ru
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Открыть в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 13 369 подписчиков, занимая 1 753 место в категории Транспорт и 2 530 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 13 369 подписчиков.

Согласно последним данным от 20 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 129, а за последние 24 часа — 8, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 38.47%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.24% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 143 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 037 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 11.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 21 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Транспорт.

13 373
Подписчики
+824 часа
+697 дней
+12930 день
Архив постов
የጊንጪ ሽኩቴ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የግንባታ እንቅስቃሴ በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ እና በኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም በተቋሙ የስራ ሃላፊዎች ዛሬ በመስክ የስራ ቅኘት ተጎብኝቷል። 59ኪ.ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን ይህንኑ ፕሮጀክት ነው ዛሬ የተቃኘው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ቀደም ብሎ በወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ሳቢያ በእቅዱ መሰረት ለመስራት ሲቸገር ቆይቶ በአሁኑ ወቀት ያሉት ዋና ዋና ችግሮች በመቀረፍቸው ፕሮጀክቱ በጥሩ ሁኔታ በመከናወን ላይ መሆኑ ተገምግሞል ። በዚህም በአሁኑ ወቅት የአስፖልት ማንጠፍ ስራ የተጀመረ ሲሆን በያዝነው አመት መጨረሻ ድረስም ዋና ዋና ስራዎች እንደሚጠናቀቁ ይጠበቃል። ይህ እንዲሆን አሁንም ከወሰን ማሰከበር ጋር ተያይዞ ያልተፈቱ ችግሮችን ለማቃለል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይበልጥ ተቀራርቦ እንዲሰራም የስራ ሃላፊዎቹ አሳስበዋል። የዛሬው የመስክ ቅኘት አላማም የፖሮጀክቱን ሂደት በአካል ከመመልከት ባለፈ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የበኩሉን ሚና ለማበርከት ያለመ ነው። የጊንጪ ሽኩቴ መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ነው ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው የተቋራጩ ባለቤት አቶ ገምሹ በየነ ያሉ ችግሮችን በጋራ በመፍታት ፕሮጀክቱን በጥራት አጠናቆ ለማስረከብ ይበልጥ እየሰራን ነው ብለዋል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለመስመሩ ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፍይዳዎችን የሚያጎናጽፍ ነው። በተያያዘ ዜናም የስራ ሃላፊዎቹ በዛሬው የመስክ ቅኝታቸው ከ1ነጥብ 26ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኘውን የሽኩቴ ጩሉጤን 63ነጥብ 2ኬሜ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን ቃኝተዋል። ከመልካ ምድራዊ አቀማመጥ ጋር ተያይዞ የአፈር መንሸራተትና ናዳ የሚስተዋልባቸውን ስፍራዎችን ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠትም ይበልጥ ይሰራል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎቹ ከወሰን ማስከበር እና ከግብአት አቅርቦት ጋር የተያያዙ ችግሮች እንዲፈቱ አቅጣጫንም አሰቀምጠዋል ። ለፕሮጀክቱ ተግዳሮት የሚሆኑ ችግሮችን በቀጣይ በጋራ በመፍታት ስራው እንዲፋጠን ይበልጥ የጎላ ሚና እንደሚያበረክቱም የስራ ሃላፊዎቹ አረጋግጠዋል። መንገዱ ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፍይዳ አኳያ ኮንትራክተሩም ሆነ አማካሪ ድርጅቱ በትኩረት እንዲሰሩም አስገንዝበዋል::

በመልካ ምድራዊ አቀማመጥና በክርምቱ ከባድ ዝናብ ምክንያት የትራንስፖርት ፍሰቱን አስተጓግሎ የነበረው የዲሪ-ማሻ መስመር ከጊምቦ እስከ ኪሎሜትር 62 የመንገድ ግንባታ ጥገና ተደርጎለት አገልግሎት መስጠት ጀመረ። ከሰላሳ አመት በፊት የተገነባው የዲሪ-ማሻ -ቴፒ የመንገድ ክፍል የሆነው ጊምቦ ኪ.ሜ 62 ከአገልግሎት ብዛት እና በተፈጥሮና ስው ሰራሽ ችግሮች በእጅጉ የተጎዳ ሲሆን በቅርቡ የትራንስፖርት ፍሰቱን እንዲሰተጓጎል ማድረጉ ይታወሳል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ መደበኛ አገልግሎት እንዲመለስ ባደረገው ጥገና ችግሩ ተፈቷል። በአሁኑ ወቅትም በስፍራው መደበኛ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ማድረግ ተችሏል። ቀድም ብሎ መንገዱን ለመገባት ውል የገባው የስራ ተቋራጭ በአቅም ውስንንት እና በጥራት ማጓደል ምክንያት ኢመባ ውሉን በማቆረጥ አለማቀፍ ጨረታ እንዲወጣ አድርጓል በአሁኑ ወቅትም የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል። ሂደቱን አጠናቆ የመንገድ ፕሮጀክቱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ በመስጠት በዋነኝነት የቅርብ ዕሩቅ ሆነው የኖሩትን የደቡብ ፣ የኦሮሚያን እና የጋምቤላ ክልሎችን በቅርበት በማስተሳሰር ለሀገራችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ሚናው የጎላ ይሆናል።

የጎሃፅዮን-ደጀን መንገድ ከባድ ጥገና ሊካሄድለት ነው ። መልካ ምድራዊ አቀማመጡ እጅግ አስቸጋሪ በሆነው በዚሁ ስፍራ በመስክ የስራ ቅኝት ተጎብኝቷል። 40 ኪሎሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው የጎሃፅዮን-ደጀን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች አማካኝነት አደጋ እየደረሰበት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በተለይም ከመልካ ምድራዊ አቀማመጡ አስቸጋሪነት ጋር ተዳምሮ በክረምቱ ወራት በቦታው የጣለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ በመንገዱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ የመሬት መንሸራተት እና ናዳ ሊያስከትል ችሏል ፡፡ ከክብደት መጠን በላይ የሚጭኑ በርካታ ከባድ ተሽከርካሪዎችም ለመንገዱ መበላሸት አሉታዊ አስተዋጽኗቸው እየጎላ ነው። ይህን ተከትሎም መንገዱ ለተሽከርካሪ አስቸጋሪ እየሆነ በምጣቱ ፈጣን መፍትሄእንደሚያስፈልገው ታምኖበታል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የትራንስፖርት ፍሰቱ እንዳይስተጓጎል አስፈላጊውን ማሽነሪ በቦታው በማሰማራት ለመንገዱ አፋጣኝ የጥገና ስራ እያካሄደለት ነው፡፡ ሆኖም ግን በመንገዱ ላይ እያጋጠመ ያለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ እንዲኖረው ለማድረግ በፕሮጀክት ታቅፎ በከባድ ጥገና ደረጃ እንዲገነባ ተወስኗል፡፡ ከመንገዱ አጠቃላይ ክፍል በእጅጉ የተጎዳውን 10 ኪሎሜትር መንገድ በቅድሚያ በአስፋልት ደረጃ ከባድ ጥገና በማድረግ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት 60 ሚሊዮን ብር የጥገና ወጪም ተመድቧል። ይህን ስራ በአፋጣኝ ለመጀመር አስፋልት ፣ ጠጠር እና ማሽነሪ የመሳሰሉ የግንባታ ግብዓቶችን የማሟላት ቅድመ ዝግጅት ስራዎች እተከናወኑ ነው፡፡ አጠቃላይ ስራውን በዚሁ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ኢመባ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል። መንገዱ አንደ ባህርዳርና ጎንደር ያሉ ትልልቅ ከተሞችን ከአዲስ አበባ እና ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ጋር የሚያገናኝ ወሳኝ የሀገራችን መንገድ ነው። ከጎረቤት ሀገራት ጋር ከሚያገናኙ የወጪ ገቢ መዳረሻ መንገዶች መካከልም አንዱ ነው፡፡

የአደሌ -ግራዋ 53 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ ዛሬ በይፋ ተጀመረ። በ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ወጪ የአደሌ -ግራዋ 53 ኪ.ሜ የአስፋልት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ስራው በይፋ ተጀመሯል፡፡ በዛሬው እለት በተካሄደው የመንገዱ ግንባታ ጅማሮ መርሃግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል ባለስልጣናት ታድመዋል፡፡ የእለቱ የክብር እንግዳ ክቡር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በመርሀ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር ህብረተሰቡ ለአመታት የቆየ የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበትና ፕሮጀክቱ ለክልሉም ሆነ ለሀገር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው መሆኑን አብራርተዋል ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ በቀለ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጉዳዮችን በፍጥነት እየቀረፉ መሄድ ወሳኝ በመሆኑ የሚመለከታችሁ የመስተዳድር አካላትና ነዋሪዎች አስፈላጊውን ትብብር እንድታደርጉ ጥሪ አቅርበዋል ። ኢመባ ኘሮጀክቱ በስኬት እንዲጠናቀቅም የቅርብ ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል ፡፡ የመንገድ ግንባታውን የሚያከናውነው ሂቤ ኮንስትራክሽን ግሩፕ በበኩሉ በገባው ቃል መሰረት ፕሮጀክቱን በጥራት አጠናቆ እንደሚያስረክብ ቃል ገብቷል። አደሌ ግራዋ ጠጠር መንገድ ሆኖ ላለፉት 50 አመታት የትራንስፖርት ግልጋሎት ሲሠጥ የቆየና በእጅጉ የተበላሸ መንገድ ነው። መንገዱን ለመገንባት የሚወጣው ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል። አሁናዊው የመንገዱ ሁኔታ ከ 6 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋት ያለውና ጠባብ ሲሆን በእስፋልት ደረጃ ሲገነባ ስፋቱ አሁን ካለው እንዲጨምር ተደርጎ በወረዳ 19 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 1ዐ ሜትር ይሆናል ። የአደሌ - ግራዋን 53 ኪሎ ሜትር መንገድ በአሁን ሰአት በተሸከርካሪ ለመጓዝ ይጠይቅ የነበረውን ከ 3፡00 ሰዓታት በላይ የትራንስፖርት ጊዜ ከግማሽ በላይ ያሳጥረዋል። የአደሌ ግራዋ መንገድ በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን ቋሚ የሰብል ምርቶችን ፣ የቁም እንስሳት ውጤቶች ፣ ፍራፍሬና ሌሎችንም ወደ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ነዋሪው ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር ጠቀሜታው የላቀ ነው። የአደሌ-ግራዋ መንገድ ግንባታ በመስመሩ ተራርቀው ለነበሩ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች በቅርበት በማስተሳሰር ይበልጥ በኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥርላቸዋል ፡፡ እንዲሁም የአካባቢውን ህብረተሰብ የስራ እድል በስፋት እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡ ጎጎት ኮንሰልቲንግ ኢንጅነሪንግ የመንገዱን ግንባታ የማማከር እና የመቆጣጣር ስራውን ያካሂዳል ፡፡

የሀዋሳ - ጩኮ 66 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ ። የሞምባሳ - ናይሮቢ - አዲስ አበባ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሀዋሳ - ጩኮ 66 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ስራ ተጠናቀቀ። አጠቃላይ የፕሮጀክቱን የማጠቃለያ ስራን የተመለከተ የመስክ የስራ ስምሪት በስፍራው ተካሂዷል ። በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የተገነባው የሀዋሳ - ጩኮ መንገድ በመስመሩ ላይ የሚገኙትን ከተሞች ፣ የእርሻና የኢንዱስትሪ ዞኖች እንዲሁም የቱሪስት መስህብ የሆኑ ስፍራዎችን ዘመናዊ በሆነ መንገድ በማስተሳሰር የጉዞ ጊዜንና ወጪን በመቀነስ ረገድ ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ በደቡብ የኢትዮጵያ የሀገራችን ክፍል የሚመረቱ የግብርና እና የኢንደስትሪ ምርት ውጤቶችን ወደ አዲስ አበባም ሆነ ወደ ኬኒያ ሞንባሳ ወደብ ለማድረስም ሆነ የገቢ ምርቶችንም እንዲሁም ከወደቡ ወደ ተቀረው ኢትዮጵያ ክፍል ለማዳረስ መንገዱ ሚናው የጎላ ነው፡፡ የሀዋሳ - ጩኮ መንገድ መገንባት የኢትዮጵያ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኘውን የቡና ምርት ውጤቶችን በአፋጣኝ ወደ አለም አቀፍ ገበያ ለማድረስ አበርክቶው የላቀ ነው ፡፡ የሁለቱን ጎረቤት አገራት ህዝቦችን እርስ በርስ በማስተሳሰር ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ከማሳደግ አንጻር አስተዋጽኦ ከአገርም አልፎ ቀጠናዊ ሚናውን ክፍ ያደርገዋል፡፡ መንገዱ የተገነባው በቻይናው አለም አቀፍ ተቋራጭ ድርጅት በሆነው ሲኖ ሀይድሮ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ ሲሆን ለግንባታው የዋለው ወጪ የተሸፈነው ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 1 ነጥብ1 ቢልዮን ብር ብድር ነው፡፡ የመንገድ ስራውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር የሰራው ደግሞ ኤ አይ ሲ ፕሮጊቲ ኤስ.ፒ.ኤ ( AIC Progetti SPA ) የተባለ የውጭ አማካሪ ድርጅት ነው። የሀዋሳ - ጩኮ መንገድ ከዚህ ቀድም መንገዱን ለመገንባት ከውጭ የስራ ተቋራጭ ጋር ውል ተፈጽሞ ወደ ስራ ተገብቶ የነበረ ቢሆንም የስራ ተቋራጩ ባስመዘገበው የአፈፃፀም ድክመትና የጥራት ችግር ምክንያት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ውሉ እንዲቋረጥ አድርጎ አዲስ ጨረታ እንዲወጣ በማድረግ ስራው ለፍጻሜ እንዲበቃ አድርጓል፡፡ የዚሁ መንገድ ቀጣይ ክፍል የሆነው ጩኮ - ይርጋጨፌ 60 ኪሜ አስፋልት ኮንክሪት ግንባታ ስራ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

ከአዋሽ ወደ ድሬዳዋ የሚዘልቀው መንገድ ዳግም ለተሽከርካሪ ክፍት መሆኑን ሆነ። ከትላንትና በስተያ ከድሬዳዋ 106 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በካራሚሌ እና ቦረዳ መሃል አይፎክሩ በሚባል መስመር ላይ ክሬሸር
ከአዋሽ ወደ ድሬዳዋ የሚዘልቀው መንገድ ዳግም ለተሽከርካሪ ክፍት መሆኑን ሆነ። ከትላንትና በስተያ ከድሬዳዋ 106 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በካራሚሌ እና ቦረዳ መሃል አይፎክሩ በሚባል መስመር ላይ ክሬሸር የጫነ ሎቤድ ከባድ የጭነት መኪና ሳቢያ መንገዱ ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የድሬዳዋ ዲስትሪክት መንገዱን ክፍት ለማድረግ ባከናወናቸው ስራዎች መስመሩ ዳግም ለትራፊክ ክፍት ሆኗል። በቀጣይም ከመንገዱ መልክአ ምድራዊ አቀማመጥና ከተፈጥሮ የመሬት መንሸራተት ጋር ተዳምሮ መስተጓጎል እንዳያጋጥም ቀጣይ ስራዎች እየተከናወኑ ነው። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ይህን የመሰሉ ችግሮች ሲያጋጥም ፣እንዲሁም ችግሮቹ እልባት እስከሚያገኙ ድረስ በትዕግስት ለሚጠባበቁት የመንገዱ ተጠቃሚዎች እና አሽከርካሪዎች ምስጋናውን ያቀርባል።

በድንገተኛ ናዳ ጉዳት የገጠመው የአባይ ሸለቆ መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው ፡፡ በጎሃጺዮን ደጀን መንገድ ላይ የሚገኘውና በድንገተኛ ናዳ ለጉዳት ተጋልጦ የነበረው የአባይ ሸለቆ መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል ፡፡ በአካባቢው በጣለው ከፍተኛ ዝናብ በአባይ ሸለቆ ውስጥ ባሉት በተለይም ሶስት የተለያዩ ስፍራዎች ላይ ነው የመሬት መንሸራተት እና ናዳ የተከሰተው ፡፡ በእነዚህ ሶስቱ ስፍራዎችም መንገዱ ተቆርሶ የመሄድ እና ከተራራው ክፍል በመጣ የአፈር ናዳ መንገዱ ላይ ጉዳት ሊያስከትል ችሏል ፡፡ የአለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ የትራንስፖርት ፍሰቱ እንዳይስተጓጎል አስፈላጊውን ማሽነሪ በማሰማራት የጥገና ስራ እያካሄደለት ይገኛል፡፡ በእስካሁኑም በተደረገው ጥገና መደበኛው የትራንስፖርት ፍሰቱ ሳይቋረጥ የቀጠለ ሲሆን በተቀረው ጉዳት በገጠመው የመንገዱ ክፍል የጥገና ስራው እተካሄደ ነው ፡፡ ከአዲስ አበባ ባህርዳር ከዛም አልፎ እስከ ጎረቤት አገራት ድረስ የሚያገናኘው የመንገድ አካል በሆነው የአባይ ሸለቆ መንገድ ካለው መልክአምድራዊ አቀማመጥ እና ከአፈሩ ባህሪ አንጻር ተደጋጋሚ የመሬት መንሸራተት እንዲሁም ናዳ ችግሮች ይገጥሙታል ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሆነው የአለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ችግሩን በጊዜያዊነት ለመቅረፍ እንዲያስችል ስፍራው ላይ በቅርበት የሚንቀሳቀስ ተጠባባቂ የራስ ሀይል በመመደብ መሰል ችግሮች ባጋጠሙ ጊዜ አስፈላጊውን ጥገና በማድረግ የትራንስፖርት ፍሰቱ እንዳይስተጓጎል እየሰራ ይገኛል ፡፡ በቀጣይም የባለስልጣኑ መ/ቤት ይህን መልክአ ምድራዊ አቀማመጡ አሰቸጋሪ የሆነውን የጎሃፅዮን ደጀን የመንገድ አውታርን ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እንዲቻል ከጃፓን አለም አቀፍ የትብብር ድርጅት ( JICA ) ጋር በጋራ ጥናቶች እየተካሄዱ ይገኛሉ፡፡ ጥናቱ በአሁን ደረጃ መነሻ ሊሆኑ በሚችሉ ግኝቶች እና በተገኙ ውጤቶች አማካኝነት ተግባራዊ የሙከራ ስራዎች ተጀምረዋል ፡፡ የጥናቱ ውጤት ሙሉ ለሙሉ እንደተጠናቀቀም ሊወሰድ የሚችለው ዘላቂ መፍትሄ ለመንግስት ቀርቦ በቀጣይ ውሳኔ እንደሚያገኝም ይጠበቃል።

የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ በኢ.መ.ባ. ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የማነቃቂያ ዘመቻ እየተካሄደ ነው ፡፡ እየተካሄደ ባለው በዚሁ የቅስቀሳ ዘመቻ ላይም ለባለስልጣኑ መ/ቤት ሰራተኞች የተለያዩ ወረርሽኙን የተመለከቱ ግንዛቤ ሰጪ ትምህርቶች እየተሰጣቸው ይገኛል። ከዚህም ባለፈ በተቋሙም ባሉ እና የተለያዩ የሰዎች ምልልስ በሚዘወተርባቸው ስፍራዎች የኬሚካል ርጭት ተካሂዷል፡፡ እንዲሁም ለሰራተኛው የሙቀት መጠን መለካት ተግባራት መከናወናቸውን ቀጥለዋል ። ለባለሥልጣኑ ሰራተኞች እና ባለጉዳዮች ወረርሽኙን የተመለከቱ የተለያዩ መልእክቶችን ያዘሉ በራሪ ወረቀቶች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎች እደላም እንዲሁ በመካሄድ ላይ ይገኛል ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ቫይረሱ በሀገራችን መከሰቱ ከተሰማ ወዲህ የወረርሽኙን ስርጭት ለመቀነስና ብሎም በተቋሙ የሚሰሩ ሰራተኞችን ደህንነት ለመጠበቅ የተለያዩ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል ። ሆኖም በአገር ደረጃ በቫይረሱ የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን በአስጊ ሁኔታ እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በህብረተሰቡ ዘንድ መዘናጋት እየተስተዋለ በመምጣቱ የተቋሙን ሰራተኞች በድጋሚ ማንቃት በማስፈለጉ ነው ዘመቻው እየተካሄደ የሚገኘው። በተመሳሳይም በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን የ ‘ምክንያት አልሆንም’ ንቅናቄ በተቋም ደረጃ ተቀብሎ ተግባራዊ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ነው። በዚህ በአንድ ሳምንት በሚቆየው እና በተቋም ደረጃ እየተተገበረ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን የመቀነስ የማነቃቂያ ዘመቻ በቀሪው ቀናትም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