የበጀት እና የግብአት እንዲሁም የማሽነሪ መለዋወጫ እጥረቶች በመንገድ ጥገና ስራዎች ላይ ተፅዕኖ ስለመፍጠራቸው ገልጸዋል፡፡ በተያያዘም በተገቢው መልኩ ጥገናዎችን ለማከናወን የበጀት ፍላጎትና አቅርቦት አለመመጣጠን በእቅዳቸው ልክ ስራዎችን እንዳያከናወኑ ስለማድረጉ የመንገድ ኤጀንሲዎች የስራ ኃላፊዎች ተናግረዋል። ይህንን አስመልክቶ የበጀት እጥረትን ለመፍታት ፣ የመንገድ ፈንድ ገቢን ለማሳደግ እና በቀጣይ የመንገዶች ጥገና ሽፋንን ለመጨመር የሚያስችል ስትራቴጂክ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ስለመሆኑ ተገልጿል። ከዚህም ባሻገር በመንገድ ኤጀንሲዎቹ የተነሱ ችግሮችን ለመፍታትና ደረጃ በደረጃ መፍትሄ ለማምጣት በጋራ መስራት እንደሚገባ የስራ መመሪያ ተሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ባለፉት ስድስት ወራት ከመንገድ ፈንድ (5.26) አምስት ነጥብ ሁለት ስድስት ቢሊዮን ብር ገቢ በማሰባሰብ ለፌዴራል፣ ለክልል፣ እና ለከተማ አስተዳደር የመንገድ ኤጄንሲዎች በመመደብ በጀቱ ለታለመለት ዓላማ መዋሉን ለማረጋገጥ በቴክኒክና ፋይናንሺያል ኦዲት ሥራዎችን ማከናወኑ ተገልጿል፡፡ ይህ ገቢ በነዳጅ ላይ ከተጣለ ታሪፍ ፤ በቅባት እና ዘይት ሽያጭ ከተጣለ ታሪፍ እና በክብደት ላይ ከተመሰረተ አመታዊ የተሸከርካሪ ፍቃድ የተገኘ ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et

የፊቅ-ሐመሮ-ኢሚ-ባሌ ምዕራፍ አንድ አስፋልት መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ ጥር 02 ፣ 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) :- የሶማሌ እና የኦሮሚያ ክልሎችን የሚያቆራኘው የፊቅ-ሐመሮ-ኢሚ-ባሌ ምዕራፍ አንድ (ከኪ.ሜ 00 እስከ ኪ.ሜ 81) አስፋልት መንገድ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 81 ኪሎሜትር የሸፈነ ሲኾን፥ ግንባታው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ሀገር በቀሉ ማክሮ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ግንባታውን አከናውኖታል። ስታዲያ የምህንድስና ሥራዎች ድርጅት የፕሮጀክቱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ተሳትፏል። ለግንባታው የዋለው 849,049,098.31 (ስምንት መቶ አርባ ዘጠኝ ሚሊዮን አርባ ዘጠኝ ሺህ ብር) በፌደራሉ መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። በግንባታው ከአስፋልት ንጣፍ፣ የፉካ ና የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ሥራዎች በተጨማሪ የተለያዩ ድልድዮች ግንባታ ሥራ ተከናውኗል። የመንገዱ ነባር ገጽታ በገጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና በአገልግሎት ብዛት በእጅጉ የተጎዳ ነበር። አሁን ላይ የመንገድ ግንባታው መጠናቀቁ፣ የክልሉን የመንገድ መሠረተ ልማት ከማሳደጉም ባሻገር፣ የፊቅ እና ሐመሮ ወረዳዎች እንዲሁም የበርካታ ቀበሌ ነዋሪዎችን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ይበልጥ ያጠናክራል። ቀደም ሲል ከጅግጅጋ ኢሚ በጎዴ በኩል ይደረግ የነበረውን የ726 ኪ.ሜ የጉዞ ርቀት ወደ 418 ኪ.ሜ በማሳጠር፣ የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በእጅጉ ያቀላል። በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶችም የጎላ ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽዖ ያበረክታል። የዚሁ መንገድ ኮሪደር ትስስር አካል የሆኑት የባቢሌ-ፊቅ ሎት-2፣3 እና 4 እንዲሁም የፊቅ-ሐመሮ-ኢሚ-ባሌ ሎት-2 መንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቅቆ ቀደም ሲል ለትራፊክ ክፍት መደረጋቸው ይታወቃል። እንዲሁም የባቢሌ ፊቅ ሎት-1 በፍጻሜ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። መንገዶቹ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ኅብረተሰቡ እንዲሁም የየአካባቢው መስተዳድር አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ኢ መ አ ያሳስባል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et Facebook https://www.facebook.com/www.era.gov.et