en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 544 subscribers, ranking 1 741 in the Transport category and 2 495 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 544 subscribers.

According to the latest data from 05 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 289 over the last 30 days and by 6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 37.99%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.97% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 145 views. Within the first day, a publication typically gains 2 299 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 544
Subscribers
+624 hours
+737 days
+28930 days
Posts Archive
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የጎዴ - ቀላፎ ሎት 1 ፣ የጎዴ-ሐርጌሌ ሎት-1እና ሰገግ ገርቦ -ደነን ሎት 3 /ሎት ሶስት /የመንገዶች ግንባታ ስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ። በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ በተካሄደው የመንገዶቹ ግንባታ ጅማሮ መርሃ ግብር ላይ የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ፣የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ፣የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ፣ የብልጽግና ፖርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ብናልፍ አንዱ አለም የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ ጨምሮ የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። በድምሩ 277.6 ኪ. ሜ እርዝማኔ ያላቸው እነዚህ ሶስት የመንገድ ፕሮጀክቶችን በአስፋልት ደረጃ መገንባት ከሀገርም አልፎ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ቀጠናዊ የንግድ እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከማሳደግ አንጻር ፋዳቸው የጎላ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ተናግረዋል። በተለይም የሀገራችን ከፍተኛ ወጪ ገቢ ንግድ የሚስተናገድበት ጅቡቲ ወደብ ሆነ በኮሪደሩ ላይ ይፈጠር የነበረውን የትራፊክ ጫና ከመቀነስ አኳያ ፕሮጀክቶቹ ሁነኛ አማራጭ ይሆናሉም ብለዋል ። የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ለአመታት የዘለቀውን የክልሉን የመሰረተ ልማት ጥያቄ ለመመለስ መንግስ እየሰራ ያለውን ስራ የሚደነቅ ነው ብለዋል። ፕሮጀክቶቹ ከክልሉም አልፍ የሃገሪቱን የወጪ ገቢ ንግድን በማቀላጠፍ የጎላ ሚና አላቸው ብለዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚደረግባቸው የጎዴ - ቀላፎ ፣ የጎዴ-ሐርጌሌ ሎት-1 እና የያአሌ-ደነን መንገዶች ግንባታ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እና የጥራት ደረጃ ለማጠናቀቅ ከመንገድ ወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ በመንገዶቹ ክልል ውስጥ ያሉ ንብረቶች በቶሎ ማንሳት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው። የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ትብብር እና ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። ፕሮጀክቶቹ ካላቸው ኢኮኖሚያዊ እና መህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር