en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 307 subscribers, ranking 1 759 in the Transport category and 2 546 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 307 subscribers.

According to the latest data from 15 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 88 over the last 30 days and by 2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 40.23%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.41% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 352 views. Within the first day, a publication typically gains 2 050 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 16 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 313
Subscribers
+224 hours
+297 days
+8830 days
Posts Archive
የአዳማ - አዋሽ መልካሳ መንገድ መልሶ ግንባታ እየተደረገለት ነው አዳማ፣ ኅዳር 08፣ 2018 (ኢ መ አ) ፡- ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት የሚያስተናግደው የአዳማ - አዋሽ መልካሳ ክፍል አንድ መንገድ መልሶ ግንባታ እተደረገለት ነው፡፡ ነባሩ መንገድ ስፋቱ ከ7 ሜትር ያልበለጠ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ያልነበረ እንዲሁም በአገልግሎት ብዛት በእጅጉ የተጎዳ ሲሆን፣ አሁን ላይ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በበቂ ሁኔታ ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ የመልሶ ግንባታ እየተደረገልት ይገኛል፡፡ የመልሶ ግንባታ ሥራው 17 ነጥብ 56 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን፣ የመንገድ አካፋይ እና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ አጠቃለይ 34 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል፡፡ አሁን ላይም የአፈር፣ የጠረጋ፣ የሰብቤዝ እና የውኃ መፋሰሻ ሥራዎች በመከናውን ላይ ናቸው፡፡ የመንገድ ግንባታውን መንግስታዊው የልማት ድርጅት ኢትዮ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን በ4 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ወጪው በፌደራል መንግስት ይሸፈናል፡፡ መከላከያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን ድርጅት የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የመንገዱ መገንባት የትራፊክ ጭንቅንቁን በእጅጉ ከማቅለሉም ባሻግር በምሠራቅ ሸዋ ዞን የሚገኙትን በርካታ ወረዳዎች በማስተሳሰር ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያፋጥን ይሆናል፡፡ የአዳማ-አሰላ መንገድ አካል ሲሆን፣ ወደ አሰላ፣ በቆጂ: ባሌ ሮቤ እና ባሌ ጎባ የሚደረገውን ጉዞ የሚያቀል ነው፡፡ በተጨማሪም የሃገሪቱን የግብርና ምርቶች ስንዴ፣ ገብስ እና ሌሎቹም የወጪ እና ገቢ ንግድን ከሚያሳልጡ አውራ መንገዶች አንዱ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የሺሺንዳ ቴፒ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ ዳግም ተጀመረ አዲስ አበባ ህዳር 06፣ 2018 (ኢመአ) ከፋ እና ሸካ ዞኖችን የሚያገናኘው 77 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ ግንባታ ስራ ገብቷል፡፡ ከዚህ ቀደም የመንገዱን ግንባታ ሲያካሂድ የነበረው የቻይናው CRCC ካምፓኒ የነበረ ሲሆን የስራ ተቋራጩ በነበረበት የአቅም ውስንነቶች እንዲሁም ከወሰን ማስከብር እና ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የመንገዱ የግንባታ ሂደት ተቋርጦ ቆይቷል። ይህንን ችግሮች ለመፍታት ይቻል ዘንድ አዲስ የሥራ ተቋራጭ ተመርጦ ሥራውን እንዲያስቀጥል ተደርጓል፡፡ አሁን ላይ የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በማካሄድ ላይ የሚገኘው