ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 369 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 754 في فئة النقل والمرتبة 2 531 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 369 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 19، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 40.59‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 423 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 060 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 369
المشتركون
+1924 ساعات
+677 أيام
+11930 أيام
أرشيف المشاركات
በከባድ የቋጥኝ ድንጋይ መንሸራተት ምክንያት ተዘግቶ የቀየው የአዲስ አበባ ጎጃም መንገድ በከፊል ተጠግኖ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ለትራንስፖርት ክፍት ሆኗል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም በሚወስደው መንገድ ዓባይ በረሃ በመባል በሚታወቀው አካባቢ ልዩ ስሙ ፍልቅልቅ በሚባለው ስፍራ ላይ ያጋጠመውን ከባድ የድንጋይ መንሸራተት ናዳ ክፍት ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ ነው። ችግሩን ለመፍታት አሰቸኳይ ጥገና የሚያደርግ ግብረ ሃይል ፣ በርካታ ማሽነሪና የሰው ሀይል በስፍራው ከሚገኘው አሰቸኳይ ጥገና ቡድን ጋር በጋራ በማሰማራት ፣ በተደረገው ጥረት መንገዱን ፣የዘጋውን ቋጥኝ ድንጋይ በደማሚትና በማሽነሪዎች በመታገዝ የመንገዱን ዋና ክፍል ፣በከፊል ነፃ ለማድረግ ተችሏል። ይህን ተከትሎም ከዛሬ ጀምሮ አንድ መኪና ከግራና ከቀኝ በየተራ ተሽከርካሪዎች ማስተላለፍ ጀምሯል። የመንገዱን ቀሪ ክፍል ከዘጋው ቋጥኘ ድንጋይ ነጻ ለማድረግና መስመሩን ወደ ነበረበት ለመመለስ ሲባል የትራንስፖርት ፍሰቱን ለሰዓታት በመዝጋትና በመከፈት ቀሪ ስራዎቹ እንደሚከናወኑ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አሳስቧል። በአካባቢው (በአባይ በርሃ) መንገድ ላይ ለቀናት የቆሙ በርካታ ተሽከርካሪዎች በመኖራቸው የትራፊክ ፍሰቱ እስኪቃለል በሁለቱም አቅጣጫ ከሚገኙ ከተሞች ጉዞ ያልጀመሩ አሽከርካሪዎች እስከ ነገ ድረስ ባይንቀሳቀሱ ይመከራል። እንደሚታወቀው የአባይ በረሃ አካባቢ የሚንሸራተት ጠመዝማዛና ናዳ የሚበዛበት በመሆኑ እና በዚሁ ስፍራ ከወትሮ የተለየ ግዙፍ ናዳ መከሰቱ ስራውን እጅግ አክብዶታል ። ይሁን እንጂ ኢመባ በቀጣይ ቀናት ይህን ጥረቱን በመቀጠል የትራንስፖርት ፈሰቱን ሙሉ ለሙሉ ወደ ነበረበት እንደሚመለስ ያረጋግጣል።

ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም በሚወስደው መንገድ ዓባይ በረሃ በመባል በሚታወቀው አካባቢ ልዩ ስሙ ፍልቅልቅ በሚባለው ስፍራ ላይ ያጋጠመውን ከባድ የድንጋይ መንሸራተት ናዳ ክፍት ለማድረግ ርብርቡ ተጠናክሮ
+5
ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም በሚወስደው መንገድ ዓባይ በረሃ በመባል በሚታወቀው አካባቢ ልዩ ስሙ ፍልቅልቅ በሚባለው ስፍራ ላይ ያጋጠመውን ከባድ የድንጋይ መንሸራተት ናዳ ክፍት ለማድረግ ርብርቡ ተጠናክሮ ቀጥሏል። እስከ ነገ ድረስም መስመሩን ለመክፈት ጥረት እየተደረገ ነው። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስቸኳይ ጥገናው ተጠናቆ መንገዱ ክፍት መሆኑን የሚያሳውቅ ይሆናል ። በመሆኑም አሽከርካሪዎች እና የመንገዱ ተጠቃሚዎች ይህን የባለስልጣን መስሪያቤቱን መረጃ ሳታረጋግጡ እንቅስቃሴ እንዳታደርጉ ያሳስባል ። ከቀናት በፊት በስፍራው የሚንሸራተት ጠመዝማዛና ናዳ በሚበዛበት በዚሁ ስፍራ ከወትሮ የተለየ ግዙፍ ናዳ መከሰቱ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ኢመባ ችግሩን ለመፍታት በስፍራው አሰቸኳይ ጥገና የሚያደርግ ግብረ ሃይል፣ በርካታ ማሽነሪና የሰው ሀይል በስፍራው ከሚገኘው አሰቸኳይ ጥገና ቡድን ጋር በጋራ በማሰማራት በተደረገው ጥረት መንገዱን የዘጋውን ቋጥኘ ድንጋይ በደማሚትና በማሽነሪዎች በመታገዝ አብዛኛው የመንገዱን ክፍል ነጻ ለማድረግ ተችሏል። ቀሪ ስራዎችን አጠናቆ መስመሩን ክፍት ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው።

ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም በሚወስደው መንገድ ዓባይ በረሃ በመባል በሚታወቀው አካባቢ ልዩ ስሙ ፍልቅልቅ በሚባለው ስፍራ ላይ ዛሬ (በ6/12/2013) ሌሊቱን ባጋጠመ የድንጋይ መንሸራተት ናዳ የትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጓል አጋጥሟል። ይህን ችግር በቶሎ ለመቅረፍም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በስፍራው አሰቸኳይ ጥገና የሚያደርግ ግብረ ሃይል በመላክ በስፍራው ከሚገኘው አሰቸኳይ ጥገና ቡድን ጋር በጋራ እየሰሩ ሲሆን ስራው ተጠናቆ መንገዱ ክፍት ሲደረግ የሚያሳውቅ መሆኑን ይገልፃል።

በባኮ-ሻምቡ የመንገድ ፕሮጀክት ላይ ያጋጠመውን የመሬት መንሸራተት አደጋን ተከትሎ የተፈጠረውን የትራፊክ መስተጓጉል ለመፍታት እየተሰራ ነው። በአከባቢው ያለው የአፈር አይነት ለመሬት መንሸራተት ተጋላ
+4
በባኮ-ሻምቡ የመንገድ ፕሮጀክት ላይ ያጋጠመውን የመሬት መንሸራተት አደጋን ተከትሎ የተፈጠረውን የትራፊክ መስተጓጉል ለመፍታት እየተሰራ ነው። በአከባቢው ያለው የአፈር አይነት ለመሬት መንሸራተት ተጋላጭ በመሆኑ እንዲሁም ሰሞኑን የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ከባኮ 26 ኬሎሜትር ርቅት ላይ አላቱ መዳረሻ ሶስት ቦታዎች ላይ የመሬት መንሸራተት አደጋ አጋጥሟል። ይህን ተከትሎም በትራፊክ ፍሰቱ ላይ መጠነኛ መሰተጓጎል ተከስቷል ። ይህን ችግር በቶሎ ለመቀረፍም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በስፍራው አሰቸኳይ ጥገና በማድረግ ላይ ይገኛል ። በአሁኑ ወቅት የትራፊክ ፍሰቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ እየሰራ ነው። አሰቸኳይ ጥገናው በፍጥነት እየተከናወነ ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም የትራንስፖርት ፍሰቱ መንቀሳቀስ ጀምሯል። ኢመባ ቀደም ብሎም በአካባቢው ያለው የመሬት አቀማመጥ እና ከባድ ዝናብ የሚከሰት መሆኑን በመረዳት ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ ዝርዝር ጥናቶችን ተግባራዊ ለማድረግ ሲሰራ ቆይቷል። በቀጣይም የተጠኑ ጥናቶችን እና መሰል መፍትሄዎችን ተግባራዊ በማድረግ ክስተቱን በዘላቂነት ለመግታት በጥናቱ ላይ የተመላከቱት መፍትሄዎችን ተግባራዊ ያደርጋል::

የአሶሳ - ዳለቲ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የስራ እንቅስቃሴ
+4
የአሶሳ - ዳለቲ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የስራ እንቅስቃሴ