የመንገድ ግንባታ ስራውን የሚያከናውኑት የስራ ተቋራጭ ድርጅቶች እና ጥራቱን የሚቆጣጠሩት አማካሪ ድርጅቶች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበው። የባለስልጣኑ መ/ቤትም አስፈላጊውን ትብብር እና ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። በዛሬው እለት የመንገድ ግንባታ ስራቸው በይፋ የተጀመሩት የጎዴ - ቀላፎ ፣ የጎዴ-ሐርጌሌ ሎት-1 መንገዶች በጠጠር መንገድ ደረጃ ያሉ ሲሆን ሎላኛውና የመንገድ ግንባታ ስራው በዛሬው እለት የተጀመረው የያአሌ - ደነን መንገድ ከዚህ ቀደም ምንም አይንት የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረው አካባቢ ሲሆን በቀጣይ ሁሉም መንገዶች ደረጃቻቸውን ከፍ በማድረግ በአስፋልት የሚገነቡ ይሆናል። የጎዴ ቀላፎ መንገድ ፕሮጀክት 94.8 ኪ ሜ እርዝማኔ አለው ፡፡ መንገዱን ለመገንባት ጨረታውን በብር አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሚሊዮን ብር (1 ,530,000 ,000.00 ) አሸንፎ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው ቻይና ሬል ዌይ ስቨን ግሩፕ ነው። የምህንድስና እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ እስታድያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች ከጂ እና ዋይ አማካሪ ድርጅት ጋር በጋራ ያከናውኑታል ፡፡ የጎዴ - ሀርገሌ ሎት 1 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 100 ኪ .ሜ እርዝማኔ አለው ፡፡ ለአጠቃላይ ግንባታው መንግስት አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ዘጠና ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሀምሳ ዘጠኝ ሺ ሶስት መቶ ሰማኒያ ስድስት .ከሰባ አራት ሳንቲም 1,893,759,386.74 ወጪ መድቦለታል፡፡ መንገዱን ለመገንባት ጨረታውን አሸንፎ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የውል ስምምነት የተፈራረመው አገር በቀሉ የሥራ ተቋራጭ ፋል ጀነራል ኮንትራክተር ነው፡፡ መንገዱ በውል ስምምነት መሰረት አራት ዓመት የግንባታ ግዜ ተሰጥቶታል፡፡ ሶስተኛው መንገድ ዮአሌ-ደናን ሎት 3 ሲሆን የፊቅ ሰገግ ገርቦ ደነን ፕሮጀክት አካል ነው፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ 82.84 ኪሜ ርዝመት አለው ። መንገዱን በአስፋልት ደረጃ የሚገነባው የሥራ ተቋራጭ አገር በቀሉ ክሮስ ላንድ ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡ የኮንትራት ውሉ 1,119,417,453.44 አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን አራት መቶ አስራ ሰባት ሺ አራት መቶ ሀምሳ ሶስት ከ አርባ አራት ሳንቲም ብር ነው ፡፡ የመንገዱ ስራ በ3 ዓመት ከ6 ወር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል፡ ሳባ ኢንጂነሪንግ መንገዱን በማማከር እና በመቆጣጠር ተሳታፊ ይሆናል፡፡ የሶስቱ መንገድ ፕሮጀክቶች የጎን ስፋት በገጠራማው ክፍል 10 ሜትር ፣በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ 19 ሜትር እንዲሁም በዞን 21.5 ሜትር ነው ፡፡ መንገዶቹ ሲጠናቀቁ ሁለተናዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳዎችን የሚያጎናፅፉ ናቸው።

