en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 587 subscribers, ranking 1 732 in the Transport category and 2 492 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 587 subscribers.

According to the latest data from 17 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 262 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 36.03%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.35% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 897 views. Within the first day, a publication typically gains 2 087 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 587
Subscribers
-124 hours
No data7 days
+26230 days
Posts Archive
81 ኪ.ሜ የሚረዝመው የደብረማርቆስ- ደብረኤሊያስ- ተምጫ-ጭምት መገንጠያ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው፡፡ በቅርቡም የአሰፋልት ማንጠፍ ስራ ተጀምሯል። የአፈር ቆረጣና ሙሌት ሥራዎች ፣ የቤዝኮርስ የድልድይ እንዲሁም የውሃ መተላለፊያ ቱቦዎች እና በርካታ የስትራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። መንገዱ ተገንብቶ እስከሚጠናቀቅ የትራንስፖርት መስተጓጎል እንዳይፈጠር ለማስቻል ተለዋጭ መንገድ ተሰርቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ የመንገድ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ ፋል ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን የሚያካሂዱት ደግሞ ሆንግ አይኬ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልታንትስ ከልደት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በመተባበር ነው። ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው አንድ ቢሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ አራት ሺህ ብር ወጪ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ መንገዱን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ለስራ ተቋራጩ የሶስት ዓመት ከአራት ወራት የጊዜ ገደብ የተሰጠው ሲሆን ፣ ግንባታው በተገቢው የጥራት ደረጃ እና ፍጥነት እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የአካባቢው ህብረተሰብ መልካም ትብብር እያደረገ ይገኛል፡፡ መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በደብረማርቆስና በደብረኤልያስ ከተሞች 21 ሜትር ፣ በቀበሌ 16 ሜትር እና በገጠር ደግሞ 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ የዚህ አካባቢ ህብረተሰብ ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ ተጠቃሚ ያልነበረ በመሆኑ ምክንያት የተለያዩ ችግሮችን ሲያስተናግድ ቆይቷል፡፡ በአካባቢው ከፍተኛ የጤፍ ፣ ስንዴ እና ሌሎች የግብርና ምርቶችን ጨምሮ ማርና የአትክልት ምርታማነቱ ከፍተኛ ነው። መንገዱ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን እነዚህን የግብርና ምርቶችን ያለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ገበያ ለማቅረብ እና የአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴ ወደ ተሻለ ደረጀ እንዲያድግ ለማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም ለኢንዱስትሪ ዞኖች የትራንስፖርት ፍሰት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር ባለሃብቶች በአካባቢው የተለያዩ የኢንዱስትሪ ዞኖችን እንዲገነቡ ለማስቻል ከፍተኛ ተነሳሽነትን ይፈጥራል ተብሎ ታምኖበታል ፡፡

የአቦቦ-ሜጤ አቦቦ-ኪ.ሜ 76 ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ
+1
የአቦቦ-ሜጤ አቦቦ-ኪ.ሜ 76 ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ

የጋምቤላ እና የደቡብ ክልሎችን የሚያስተሳስረው የአቦቦ-ሜጤ አቦቦ-ኪ.ሜ 76 ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ ሥራ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ነው። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ግንባታ 98 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን መንገዱ ሙሉ ለሙሉ ለትራፊክ ክፍት ሆኖ አገልግሎት እየሰጠ ነው። የግንባታው ቀሪ ውስን ስራዎች ማለትም የእግረኛ መተላለፊያ ዜብራ ፣ የመንገድ ላይ የትራፊክ ቅቦች የማቅለም ሥራ እንዲሁም ሌሎች ከመንገድ ግንባታው ጋር የተያያዙ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል። 960 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ፕሮጀክቱ ወጪው ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት ነው የተሸፈነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬይል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ የተባለ አለምአቀፍ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን ፤ ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ ሲቪል ወርክስ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ እየሠራ ይገኛል ፡፡ 74.65 ኪ.ሜ የሚረዝመው መንገዱ መነሻውን የ አኝዋ ዞን መቀመጫ ከሆነችው አቦቦ ወረዳ በማድረግ አልዌሮ ግድብ ሰፈራ ፤ ቴኒ ፤ ዱቦንግ ፤ ፖታለም እንዲሁም ኩኩሪ የተሰኙ ከተሞችን ያቆራኛል፡፡ በአካባቢው የሚመረቱ በቆሎ ፤ ሩዝ እና ፍራፍሬ እንዲሁም የቅባት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በስፋት እና በአነስተኛ ወጪ ለማድረስ የመንገዱ መገንባት ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው፡፡ በአልዌሮ ወንዝ ላይ የተገነባው ሰው ሰራሹ አልዌሮ ግድብ በውስጡ የሚገኘውን ከፍተኛ የዓሣ ሀብት ክምችት በ ዘመናዊ መልክ አልምቶ ወደ የተለያዩ ገበያዎች ተደራሽ ለ ማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመንገዱ እውን መሆን አስተዋፆው የጎላ ነው፡፡ ከዚህም ባለፈ ግድቡ እሰከ 10 ሺህ ሄክታር መሬት እንዲያለማ ታልሞ የተገነባ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ሰፋፊ ሜካናይዝድ እርሻ ስራ ላይ የሚሰማሩ ኢንቨስተሮችን በመሳብ ረገድ ፋይዳው ከፍተኛ ነው፡፡ ቀደም ሲል ከ አጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 52 ኪ.ሜትሩ በ ጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና የጎን ስፋቱ ከ 5-6 ሜትር ያልበለጠ እጅግ ጠባብ ሲሆን ቀሪው ክፍል ምንም አይነት ተሸከርካሪ የሚያልፍበት አልነበረም፡፡ አሁን ላይ ግንባታው በፍፃሜ ምዕራፍ ላይ የሚገኘው መንገዱ በዞን ከተማ 21.5 ሜትር ፤ በወረዳ (ቀበሌ) 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት አለው፡፡ በመሆኑም የመንገዱ መገንባት ለዘመናት በምቹ መንገድ እጦት ምክንያት ተራርቀው የነበሩትን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በቅርበት ያገናኛል፡፡ የነዋሪውን የአመታት እንግልት ከማስቀረቱም በላይ የጉዞ ጊዜ እና ወጪን በእጅጉ ያሳጥራል፡፡ የዚሁ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው ቁቢቶ ማዞሪያ-ሜጢ 82ኪሜ የአስፋልት መንገድ ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል።

የጉደር - ጌዶ 54 ኪሎሜትር ከባድ የጥገና ግንባታ ፕሮጀክት
+2
የጉደር - ጌዶ 54 ኪሎሜትር ከባድ የጥገና ግንባታ ፕሮጀክት

የአዲስ-አምቦ-ባኮ-ነቀምት-አሶሳ የመንገድ አካል የሆነው የጉደር-ጌዶ 54 ኪሎሜትር ከባድ የጥገና ግንባታ ፕሮጀክት በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ከመንገድ ፕሮጀክቱ 92 በመቶ የሚሆነው የከባድ ጥገና ስራው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል። ቀሪ የፕሮጀክቱ ክፍል በያዝነው በጀት አመት ይጠናቀቃል። መንገዱ በአገልግሎት መደራረብ ሳቢያ በእጅጉ የተጎዳ የነበረ በመሆኑና ከሚያስገኘውም ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲሁም በየጊዜው እየጨመረ ከመጣው ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ምክንያት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጎ ጥገናው ተገባዷል። ለመንገዱ ከባድ ጥገና (431,596,708.75)ከአራት መቶ ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ብር በላይ ከመንግስት በጀት ወጪ ተደርጎበታል፡፡ ከፍተኛ ጥገናውን እያካሄደ የሚገኘው አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ዞሆንግሚ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ ሊሚትድ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ስራዎች ኮርፖሬሽን ትራንስፖርት ዲዛይንና ቁጥጥር ስራዎች ዘርፍ እየሰራው ይገኛል፡፡ በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይም አነስተኛ የአፈር ቁፋሮና ሙሌት፣ የሰብቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ንጣፍ ስራ፣ከፍተኛ የሆነ የአስፋልት ኦቨርሌይ ንጣፍ የውሃ ማስተላለፊያና የአቃፊ ግንብ ስራዎች በዋናነት ተሰርተዋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ጉደር፣ ባቢች፣ ጎሮሶል እና ጌዶ ከተሞችን በቅርበት በማገናኘት የአካባቢውን ህብረተሰብ ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡ እንዲሁም ከአሶሳ፣ነቀምት እና ባኮ የሚመጡ የእምነበረድ ምርትንና የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን እንደ ቡና፣ሰሊጥ፣ገብስ፣ጤፍና በቆሎ ማስተላለፊያ ኮሪደር ሆኖ ያገለግላል፡፡ በተጨማሪም በግንባታ ላይ ለሚገኘው የወንጪ የቱሪዝም ማዕከል መዳረሻ ለመሄድ እንደ አማራጭ መንገድ በመሆኑ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡

የኤፌሶን - መሃልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+8
የኤፌሶን - መሃልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

61ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የኤፌሶን-መሀልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በያዝነው በጀት አመት ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል ። በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የግንባታው አፈጻጸም 95 ከመቶ ላይ ደርሷል ። ቀሪ የፕሮጀክቱን ክፍል ለመፈጸም በትኩረት እየተሰራ ነው። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው የንኮማድ ሀገር በቀል የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የቁጥጥርና የማማከሩን ስራ ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነሪንግ እየሰራ ነው ፡፡ ለግንባታው ስራው የተመደበው አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ ሃምሳ ሁሉት ሚሊየን ብር /1,352,642538.82 /የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የኤፌሶን-መሃልሜዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በስፋት የአፈር ጥንካሬን መጨመር በሚያስችል (Mechanically Stabilized Earth Wall) ቴክኖሎጂን በመጠቀም ግንባታው የተከናወነ ሲሆን ይህም የመሬት መንሸራተትን በከፍተኛ ሁኔታ ለመከላከል የሚያግዝ የግንባታ ሂደት ነው፡፡ ይህ የግንባታ ቴክኖሎጂ ከዚህ በፊት በተለያዩ ፕሮጀክቶች ላይ ለመተግበር የተሞከረ ቢሆንም በዚህ ፕሮጀክት ላይ ግን በስፋት ጥቅም ላይ ውሏል ፡፡ የመንገዱ ግንባታ የኤፌሶን ከተማን ከመሀል ሜዳ ከተማ ጋር ያስተሳስራል ። በኤፍራታ ግድም ወረዳ እና በመንዝ ወረዳዎች የሚመረቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ለማውጣት፣ የጎላ ሚናን ያበረክታል ። በአካባቢው የሚገኘውን ለጎጎ ጥብቅ የማህበረሰብ ፓርክ የቱሪስት ፍሰቱን ለመጨመር እንዲሁም የመንገድ ትስስርን ለማሳደግ ይጠቅማል ፡፡ የጤና፣ ትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለማህበረሰቡ ተደራሸ በማድረግ በኩልም ላቅ ያለ ጠቀሜታ ያለው ነው።

የአሳይታ - አፈምቦ - ጅቡቲ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+3
የአሳይታ - አፈምቦ - ጅቡቲ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ጋር የሚያስተሳስረው የአሳይታ-አፈምቦ-ጅቡቲ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በመልካም እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። ከነባሩ የሚሌ-ጋላፊ-ጅቡቲ መንገድ በተጨማሪነት የሚገነባው የአሳይታ-አፈምቦ-ጅቡቲ ጠረፍ መንገድ በጥሩ አፈፃፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 65 ከመቶ ላይ ደርሷል፡፡ 49ኪ.ሜ የሚረዝመው ፕሮጀክቱ በእስከ አሁን ሥራ የአፈር ሙሌት እና ቆረጣ ሥራ፣ የስትራክቸር ሥራ፣ የሰብ ቤዝ ሥራዎች ተከናውኗል፡፡ የሶስት ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ የተካተተ ሲሆን የአንድ ድልድይ ግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል፡፡ ፕሮጀክቱ ሁለቱን ሀገራት በቅርበት ከማገናኘቱም በተጨማሪ የሀገራችንን የገቢ እና ወጪ ንግድ በማቀላጠፍ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ የመንገድ መሰረተ ልማቱ በክልሉ በስፋት የሚገኘውን የጨው ምርት ገቢ በማሳደግ ረገድም ጉልህ ድርሻ ያበረክታል። በአካባቢው እያደገ የመጣውን የመስኖ ግብርና ሥራ በማሳለጥ ዘርፉን በማሳደግ አስተዋፆው ከፍተኛ ነው፡፡ የትምህርት፣ የጤና እንዲሁም የተለያዩ ማሕበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን ይጨምራል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በሥፍራው የሚገኙትን ትንንሽ መንደሮች ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ እድል ይፈጥራል፡፡ ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በማሳጠር በቂ የሆነ የትራንስፖርት ምልልስ እንዲኖር በማድረግም ሚናው የጎላ ነው፡፡ መንገዱን በ 1,691,940,084.78 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ዘጠና አንድ ሚሊየን ዘጠኝ መቶ አርባ ሺህ/ ብር ወጪ እየገነባ የሚገኘው አገር-በቀሉ አሰር ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡ የግንባታው ወጪ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንገስት ነው፡፡ ይዲዲያ ኮንስትራክሽን ግንባታውን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ እየሰራ ይገኛል።

የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ
+4
የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ

የኦሮሚያ ክልልን ከሲዳማ ክልል ጋር በማገናኘት ከማዕከላዊ የሀገራችን ክፍል ጋር የሚያስተሳስረው የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ በመልካም አፈጻጸም ላይ ይገኛል ። በአሁኑ ወቅትም ከ6 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዪብ በላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ስራን በማገዳደብ ለአስፋልን ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ ተከናውኗል። የመሬት ድልዳሎ፣ የቱቦ ቀበራ፣ የሰብ ቤዝ ጨምሮ አስቸጋሪ የሚባሉ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ስራ በጥሩ መልኩ እየተሰሩ ይገኛል። የዚህ መንገድ ግንባታ 6 ድልድዮችን ያካተተ ሲሆን የሶስቱ ድልድዮች ስራም ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹም በግንባታ ሂድት ላይ ናቸው። 74 ኪሜ የሚረዝመው የኤዶ - ሴሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ አጠቃላይ አፈፃፀሙ በጥሩ ደረጃ ላይ ሲሆን በቅርቡ ወደ አሰፋልን ጥጣፍ ስራ ይሸጋገራል። በያዝነው በጀት አመት መጨረሻ ድረሰም 35ኪሎሜትሩ ሙሉ ለሙሉ በአሰፋልት ለመሸፍን በትኩረት እየተሰራ ነው። የአካባቢው ህብረተሰብ ለመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ የሚያደረገው ቀና ትብብርና ድጋፍ ለግንባታው መፋጠን የጎላ አስተዋጾ አብርክቷል። መንገዱን እየገነባ የሚገኘው ሀገር በቀሉ አለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ጎንድዋና ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነ ይገኛል። ለዚህ መንገድ ግንባታ የተመደበው 1,687,343,877.00 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሰማኒያ ሰባት ሚሊዮን ሶስት መቶ አርባ ሶስት ሺህ ብር ሲሆን የግንባታ ወጪውም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በወረዳ 12 ሜትር በገጠር ከ8-10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ አካባቢዎቹ በግብርና ምርታማነት በተለይም በስንዴ፣ገብስ እና ለሀገራችን የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ረገድ ዋነኛ የሆነው የጫካ ቡናም በስፋት ይመረትበታል ። ይህ የመንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ፍሰትን ምቹ በማድረግ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል በተጨማሪም የጤና፣ የትምህርት እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲስፋፉ እና በአካባቢው የሚገኙ ትንንሽ ከተሞች እንዲያድጉ ከማድረግ አኳያ የሚኖረው ፋይዳም ከፍተኛ ነዉ፡፡ ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በማሳጠር በቂ የሆነ የትራንስፖርት ምልልስ እንዲኖር በማድረግም ሚናው የጎላ ነው።

photo_2021-10-21_11-41-25.jpg0.80 KB

photo_2021-10-21_11-41-38.jpg1.14 KB

photo_2021-10-21_11-42-04.jpg0.99 KB

photo_2021-10-21_11-42-41.jpg0.58 KB

photo_2021-10-21_11-43-31.jpg0.49 KB

የኤዶ - ሶሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ

ዲማ ራድ ብሪጅ

የሚረዝምው የጅግጅጋ-ገለለሽ ኮንትራት ሁለት እና ሶስት የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+4
የሚረዝምው የጅግጅጋ-ገለለሽ ኮንትራት ሁለት እና ሶስት የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

110 ኪሎ ሜትር የሚረዝምው የጅግጅጋ-ገለለሽ ኮንትራት ሁለት እና ሶስት የአስፋልት መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ ባሳለፍነው በጀት አመት የተጀመረው ይህው ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ ትንንሽና መካከለኛ ማፋሰሻዎችን እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎችን አካቶ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቤአይካ ጄኔራል ቢዝነስ ፒኤልሲ ነው። የግንባታዉ ሙሉ ወጪም (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃያስምንት ሚሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ አራት ሺህ ብር በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ አጠቃላይ ስራውን በሶስት ዓመት ተኩል ዉስጥ ለማጠናቀቅ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር የስምምነት ውል የተፈራረመው ይህ የስራ ተቋራጭ ግንባታውን ቀድሞ በመጀመር አጠቃላይ አፈጻጸሙ በአሁኑ ሰዓት 20 በመቶ ላይ ደርሷል ። የመንገዱን የማማከርና የቁጥጥር ስራ ሲ ቴክ ኢንጂነሪንግ ፒኤልሲ (C Tech Enginnering P.L.C) እየሰራ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ በዞን ከተማ 21 ሜትር እና በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ መስመሩ ከሚያስተናግደው የተሸከርካሪ ብዛት፣ ማህበራዊና ኢኮኖማዊ ፋይዳ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ እድገት ጋር ታልሞ በአስፋልት ደረጃ እንዲገነባ እየተደረገ ነው። ግንባታው ሲጠናቀቅ የገለለሽ ፣ ደጋሃመድ እና እንሰግድ አካባቢዎችን ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጅጋ ከሚወስደው ዋና መንገድ ጋር በማስተሳሰር ከዚህ ቀደም በአካባቢው ይከሰት የነበረውን የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ ያስችላል፡፡ ከጅግጅጋ ወደ ደነን የሚወስድ ተለዋጭ መንገድ ስለሚኖረው የአካባቢዉን ማህበረሰብ አማራጭ የትራንስፖርት ተጠቃሚ እንዲሆን ያደርገዋል። በተጨማሪም የጤና ፣ የትምህርት እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲስፋፉ እና በአካባቢው የሚገኙ ትንንሽ ከተሞች እንዲያድጉ ከማድረግ አኳያ የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ነዉ፡፡ ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በማሳጠር በቂ የሆነ የትራንስፖርት ምልልስ እንዲኖር ያደርጋል።