አገር በቀሉ ሱር ኮንስትራክሽን የስራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራ ውን በማከናወን ላይ የሚገኘው ደግሞ ክላሲክ ኮንሰልቲንግ ነው ። አሁን ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለአዲሱ የሥራ ተቋራጭ የሥራ ቦታውን በማስረከብ ስራው በይፋ ተጀምሯል፡፡ በእስካሁኑ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የማፋሰሻ እና የስትራክቸር ፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ እንዲሁም አስር ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ስራዎች ተከናውነዋል ። ፕሮጀክቱን ለማካሄድ ጥቅም ላይ የሚውለው ከ1,556,000000 (አንድ ቢለየን አምስት መቶ ሀምሳ ስድስት ሚሊዮን ብር) በላይ የግንባታ ወጪ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ። መንገዱ በገጠር 7 ሜትር ፣ በቀበሌ 12ሜትር ፣ በወረዳ ደግሞ 19 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በመስመሩ የሚገኙትን ሺሺንዳ ፣እና ቴፒ ከተሞች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መስተጋብር ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይታመናል። በአካባቢው እንደ ቡና ፣ ሙዝ ፣ አቮካዶ ፣ ማር ፣ እንደ ቁንዶ በርበሬ እና ኮረሪማ ያሉ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች በስፋት የሚገኙ ሲሆን የመንገዱ መገንባት እነዚህን ምርቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ በፍጥነት እና በቀላሉ በማድረስ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር የኪነ-ጥበብ ምሽት አካሄደ አዲስ አበባ ህዳር 05 ፣ 2018 (ኢ .መ.አ ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ‘’መንገድ እና ሃገር” በሚል መሪ ቃል ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር የኪነ ጥበብ ምሽት አካሂደዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የኢዜአ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን ፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰይፈ ደርቤ ፣ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የመርሃ-ግብሩ ተሳታፊዎች ታድመዋል፡፡ በኪነ-ጥበብ ምሽቱ ላይ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ኢዜአ ላለፉት 75 ዓመታት ተቋሙ በመንገድ ዘርፍ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ፣ የተገኙ ውጤቶች ፣ ፋይዳዎች እንዲሁም ተግዳሮቶችን ጭምር በስፋት የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኙ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ተገቢ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ስለመስራቱ ገልፀዋል፡፡ ሁለቱ ተቋማት ያላቸውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት በማስቀጠል በቀጣይም ሰፊ ስራዎችን በጋራ እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው ከፍተኛ መዋለ ነዋይ የሚፈስበት የመንገድ መሰረተ ልማት ጉዳት ሳይደርስበት ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ይችል ዘንድ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በህብረተሰቡ ዘንድ የባለቤትነት መንፈስ የመፍጠር አቅሙ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ይህን አቅማቸውን በመገንዘብ ውድ የሀገር ሀብት የፈሰሰበትን የመንገድ መሰረተ-ልማት በጋራ በመጠበቅ የዜግነት ግዴታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የተቋሙ የቀድሞ ከፍተኛ የስራ ኃላፊ የነበሩት አቶ አለማየሁ መንገሻ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ላለፉት 75 ዓመታት ያካበተውን ልምድ በአግባቡ በመጠቀም በቀጣይም ኃላፊነቱን በብቃት እንደሚወጣ እተማመናለሁ ብለዋል፡፡ በዚህም ረገድ የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሃብት በበለጠ ቅልጥፍና ለመጠቀም ፤ የኢኮኖሚ ዕድገት እና ውህደትን ለማጠናከር ፤ የትምህርት እና የጤና እንዲሁም የከተሞች ልማትን በላቀ ሁኔታ ለማስፋፋት ፣ የግብርና ኢንዱስትሪ ፍጆታዎችን በወቅቱ እና በብቃት ለማቅረብ እንዲሁም የማህበራዊ እና ባህላዊ ግንኙነቶች እንዲዳብሩ ለማስቻል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሚና ይበልጥ ጎልቶ ሊወጣ ይገዋል ብለዋል፡፡ አክለውም የአገራችን የውጭ ንግድ ዕድገት ይበልጥ እንዲጠናከር እና በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነቷ እንዲጎለብት ለማስቻል መንገዶች ከሎጂስቲክስ ፍላጎት ጋር በተቀናጀ መልኩ በተጠናከረ መልኩ ሊስፋፉ እና ሊሻሻሉ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ በመርሃ-ግብሩ ላይ ሙዚቃዊ ተውኔት እና የተለያዩ ስነ-ጽሁፋዊ ዝግጅቶች ቀርበዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የአቦምሳ - አሰኮ - ዲቡ ወንዝ መንገድ ግንባታ በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ኅዳር 04፣ 2018 (ኢ መ አ):- በምዕራብ አርሲ ዞን የአቦምሳ - አሰኮ - ዲቡ ወንዝ ክፍል አንድ መንገድ ግንባታ በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 60 ነጥብ 91 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ የአቦምሳ - አሰኮ - በደዩ ጨለለቃ መንገድ ፕሮጀክት ትስስር የመጀመሪያው ክፍል ነው። አሁን ላይ ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ሥራ 59 ነጥብ 46 በመቶው ተጠናቅቋል። እየተከናወኑ ከሚገኙ የግንባታ ሥራዎች መካከልም የአስፋልት፣ ሰብ ቤዝ፣ ቤዝ ኮርስ፣ የአፈርና ድንጋይ ቆረጣ፣ የተመረጠ አፈርና ድንጋይ ሙሌት እንዲሁም የውኃ ማፋሰሻ ቱቦ የምርት ሥራዎች ይጠቀሳሉ። የሦስት ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ ተካትቷል።  የመንገድ ግንባታውን ሀቨሪም ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ከዓለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ጋር በጥምረት ያከናውናሉ። በተመሳሳይ መታፈሪያ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ እና ኤልዳ የምህንድስና አማካሪዎች የፕሮጀክቱን ጥራት ቁጥጥር እና የማማከር ሥራ በጋራ ያከናውናሉ። ለግንባታው ማስፈጸሚያ 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት በጀት ተይዟል። በግንባታው ሂደት ላይ የገጠሙ ከወሰን ማስከበር እና ከጸጥታ መደፍረስ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመቅረፍ ተቋማችን የአቦምሳ እና አሰኮ ወረዳዎች የጸጥታ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ማኅበረሰቡን ያማከለ የሦስትዮሽ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በነባሩ የጠጠር መንገድ ከአቦምሳ - አሰኮ ድረስ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን 2 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 30 ደቂቃ ያሳጥረዋል። እንዲሁም ከአሰኮ ዲቡ ወንዝ ለመጓዝ ምንም ዓይነት መንገድ ባለመኖሩ በእግር ይደረግ የነበረውን አድካሚ ጉዞ በማስቀረት በ20 ደቂቃ መድረስ ያስችላል። ከዚህም ባሻገር በሥፍራው በስፋት የሚመረቱትን የጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ የበቆሎ፣ ሽንኩርት እና የጫት ምርት ውጤቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲደርሱ በማስቻል የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ይጨምራል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የቀላፎ ተገጣጣሚ የብረት ድልድይ ጥገና ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ 29፣ 2018 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል 60 ሜትር ርዝመት ያለው እና ጉዳት ደርሶበት የነበረው የቀላፎ ተገጣጣሚ የብረት ድልድይ መልሶ ግንባታ ተጠናቅቋል። ለረጅም ጊዜ ብቸኛ አማራጭ ሆኖ የሸበሌ ወንዝን አቋርጦ ለኅብረተሰቡ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው ይህ ድልድይ ከፍተኛ ክብደት በጫነ ተሽከርካሪ ጉዳት የደረሰበት መኾኑን ጠቅሰን የድልድዩ መልሶ ግንባታ ሥራ በመጠናቀቅ ላይ መኾኑን በቅርቡ መግለጻችን ይታወቃል። አሁን ላይ የተገጣጣሚ የብረት ድልድዩን ወደ ቀደመ አገልግሎቱ ለመመለስ በተደረገው ከፍተኛ ጥረት የመልሶ ግንባታ ሥራው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ በቀጣይ ቀናቶች ውስጥ ለተሽከርካሪ አገልግሎት ክፍት የሚደረግ ይኾናል። በኢ መ አ የጎዴ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እንዲሁም የድልድይ እና ስትራክቸር ዳይሮክቶሬት በመልሶ ግንባታ ሥራው ላይ ተሳትፈዋል። ይህ የቀላፎ ድልድይ እስከ 20 ቶን (200 ኩንታል) ድረስ የመሸከም አቅም ያለው በመኾኑ አሽከርካሪዎች በከፍተኛ ኅላፊነት እንዲገለገሉ ኢመአ ያሳስባል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኦሞ-ሳይ እና ሌፍት ካናል ብሪጅ መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 49 ነጥብ 24 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2018 (ኢ መ አ):- በምዕራብ ኦሞ ዞን የኦሞ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ የኾናው የኦሞ-ሳይ እና ሌፍት ካናል ብሪጅ መንገድ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸም 49 ነጥብ 24 በመቶ ደርሷል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 64 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ የኦሞ ብሔራዊ ፓርክ አማራጭ መዳረሻ በመኾን የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ከማነቃቃቱም ባሻገር በርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎችን የሚያስተሳስር ነው። አሁን ላይ የዲዛይን፣ የለውጥ መንገድ፣ የአፈር ጠረጋ፣ ቆረጣ እና ሙሌት፣ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የስትራክቸር እንዲሁም የሰብቤዝ እና የቤዝኮርስ ጠጠር ማምረት ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። አሁን ላይ የተመዘገበውን አበረታች አፈጻጸም በማጠናከር በዚህ ዓመት አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ለመጀመር ዕቅድ ተይዟል። ሀገር በቀሉ ዮቴክ ኮንስትራክሽን ግንባታውን በማከናወን ላይ ሲኾን፥ ዳና እና አሶሼት ምህንድስና አማካሪዎች ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ ያከናውናል። ለግንባታው 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ከፌደራል መንግስት በጀት ተይዞለታል። በአካባቢው በተለያየ ምክንያት የሚነሱ የጸጥታ ችግሮች በተደጋጋሚ ለግንባታው መቋረጥ ምክንያት መኾን፤ የሥራ ተቋራጩ የግንባታ ማሽነሪዎችን በወቅቱ አለማቅረቡ፤ የግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድሯል። የጸጥታ ችግሮችን ለመቅረፍ የኢ መ አ የጂንካ አካባቢ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከየአካባቢው የመስተዳድር አካላት ጋር በቅርበት እየሠራ ይገኛል። የፕሮጀክቱ መነሻ ኦሞ ወንዝ የሚያቋርጥበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወንዙን ተንተርሰው የሚመረቱ የግብርና ምርት ውጤቶችን በስፋት ወደ የተለያዩ የገበያ ማዕከሎች ለማድረስ ያስችላል። በተለይም በአካባቢው ለተገነቡ ግዙፍ የስኳር ፋብሪካዎች የማምረቻ ግብዓቶችን እንዲሁም የስኳር ምርት በቤንች ማጂ በኩል ወደ ተለያዪ የሀገራችን ከተሞች በተሻለ ፍጥነት ለማድረስ ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኝዎች በአካባቢው ወደ ሚገኘው የኦሞ ብሔራዊ ፓርክ የሚያደርጉትን ጉዞ በማቀላጠፍ የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት ይጨምራል።  