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የጊምባ-ተንታ-ተንታ-መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ። በተንታ ወረዳ በአጅባር ከተማ በተካሄደው የፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ብናልፍ አንዱአለም ፣የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራልና እና የክልል የስራ ሃላፊዎች ታድመዋል። መንግስት በመደበው ከ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የጊምባ -ተንታ-ተንታ መገንጠያ 80.2 ኪ. ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የህዝቡን የአመታት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ። ለረዥም ዓመታት የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ የዚህ አካባቢ ነዋሪ በከፍተኛ ሁኔታ ሲቸገር እንደቆየም ተናግረዋል። ይህ ታሪክ ሊሆን በመቃረቡ ለመላው ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁመልክታቸውንአስተላልፈዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አካባቢውን ፣ ከክልሉ፣ ክልሎችን ከሀገሪቱ የወጪ ገቢ ንግድ ጋር የሚያስተሳስሩ ሌሎች በርካታ ፕሮጀክቶችን ደረጃ በደረጃ እንዲተገበሩ መንግስት አቅጣጫ ማስቀመጡንም አብራርተዋል። ይህ ፕሮጀክትም ከተያዘለት ጊዜ በፊት እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የአመራር አካላት በብርታትና በጥንካሬ ከተቋራጮቹ ጋር በመሆን የሚያጋጥሙ የወሰን ማስከበር ችግሮችን ቀድመው እንዲፈቱም አሳስበዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው ፕሮጀክቱን በስኬት ለማጠናቀቅ ተገቢውን የድጋፍ፣ የክትትል እና የቁጥጥር ሥርዓትን እንደሚያደርግ ገልፀዋል። መላው የአካባቢው ነዋሪ ፣የሥራ ተቋራጩም ሆነ የአማካሪ ድርጅቱ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ሀላፊነት በብቃት እንዲወጡም አስገንዝበዋል ። እንዲሁም ግንባታውን የሚያከናውነው የስራ ተቋራጭ የድርጅቱ ተወካይ በገቡት የኮንትራት ውሉ መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን ገንብቶ ለማስረክብ ቃል ገብተዋል። አጠቃላይ ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ደቡብ ወሎ ዞን ውስጥ ይገኛል። የጊምባ-ተንታ-ተንታ መገንጠያ የመንገድ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ 568 ኪ. ሜትር ይርቃል። የፕሮጀክቱ ስም ፦ ጊምባ-ተንታ-ተንታ መገንጠያ ርዝመት ፦     80.2 ኪ. ሜትር          የሥራ ተቋራጭ፡-             ጂያንግዢ ዘ ሰከንድ ኮንስትራክሽን የቻይና ስራ ተቋራጭ ነው። የግንባታው አይነት ፡-        DBB አማካሪ ድርጅት፡-    ሲቪል ወርክስ ኢንጂነርስ፣የኮሪያ ካምፓኒ ዮሺን ኮርፖሬሽን እንዲሁም ጂ እና ዋይ በጋራ በመተባበር      የግንባታ ወጪ፡-         2,185,228,256.12    የግንባታው ወጪ ሽፋን፡-   የኢትዮጵያ መንግስት የግንባታው ደረጃ ፦    አስፋልት ኮንክሪት     ለግንባታው የተሰጠው ጊዜ፡- 3 ዓመት መንገዱ የሚያቋርጥባቸው           ወረዳዎች ፦ ለጋምቦ፣ተንታ፣ደላንታ በርካታ ቀበሌዎች                     በመንገድ ፕሮጀክቱ ውስጥ የሚካተቱ ስራዎች የአፈር ቆረጣና ሙሌት ሥራ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ሥራ የሁለት ድልድዮች ስራ ትንንሽና መካከለኛ የተፋሰስ ስራዎች የመንገድ ዳር ትራፊክ ምልክቶች ግንባታ ሥራ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ሥራዎች የመንገድ ፕሮጀክቱ መገንባት ሁለንተናዊ ፋይዳ በጠጠር ደረጃ የነበረው የመንገዱ ግንባታ ተገንብቶ በሚጠናቀቅበት ወቅት ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ  ህብረተሰቡ ተሸከርካራዎችን ተጠቅሞ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ከዚህ ቀደም ከደሴ ተነስቶ ተንታ ለመድረስ በመንገዱ መበላሸት ሳቢያ ይደርስ የነበረውን የዙሪያ ጥምጥም መንገድ በአንድ ሰዓት ተኩል ይቀንሰዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ መገንባት ግንባታው ከሚካሄድበት አስራ አምስት ኪ. ሜትር ወደ ጎን ተገንጥሎ መቅደላ የሚገኘውን የአጼ ቴዎድሮስ ታሪካዊ የጀግንነት ሰፍራ እንዲሁም ለትግል ሲጠቀሙበት የነበረውን ሴባስቴፖል መድፍ ለመጎብኘት ለቱሪስት ምቹ ሁኔታን