የአሶሳ-ዳለቲ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አሰፋልት ንጣፍ ስራ ተሸጋገረ ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ስራን ፣ የድልድይ ፣ የተፋሰስ ስራዎችን እና የመንገድ ዳር የትራፊክ ምልክቶች ግንባታን እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎችን አካቶ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 52 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ በአካባቢው የነበረው የፀጥታ ችግር በግንባታ ሂደቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ የነበረ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት ችግሩ በመቀረፉ ፕሮጀክቱን በተገቢው የጥራት ደረጃ በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ 69 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ፣ ግንባታውን ከመንግስት በተመደበ ከ731 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማከናወን ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ እንይ ኮንስትራክሽን ነው። የግንባታውን ቁጥጥርና የማማከር ሥራው ደግሞ ሃምዳ በተባለ ሀገር በቀል አማካሪ ድርጅት እየተሰራ ይገኛል ፡፡ በአካባቢው ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነት ያልነበረው በመሆኑ ፕሮጀክቱ በአካባቢው ያለውን የትራፊክ ፍሰትና የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ በአስተማማኝ መልኩ ለማስተናገድ ወሳኝ ሚናን ያበረክታል ። መንገዱ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ፤ ከአሶሳ - ኦዳቢልዱ - ዳለቲ ያለውን የትራንስፖርት ፍሰት ለማሳለጥ ያስችላል፡፡ ከዚህም ባሻገር በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ የሰሊጥ ፣ የአትክልት ፣ የተለያዩ አዝዕርቶችና የመአድን ምርት መገኛ በመሆኑ እነዚህን የግብርና ምርቶችና የኢንዱስትሪ ግብዓቶች በቀላሉ ለገበያ ለማቅረብ የሚደረገውን የትራንስፖርት ፍሰት ቀልጣፋ ያደርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞች እና አመራሮች በመንገድ ልማት ዘርፍ የስነ -ሕይወት መመናመን ይብቃ ፤ኑ ኢትዮጵያን እናልብሳት በሚል መሪቃል ዛሬ የሁለተኛ ዙር የችግኘ ተከላ መርሃግብር አከናወኑ። የዋናው መስሪያ ቤት፤ የአለም ገና ማሰለጠኛ እና የምርምር ማዕከላት ሰራተኞች ፣ አመራሮች ናቸው በጋራ በመሆን 10ሺህ ችግኞችን ዛሬ በሞጆ -ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ የአረንጓዴ ስፍራ ክልል ውስጥ የተከሉት። በተመሳሳይ የበለስልጣን መስሪያ ቤታችን ሁሉም ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላትም ችግኞችን በየአካባቢያቸው መትከላቸውን ቀጥለዋል። ኢመባ ባለፋት ዓመታት ጀምሮ ሀገራዊ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ሀላፊነቱን ይበልጥ እየተወጣ ነው ። የተቋሙ ሰራተኞችም አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ በመሆኑና ሀገራዊ ባህል እየሆነ በመምጣቱም ተሳትፍና ንቃቱ በማደጉ ደስተኞች እንደሆኑም ተናግረዋል ። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። እንደ ተቋም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግ ግብረ -ሀይል በመቋቋሙምም የመጽደቅ ምጣኔው አጥጋቢ ውጤት እንዲገኘ አስችሏል ። በተለይም የመንገድ ግንባታን ተከትሎ በደኖች ላይ ጉዳት እንዳይከሰት የመጠንቀቅ ፥ የዲዛይን ስራዎችን ታሳቢ አድርጎ ቀድሞ መስራት እንዲሁም ተቋራጮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካለት የችግኘ ተከላ መርሃ -ግብርን አጠናክረው እንዲቀጥሉ በመደረጉ ውጤት እየተገኘ ነው። የዘንድሮ መሪ ቃልም የመንገድ ግንባታ ስነ ህይወት ላይ ተጽህኖ ሳያሳድርስ ተመጋግበው እውን እንዲሆኑ ታስቦበት በዘላቂነት የሚተገበር ነው ። ባለፉት ዓመታት በኢመባ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከ3ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። ኢመባ የችግኝ ተከላ-መርሃ ግብሩ ተገቢውን ሳይንሳዊ ሂደት ጠብቆ እንዲተከል፤ ከአካባቢው ስን- ምህዳር ጋር የሚጣጣሙ ሀገር በቀል ችግኞች እውን እንዲሆኑ፤ ከተተከሉም ብኋሏ የመጸደቅ ምጣኔው መቶ በመቶ እንዲረጋገጥ፤ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ ጋር በትብብር መስራቱ የዘንደሮውን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ልዩ ያደረገዋል።

Training: Superpave Asphalt Mix Design Start Date: August 26 Instructor: Dr. Habtamu Melese Link: https://www.etonline.edu.et/courses/course/superpave-asphalt-mix-design/

102 ኪ. ሜትር የሚረዝመው የሀገረ- መኮር - ቁንዲ ኮንትራት ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አስፋልት ማልበስ ስራ ተሸጋገረ ። እስካሁን በተከናወነው ስራም አስር ኪሎ ሜትሩ በአሰፋልት ተሸፍኗል ። አጠቃላይ አፈጻጸሙም 70 ከመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን የአፈር ሙሌትና፣ ድልዳሎ፣ የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ የሰብ ቤዝ ስራ እንዲሁም የቤዝ ኮርስ ስራ በጥሩ መልኩ መካሄዱን ቀጥሏል ። የሀገረመኮር - ቁንዲ ኮንትራት ሁለት የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ከ 1ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተሸፈነ ያለው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ግንባታውን የሚያካሂደው ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካንፓኒ/ cccc/ የተባለ አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን ስታድያ አማካሪ ድርጅት ደግሞ የማማከርና ቁጥጥር ስራውን እየሰራ ነው። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ በወረዳ 19 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር ሲሆን በገጠር 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው። በሶማሌ ክልል ሊበን ዞን ውስጥ የሚገኘው የሀገረመኮር - ቁንዲ ኮንትራት ሁለት መንገድ ከዚህ ቀደም የበጋ መንገድ ደረጃ (dry weathered road) የነበረና ለትራንስፖርት ምልልስ እጅግ አሰቸጋሪ የነበረ ነው። መስመሩ ካለው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ አድገት አንጻር በአስፋልት ደረጃ እየተገነባ ይግኛል ። በተጨማሪም ግንባታው በውስጡ እግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ ያካተተም ይሆናል ፡፡ የሀገረመኮር - ቁንዲ ኮንትራት ሁለት አስፋልት መንገድ ለአካባቢው ህብረተሰብ የስራ እድልን በመፍጠር ወጣቶችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። የጨረርቲ ሀገረ መኮር ጎርዳምቤሎ የመንገድ ክፍል አካል የሆነው የሀገረመኮር - ቁንዲ ኮንትራት ሁለት የአስፋልት መንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን ከፍተኛ የግብርና ምርቶች እንዲሁም የቁም እንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ አምራች እና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞች እና አመራሮች በመንገድ ልማት ዘርፍ የስነ -ሕይወት መመናመን ይብቃ ፤ኑ ኢትዮጵያን እናልብሳት በሚል መሪቃል ዛሬ ችግኘ ተከሉ። የዋናው መስሪያ ቤት፤ የአለም ገና ማሰለጠኛ እና የምርምር ማዕከላት ሰራተኞች አመራሮች ናቸው በጋራ በመሆን 10ሺህ ችግኞችን ዛሬ በሞጆ -ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ የአረንጓዴ ስፍራ ክልል ውስጥ የተከሉት። በተመሳሳይ የበለስልጣን መስሪያ ቤታችን ሁሉም ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላትም ችግኞችን ዛሬ ተክለዋል። በመርሃ -ግብሩ ላይ የተገኘት የተቋሙ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ በቀለ ባለፋት ዓመታት ሀገራዊ አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ የተቋሙ መላው ሰራተኛ በመሳተፍ ሀላፊነታቸውን እንደተወጡ ተናግረዋል። የተቋሙ ሰራተኞች በበኩላቸው አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ሀገራዊ ባህል እየሆነ በመምጣቱ ተሳትፍና ንቃቱ በማደጉ ደስተኞች እንደሆኑም ተናግረዋል ። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱርአማን በበኩላቸው ባለፋት ዓመታት መላው ሰራተኛ በዚህ ሀገራዊ ሀላፊነት ላይ በንቃት በመሳተፍ አሻራ ማኖሩን ቀጥሏል ብለዋል። በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እንደተቋም የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግ ግብረ -ሀይል በመቋቋሙም የመጽደቅ ምጣኔው አጥጋቢ ውጤት ማስገኘቱን ገልጸዋል። በተለይም የመንገድ ግንባታን ተከትሎ በደኖች ላይ ጉዳት እንዳይከሰት የመጠንቀቅ ፥ የዲዛይን ስራዎችን ታሳቢ አድርጎ ቀድሞ መስራት እንዲሁም ተቋራጮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካለት የችግኘ ተከላ መርሃ -ግብርን አጠናክረው እንዲቀጥሉ በመደረጉ ውጤት እየተገኘ መሆኑን ምክትል ዋና የዳይሬክተሩ ተናግረዋል። የዘንድሮ መሪ ቃልም የመንገድ ግንባታ ስነ ህይወት ላይ ተጽህኖ ሳያሳድርስ ተመጋግበው እውን እንዲሆኑ ታስቦበት በዘላቂነት የሚተገበር ነው ብለዋል ። ባለፉት ዓመታት በኢመባ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከ3ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። ኢመባ የችግኝ ተከላ-መርሃ ግብሩ ተገቢውን ሳይንሳዊ ሂደት ጠብቆ እንዲተከል፤ ከአካባቢው ስን- ምህዳር ጋር የሚጣጣሙ ሀገር በቀል ችግኞች እውን እንዲሆኑ፤ ከተተከሉም ቡኋሏ የመጸደቅ ምጣኔው መቶ በመቶ እንዲረጋገጥ፤ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ ጋር በትብብር መስራቱ የዘንደሮውን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ልዩ ያደረገዋል።