የዚህ ፕሮጀክት አካል የኾነው ከሳይ ማጂ ያለው መንገድ ከዚህ ቀደም ግንባታው ተጠናቅቆ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት መደረጉ ይታወቃል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች የግንባታ ሂደታቸው የተጓተቱ ፕሮጀክቶችን ለማስቀጠል እየተሰራ ነው አሶሳ፣ ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ): በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለያዩ ምክንያቶች የግንባታ ሂደታቸው የተጓተቱ ፕሮጀክቶችን ማስቀጠል ላይ ትኩረት ያደረገ የመስክ ምልከታ ተካሄደ። በአሶሳ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ስር ከሚገኙት የመንገድ ኘሮጀክቶች መካከል የአሶሳ - ዳለቲ - ባሮዳ (ሎት አንድ ) እና የሆሞሻ - ህዳሴ ፕሮጀክቶች ይገኙባቸዋል፡፡ ግንባታው ቀደም ሲል ተጀምሮ የነበረው የአሶሳ - ዳለቲ ባሩዳ (ሎት አንድ) ሰላሳ ስድሰት ኪሎ ሚትር(36 ኪ.ሜ) የሚሸፍን ሲሆን፤ የግንባታው አፈጻጸሙ ሰባ በመቶ መድረሱ የሚታወስ ነው ፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ ሰናን ኮንስራክሽን ኃ.የተ.የግል ማህበር ሲሆን በአካባቢው በነበረው የፀጥታ ችግር እና የስራ ተቋራጩ አፈፃፀም ደካማ መሆን ለፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ አለመጠናቀቅ ምክንያት ሆኗል፡፡ ይህን ችግር ለመፍታት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ከክልሉ መንግስት ጋር በመነጋገር ችግሮችን ለመቅረፍና ፕሮጀክቶቹን ወደ ስራ ለማስገባት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡  በሥፍራው በመገኘት በተደረገው ውይይት በሥራ ተቋራጩ በኩል ያሉ ውስንነቶችን በመቅረፍ የመንገድ ስራው ላይ የሚያስፈልጉ የኮንስትራክሽን ግብዓት  እና የነዳጅ አቅርቦት በተገቢው ጊዜ ቀርቦ ወደ ስራ  እንዲገቡ ፣ አስፋልት ለማንጠፍ የሚያስችሉ  የሰብቤዝ እና የቤዝኮርስ ጠጠሮችን አምርቶ ፕሮጀክቱን ለማፋጠን አስቻይ ሁኔታዎች ለመፍጠር ይቻል ዘንድ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ በተመሳሳይ የሆሞሻ - ህዳሴ (ሎት አንድ)  መንገድ ፕሮጀክት በሀገር - በቀሉ እንይ ኮንስትራክሽን ሲከናወን ቆይቶ ከጸጥታ እና ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ችግር ተቋርጦ ቆይቷል። አሁን ላይ በተደረጉ ጥረቶች ፕሮጀክቱ ወደ ግንባታ እየተመለሰ ሲሆን፤ በቅድመ-ዝግጅት ሂደት ላይ ይገኛል። ከዚሁ ጎን ለጎን የትራንስፖርት እንቅስቃሴው   መስተጓጎል እንዳይገጥመው  የጥገና ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግና ሥራው እንዲቀጥል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን በቦታው ባደረጉት የመስክ ቅኝት ላይ  አቅጣጫ ሰጥተዋል ። ይህ ፕሮጀክት ወረዳዎችን ከቀበሌዎች በማስተሳሰር ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ መስተጋብር የሚያጠናክር ከመሆኑ በተጨማሪ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ እንደ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል ፡፡ በክልሉ የሚገኙ ሌሎች የመንገድ ፕሮጀክቶችንም በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጎዴ ቀላፎ የብረት ድልድይ ጥገና በመጠናቀቅ ላይ ነው አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓም(ኢመአ)፦ በሶማሌ ክልል ጉዳት አጋጥሞት የነበረው የጎዴ ከተማን ከቀላፎ ወረዳ የሚያገናኘው የብረት ድልድይ የመልሶ ግንባታ ስራ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። ለረጅም ጊዜ ብቸኛ አማራጭ ሆኖ የሸበሌ ወንዝን አቋርጦ ለህብረተሰቡ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው ይህ ድልድይ ከፍተኛ ክብደት በጫነ ተሽከርካሪ ተሰብሮ ከጥቅም ውጪ ሆኖ ተገቢውን አገልግሎት ሳይሰጥ መቆየቱ የሚታወስ ነው ። ድልድዩ ከፍተኛ ርዝመት ያለው ሲሆን፤ ሁለቱን ከተሞች በብቸኝነት ሲያገናኝ የቆየ እንደሆነና ነሃሴ 21 ቀን 2017 ዓ.