ከመፍጠርም አልፎ የቱሪዝም ፍሰቱን በመጨመር የውጭ ምንዛሬን ከማምጣት አኳያ ሃገራዊ ፋይዳው የጎላ ነው። የአካባቢው ነዋሪዎች  የሰብል ምርቶችን እንደ ጤፍ፣ገብስ፣ባቄላ እንዲሁም የቁም እንስሳት ውጤቶች ትራንስፖርትን ተጠቅመው  ወደ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ነዋሪው  ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ በመስመሩ የሚገኙ ዞኖች ወረዳዎች እና ቀበሌዎች በአስፋልት መንገድ በቅርበት ያስተሳስራል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የሀይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታስራን ዛሬ በይፋ አስጀመሩ። በወረባቦ ወረዳ በቢስቲማ ከተማ ላይ በተካሄደው የፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ብናልፍ አንዱአለም ።፣የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራልና እና የክልል የስራ ሃላፊዎች ታድመዋል። መንግስት በመደበው ከ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የሀይቅ- ቢስቲማ -ጭፍራ 74.3 ኪ. ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የህዝቡን የአመታት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ። ለረዥም ዓመታት የመንገድ መሰረተ ልማት ባለመኖሩ የዚህ አካባቢ ነዋሪ በከፍተኛ ሁኔታ ሲቸገር እንደቆየም ተናግረዋል። ይህ ታሪክ ሊሆን በመቃረቡ ለመላው ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁመልክታቸውንአስተላልፈዋል። መንገድ መጀመር አንድ ትልቅ ምዕራፍ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተያዘለት ጊዜ በፊት እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የአመራር አካላት በብርታትና ጥንካሬ ከተቋራጮቹ ጋር በመሆን የሚያጋጥሙ የወሰን ማስከበር ችግሮችን ቀድመው እንዲፈቱም አሳስበዋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ፕሮጀክቱ የህዝቦችን ጥያቄ ምላሽ የሰጠና ሀገራዊና ክልላዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ የበኩላቸውን ድጋፋና ክትትል እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በበኩላቸው ተቋማቸው የሀይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ መንገድ ፕሮጀክትን በስኬት ለማጠናቀቅ ተገቢውን የድጋፍ፣ የክትትል እና የቁጥጥር ሥርዓትን እንደሚያደርግ ገልፀዋል። መላው የአካባቢው ነዋሪ ፣የሥራ ተቋራጩም ሆነ የአማካሪ ድርጅቱ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ሀላፊነት በብቃት እንዲወጡም አስገንዝበዋል ። ። የመንገድ ግንባታውን ፓወርኮን ኃላ.የተ. የግል ማህበር እና አሰር ኮንስትራክሽን ኃላ.የተ. የግል ማህበር በሽርክና በመሆን የሚገነቡት ነው። የሀይቅ- ቢስቲማ -ጭፍራ ጠጠር መንገድ ለረጅም ጊዜ በአገልግሎ ሳቢያ በከፍተኛ ሁኔታ የተበላሸ ሲሆን መንገዱን ለመገንባት የሚወጣው ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል። አሁናዊው የመንገዱ ሁኔታ ከ 6 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋት ያለውና ጠባብ ሲሆን በእስፋልት ደረጃ ሲገነባ በወረዳ 19 ሜትር ፣ በቀበሌ 15ሜትር እንዲሁም በገጠር 1ዐ ሜትር ስፋት ይኖረዋል፡፡ የመንገዱ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት ከዚህ በፊት ከደሴም ይሁን ከሀይቅ ወደ ጭፍራ ለመሄድ በወልድያ በኩል በሚሌ-ጭፍራ ይደረግ የነበረውን የዙሪያ ጥምጥም ጉዞ በማስቀረት በአቋራጭ በቀጥታ ከሀይቅ በቢትሰማ አድርጎ ጭፍራ ዘመናዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ስለሚያስችል የትራንስፖርት ጊዜን ከመቀነስ አኳያ ትልቅ ፋይዳ ያለው መንገድነው። እንዲሁም በመስመሩ የሚገኙትን ዞኖችና ወረዳዎች በቅርበት በማስተሳሰር ከዚህ ቀደም 74 ኪ.ሜትሩ ን በትራንስፖርት ለመጓዝ ይፈጅ የነበረውን አራት ሰዓት ከግማሽ በታች ያሳጥረዋል። ከዚህም ባለፈ የቁም እንስሳት ውጤቶች ፣ፍራፍሬና ሌሎችንም ምርቶችን ወደገብያ አውጥቶ በመሸጥ አምራቾችንና ሸማቾችን የጋራ ተጠቃሚ ያደርጋል። ፕሮጀክቱ የውል ስምምነት መሰረት በአራት አመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ።

በባህርዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራ እየተፋጠነ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱን የስራ እንቅስቃሴ እና የባህርዳር ጢስ እሳት የመንገድ ግንባታ ስራን በዛሬው እለት በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣በኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኘ እና የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በመስክ የስራ ቅኘት ተጎብኝቷል። አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ 380 ሜትር ርዝመት እና 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ድልድይ ነው። በጉብኝቱ ወቅት ፕሮጀክቱ ላይ በዋነኛነት የድልድይ ተሸካሚ ምሰሶዎችን (piers) ለአርማታ ሙሌት ስራ ማመቻቸት እንዲሁም የድጋፍ ግንቡን ከመሬት በታች የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች (Abutment piles) ቁፋሮ እና አርማታ ሙሌት ስራ ነው እየተከናወነ የሚገኘው፡፡ ለድልድዩ ከሚያስፈልጉት 4 ቋሚ የድልድይ ተሸካሚ ምሶሶውች የመሰረት ስራቸው ከነ ማቀፊያው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል:: በተጨማሪም የአንዱ ድልድይ ተሸካሚ ምሶሶ የኮንክሪት ሙሌት ስራ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ የቀሪዎቹ ሶስት ድልድይ ተሸካሚ ምሶሶ ሙሌት ስራም በመጪዎቹ ሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ከመሬት በታች የሚቀበሩት የክብ ቅርፅ ያላቸው የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች በዲዛይኑ መሰረት ከዝቅተኛው 14 ሜትር እስከ ከፍተኛው 23 ሜትር ድረስ ጥልቀት ያላቸው ሲሆኑ የአንዱ የቋሚ ተሸካሚ መሰረት የመሀል መለኪያ ስፋት በድልድዩ የድጋፍ ግንብ ጋር 1.5 ሜትር ሲሆን የመካከል ተሸካሚዎች ጋር ደግሞ 1.8 ሜትር ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራ ፕሮጀክት በእስካሁኑ አፈፃፀም በአጠቃላይ ድልድዩን ለመሸከም ከሚያስፈልጉ 88 የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች ውስጥ 54 የሚሆኑት የቁፋሮ እና የአርማታ ሙሌት ስራ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቁ የቀሪዎቹን የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶችም በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የድልድዩ ስራ አሁናዊ የግንባታ ስራዎች አራት ቋሚ ተሸካሚ ምሶሶዎች የኮንክሪት ሙሌት እና የብርት ማሰር ስራዎች ተከናውነዋል። የድልድዩን ዋና ዋና ስራዎችን በእቅዱ መሰረት ለማከናወን አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ በመፍጠን ላይ መሆኑ በስራ ሃላፊዎቹ ተገምግሟል። የስራ ሃላፊዎቹ በቀጣይ የሚጠበቁ ጉልህ ስራዎችን ኮንትራክተሩ በገባው ውል መሰረት በጥራት እንዲሰራም ቀጣይ የስራ አቅጣጫን ሰተዋል። ድልድዩ በግራና በቀኝ በአንድ ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን በተጨማሪም 5 ሜትር የእግረኛ መንገድ እንዲሁም የብስክሌት ተጠቃሚዎችን መስመር ባካተተ መልኩ ነው እየተገነባ የሚገኘው ፡፡ በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 1.4 ቢሊዮን ብር ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ የተባለው ተቋራጭ ነው። በባህር ዳር ከተማ ከሚገኘው ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እየተገነባ ያለው ይህ ዘመናዊ ድልድይ ተሰርቶ ሲጠናቀቅ ከሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ ጎን ለጎን ምቹ የሆነ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር በማድረግና መስመሩን ከአደጋ የፀዳ እንዲሆን ከማስቻሉ ባሻገር ከተማዋ ተጨማሪ ውበት እንድትላበስ ብሎም የሀገሪቱ ወጪና ገቢ ንግድ እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋዕፆ ያበረክታል፡፡ በተያያዘ ዜናም የስራ ሃላፊዎቹ በዛሬው የመስክ ጉዞቸው የባህርዳር ጢስ እሳት መንገድ ፕሮጀክትን ቃኝተዋል ። ፕሮጀክቱ ወደ ጢስ አባይ ፏፏቴ ቱሪስት መዳረሻ የሚወስድ ሲሆን 22.3 ኪሎሜትር እርዝመት ያለው ነው። የዚህ መንገድ መገንባት የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ጎብኚዎች ከዚህ ቀደም ይፈጠርባቸው የነበረውን እንግልት በማስቀረት ለአካባቢውም ሆነ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭን ይፈጥራል፡፡ የመስክ ቅኝቱ በዋነኝነት የፕሮጀክቶቹን አፈጻጸም ለመገምገምና እና በግንባታ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ከወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮችን እየቀረፉ የግንባታ ስራቸውን ማፋጠን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከሚመለከታቸው ጋር ለመምከር ነው።

የጊንጪ ሽኩቴ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የግንባታ እንቅስቃሴ በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ እና በኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም በተቋሙ የስራ ሃላፊዎች ዛሬ በመስክ የስራ ቅኘት ተጎብኝቷል። 59ኪ.ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን ይህንኑ ፕሮጀክት ነው ዛሬ የተቃኘው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ቀደም ብሎ በወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ሳቢያ በእቅዱ መሰረት ለመስራት ሲቸገር ቆይቶ በአሁኑ ወቀት ያሉት ዋና ዋና ችግሮች በመቀረፍቸው ፕሮጀክቱ በጥሩ ሁኔታ በመከናወን ላይ መሆኑ ተገምግሞል ። በዚህም በአሁኑ ወቅት የአስፖልት ማንጠፍ ስራ የተጀመረ ሲሆን በያዝነው አመት መጨረሻ ድረስም ዋና ዋና ስራዎች እንደሚጠናቀቁ ይጠበቃል። ይህ እንዲሆን አሁንም ከወሰን ማሰከበር ጋር ተያይዞ ያልተፈቱ ችግሮችን ለማቃለል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይበልጥ ተቀራርቦ እንዲሰራም የስራ ሃላፊዎቹ አሳስበዋል። የዛሬው የመስክ ቅኘት አላማም የፖሮጀክቱን ሂደት በአካል ከመመልከት ባለፈ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የበኩሉን ሚና ለማበርከት ያለመ ነው። የጊንጪ ሽኩቴ መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ነው ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው የተቋራጩ ባለቤት አቶ ገምሹ በየነ ያሉ ችግሮችን በጋራ በመፍታት ፕሮጀክቱን በጥራት አጠናቆ ለማስረከብ ይበልጥ እየሰራን ነው ብለዋል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለመስመሩ ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፍይዳዎችን የሚያጎናጽፍ ነው። በተያያዘ ዜናም የስራ ሃላፊዎቹ በዛሬው የመስክ ቅኝታቸው ከ1ነጥብ 26ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የሽኩቴ ጩሉጤን 63ነጥብ 2ኬሜ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን ቃኝተዋል። ከመልካ ምድራዊ አቀማመጥ ጋር ተያይዞ የአፈር መንሸራተትና ናዳ የሚስተዋልባቸውን ስፍራዎችን ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠትም ይበልጥ ይሰራል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎቹ ከወሰን ማስከበር እና ከግብአት አቅርቦት ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲፈቱ አቅጣጫንም አሰቀምጠዋል ። ለፕሮጀክቱ ተግዳሮት የሚሆኑ ችግሮችን በቀጣይ በጋራ በመፍታት ስራው እንዲፋጠን ይበልጥ የጎላ ሚና እንደሚያበረክቱም የስራ ሃላፊዎቹ አረጋግጠዋል። መንገዱ ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፍይዳ አኳያ ኮንትራክተሩም ሆነ አማካሪ ድርጅቱ በትኩረት እንዲሰሩም አስገንዝበዋል::

በመልካ ምድራዊ አቀማመጥና በክርምቱ ከባድ ዝናብ ምክንያት የትራንስፖርት ፍሰቱን አስተጓግሎ የነበረው የዲሪ-ማሻ መስመር ከጊምቦ እስከ ኪሎሜትር 62 የመንገድ ግንባታ ጥገና ተደርጎለት አገልግሎት መስጠት ጀመረ። ከሰላሳ አመት በፊት የተገነባው የዲሪ-ማሻ -ቴፒ የመንገድ ክፍል የሆነው ጊምቦ ኪ.ሜ 62 ከአገልግሎት ብዛት እና በተፈጥሮና ስው ሰራሽ ችግሮች በእጅጉ የተጎዳ ሲሆን በቅርቡ የትራንስፖርት ፍሰቱን እንዲሰተጓጎል ማድረጉ ይታወሳል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ መደበኛ አገልግሎት እንዲመለስ ባደረገው ጥገና ችግሩ ተፈቷል። በአሁኑ ወቅትም በስፍራው መደበኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ ተችሏል። ቀድም ብሎ መንገዱን ለመገባት ውል የገባው የስራ ተቋራጭ በአቅም ውስንንት እና በጥራት ማጓደል ምክንያት ኢመባ ውሉን በማቆረጥ አለማቀፍ ጨረታ እንዲወጣ አድርጓል በአሁኑ ወቅትም የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል። ሂደቱን አጠናቆ የመንገድ ፕሮጀክቱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ በመስጠት በዋነኝነት የቅርብ ዕሩቅ ሆነው የኖሩትን የደቡብ ፣ የኦሮሚያን እና የጋምቤላ ክልሎችን በቅርበት በማስተሳሰር ለሀገራችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ሚናው የጎላ ይሆናል።

የጎሃፅዮን-ደጀን መንገድ ከባድ ጥገና ሊካሄድለት ነው ። መልካ ምድራዊ አቀማመጡ እጅግ አስቸጋሪ በሆነው በዚሁ ስፍራ በመስክ የስራ ቅኝት ተጎብኝቷል። 40 ኪሎሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው የጎሃፅዮን-ደጀን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች አማካኝነት አደጋ እየደረሰበት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በተለይም ከመልካ ምድራዊ አቀማመጡ አስቸጋሪነት ጋር ተዳምሮ በክረምቱ ወራት በቦታው የጣለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ በመንገዱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ የመሬት መንሸራተት እና ናዳ ሊያስከትል ችሏል ፡፡ ከክብደት መጠን በላይ የሚጭኑ በርካታ ከባድ ተሽከርካሪዎችም ለመንገዱ መበላሸት አሉታዊ አስተዋጽኗቸው እየጎላ ነው። ይህን ተከትሎም መንገዱ ለተሽከርካሪ አስቸጋሪ እየሆነ በምጣቱ ፈጣን መፍትሄእንደሚያስፈልገው ታምኖበታል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የትራንስፖርት ፍሰቱ እንዳይስተጓጎል አስፈላጊውን ማሽነሪ በቦታው በማሰማራት ለመንገዱ አፋጣኝ የጥገና ስራ እያካሄደለት ነው፡፡ ሆኖም ግን በመንገዱ ላይ እያጋጠመ ያለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ እንዲኖረው ለማድረግ በፕሮጀክት ታቅፎ በከባድ ጥገና ደረጃ እንዲገነባ ተወስኗል፡፡ ከመንገዱ አጠቃላይ ክፍል በእጅጉ የተጎዳውን 10 ኪሎሜትር መንገድ በቅድሚያ በአስፋልት ደረጃ ከባድ ጥገና በማድረግ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት 60 ሚሊዮን ብር የጥገና ወጪም ተመድቧል። ይህን ስራ በአፋጣኝ ለመጀመር አስፋልት ፣ ጠጠር እና ማሽነሪ የመሳሰሉ የግንባታ ግብዓቶችን የማሟላት ቅድመ ዝግጅት ስራዎች እተከናወኑ ነው፡፡ አጠቃላይ ስራውን በዚሁ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ኢመባ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል። መንገዱ አንደ ባህርዳርና ጎንደር ያሉ ትልልቅ ከተሞችን ከአዲስ አበባ እና ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ጋር የሚያገናኝ ወሳኝ የሀገራችን መንገድ ነው። ከጎረቤት ሀገራት ጋር ከሚያገናኙ የወጪ ገቢ መዳረሻ መንገዶች መካከልም አንዱ ነው፡፡

የአደሌ -ግራዋ 53 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ ዛሬ በይፋ ተጀመረ። በ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ወጪ የአደሌ -ግራዋ 53 ኪ.ሜ የአስፋልት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ስራው በይፋ ተጀመሯል፡፡ በዛሬው እለት በተካሄደው የመንገዱ ግንባታ ጅማሮ መርሃግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል ባለስልጣናት ታድመዋል፡፡ የእለቱ የክብር እንግዳ ክቡር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በመርሀ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር ህብረተሰቡ ለአመታት የቆየ የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበትና ፕሮጀክቱ ለክልሉም ሆነ ለሀገር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው መሆኑን አብራርተዋል ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ በቀለ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጉዳዮችን በፍጥነት እየቀረፉ መሄድ ወሳኝ በመሆኑ የሚመለከታችሁ የመስተዳድር አካላትና ነዋሪዎች አስፈላጊውን ትብብር እንድታደርጉ ጥሪ አቅርበዋል ። ኢመባ ኘሮጀክቱ በስኬት እንዲጠናቀቅም የቅርብ ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል ፡፡ የመንገድ ግንባታውን የሚያከናውነው ሂቤ ኮንስትራክሽን ግሩፕ በበኩሉ በገባው ቃል መሰረት ፕሮጀክቱን በጥራት አጠናቆ እንደሚያስረክብ ቃል ገብቷል። አደሌ ግራዋ ጠጠር መንገድ ሆኖ ላለፉት 50 አመታት የትራንስፖርት ግልጋሎት ሲሠጥ የቆየና በእጅጉ የተበላሸ መንገድ ነው። መንገዱን ለመገንባት የሚወጣው ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል። አሁናዊው የመንገዱ ሁኔታ ከ 6 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋት ያለውና ጠባብ ሲሆን በእስፋልት ደረጃ ሲገነባ ስፋቱ አሁን ካለው እንዲጨምር ተደርጎ በወረዳ 19 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 1ዐ ሜትር ይሆናል ። የአደሌ - ግራዋን 53 ኪሎ ሜትር መንገድ በአሁን ሰአት በተሸከርካሪ ለመጓዝ ይጠይቅ የነበረውን ከ 3፡00 ሰዓታት በላይ የትራንስፖርት ጊዜ ከግማሽ በላይ ያሳጥረዋል። የአደሌ ግራዋ መንገድ በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን ቋሚ የሰብል ምርቶችን ፣ የቁም እንስሳት ውጤቶች ፣ ፍራፍሬና ሌሎችንም ወደ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ነዋሪው ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር ጠቀሜታው የላቀ ነው። የአደሌ-ግራዋ መንገድ ግንባታ በመስመሩ ተራርቀው ለነበሩ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች በቅርበት በማስተሳሰር ይበልጥ በኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥርላቸዋል ፡፡ እንዲሁም የአካባቢውን ህብረተሰብ የስራ እድል በስፋት እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡ ጎጎት ኮንሰልቲንግ ኢንጅነሪንግ የመንገዱን ግንባታ የማማከር እና የመቆጣጣር ስራውን ያካሂዳል ፡፡