ም. በገጠመው የመሰበር አደጋ ለበርካታ ጊዜያት ለነዋሪዎቹ ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል። በዚህም ማህበረሰቡ ላይ እየደረሰ ያለውን መንገላታት ለመግታት በተደረገው ርብርብ ተገጣጣሚ የብረት ድልድይ ገንብቶ በማጠናቀቅ ላይ ሲሆን በቅርብ ጊዜ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል ። ቀሪ የድልድይ ስራ ማለትም ለውንቺንግ ኖዝ የመፍታት እና የድልድዩን ወለል የማንጠፍ ስራ እየተሰራ ይገኛል ። ይህ የቀላፎ ተገጣጣሚ ብረት ድልድዩ ያለምሰሶ ተሸካሚ 60.96 ሜትር ሆኖ የተሰራ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግለት ይገባል። በመሆኑም ከ20ቶን (ከ200 ኩንታል) በላይ በድልድዩ ላይ ማሳለፍ እንዲሁም ድልድዩን እንዲያቋርጡ የሚፈቀድላቸው ተሽከርካሪዎች የፍጥነት ገደባቸውን ቀንሰው መጓዝ እንዲችሉ ኢ.መ.አ. በቦታው ተገቢውን የትራፊክ ምልክቶች አስተክሎ ጥቅም ላይ እንዲውል አድርጓል ። በተጨማሪም የመስተዳድር አካላት ለድልድዩ ተገቢውን ጥበቃ እና ኬላ እንዲያቋቁሙ ከመግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የመቂ - ባቱ የፍጥነት መንገድ የ ITS ቴክኖሎጂ ዝርጋታን አስመልክቶ የመስክ ቅኝት ተካሄደ ሞጆ፣ ጥቅምት 14፣ 2018 (ኢ መ አ) ፡-  በሞጆ - ሐዋሳ ክፍል 2 የመቂ - ባቱ የፍጥነት መንገድ ዘመናዊ የመንገድ ላይ ደኅንነት መጠበቂያ ቴክኖሎጂ (ITS) ዝርጋታን አስመልክቶ የመስክ ቅኝት የተካሄደ ሲሆን፤ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን አስመልክቶም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል ። በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የ ITS ኘሮጀክትን አስመልክቶ እንደተገለፀው፤ ይህን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የአገራችንን  የመንገድ ላይ ደኅንነት ለማስጠበቅ የላቀ ውጤት እንደሚያስገኝ ታምኖበት በአፋጣኝ ተጠናቆ ወደ ስራ እንዲገባ ታቅዶ ሲሰራ ቆይቷል። ነገር ግን ፕሮጀክቱ ከተጀመረ 1 ዓመት ከ6 ወራት ቢያስቆጥርም ተጠናቆ ወደ ትግበራ እንዳይገባ የሚያደርጉ ችግሮች በተደጋጋሚ እያጋጠሙ መሆኑ ታውቋል። ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከስራ ተቋራጭ ፣ ከፀጥታ አካላት እንዲሁም  ከሚመለከታቸው ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ ፣ በየአካባቢው የጥበቃ ማማ ተሰርቶ  ጥበቃ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ፣   በህገወጥ ተግባር ላይ በተሰማሩ ግለሰቦች ላይም አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድ እንዲሁም ሃላፊነቱን ያልተወጣ አካል እንዲጠየቅ ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል ፡፡ በመጨረሻም የኢመአ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ብርሃኑ ተስፋዬ  የፕሮጀክቱን ሂደት ለማሳካት ፕሮጀክቱ በሚተገበርባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ የማህበረሰብ አባላት አፋጣኝ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንዲከናወን ፣ በአሰራር ሂደት ወቅት ያሉ ክፍተቶችን በጥልቀት ማጥናት እንደሚያስፈልግ እና ዘላቂ  መፍትሔ መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተሾመ !! ኢንጅነር ገላና ኮራ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በምክትል ዋና ዳይሬክተር ማዕረግ የልዩ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች አስተዳደር ፕሮ
ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተሾመ !! ኢንጅነር ገላና ኮራ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በምክትል ዋና ዳይሬክተር ማዕረግ የልዩ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች አስተዳደር ፕሮግራም አስተባባሪ ኾነው በጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጥቅምት 12 ቀን 2018 ጀምሮ ተሹመዋል። ኢንጅነር ገላና ኮራ ተቋማችን ከመንግስት የተሰጠውን ሃገራዊ ተልዕኮ በተሻለ ብቃት እና ቁርጠኝነት በመከወን የዘርፉን ራዕይ ይበልጥ እንደሚያሳኩ በመተማመን በከፍተኛ አመራርነት እንኳን ወደ ተቋማችን ተቀላቀሉ በማለት መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን! የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር