en
Feedback
ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

Open in Telegram

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ውስጥ የተጻፉ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸውና አስገራሚ ታሪካቸው ዓመቱን ሙሉ ምንም ሳይቋረጥ በየቀኑ ይነገርበታል! ለአሥትያየትዎ @abitago

Show more
1 210
Subscribers
+124 hours
-17 days
-530 days
Posts Archive
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን ጳጉሜን 2-ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት የጻፈለት የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ቲቶ ዐረፈ፡፡ ይህም ቅዱስ ሐዋርያ ቀርጤስ ከሚባል አገር ሲሆን ለዮናናውያን ወገን ለሆነ ለአገረ ገዥው እኅት ልጇ ነው፡፡ ሐዋርያው ከታናሽነቱ ጀምሮ የዮናናውያንን ትምህርትና ፍልስፍና ተምሮ እጅግ አዋቂ ሆነ፡፡ በጠባዩም ቅን፣ ሥራው ያማረ፣ ለድኆችና ጦም አዳሪዎች መራራት የሚወድ ነው፡፡ ከዕለታትም በአንዲቱ ዕለት ‹‹ቲቶ ሆይ ስለነፍስህ ድኅነት ተጋደል፣ ይህ ዓለም አይጠቅምምና›› የሚለውን በራእይ ተመለከተ፡፡ ምን እንደሚሠራም አላወቀምና ከእንቅልፉ በነቃ ጊዜ ደነገጠ፡፡ ከዚህም በኋላ የጌታችንን ተአምራት እያነሡ ሰዎች ሲነጋገሩ የአክራጥስ መኮንን ሰማ፡፡ መኮንኑም የሰማውቸው የጌታችን ተአምራቶች እውነት መሆናቸውን ወይም የሥራይ ሥራ እንደሆነ ያረጋግጥ ዘንድ የሚልከውን ብልህና አዋቂ ሰው ፈለገ፡፡ ከእርሱ የሚሻል አዋቂ የለምና መኮንኑ የእኅቱን ልጅ ቲቶን መርጦ ስለ ጌታችን ተአምራቶች ጥልቅ ምርምር ያደርግለት ዘንድ አዘዘው፡፡ ቅዱስ ቲቶም ከይሁዳ ምድር በደረሰ ጊዜ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ድንቅ ድንቅ ተአምራት በዐይኑ ተመለከተ፡፡ ትምህቶቹንም ሰማና የጌታንን ትምህርቶች ከዮናናውያን ትምህርትና ፍልስፍና ጋር አነጻጸረ፡፡ የዮናናውያንም ትምህርት የቀናች እንዳልሆነች ለይቶ ዐወቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ቲቶ በጌታችን አመነ፣ ደቀ መዝሙሩም ሆኖ ተከተከለው፡፡ ቅዱስ ቲቶ ወደ እናቱ ወንድም ወደ አገረ ገዥው መልአክትና ላከና ጌታችን የሚያደርጋቸው ተአምራቶችና የሚያስተምራቸው ትምህርቶች እውነት እንደሆኑ ነገረው፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ቲቶን ቁጥሩን ከ72ቱ አርድእት ወገን አደረገው፡፡ ቅዱስ ቲቶም ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያት ጋር የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተቀብሎ በሀገሮች ሁሉ ዞሮ የከበረች ወንጌልን አስተማረ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በጌታችን ተጠርቶ ወንጌልን መስበክ ሲጀምር ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን ተከትሎት በብዙ አገሮች ወንጌልን ሰበከ፡፡ የከበረ ቅዱስ ጳውሎስም በሮሜ ከተማ ሰማዕት ከሆነ በኋላ ቅዱስ ቲቶ ወደ ሀገረ አክራጥስ ተመለሰ፡፡ በዚያም ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው፡፡ በዙሪያቸው ባሉ ሀገሮችም እንዲሁ አደረገ፡፡ በመጨረሻም ሐዋርያዊ አገልግሎቱን ፈጽሞ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሄደ፡፡ ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ከ470,000 በላይ ክርስቲያኖችን በግፍ የገደለውን የሃዲውን ንጉሥ የዲዮቅልጥያኖስን መንግሥት ካጠፋ በኋላ የታሰሩትን ቅዱሳን አስፈትቶ በሚገዛቸው አገሮች ሁሉ አብያተ ክርስቲያናትን አሳነጸ፡፡ ይልቁንም ቁስጥንጥንያ መናገሻ ከተማው ናትና ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን ካሳነጸባት በኋላ የቅዱሳን ሐዋርያን እና የቅዱሳን ሰማዕታትን ሥጋቸውን ከየቦታው እየሰበሰበ በክብር በማምጣት በውስጣቸው አኖረ፡፡ የሐዋርያውም የቅዱስ ቲቶ ሥጋ አቅራጥስ በሚባል አገር መኖሩን ሲሰማ የካህናት አለቆችን ከብዙ ገንዘብና ሠራዊት ጋር ልኮ ወደ ቁስጥንጥንያ በክብር አስመጣው፡፡ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ የቅዱስ ቲቶ ሥጋ አቅራጥስ በሚባል አገር አፍልሶ ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ በክብር ካስመጣው በኋላ ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርቶለት የቅዱስ ቲቶን ሥጋ በውስጧ በክብር አኖረ፡፡ ከሥጋውም ብዙ አስገራሚ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ይኸውም የሆነው ታኅሣሥ 18 ቀን ነው፡፡ የቅዱሱን ሥጋ ከከበረ እምነበረድ በተሠራው ሣጥን ውስጥ አድርገው ተሸክመው ሲወስዱ ከሰው ግፊያ የተነሣ ሣጥኑ ወድቆ የአንዱን ሰው እግር ሰበረው፡፡ እርሱም የቅዱስ ቲቶ ሥዕል ካለበት የመብራት ቅባት ላይ ወስዶ የተሰበረ እግሩን ቀባውና ሲያመው እየጮኸ አሰረው፡፡ ወደ ቤቱም መሄድ ባልቻለ ጊዜ የቅዱስ ቲቶ ሥጋ ሣጥን ባለበት በዚያው አደረ፡፡ በማግሥቱም አይቶ መድኃኒት ሊያደርግ ተሰብሮ የታሰረ እግሩን በፈታው ጊዜ ከቶ ምንም ምን ሕማም እንዳላገኘው ደህና ሆነ፡፡ ለምልክት ይሆን ዘንድ ግን ደም ነበረበት፡፡ ሰውየውም ተነሥቶ እየሮጠ በመሄድ የተደረገለትን ተአምር ለሰው ሁሉ ተናገረ፡፡ ያዩትም ሁሉ የቅዱስ ቲቶን አምላክ ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ የሐዋርያ የቅዱስ ቲቶ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን እንኳን ለወርኀ ጳጉሜን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! + ጳጉሜን 1-የወንጌላዊው የቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ዑቲኮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ + ሰማዕቱ አባ ብሶይ ዐረፈ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ዑቲኮስ፡- የወንጌላዊው የቅዱስ ዮሐንስ ረድእ የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ዑቲኮስ ዐረፈ፡፡ ይህም ቅዱስ ዑቲኮስ ወንጌላዊውን ቅዱስ ዮሐንስን ሲያገለግለው ኖረ፡፡ በኋላም ወደ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዘንድ በመሄድ እርሱንም አገለገለው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በጌታችን ስም እንዲሰብክ አዘዘው፡፡ ቅዱስ ዑቲኮስም ለአረማውያን የክርስቶስን አምላክነት በመስበክ ብዙዎችን ወደእውነት መልሷቸዋል፡፡ ብዙዎችን አስተምሮ ጌታችንን ወደማወቅና ወደማመን ከመለሳቸው በኋላ አጠመቃቸው፡፡ ከዚህም በኋላ የጣዖታት ቤቶችን አፈራርሶ አብያተ ክርስቲያናትን ሠራ፡፡ በዚህም ምክንያት ከሃድያን የሆኑ ክፉዎች ይዘው ብዙ አሠቃዩት፡፡ በጽኑ እየገረፉ በእስር ቤት አያቆዩት ነገር ግን የታዘዘ መልአክ ወደ እስር ቤቱ እየመጣ ሰማያዊ ምግብ ይመግበው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ዑቲኮስን ከእስር ቤት አውጥተው በእሳት ውስጥ ጣሉት ነገር ግን ጌታችን መልአኩን ልኮ አድኖታልና እሳቱ ምንም አልነካውም፡፡ ዳግመኛም ለተራቡ አንበሶች ሰጡት እነርሱም እንደበጎች ሆኑለት፡፡ ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ እየመራውና እያጽናናው ወደ ቁስጥንጥንያ አገር ሄደ፡፡ በዚያም ተጋድሎውንና አገልግሎቱን ፈጽሞ በበጎ ሽምግልና ኖሮ ዐረፈ፡፡ የሐዋርያው ቅዱስ ዑቲኮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ + + + አባ ብሶይ ሰማዕት፡- ከአንጾኪያ አገር ከታላላቅ ወገኖች የተገኘ ሰማዕት ነው፡፡ እርሱም ስለ ሃይማኖቱ ጽናትና ስለ ዕውቀቱ ቅስና ተሾመ፡፡ ወንድሙ አባ ሖርና እናቱ ወደ ግብፅ አገር ሄደው በሰማዕት ካረፉ በኋላ እርሱም ተነሥቶ ወደ እስክንድርያ ሄደ፡፡ ንብረቱን ሁሉ ለድኆችና ጦም አዳሪዎች ሰጥቶ በትሩን ብቻ ይዞ ነው ወደ ሰማዕትነት የሄደው፡፡ እስክንድርያም በደረሰ ጊዜ የእናቱና የወንድሙ ሥጋ ወዳለበት ቦታ ሰዎች መርተው አደሱት፡፡ የእናቱንና የወንድሙንም በድን ባየ ጊዜ ሰማዕት በመሆን ከእነርሱ ስለተለየ መሪር ልቅሶን አለቀሰ፡፡ ወዲያውም ወደ ከሃዲው መኮንን ዘንድ ሄዶ ከፊቱ በመቆም የክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ መኮንኑም አባ ብሶይ የአባ ሖር ወንድም መሆኑን ዐወቀ፡፡ ወዲያውም ታላቅ የድንጋይ ምሰሶ በሆዱ ላይ በማቆም በእጅጉ አሠቀየው፡፡ በዚሁም ቅድስት ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ሰማዕትነቱን ፈጸመ፡፡ ሥጋውንም ከእናቱና ከወንድሙ እንዲሁም ከሌሎች 88 ሰማዕታት ሥጋ ጋር በአንድነት ያቃጥሉት ዘንድ መኮንኑ አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም የቅዱሳኑን ሥጋ በእቶን እሳት ውስጥ ጨመሩት ነገር ግን የእቶኑ እሳት የቅዱሳኑን ሥጋ ማቃጠል አልተቻለውም፡፡ መእመናንም መጥተው የመከራው ዘመን እስኪያልፍ የቅዱሳኑን ሥጋ በክብር አቆይተው በመጨረሻ አብያተ ክርስቲያናት ሠርተውላቸው በውስጣቸው አኖሩ፡፡ ከቅዱሳኑም ሥጋ የተለያዩ ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተገለጡ፡፡ የአባ ብሶይ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

ትወቅሷቸው ዘንድ፤ የእኔንም ማንነት ትነግሯቸው ዘንድ› ብሎ ጌታችን ሥዕሏን ላካት፡፡ የቅርጺቱም ሥዕል ይህንን ከጌታችን ከሰማችና ከተላከች በኋላ ሁላችንም እያየናት ሄደችና ወደ አብርሃም መቃብር ደርሳ በውጭ ቁማ ጠራችው፡፡ ወዲያውኑም ከሦስቱ አርእስተ አበው ጋር 12ቱ ወጡና ‹ከእኛ ውስጥ ወደማን ነው የተላክሽ?› አሏት፡፡ ሥዕሊቱም ‹ወደ ሦስቱ የአባቶች አለቆች ነው እናንተ ግን እስከ ትንሣኤ ሙታን ድረስ ተኙ› አለቻቸውና ተመልሰው አንቀላፉ፡፡ እነኛ ሦስቱ አባቶች የካህናት አለቆችና እኛ ወዳለንበት ከቅርጺቱ ሥዕል ጋር አብረው መጥተው ወቀሷቸው፡፡ የጌታችንንም ማንነት አስረዷቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን አባቶችን ‹ወደቦታችሁ ሂዱ› አላቸውና ተመለሱ፡፡ የቅርጺቱንም ሥዕል ‹ወደቦታሽ ተመለሽ› አላትና ወደቀደመው አኗኗሯ ተመለሰች፡፡ ይህንንም አይተው የካህናት አለቆች አላመኑም፤ ሌላም ብዙ ነገር አለ ብነግርህ ግን መወሰን አትችልም ነገር ግን ለብልህ ጥቂት ትበቃዋለች…›› እያለ እንድርያስ በሊቀ ሐመር ለተመሰለ ጌታችን በዝርዝር ነገረው፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ማነጋገሩን ገታ አደረገውና ራሱን እንደሚያንቀላፋ አደረገ፡፡ እንድርያስም አብሮ አንቀላፋ፡፡ ጌታችንም እንድርያስንና ደቀ መዛሙርቱን እንዲሸከሟቸውና ሊገቡበት ወደሚሹት አገር አድርሰው በውጭ እንዲያኖሯቸው መላእክቱን አዘዛቸው፡፡ እንድርያስም በነቃ ጊዜ የከተማን በር ተመለከተ፡፡ በየብስም ላይ እንዳለ ዐውቆ ደነገጠ፡፡ እጅግም አደነቀና ደቀ መዛሙርቱን ቀሰቀሳቸውና ‹‹በባሕር ላይ ሳለን ጌታችን መልኩን ለውጦ እንደ ሰው ሆኖ ይዞን መጥቷል›› ብሎ በሥዕሊቱም ያደረገውን ተአምር ነገራቸው፡፡ ደቀ መዘሙርቱም እንድርያስን እንዲህ አሉት፡- ‹‹እኛም እንጂ ደግሞ በጌትነቱ ዙፋን ላይ ሆኖ የመላእክት ሠራዊት ሁሉ በዙሪያው ሆነው ጌታችንን አየነው፡፡ አብርሃም፣ ይስሐቅና ያዕቆብን ቅዱሳንንም ሁሉ አየናቸው፡፡ ንጉሥ ዳዊትም በመሰንቆ ይዘምር ነበር፡፡ እናንተንም 12 ሐዋርያት በፊቱ ቆማችሁ 12ቱንም የመላእክት አለቆች በፊታችሁ ሌሎች መላእክት በኋላችሁ ሆነው አየናችሁ፡፡ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስንም መላእክቱን ‹የሚሏችሁን ሁሉ ሐዋርያትን ስሟቸው› ብሎ ሲያዛቸው ሰማን›› አሉት፡፡ እንድርያስ ከደቀ መዛሙርቱ ይህንን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ታላቅ ምሥጢር ያዩ ዘንድ ደቀ መዛሙርቱ የተገባቸው ሆነው ስላገኛቸው ተደሰተ፡፡ ከዚህም በኋላ እንድርያስ ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከእኛ ከባሮችህ ሩቅ እንዳልሆንህ ዐወቅሁ ነገር ግን በመርከብ ላይ እኔ እንዳስተምረው ሰው መስለህ በድፍረት ተናግሬሃለሁና ጌታዬ ይቅር በለኝ›› አለ፡፡ ጌታችንም ያንጊዜ ለእንድርያስ ዳግመኛ ተገለጠለትና ‹‹አዎ እኔ ነኝ፣ በሊቀ ሐመር አምሳል በባሕር ውስጥ የተገለጥኩልህና መርከቡንም የቀዘፍኩልህ እኔ ነኝ፡፡ አትፍራ አትደንግጥም፡፡ እኔ ሁልጊዜ ከአንተ ጋር እኖራለሁና›› ብሎት ተመልሶ በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን ነሐሴ 30-ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ሚልክያስ ዕረፍቱ ነው፡፡ + ጌታችን ለሐዋርያው ለቅዱስ እንድርያስ በባሕር ውስጥ በሊቀ ሐመር አምሳል የተገለጠለትና ድንቅ ተአምር ያደረገበት ነው፡፡ ይኸውም አንዲትን ሥዕል አፍ አውጥታ የጌታችንን አምላክነት ለአይሁድ እንድትመሰክር ያደረገበት ነው፡፡ ሥዕሏም አብርሃምን ይስሐቅንና ያዕቆብን ጠርታ በማምጣት እነርሱም የክርስቶስን አምላክነት ለአይሁድና ካህናት አለቆቻቸው መስክረውላቸዋል፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ሚልክያስ፡- ይህም ታላቅ ነቢይ የእስራኤል ልጆች ከተሰደዱበት ከባቢሎን አገር በተመለሱ ጊዜ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በመተላለፋቸው ገሥጹዋቸዋል፡፡ ዳግመኛም ስለ አሥራር በኩራትና ስለ መሥዋዕት ገሥጹዋቸዋል፡፡ በዚህ ነቢይ አንደበት እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ተናግሯልና፡- "ከአባቶቻችሁ ዘመን ጀምር ከሥርዓቴ ፈቀቅ ብላችኋል፣ እርስዋንም አልጠበቃችሁም። ወደ እኔ ተመለሱ፥ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። እናንተ ግን <የምንመለሰው በምንድር ነው?> ብላችኋል። ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም <የሰረቅንህ በምንድር ነው?> ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው። እናንተ ይህ ሕዝብ ሁሉ እኔን ሰርቃችኋልና በእርግማን ርጉሞች ናችሁ። በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፡፡" ሚል 3፡7-10፡፡ ይህም ክቡር ነቢይ ዳግመኛ ከክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አስቀድሞ መጥምቁ ዮሐንስ ስለ መምጣቱ ስለ ነቢዩ ኤልያስም ተናገረ፡፡ ደግሞም ስለ አይሁድ የሥርዓተ ክህነት ፍጻሜ ተናገረ፡፡ ይኸውም በአሕዛብ አገር ውስጥ ለእግዚአብሔር የሚቀበላቸውን መሥዋዕት የሚያሳርጉ ዕውነተኞች ንጹሐን ካህናት እንዳሉ ገለጠላቸው፡፡ ይህም ታላቅ ነቢይ በበጎ ተጋድሎው እግዚአብሔርን ካገለገለ በኋላ በሰላም ዐረፈ፡፡ የነቢዩ የቅዱስ ሚልክያስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ + + + + + + + ዳግመኛም በዚኽች ዕለት የሀገረ ፈርማው ኤጲስቆጶስ አባ ሙሴ ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ + + + + + + ጌታችን ለሐዋርያው ለቅዱስ እንድርያስ በባሕር ውስጥ በሊቀ ሐመር አምሳል ስለመገለጡ፡- ጌታችን በሊቀ ሐመር አምሳል ለእንድርያስ ቢገለጥለት ጌታችንን ‹‹በመርከብህ አሳፍረን ነገር ግን የምንከፍልህ የመርከብ ዋጋ የለንም›› አለው፡፡ ጌታችንም ‹‹ስለምን የላችሁም?›› ቢለው እንድርያስም ‹‹በከረጢታችን ወርቅንና ብርን እንዳንይዝ ጌታችን ስለአዘዘን ነው›› አለው፡፡ በሊቀ ሐመር የተመሰለ ጌታችንም ይህን ጊዜ ‹‹እንዲህ ከሆነስ ወደ መርከቤ ወጥታችሁ ተሳፈሩ›› አላቸውና እንድርያስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወጥቶ ተሳፈረ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን እንድርያስንና ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ከባሕር ማዕበል የተነሣ መታገስ እንድትችሉ ተነሥታችሁ እንጀራ ብሉ›› አላቸው፡፡ እንድርያስም በርህራሄውና በደግነቱ ተደንቅ ጌታችንን ‹‹በመንግሥተ ሰማያት የሕይወት እንጀራ እግዚአብሔር ይስጥህ›› አለው፡፡ የእንድርያስ ደቀ መዛሙርቱ ግን በባሕር ላይ መሄድ ስላልለመዱ ከባሕሩ ማዕበል ፍርሃት የተነሣ መብላትም ሆነ መነጋገር ተሳናቸው፡፡ ጌታችንም መፍራታቸውን ዐውቆ እንድርያስን ‹‹አንተ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ከሆንክ መክረህ አጽናናቸው ይህ ካልሆነ ግን ወደ ምድር ይውረዱ›› አለው-መርከቡን እየቀዘፈ፡፡ እንድርያስም ማስተማርና ማጽናናት እንደጀመረ እነርሱ ከባድ እንቅልፍ አንቀላፉና ተኙ፡፡ እንድርያስም ስለተኙለት ተደስቶ ወደ ጌታችን በመመለስ እንዲህ አለው፡- ‹‹14 ጊዜ በባሕር ላይ ጉዞ አድጌአለሁ እንደ አንተ የሚቀዝፍ ግን አላገኘሁም›› አለው፡፡ ጌታችንም ‹‹እኛስ በባሕር ላይ ስንጓዝ ሁልጊዜ እንቸገራለን፡፡ ነገር ግን አሁን አንተ የክብር ባለቤት የእግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙሩ ስለሆንክ ባሕር ስላወቀችህ ማዕበሏን በአንተ ላይ አላነሳችም›› አለው፡፡ ይህን ጊዜ እንድርያስ በታላቅ ቃል ጮኾ ‹‹የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንተን ከሚያከብርህ ሰው ጋር ተገናኝቼ ተነጋግሬአለሁና አመሰግንሃለሁ›› አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ሲጓዙ ጌታችን እንድርያስን ‹‹አንተ የክርስቶስ ደቀ መዝሙሩ ነህና ንገረኝ እስቲ አይሁድ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ስለምን አላመኑም? የሠራውን ብዙ ድንቅ ተአምርን አይተዋል፣ ሰምተውማልና›› አለው፡፡ እንድርያስም ‹‹አዎን ወንድሜ ልክ ነህ… ሣሩ በእንጀራ እስኪሸፈን ድረስ እንጀራን አበርክቶ አብልቶ ቢያጠግባቸውም ሌሎች እጅግ ብዙ ተአምራት ቢያደርግላቸውም እነርሱ ግን አላመኑበትም…›› ብሎ ጌታችን ያደረጋቸውን ተአምራቶቹን በሙሉ ዘርዝሮ ነገረው፡፡ ጌታችንም ‹‹ይህን ያደረገው በስውር ነው ወይስ በግልጥ?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ እንድርያስም ‹‹ይህንንስ ያደረገው በግልጥ ነው በሥውርም ያደረገው ብዙ አለ›› አለው፡፡ ቀጥሎም እንድርያስ ጌታችንን ‹‹የምትፈትነኝ መሰለኝ›› አለው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወንድሜ ሆይ ልቤን ደስ ስለሚላት ነውና ንገረኝ?›› አለው፡፡ እንድርያስም አሁን ስማኝ ልንገርህ ካለው በኋላ ቀጥሎ ያለውን ታሪክ በሊቀ ሐመር ለተመሰለ ጌታችን ነገረው፡- ‹‹እኛ ዓሥራ ሁለታችን ሐዋርያቶቹ ከጌታችን ጋር ስንጓዝ ከሊቃነ ካህናትና ከሕዝቡ መካከል ብዙዎች ወዳሉበት ወደ ምኩራብ ደረስንና ጌታችን እነርሱን ‹‹በኪሩቤልና በሱራፌል አምሳል በምድር ላይ ሰው የሠራትን ይህችን የተቀረጸች ሥዕል ታያላችሁን?›› ካላቸው በኋላ ወደ ሥዕሊቱ ተመልሶ ‹‹ከቦታሽ ተነቅለሽ ውረጂና የካህናት አለቆችን ውቀሻቸው፣ እኔም ዕሩቅ ብእሲ ወይም እግዚአብሔር እንደሆንኩ መስክሪ›› አላት፡፡ ሥዕሊቱም ወዲያው ከቦታዋ ተነቅላ በመውረድ እንደሰውም በመናገር እንዲህ አለች፡- ‹‹እናንተ የደነቆራችሁ አይሁድ የራሳችሁ መደንቆር ያልበቃችሁ ሌሎችንም ለማደንቆር የምትሹ ለደኅንነታችሁ ሰው የሆነ እግዚአብሔርን እንዴት ዕሩቅ ብእሲ ትሉታላችሁ? አስቀድሞ ሰውን የፈጠረው በንፍሐት ልጅነትንም የሰጠው እርሱ ይህ ነው›› አለቻቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹አብርሃምን የተናገረው፣ ይስሐቅንም ከመታረድ ያዳነው፣ ያዕቆብንም ወደ አገሩ ያስገባው እርሱ ይህ ነው፡፡ ለሚፈሩት በረከትን የሚሰጥ ለማይታዘዙለት ቅጣትን የሚያዘጋጅ እርሱ ይህ ነው›› አለቻቸው፡፡ እንዲሁም ‹‹እውነት እላችኋላሁ እናንተ ስለምትክዱትና ሕጉን ሥርዓቱንም ትለውጣላችሁና ስለዚህ እነሆ መሥዋዕታችሁ ይሻራል፤ ምኩራቦቻችሁም በዋሕድ ወልደ እግዚአብሔር ስም አብያተ ክርስቲያናት ይሆናሉ …..›› እያለች ሥዕሏ ይህንና ይህንን የመሳሰለውን ሁሉ በሰው አንደበት ለአይሁድ ተናግራ ዝም አለች፡፡ ከዚያም እንድርያስ ለጌታችን እንዲህ አለው፡- ‹‹እኛም የካህናት አለቆችን መልሰን እነሆ ቅርጺቱ ሥዕል ተናግራ ወቀሰቻችሁ ታምኑ ዘንድ ይገባችኋል›› ስንላቸው እነርሱም ‹‹ይህን ያደረገውና ሥዕሊቱም ስለ እርሱ እንድትናገር ያደረገው በሥራይ ነው፡፡ አብርሃምን ወዴት አገኘው እርሱ ከሞተ ብዙ ዘመኑ ነውና›› አሉን፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ወደ ቅርጺቱ ሥዕል መለስ ብሎ ‹‹አንቺ ሥዕል ሆይ እነሆ ሄደሽ አብርሃምን እንዲህ በይው- ‹አስቀድሞ አዳምን የፈጠረው አንተንም ወዳጁ ያደረገህ አንተ ልጆችህ ይስሐቅንና ያዕቆብን ይዘህ ተነሥ፣ ከመቃብርም ወጥተህ ወደዚህ ኑ የካህናት አለቆችን

መልአኩም ‹‹አንተን ልትከተል ገና አንድ እግሯን ከቤት ስታወጣ ኃጢአቷ በሙሉ ተፍቆላታል፤ አሁን ወደ ገነት እየወሰድናት ነው›› አላቸው፡፡ አባ ዮሐንስ ሐጺርም ተገርመው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ‹‹የመቃብሯስ ነገር እንዴት ነው?›› ብለው ጠየቁት፡፡ መልአኩም ‹‹አንበሶች ይመጣሉ የመቃብሯን ቦታ ለክተህ አሳያቸው›› ብሏቸው ተሰወረ፡፡ አንበሶቹም መጥተው አባ ዮሐንስ ቦታውን ለክተውላቸው አንበሶቹ መቃብሩን ቆፍረው በክብር ቀብረዋታል፡፡ በአንዲት ዕለት ወደ በዓታቸው ሲገቡ ጌታችን ተገልጦላቸው ዕለተ ሞታቸው መቅረቡን ከነገራቸው በኋላ ታላቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸው ጥቅምት 20 ቀን 409 ዓ.ም በሰላም ዐርፈዋል፡፡ የአቡነ ዮሐንስ ሐጺር የሥጋው ፍልሰት፡- ይኸኸም የሥጋው ፍልሰት የሆነው በቁልዝም ገዳም ካረፈ በኋላ ነው፡፡ ለአባቶች ሊቃ ጳጳሳት 48ኛ የሆነው አባ ዮሐንስ ወደ አስቄጥስ ገዳም በሄደ ጊዜ መነኮሳት ‹‹የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ሥጋውን አፍልሰን በዚህ በቤተ ክርስቲያኑ ሥጋው ባለበት ለፈጣሪያችን እንስገድ›› አሉት፡፡ የአቡነ ዮሐንስ ሐጺር ሥጋው ይጠበቅ የነበረው የኬልቄዶንን ጉባኤ በሚቀበሉ ከሃዲያን ነበር፡፡ አባ ዮሐንስም መልእክት ጽፎ ወደ ቁልዝም አገር ቢልክም እነዚህ ከሃድያን የቅዱሱን ሥጋ ከለከሏቸው፡፡ ነገር ግን ሥጋው ያለበትን ቦታ አዩት፡፡ ከጥቂት ቀን በኋላ ከታላላቅ ዐረቦች ወገን የሆነ ለቁልዝም አገር መኮንን ሆኖ ተሾመ፡፡ እርሱም ለአገሪቱ ኤጲስ ቆጶስ ለአባ ሚካኤል ወዳጁ ነው፡፡ አባ ዮሐንስም ይህንን ሲሰማ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የሥጋው ፍልሰት መነኮሳትን እንዲረዳቸው ለአባ ሚካኤል መልአክት ላከ፡፡ አባ ሚኤልም ከከሃድያን እጅ ሊወጣ መሆኑን አስቦ ደስ አለው፡፡ ጉዳዩንም ወዳጁ ለሆነው መኮንን ነገረውና ሁለቱም መነኮሳቱን አስከትለው ወደ ገዳሙ ሄዱ፡፡ መኮንኑም መነኮሳቱን ይዞ ወደ ገዳሙ እንዴት እንደሚገባ ካሰበ በኋላ መነኮሳቱን ከላይ የዐረቦቹን ልብስ አስለብሶ ብዙ ፈረሰኞችን ይዞ ቁልዝም ገዳም ደረሱ፡፡ መኮንኑም በዚያ የሚኖረውን የመለካውያንን ኤጲስቆጶስ ‹‹በዚህች ሌሊት በዚህ ገዳም ማደር እፈልጋለሁና ያንተን መነኮሳት ከገዳሙ አስወጣቸው›› ብሎ አዘዘው፡፡ ኤጲስቆጶሱም እንደታዘዘው አደረገ፡፡ ከዚህም በኋላ መነኮሳቱ የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ሥጋ ይዘው ወደ ምስር አገር ከደረሱ በኋላ አስቄጥስ ገዳም ደረሱ፡፡ የአባ መቃርስ ገዳም መነኮሳትም ወንጌልን፣መስቀሎችን፣ መብራቶችን ይዘው እየዘመሩ በታላቅ ክብር ተቀበሏቸው፡፡ ወደ አባ መቃርስ ሥጋም አቅርበውት የቁርባን ቅዳሴን ቀደሱ፡፡ በቅዳሴው ላይ ቅዱስ ወንጌል በተነበበ ጊዜ ታላቅ የሆነ ድንቅ ተአምር ተፈጸመ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ሁለመናዋ በሰማያዊ ብርሃን ተጥለቀለቀች፡፡ ከቶ እንደ እርሱ ሆኖ የማያውቅ በጎ መዓዛም ሸተተ፡፡ ይህም ተአምር ለ7 ቀናት ቆየ፡፡ ከዚህም በኋላ የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ሥጋ ወደ ራሱ ቤተ ክርስቲያን በክብር ወስደው ሲያኖሩት አሁንም ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ አባ ማርቆስም የእስክንድርያ አገር ታላላቅ ሰዎችን አስከትሎ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ገብቶ የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ሥጋ የተጠቀለለበትን ሰሌን ገልጦ ሲሳለመው ታላቅ መብረቅና ነጎድጓድ ሆነ፡፡ ወዲያውም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉት ሁሉም ደንግጠው ወደቁ፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም ሰሌኑን መልሶ ሥጋውን በጠቀለለ ጊዜ ሰላም ሆነ፡፡ እነርሱም እንዲህ እያሉ ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን አመሰገኑት፡- ‹‹ፈጣን ደመና ሆነህ የመንፈስ ቅዱስን ዝናብ የተሸከምህ፣ ሠለስቱ ደቂቅ ወዳሉበት ወደ ባቢሎን የሄድህ፣ በላይ ባደረ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ወደ እስክንድርያ የተመለስህ፣ ሁለተኛም ወደ ቁልዝም አገር የሄድህ፣ የጣዖታትን ቤቶች አፍርሰህ ሃይማኖትን የሰበክህ፣ ሕሙማንን የፈወስህ አጋንንትን ያወጣህ ወደ ርስትህም የተመለስህ አንተ የበረከት ማደሪያ ነህ›› እያሉ አመሰገኑት፡፡ የአባታችን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን ነሐሴ 29-ቅዱስ አትናቴዎስና አገልጋዮቹ የሆኑ ቅዱስ ገርሲሞስና ቅዱስ ቴዎዶጦስ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ + ዳግመኛም በዚኽች ዕለት የከበረ የአቡነ ዮሐንስ ሐጺር የሥጋው ፍልሰት ሆነ፡፡ ቅዱሳን ሰማዕታት አትናቴዎስ፣ ገርሲሞስና ቴዎዶጦስ፡- የንጉሡን የአርስያኖስን ጭፍሮች ከሆኑት ውስጥ የአንዱን ሴት ልጅ ቅዱስ አትናቴዎስ አሳምኖ ስላስጠመቃት ይኸው ከሃዲ ንጉሥ አስመጥቶ ስለ እምነቱ መረመረው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስም የጌታችንን አምላክነት ለንጉሡ መሰከረ፡፡ ንጉሥ አርስያኖስም ቅዱስ አትናቴዎስ በእጅጉ አሠቃየው፡፡ ሃይማኖቱንም እንዳልካደለትና እስከመጨረሻው እንደጸና ባወቀ ጊዜ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ የኤጲስቆጶስ ቅዱስ አትናቴዎስ አገልጋዮቹ የሆኑ ቅዱስ ገርሲሞስንና ቅዱስ ቴዎዶጦስንም በስቅላት ከቀጣቸው በኋላ እነርሱንም አንገታቸውን በሰይፍ አስቆረጣቸውና የሰማዕትነት ፍጻሜአቸው ሆነ፡፡ ክርስቲያኖችም መጥተው ለወታደሮቹ ገንዘብ ከፍለው የቅዱሳን ሰማዕታቱን ሥጋ ወስደው በክብር አስቀመጡት፡፡ ከቅዱሳኑም ሥጋ ታላላቅ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ + + + + + ዳግመኛም በዚህች ዕለት የታላቁ አባት የአቡነ ዮሐንስ ሐጺር የሥጋው ፍልሰት ነው፡፡ ከሥጋውም ብዙ አስገራሚ ተአምራት ተፈጽመው ታይተዋል፡፡ አቡነ ዮሐንስ ሐጺር ቁመታቸው አጭር ስለነበር ‹‹ዮሐንስ ሐጺር›› አጭሩ ዮሐንስ ተብለዋል፡፡ በ309 ዓ.ም ከተወለዱ በኋላ በ18 ዓመታቸው አስቄጥስ ገዳም ገቡ፡፡ አበምነቱ አባ ባይሞይ የምንኩስና ኑሮ እጅግ ከባድ መሆኑን በመንገር ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ ቢመክሯቸውም እሳቸው ግን በቁርጥ ሀሳብ ወሰኑ፡፡ አባ ባይሞይ ግን የዚህን ወጣት ዕጣ ፈንታ ግለጥልኝ ብለው ሱባኤ ያዙ፡፡ የታዘዘ መልአክም መጥቶ ‹‹እርሱ የተመረጠ ዕቃ ይሆናልና ተቀበለው ብሎሃል›› ብሎ ነገራቸው፡፡ እንደታዙትም ተቀበሉት፡፡ አቡነ ዮሐንስም ገዳሙ እንደገቡ በብዙ ተጋድሎ ሲኖሩ ምንጣፍ ሳያነጥፉ መሬት ላይ ነበር የሚተኙት፡፡ አባታችን በታዛዥነታቸው በእጅጉ ይታወቃሉ፡፡ ይህንንም ለመፈተን አንድ ቀን አባ ባይሞይ የደረቀ እንጨት አንስተው ለአቡነ ዮሐንስ ሰጧቸውና ‹‹ይህን ደረቅ እንጨት ትከለውና ውሃ እያጠጣህ አብቅለው፣ ፍሬ እስኪያፈራም ተንከባከበው›› አሏቸው፡፡ አቡነ ዮሐንስም በፍጹም መታዘዝ እሺ ብለው ደረቁን እንጨት ተከለው ሦሰት ዓመት ሙሉ ከሩቅ ቦታ በቀን ሁለት ጊዜ ውኃ እየቀዱ በማምጣት ማጠጣት ጀመሩ፡፡ በ3ኛውም ዓመት ደረቁ እንጨት ጸድቆ ለመለመ፣ ታላቅ ዛፍም ሆኖ አብቦ አፍርቶ ጣፋጭ ፍሬ አፈራ፡፡ አባ ባይሞይም ፍሬውን ቆርጠው ወስደው ‹‹የታዛዡን የትሑቱን ፍሬ እነሆ ቅመሱ›› እያሉ ለቅዱሳን ሰጧቸው፡፡ ቅዱሳኑም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ተመገቡት፡፡ ዛፉም ‹‹የመታዘዝ ዛፍ›› እየተባለ መጠራት ጀመረ፡፡ ቅዱሳን ትልቁ የቅድስና ደረጃ ላይ ሲደርሱ ቀና ቢሉ ሥሉስ ቅዱስን ይመለከታሉ ዝቅ ቢሉ ደግሞ እንጦሮጦስን ያያሉ፡፡ አቡነ ዮሐንስ ሐጺር በታላቅ ተጋድሎአቸው ሥሉስ ቅዱስን በገሃድ ለማየት የበቁ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ በአባ ቴዎፍሎስ እጅ በገዳሙ ላይ አበምኔትነት ሲሾሙ ይገባዋል የሚል ድምፅ ከሰማይ ተሰምቷል፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ቴዎፍሎስ አቡነ ዮሐንስን የቅዱሳን የሠለስቱ ደቂቅን ሥጋቸውን እንዲያመጡ ወደ ባቢሎን ልከዋቸው ሄደው አምጥተዋል፡፡ አባ ባይሞይ ጋር መንፈሳዊ ምክርንና ስለ ምንኩስና ትምህርት ለማመር ወደ እርሳቸው የሚመጡትን ሁሉ ወደ አቡነ ዮሐንስ ዘንድ ይልኳቸው ነበር፡፡ አቡነ ባይሞይ ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ መነኮሳቱን ሰብስበው የአቡነ ዮሐንስን እጅ በመያዝ ‹‹በምድር ያለ መልአክ ነውና ተቀበሉት›› ብለው ገዳማቸውንና ልጆቻቸውን እንዲጠብቁላቸው አደራ ሰጧቸው፡፡ አቡነ ዮሐንስ የበቃውንና ያልበቃውን ያውቁ ስለነበር ያልተገባው ሰው ሥጋ ወደሙን ሊቀበል ሲመጣ ንስሓ ገብቶ እንመለስ ይነግሩታል፡፡ አባታችን ሲቀድሱ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል የማይገባቸውን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ዐውቀው እየለዩ ‹‹ዛሬ ሄዳችሁ ንስሓ ገብታችሁ ተመለሱ›› ይሏቸዋል፡፡ የወደፊቱንም በትንቢት ይናገሩ ነበር፡፡ አንድ ሰው በኃጢአት ወድቆ ባዩ ጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር፡- ‹‹ይህ ወንድሜ ኃጢአት የሠራው ዛሬ ነው፣ ምናልባት እኔ ደግሞ ነገ ኃጢአት እሠራ ይሆናል፡፡ እርሱን በፈተና የጣለ ሰይጣን እኔንም ይጥለኝ ይሆናል፡፡ እርሱ ዛሬ ቢበድል ነገ በንስሓ ይታጠባል፣ አቤቱ እኔ ግን ከኃጢአቴ የምነጻበት ሰዓት አይኖረኝ ይሆናል›› እያሉ አምርረው ያለቅሳሉ፡፡ የቅድስና ሕይወታቸውንም እንዴት ዕለት ዕለት እንደሚጠብቁ እንዲህ በማለት ተናግረዋል፡- ‹‹አንድ ሰው በጾምና በርሃብ ከጸና የነፍሱ ጠላቶች ይደክማሉ፤ እኔ በትልቅ ዋርካ ሥር የተቀመጠንና አራዊት ሊጣሉት የመጣን ሰው እመስላለሁ፣ ሊቋቋማቸው እንደማይችል ከተረዳ ሸሽቶ ወደ ዛፉ በመውጣት ነፍሱን ያድናል፡፡ በእኔም የተፈጸመው ይሄው ነው፡፡ በበዓቴ ተቀምጬ ክፉ ሀሳቦች ሊቃወሙኝ ሲመጡ ልቋቋማቸው እንደማልችል ባወቅሁ ጊዜ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ሸሽቼ እመሸጋለሁ፡፡ በዚያም ከጠላቶቼ ፍላጻ እድናለሁ›› በማለት እንዴት የቅድስና ሕይወታቸውን ይጠብቁ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ አቡነ ዮሐንስ ሐጺር ሌላው የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ግብራቸው የአትናስያን ሞት ወደ ሕይወት የለወጡበት ነው፡፡ አትናስያ መጀመሪያ ላይ ጻድቅ ነበረች፣ በገንዘቧ ገዳማትንና መነኮሳትን የምትረዳ አገልጋዮችን የምትራዳ ደግ ሴት ነበረች ነገር ግን በኋላ ላይ ጠላት ሰይጣን በወጥመዱ ጣላትና በዝሙት እንድትወድቅ አደረጋት፡፡ ዘማዊ ሴትም ሆነች፡፡ በቀድሞ የቅድስና ሕይወቷ የሚያውቋት መነኮሳት ሁሉ መክረው ሊመልሷት ቢሞክሩ አልመለስላቸው አለች፡፡ ይልቁንም ሊመክሯት ሲመጡ እየሳቀችባቸው ታሾፍባቸው ጀመር፡፡ በመጨረሻም መነኮሳቱ አቡነ ዮሐንስ ሐጺርን ላኳቸው፡፡ እርሳቸውም ተራ ሰው መስለው ወደ ቤቷ ገቡ፡፡ ለዝሙት የመጣ ተራ ሰው መስሏት በደስታ ተቀበለችው፡፡ ልታጫውተውም ስትሞክር ዮሐንስ ሐጺር ማልቀስ ጀመረ፡፡ ‹‹ለምን ታለቅሳለህ?›› ብትለው ‹‹መልክሽ ደስ ብሎኝ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ታዲያ ደስ የሚል መልክ ያስቃል እንጂ መች ያስለቅሳል?›› ስትለው ‹‹የለም ነገ ገሃነም እንደምትወርጂ ታይቶኝ ነው፣ እነሆ የሰይጣን ማደሪያ ሆነሽ ብዙ አጋንንት በሰውነትሽ ሲወጡ ሲወርዱ አያለሁ…›› እያሉ ብዙ መክረው አስተማሯት፡፡ እርሷም ዓይነ ልቡናዋ ተከፍቶላት ወደ ልቧ ተመለሰች፡፡ አትናስያም በጣም ደንግጣ በመጸጸት ‹‹ታዲያ ምን ባደርግ ይሻለኛል?›› አለቻቸው፡፡ ‹‹ንስሃ ግቢ›› አሏት፡፡ ‹‹በውኑ አሁን እኔ ምሕረት አገኛለሁን? ኃጢያቴ ብዙ ነው፣ ከእግዚአብሔር ጋር ማን ያስታርቀኛል?›› ስትላቸው ‹‹እኔ አስታርቅሻለሁ ተከተይኝ›› ብለው ወጥተው ሄዱ፡፡ እርሷም ልዋል ልደር ሳትል በሯ እንደተከፈተ ቤት ንብረቷን ትታ አባ ዮሐንስን ተከተለቻቸው፡፡ እሳቸው ላይ ለመድረስ እየሮጠች ስትሄድ በልስላሴ የኖረ እግሯ እየቆሰለና እየተሰነጣጠቀ ደሟ እንደ ውኃ በመሬት ላይ ፈሰሰ፡፡ ሲመሽ ከገዳሙ በር ላይ ደርሳ የምታርፍበትን ቦታ ለይተው ሰጧትና እዚያ ተኛች፡፡ አባ ዮሐንስ ሌሊት ለጸሎት ሲነሡ መላእክት ሲወጡ ሲወርዱ ተመልክተው ‹‹ይህ የማየው ነገር ምንድን ነው?›› በማለት አንዱን መልአክ ጠየቁት፡፡ ‹‹ትላንትና አንተን ተከትላ የመጣችው ሴት ሞታ ነፍሷን እያሳረግን ነው›› አላቸው፡፡ ‹‹እግዚኦ ንስሓ ሳትገባ›› ብለው ደነገጡ፡፡

መልክዐ_አብርሃም_ይሥሐቅ_ወያዕቆብ_ዘአኅተሞ_ገብረ_ሥላሴ.pdf5.98 KB

እርሱም ከአባቱ ከያዕቆብ ሚስቶች ከዘለፋ ልጆችና ከባላ ልጆች ጋር የአባቱን በጎች ይጠብቅ ነበር፡፡ ያዕቆብም በእርጅናው ዘመን ወልዶታልና አብልጦ ይወደው ነበር፡፡ ወንድሞቹም በዚህ ምክንያት ጠሉት፡፡ (ከዚህም በኋላ ዮሴፍ በወንድሞቹ የደረሰበትንና ወደ ግብፅም መውረዱን ያስታውሷል፡፡) ዮሴፍ በወንድሞቹ ግፍ ደርሶበት ወደ ግብፅ ተሸጦ ከሄደ በኋላ እዚያም ብዙ ፈተና አሳለፈ፡፡ ነገር ግን እግዚአሔር ሞገስ ሆኖት በግብፅ ተሾመ፡፡ የሸጡት ወንድሞቹም በረሀብ ምክንያት ስንዴ ሊለምኑ ወደ ግብፅ ሲወርዱ ዮሴፍን በስልጣን ሆኖ አገኙት፡፡ እርሱም ራሱን ገለጠላቸው፡፡ ያደረጉበትንም ነገራቸው፡፡ የርኃቡም ዘመን ገና 5 ዓመት ይቀረው ነበርና ዮሴፍ ወንድሞቹን ‹‹ስለሸጣችሁኝ አትዘኑ እነሆ ሕይወታችሁን ለማዳን እግዚአብሔር አስቀድሞ ከእናንተ በፊት ወደ ግብፅ ልኮኛል›› አላቸው፡፡ አባቱንም ወደ እርሱ እንዲያመጡት ላካቸው፡፡ ያዕቆብም ከነቤተሰቡ ንብረቱንም ሁሉ ሰብስቦ ወደ ግብፅ ወረደ፡፡ ልጁን ዮሴፍንም ባየው ጊዜ እያለቀሰ አቅፎ ከሳመው በኋላ ሞቱን ተመኘ፡፡ በግብፅ የያዕቆብ የልጅ ልጆቹ ቁጥር 66 ሆነ፡፡ ከዮሴፍም ልጆች ጋር አንድ ላይ 70 ሆኑ፡፡ ያዕቆብም ፈርዖንን ገብቶ ከባረከው በኋላ በግብፅ ጌሤም ምድር 17 ዓመት ተቀመጠ፡፡ ዘመኑም 140 በሆነ ጊዜ በሞት ማረፉን ዐውቆ ልጁን ዮሴፍን ጠርቶ በአባቶቹ መቃብር ቤት ውስዶ እንዲቀብረው ነገረው፡፡ የዮሴፍንም ሁለቱን ልጆች ምናሴንና ኤፍሬምን ባረካቸው፡፡ ‹‹አባቶቼ አብርሃምና ይስሐቅ በፊቱ የሄዱለት እርሱ እግዚአብሔር፣ ከታናሽነቴ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እኔን የመገበኝ እግዚአብሔር፣ ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ እርሱ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ፤ ስሜም የአባቶቼ የአብርሃምና የይስሐቅ ስም በእነርሱ ይጠራ፤ በምድርም መካከል ይብዙ›› ብሎ ባረካቸው፡፡ ያዕቆብም ልጆቹን ጠርቶ ወደፊት የሚሆነውን ሁሉ ይልቁንም የጌታችንን የመወለዱን ነገር በምሳሌ እያደረገ ነገራቸው፡፡ እያንዳንዳቸውንም እንደ በረከታቸው ባረካቸውና በአብርሃምና በይስሐቅ ሣራም በተቀበረችበት መቃብር ወስደው እንዲቀብሩት ከነገራቸው በኋላ በ137 ዕድሜው እግሮቹን በአልጋው ላይ ሰብስቦ በሰላም ዐረፈ፡፡ የግብፅ ሰዎችም 70 ቀን አለቀሱለት፡፡ ዮሴፍም አባቱን ባዘዘው ቦታ በእነ አብርሃም መቃብር ከቀበረው በኋላ ወደ ግብፅ ተመለሰ፡፡ + + + ዳግመኛም በዚህች ዕለት አባ በርሳቦ ቀደ መዛሙርቶቹ ከሆኑ 12 መነኮሳት ጋር ደግሞም ከፋርስ ንጉሥ ባልደራሶች ጋርና 6 ሺህ ከሆኑ ከኤስድሮስ ማኅበር ጋር በሰማዕትነት እንዳረፈ ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡ የአባቶቻችን በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

ያሰናብተው ዘንድ ላባን ጠየቀው፡፡ ላባም ‹‹ደመወዝህን ንገረኝ›› ሲለው ያዕቆብ ‹‹ዳግመኛ በጎችህን እጠብቃለሁ፣ በጎችህም ሁሉ በፊትህ ይለፉ ከበጎችህ ጸጉራቸው ነጫጭ የሆኑትንና መልኩ ዓይነቱ ዥንጉርጉር የሆነውን ለይተህ ስጠኝ፣ ይህም ደመወዜ ይሁነኝ›› አለው፡፡ ‹‹መልኩ ነጫጭ ያልሆነውና መልኩ ዓይነቱ ዥንጉርጉር ያልሆነው ግን ላንተ ይሁን›› አለው፡፡ ለባም በዚህ ተስማቶ ‹‹እንዳልክ ይሁን›› አለው፡፡ ላባም ነጩን ዥንጉርጉሩን ሁሉ መርጦ ለልጆቹ ሰጣቸውና የሦስት ቀን መንገድ ይዘው ሄዱ፡፡ ያዕቆብም ተመርጠው የቀሩትን የላባን በጎች እየጠበቀ ሳለ እርጥብ የልምጭ በትር፣ ታላቅ የሎሚ በትር ኤርሞን የሚባሉ ሦስት በትሮችን አንሥቶ ሁለቱን ቅርፊታቸውን ልጦ አንዱን ዥንጉርጉር አድርጎ በውኃው ገንዳ ውስጥ ጣላቸው፡፡ ሁለቱም የተላጡት በትሮች ነጭ ሆነው ታዩ፡፡ በጎቹም ውኃ ሊጠቱ በመጡ ጊዜ በትሮቹን አስመስለው ፀነሱ፡፡ ይኸውም በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የበትሩ ጥላ ውኃው ላይ ሲያርፍ በጎቹ ያንን እያዩ ሲጠጡ ፈቃዳቸው ይነሣባቸዋል ያንጊዜም አውራዎቹን ይለቃቸዋል፡፡ ያንጊዜም በትሮቹን አስመስለው ይፀንሳሉ፡፡ ያዕቆብም አውራ አውራውን ከለየ በኋላ ዥንጉርጉር ሆነው የተወለዱትን ለብቻቸው እየለየ ያቆማቸዋል እንጂ ከላባ በጎች ጋር አያደባልቃቸውም ነበር፡፡ ዳግመኛም እንዲሁ እያደረገ አራባቸው ነገር ግን በጎቹ ከወለዱ በኋላ በትሮቹን በገንዳው ውስጥ አያኖራቸውም ነበር፡፡ በመጨረሻም ምልክት ያላቸው ብርቱዎቹ በጎች ለያዕቆብ ሲሆን ምልክት የሌላቸው ደካሞቹ በጎች ደግሞ ለላባ ሆነዋል፡፡ ያዕቆብም ይህንን ያደረገው እግዚአብሔር በሕልሙ አሳይቶት ነው፡፡ ይኸውም ለጊዜው ይህ ቢደረግም ለኋላው ግን ምሳሌ ነው፡፡ ሦስቱ በትሮች የሥላሴ ምሳሌ ሲሆኑ የተላጡት ሁለቱ በትሮች የአብና የመንፈስ ቅዱስ፣ ዥንጉርጉር የሆነው አምላክና ሰው የሆነው የወልድ አምሳል ነው፡፡ በጎቹ በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቁ የምእመናን ምሳሌ ናቸው፡፡ ውኃው የጥምቀት፣ አውራዎቹ የመምህራን የቀሳውስት ምሳሌ ሲሆኑ በጎቹ በትሮቹን እየመሰሉ እንደተወለዱ ሁሉ ምእመናንም በጥምቀት ምክንያት ከሥላሴ ይወለዳሉ፡፡ ያዕቆብ የጌታችን፣ ላባ የዲያብሎስ ምሳሌ ነው፡፡ ዳግመኛም በትር የእመቤታችን ምሳሌ ስትሆን ሦስቱን በትሮች አይተው ፍሬ ያፈሩት በጎች በሦስት ወገን ማለትም ንጽሐ ሥጋን ንጽሐ ነፍስንና ንጽሐ ልቡናን አስተባብራ በያዘች በእመቤታችን ቃልኪዳን አማላጅነት የጽድቅ ፍሬን የሚያፈሩ የክርስቲያኖች ምሳሌ ናቸው፡፡ ምልክት ያላቸው ብርቱዎቹ በጎች ለያዕቆብ፣ ምልክት የሌላቸው ደካሞቹ በጎች ደግሞ ለላባ እንደሆኑት ሁሉ ሀብተ ውልድና ስመ ክርስትና ያላቸውና በእመቤታችን ቃልኪዳን ያመኑ ምእመናን ሁሉ ለጌታችን ሲሆኑ ሀብተ ውልድና ስመ ክርስትና የሌላቸውና በእመቤታችን ቃልኪዳን ያላመኑ ምእመናን ግን ለዲያብሎስ ሆነዋል፡፡ በትር እመቤታችን ከነገደ ዕሴይ ተገኝታ ጽጌ ክርስቶስን እንደምትወልድ ኢሳይያስ በትንቢት ተናሮላታል፡፡ ኢሳ 11፡1፡፡ ያዕቆብም ከዚህ በኋላ ሀብታምና ባለጸጋ ሆነ፡፡ ሚስቶቹንና ንብረቱንም ይዞ ወደ አባቱ ርስት ወደ ምድረ ከነዓን ጉዞ ጀመረ፡፡ ላባም ተከትሎት ሄዶ በገለዓድ ተራራ ሳለ ለክፋት ቢፈልገውም እግዚአብሔር ለላባ በራእይ ተገልጦለት ‹‹በባሪያዬ ላይ አንዳች ክፉ እንዳታደርግ›› ብሎ ከለከለው፡፡ ላባም ከያዕቆብ ጋር ተስማምቶ ዳግመኛል ላይጣላ ተማምሎ ተመለሰ፡፡ ያዕቆብም ወንድሙን በመፍራት ለኤሳው ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ እንስሳትን እጅ መንሻ በመላክ እንዲታረቀው መልእክተኛ ላከ፡፡ በመንገድም ሳለ የያቦቅን ወንዝ እንደተሻገረና ብቻውን በቀረ ጊዜ እስከነጋ ድረስ አንድ ሰው እርሱም በአምሳለ ብእሲ ታይቶት ጌታችን ያዕቆብን ሲታገለው አደረ፡፡ ያም ሰው ሲነጋ ‹‹ጎሕ ቀዷልና ልቀቀኝ›› ሲለው ያዕቆብ ‹‹ካልመረቅኸኝ አንድም ስም ካላወጣህልኝ አልቀህም›› አለው፡፡ እርሱም ‹‹ስምህ ማን ነው?›› አለው፡፡ ‹‹ያዕቆብ ነኝ›› ሲለው ‹‹ከእንግዲህስ ስምህ እስራኤል ይባል›› ካለው በኋላ ባረከው፡፡ ያዕቆብም እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁት ሲል ቦታውን ‹‹ራእየ እግዚአብሔር›› ብሎ ሰየመው፡፡ መታገሉ ስለምን ነው? ቢሉ በረድኤት እቀርብሃለሁ፣ አልለይህም ሲል ነው፡፡ ያዕቆብ ጌታን ይዞ መጣሉ እኔን ከያዝክ ጠላትህን ትጥላለህ ሲል፣ በውስጥ ሆኖ ጌታ ያዕቆብን ማስጨነቁ እኔን ብትጥል እኔም አንተን አስጨንቅሃለሁ ሲል ነው፡፡ ፍጻሜው ግን መታገል ደረት ለደረት ገጥሞ እንደሆነ ሁሉ ከሥጋህ ሥጋ ከነፍስህ ነፍስ ነስቼ አካልህን አካል ባሕርይህን ባሕርይ አድርጌ አድንሃለሁ ብሎ በአብራኩ ካለች ከእመቤታችን የመወለዱን ምሥጢር ሲገልጥለት ነው፡፡ ይህን የተረዳው የ12ቱ ነገደ እስራኤል አባት የሆነው ያዕቆብም በመጨረሻው ዘመን ልጆቹን ሰብስቦ በኋለኛው ዘመን የሚሆኑትንና የሚያገኛቸውን ነግሮ ባርኳቸዋል፡፡ በተለይም የጌታችንን መወለድ ሲናገር ‹‹በትረ መንግሥት ከይሁዳ አይጠፋም፣ የገዥም ዘንግ ከእግሮቹ መካከል ገዥ የሆነው እስኪመጣ ድረስ የአህዛብ መታዘዝም ለእርሱ ይሆናል….›› እያለ ጌታችንን በአንበሳ ደቦል እየመሰለ ሰፊ ትንቢት ተናግሯል፡፡ ዘፍ 49፡10፡፡ ይኸውም ያዕቆብ በትንቢት እንደተናገረው ጌታችን ከነገደ ይሁዳ ከተወለደች ከእመቤታችን ተወልዶ ዲያብሎስን ድል ነሥቷል፡፡ ይህንንም ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ገልጦታል፡፡ በራእ 5፡5 ላይ ‹‹እነሆ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም መኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቷል›› ተብሎ እንደተጻፈ፡፡ እንዲሁም በቀደሙት መጻሕፍት ላይ ‹‹ኮከብ ከያዕቆብ ይወጣል፣ ለርስቱ እኛን መረጠን የወደደውን የያዕቆብን ውበት›› እየተባለ ትንቢቱ ተነግሮታል፡፡ ዘኁ 24፡17፣ መዝ 46፡4፡፡ ያዕቆብም እንደፈራው ወንድሙ ኤሳው በክፉ ሳይሆን 40 ሰዎችን አስከትሎ መጥቶ በበጎ ተቀበለው፣ ተቃቅፈውም እየተላቀሱ ተሳሳሙ፡፡ ያዕቆብም በምድረ በዳ አቅራቢያ ባለች አብርሃም ይቀመጥባት ከነበረች አገር ከአባቱ ከይስሐቅ ዘንድ ደረሰ፡፡ ይህችውም በከነዓን ያለችው ኬብሮን ናት፡፡ አባቱ ይስሐቅ አብርሃም ይቀመጥባት በነበረችው የወይራ ዛፍ ሥር ተቀምጦ አገኘው፡፡ ከዚህም በኋላ ይስሐቅ አርጅቶ ዘመኑን ጨርሶ ሞተ፡፡ ከኤሞር ልጆች በገዛውና እናቱ ሣራ በተቀበረችበት በአብርሃም መቃብር ልጆቹ ኤሳውና ያዕቆብ አልቅሰው ቀበሩት፡፡ ያዕቆብም አባቱ ይስሐቅ ይኖርባት በነበረች አገር ኖረ፡፡ የያዕቀብም ልጆች 12 ሲሆኑ እርሱም ከትልቁ ጀምሮ በቅደም ተከተላቸው የልያ ልጆች ሮቤልና ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፤ የራሄልም ልጆች ዮሴፍና ብንያም፤ የራሄል ገረድ የባላ ልጆች ዳንና ንፍታሌም፤ የልያ ገረድ የዘለፋ ልጆች ጋድና አሤር ናቸው፡፡ ያዕቆብ የወንድሙን የኤሳውን በረከት ከአባቱ ከወሰደ በኋላ ከኤሳው ሸሽቶ ወደ አጎቱ ላባ ዘንድ ተሰዶ 14 ዓመት ለላባ ተገዝቶ ራሄልንና ርብቃን አግብቶ ብዙ ልጆችን ወለደ፡፡ ሀብት ንብረትም ካፈራ ከ21 ዓመት በኋላ ወደ አባቱ አገር ተመልሶ ከወንድሙ ጋር ታረቀ፡፡ ያዕቆብም በምድረ በዳ አቅራቢያ ባለች አብርሃም ይቀመጥባት ከነበረ አገር ከአባቱ ከይስሐቅ ዘንድ ደረሰ፡፡ ይህችውም በከነዓን ያለችው ኬብሮን ናት፡፡ አባቱ ይስሐቅ አብርሃም ይቀመጥባት በነበረችው የወይራ ዛፍ ሥር ተቀምጦ አገኘው፡፡ ከዚህም በኋላ ይስሐቅ አርጅቶ ዘመኑን ጨርሶ ሞተ፡፡ ያዕቆብም አባቱ ይስሐቅ ይኖርባት በነበረች አገር ኖረ፡፡ ያንጊዜም ልጁ ዮሴፍ 17 ዓመት ሆኖት ነበር፡፡

ተመረቀ፤ በረከትንም ተቀበለ፡፡ ይስሐቅም ሲዳስሰው የአሳውን ልብስ ለብሶ ስለነበር ያዕቆብ እንደሆነ አላወቀውም ነበር፡፡ ያዕቆብም አባቱ ከመረቀው በኋዋላ ወጥቶ ሄደ፡፡ ኤሳውም አደን ከዋለበት ተመልሶ መጣና ለአባቱ አድኖ ያመጣውን አቀረበለት፡፡ ይስሐቅም የኤሳውን ማንነት ካወቀና ያዕቆብም እንደዋሸው ዐወቀ፣ ጥንቱንም ተጠራጥሮ ነበርና በዚህም ጊዜ እጅግ ደነገጠ፡፡ ‹‹ለወንድምህ ጌታ ሁነው፣ እርሱም ይገዛልህ፤ የሚረግምህ የተረገመ ይሁን….›› ብሎ መርቆታልና፡፡ ያዕቆብም ወደ አጎቱ ላባ ዘንድ ተሰዶ 14 ዓመት ለላባ ተገዝቶ ራሄልንና ርብቃን አግብቶ ብዙ ልጆችን ወለደ፡፡ ሀብት ንብረት ካፈራ ከ21 ዓመት በኋላ ወደ አባቱ አገር ተመልሶ ለወንድሙ ብዙ ሀብት እጅ መንሻን ሰጥቶ ታረቀ፡፡ ኤሳው ግን እጅ መንሻውን አልተቀበለውም፡፡ 40 ሰዎችን አስከትሎ መጥቶ በሰላም ከተቀበለው በኋላ ተቃቅፈው እየተላቀሱ ተሳስመዋል፡፡ ያዕቆብም በምድረ በዳ አቅራቢያ ባለች አብርሃም ይቀመጥባት ከነበረ አገር ከአባቱ ከይስሐቅ ዘንድ ደረሰ፡፡ ይህችውም በከነዓን ያለችው ኬብሮን ናት፡፡ አባቱ ይስሐቅ አብርሃም ይቀመጥባት በነበረችው የወይራ ዛፍ ሥር ተቀምጦ አገኘው፡፡ ይስሐቅም ዕድሜው 180 ሆኖ ነበር፡፡ የአብርሃም ዘመን 175 ነው፡፡ ለይስሐቅ ስለ ንጽሕናው 5 ዓመት ተጨምሮለታል፡፡ ከዚህም በኋላ አርጅቶ ዘመኑን ጨርሶ ሞተ፡፡ እርሱም ከኤሞር ልጆች በገዛውና እናቱ ሣራ በተቀበረችበት በአብርሃምም መቃብር ልጆቹ ኤሳውና ያዕቆብ አልቅሰው ቀበሩት፡፡ ዕፍቱም ነሐሴ 28 ነው፡፡ ኤሳውም አባቱን ‹‹ለእኔ ያስቀረህልኝ ምርቃት የለምን? ምርቃትህ አንዲት ብቻ ናትን?›› እያለ በመጮህ አምርሮ አለቀሰ፡፡ አባቱም ‹‹ለወንድምህ ተገዛ ነገር ግን የወንድምህን አገዛዝ ካንተ ልታርቅ ብትወድ እርሱን ተለማመጠው›› ሲለው ኤሳው አባቱ ሞቶ ወንድሙን የሚበቀልበትን ቀን ተመኘ፡፡ ርብቃም ይህን ስትሰማ ያዕቆብን በካራን ወደሚኖረው ወንድሟ ወደ ላባ ዘንድ ሄዶ የወንድሙ ቁጣ እስኪበርድ በዚያ እንዲቀመጥ ነገረችው፡፡ ይስሐቅም ያዕቆብን ጠርቶት ከከነዓን ሴቶች ውስጥ ሚስት እንዳያገባ ይልቁንም ከአጎቱ ከላባ ልጆች ውስጥ አንዷን እንዲያገባ ከነገረው በኋላ እግዚአብሔር ዘሩን እንዲያበዛለት መርቆ ላከው፡፡ ያዕቆብም ወንድሜ ቢከተለኝ፣ አውሬ ቢመጣብኝ እያለ እየፈራ ወደ ካራን ሄደ፡፡ ሲመሽም ከአንድ ቦታ አድሮ ድንጋይ ተንተርሶ ተኛ፡፡ በዚያችም ሌሊት በራእይ የወርቅ መሰላል ተተክሎ ከምድር እስከ ሰማይ ደርሶ ቅዱሳን መላእክት በእርከኑ ሲወጡበት ሲወርዱበት በላዩም እግዚአብሔር ተቀምጦ አየ፡፡ ‹‹የአብርሃምና የይስሐቅ ፈጣሪ እኔ ነኝና ወንድሜ ይገድለኛል እንደወጣሁም እቀራለሁ ብለህ አትፍራ እኔ በረድኤት ከአንተ ጋር ነኝ›› አለው፡፡ ልጆቹም በዝተው ምድርን በአራቱም ማዕዘን እንደሚሞሏት አሕዛብም ሁሉ በእርሱና በልጆቹ እንደሚባረኩ ነገረው፡፡ ያዕቆብም ከእንቅልፉ ነቅቶ ያደረባትን ቦታ እግዚአብሔር ቆሞባት መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት አይቷታልና ‹‹ይህቺ የሰማይ ደጅ ናት›› ብሎ ስሟን ቤቴል አላት፡፡ ትርጓሜውም የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው፡፡ ትራስ አድርጎት የነበረውንም ድንጋይ አንስቶ ሐውልት አድርጎ ካቆማት በኋላ በራሷ ላይ ዘይት አፈሰሰባት፡፡ ይኸውም ምሳሌ ነው፡፡ ያዕቆብ የጌታችን፣ የወርቁ መሰላል የረድኤት፣ እርከኑ ብዙ መሆኑ በብዙ ወገን እረዳሃለሁ ሲል ነው፡፡ መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት ማየቱ እኔ ስረዳህ መላእክትም አብረው ይረዱሃል ሲል ነው፡፡ መሰላሉ በድንጋይ ላይ መሆኑ በጽኑ ረድኤት እረዳሃለሁ ሲል ነው፡፡ አንድም መሰላሏ የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ወርቁ የንጽሕናዋ የቅድስናዋ ምሳሌ ሲሆን የመሰላሏ እርከኗ ብዙ መሆኑ የእመቤታችን የሀብቷ የማዕረጓ ምሳሌ ነው፡፡ መሰላሏ ከምድር እስከ ሰማይ ተተክላ ማየቱ የልዕልናዋ፣ ድንጋዩ የትንቢተ ነቢያት ምሳሌ ሲሆኑ መሰላሏ በድንጋይ ላይ ተተክላ ጸንታ ማየቱ እመቤታችን በነቢያት ትንቢት ጸንታ የመኖሯ ምሳሌ ነው፡፡ መሰላሏን መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት ማየቱ ዓለማቸውን ጌታችንን በፀነሰች ጊዜ መላእክት ማኅፀኗን ዓለም አድርገው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የማመስገናቸው ምሳሌ ነው፡፡ ጌታችንን በመሰላሉ ላይ በዙፋን ተቀምጦ ማየቱ እመቤታችን ጌታችንን በሰውነቱ ስትሸከመው እርሱም በመለኮትነቱ ይሸከማታልና ነው፡፡ አንድም ያዕቆብ የሊቃነ ጳጳሳት፣ የጳጳሳት፣ ድንጋዩ የታቦት፣ ዘይቱ የሜሮን ምሳሌ ሲሆኑ በድንጋዩ ላይ መሰላል በመሰላሉ ላይ ጌታችን መታየቱ የጌታችንና የእመቤታችን ስም በታቦት ላይ የመጻፉ ምሳሌ ነው፡፡ ዛሬም የጌታችንና የእመቤታችን ስም ያልተጻፈበት ታቦት ሊቀደስበትና ሊሰገድበት አይገባም፡፡ ያዕቆብም ሲነጋ አጎቱ ላባ ዘንድ ሄደ፡፡ አሻግሮም ሲመለከት የውኃውን ጉድጓድ አየ፡፡ የውኃውም ጉድጓድ በድንጋይ ተገጥሞ በድንጋዩ ላይ ሰላሳ በጎት ተኝተው ነበር፣ በጎቹን ከዚያ ያጠጧቸው ነበርና፡፡ እረኞቹም ትልቁን ድንጋይ አንስተው በጎቹን ያጠጧቸው ከጨረሱም በኋላ ትልቁን ድንጋይ መልሰው ይገጥሙት ነበር፡፡ ያዕቆብም ከእረኞቹ ጋር እየተነጋገረ እያለ የአጎቱ ልጅ ራሄል የአባቷን በጎች ይዛ መጣችና ያዕቆብ ድንጋዩን አንስቶ የአጎቱን በጎች አጠጣቸው፡፡ ከእርሷም ጋር ወደቤት ሄደ፡፡ ይኸውም ምሳሌ ነው፡፡ ያዕቆብ የጌታችን፣ በጎቹ የምእመናን፣ ድንጋዩ የአረፍተ ዘመን፣ እረኞቹ የነቢያት የካህናት፣ ውኃው የጥምቀት ምሳሌ ናቸው፡፡ በጎቹ ውኃው በድንጋይ ተዘግቶ ሳለ ዙሪያውን ከበው መተኛታቸው ምእመናን 5500 ዘመን እስከፈጸም ድረስ ዐረፍተ ዘመን ገቷቸው ተስፋ ጥምቀትን እየሰሙ ደጅ ሲጠኑ የመኖራቸው ምሳሌ ነው፡፡ እረኞች ከዚያ አስቀድመው ድንጋዩን አንሥተው በጎቹን ውኃ መጠጣታቸው ነቢያት መሥዋዕት ሠውተው ማየ ምንዛህ እረጭተው አፍአዊ ኃጢአት የማስተሠርያቸው ምሳሌ ነው፡፡ አንድም ነቢያት የጥምቀትን ነገር ተናግረዋልና ነው፡፡ መዝ 109፣ ኤር 2፡12፡፡ ያዕቆብ ብቻውን ድንጋዩን አንስቶ የተጠሙትን በጎች እንዳጠጣ ጌታችንም 5500 ዘመን ሲፈጸም ሰው ሆኖ ከምእመናን ፍዳ መርገምን በጥምቀት አጥፍቷል፡፡ ከዚህም በኋላ ላባ ያዕቆብን አንተ የሥጋዬ ቁራጭ የአጥንቴ ፍላጭ ነህና ከእኔ ጋር ተቀመጥ አለው፡፡ ያዕቆብም አብሮት ሲኖር ከላባ ሁለት ሴቶች ልጆች ውስጥ ትንሽቱን ራሄልን ስለወደዳት ላባን ‹‹ስለትንሹዋ ልጅህ ሰባት ዓመት ልገዛልህ እሷን ሚስት አድርገህ ስጠኝ›› አለው፡፡ ላባም እሺ አለው፡፡ ከሰባት ዓመትም በኋላ ሠርግ አድርጎ ላባ በራሄል ፋንታ ታላቋን ልያን ሸፋፍኖ ለያዕቆብ ሰጠው፡፡ እርሱም ማታ ሲጫወት አድሮ ጠዋት ቢያያት ልያ ሆና በማግኘቱ ላባን ‹‹ሰባት ዓመት የተገዛሁልህ ስለ ራሄል አይደልምን? ለምን እንዲህ ታደርገኛለህ?›› ቢለው ላባም ‹‹ታላቅ ሳለ ታናሽ አይዳርም›› አለው፡፡ ያዕቆብም እንደገና ሌላ ሰባት ተገዛለትና ራሄልን ሰጠው፡፡ ራሄልም መካን ሆና ሳለ ልያ ፀንሳ ሮቤልን ወለደች፡፡ ዳግመኛም ስምዖንን፣ ሌዊንና ይሁዳን ወለደች፡፡ ራሄልም እርሷ ብትመክን ያዕቆብን ከገረዷ ጋር እንዲተኛ እያደረገችው ዳንና ንፍታሌምን እንዲወልድ አደረገች፡፡ ልያም ራሄል ያደረገችውን አይታ እርሷም በተራዋ ያዕቆብን ከገረዷ ጋር እንዲተኛ እያደረገችው ጋድንና አሴርን እንዲወልድ አደረገች፡፡ ዳግመኛም ልያ ከያዕቆብ ይሳኮርንና ዛብሎንን እንዲሁም ሴቷን ዲናን ወለደች፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ራሄልን በረድኤት ጎብኝቷት ፀንሳ ዮሴፍን ወለደች፡፡ ያዕቆብም ዮሴፍን ከወለደ በኋላ ወደ ርስቱ አገር እንዲመለስ

አብርሃምም ከሰዶምና ገሞራ ጥፋት በኋላ በምሥራቅ በኩል ወዳለው ሀገር ሄዶ በጌራራ ከተቀመጠ በኋላ እግዚአብሔር አስቀድሞ እንደነገራቸው ሣራ ወንድ ልጅ ወለደች፡፡ አብርሃምም ስሙን ይስሐቅ ብሎ ጠራው፣ በ8ኛውም ቀን ገዘረው፡፡ ከብዙ ጊዜም በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ልጁን ይስሐቅን ወደ አንድ ተራራ ላይ ወስዶ በዚያ ላይ እንዲሠዋለት ባዘዘው ጊዜ አብርሃም በጠዋት ተነሥቶ አህያውን ጫነ፡፡ ልጁ ይስሐቅንና ሁለቱን ብላቴኖቹንም ወስዶ ለመሥዋዕት የሚሆነውን ዕንጨት ፈልጦ አሸክሞ ሄደ፡፡ በ3ኛውም ቀን እግዚአብሔር ወዳዘዘው ቦታ በደረሰ ጊዜ ሁለቱን ብላቴች ‹‹እናንተ አህያውን ይዛችሁ ከዚህ ቆዩ፣ እኔና ልጄ ግን ወደ ተራራው ሄደን ሰግደን ተመልሰን እንመጣለን›› አላቸውና ከዚያ አስጠብቋቸው ልጁንም ዕንጨቱን አሸክሞት ወደ ተራራው ወጣ፡፡ እርሱም ወቅለምቱንና እሳቱን በእጁ ይዞ አብረው ሄደው በቦታው ሲደርሱ አብርሃም ዕንጨቱን በመሠዊያው ላይ ረበረበ፡፡ ይስሐቅም አስቀድሞ አባቱን ‹‹እነሆ ዕንጨቱና እሳቱን አለ ለመሥዋዕት የሚሆነው በግ ግን ወዴት አለ?›› ብሎ ሲጠይቅ አብርሃም ‹‹እግዚአብሔር ያዘጋጃል›› ያለው ቢሆንም ይስሐቅ ግን በዚህ ጊዜ ራሱ መሥዋዕት እንደሚሆን ዐውቆ አባቱን እንዲህ አለው፡- ‹‹እነሆ እኔን ስትሠዋኝ ስወራጭ እጅህን እንዳላስቆርጥህ እጄን እግሬን እሰረኝ›› አለው፡፡ ዳግመኛም ይስሐቅ ‹‹ዐይኔ ብክን ብክን ሲል ተመልክተህ ራርተህ ትተኸኝ ከፈጣሪህ ትጣላለህና ፊቴን ወደ መሬት ደፍተህ አስተኝተህ ሠዋኝ›› አለው፡፡ አብርሃምም ልጁ እንዳለው እጁንና እግሩን አስሮት ፊቱን ወደ ምድር በመድፋት በመሠዊያው በእንጨቱ ላይ አጋደመው፡፡ አብርሃምም ልጁን ያርደው ዘንድ ወቅለምቱን (ቢላዋውን) መዞ እጁን በዘረጋ ጊዜ እግዚአብሔር አብርሃምን ጠራውና ‹‹በብላቴናው ላይ እጅህን አትዘርጋ፣ አንዳችም አታድርግበት፤ አንድ የምትወደውን ልጅህን ከእኔ ይልቅ አልወደድክምና እኔን የምትፈራና የምትወድ እንደሆንህ አሁን ዐውቄአለሁ›› አለው፡፡ አብርሃምም ዐይኑን ባነሣ ጊዜ በኋላው አንድ ጸዐዳ በግ በዱር ውስጥ ቀንዶቹ በዕፀ ሳቤቅ ተይዞ አየ፡፡ በጉንም ወስዶ በልጁ ፋንታ መሥዋዕት አድርጎ ሠዋው፡፡ ዘፍ 22፡1-14፡፡ ይኸውም ምሳሌ ነው፣ አብርሃም የእግዚአብሔር አብ፣ ይስሐቅ ደግሞ የእግዚአብሔር ወልድ ምሳሌ ነው፡፡ አብርሃም አንድያ ልጁን ይስሐቅን በሕሊናው ሠውቶታልና አብም አንድያ ልጁን ወልድን በሥጋ ሠውቶታል፡፡ በጉ የታሰረበት ዕፅ የቅዱስ መስቀሉ፣ እሳቱ የመንፈስ ቅዱስ፣ ወቅለምቱ (ቢላዋው) የሥልጣነ እግዚአብሔር ምሳሌ ናቸው፡፡ ወቅለምት አጥንትን ከሥጋ እንደሚለይ ሁሉ ጌታንችንም በገዛ ሥልጣኑ ነፍሱን ከሥጋው ለይቷል፡፡ አብርሃም ሦስት ቀን በእግሩ ተጉዞ ሄዶ ልጁን እንደሠዋው ሁሉ ጌታችንም ምክረ ሞቱ በተፈጸሞ በሦስተኛው ቀን ተሠውቷል፡፡ የአብርሃም ኅሊና የመቃብር ምሳሌ ነው ይህም ይስሐቅ በአብርሃም ኅሊና በተሠዋ በሦስተኛው ቀን እንደዳነ ሁሉ ጌታችንም ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሮ የመነሣቱ ምሳሌ ነው፡፡ እንዲሁም በጉ የጌታችን ይስሐቅም የምእመናን ምሳሌ ናቸው፡፡ ጸዐዳ በጉ ከሰማይ እንደወረደ ሁሉ ጌታችንም ከሰማየ ሰማያት ወርዷል፤ በጉ ከዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ ሁሉ መድኃኔዓለም ክርስቶስም ከእመቤታችን የማኅፀን ፍሬ ተገኝቷል፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ የጸዐዳ በጉ ምሳሌ እንደሆነ ሁሉ ጸዐዳ በጉን የያዘችው ዕፀ ሳቤቋ ወይም ሐረጓ ደግሞ የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ በጉ ከኅቱም ጉንደ ዕፅ ተገኝቶ ለይስሐቅ መድኀኒት ሆኖ በሞርያ ተራራ እንደተሠዋ ሁሉ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግደው በግ መድኃኔዓለም ክርስቶስም ከእመቤታችን በድንግልና ተወልዶ በቀራንዮ ተሠውቷል፡፡ ኢሳ 53፡7፣ 1ኛ ጴጥ 1፡19፣ራእ 7፡10፡፡ ይህንንም ዮሐንስ መጥምቅ ሲገልጠው ‹‹የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ›› ሲል ተናግሮለታል፡፡ ዮሐ 1፡29፡፡ በመጨረሻም እግዚአብሔር አብርሃምን ‹‹500 ዓመት ትኖራለህ›› ቢለው አብርሃም ‹‹1000 ዘመን ኖሬ እንደገና ካልታደስኩ በቀር ለ500 ዘመንስ ቤት አልሠራም›› ብሎ ዕድሜ ዘመኑን ሁሉ ቤት ሳይሠራ በድንኳን ኖሯል፡፡ ሚስቱ ሣራ በ127 ዓመቷ ስትሞት በኬብሮን መቃብር ገዝቶ አልቅሶ ከቀበራት በኋላ እርሱም ከብዙ ጊዜ በኋላ በ175 ዓመቱ ነሐሴ 29 ቀን ዐርፎ ከሚስቱ ጋር በኬብሮን ተቀብሯል፡፡ በሀገራችን በስሙ የተሠሩ ሦስት አብያተ ክርስቲያናት አሉ፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀል በአብርሃም ስም የተሠራውን ታቦት ከግብፅ ለመጀመሪያ ጊዜ አስመጥተውታል፡፡ ይስሐቅ ማለት ‹‹ይስቃል›› ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን ለአብርሃም ገልጦለት ሳለ ምንም እንኳን በዕድሜአቸው ያረጁ ቢሆኑም እርሱና ሚስቱ ሣራ ልጅ እንደሚወልዱ እግዚአብሔር ሲናገር ሣራ ብትሰማ እውነት አልመስላት ብሎ ስቃ ነበር፡፡ ዘፍ 18፡10-15፡፡ ይስሐቅ አባታችን አባቱ አብርሃም በመቶ ዓመቱ እናቱ ሣራ በዘጠና ዓመቷ ሁለቱም ካረጁ ካፈጁ በኋላ የወለዱት አንድያ ልጃቸው ነው፡፡ አብርሃም ከደግነቱና እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በተመሳቀለ ጎዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ የወጣ የመረደውን፣ የመጣ የሄደውን ሁሉ እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ የሚኖር እጅግ ጻድቅ ሰው ስለነበር አብርሃም በወይራ ግራር (በመምሬ) ዛፍ ሥር ተቀምጦ እንግዳ እየጠበቀ ሳለ ነው እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠለት፡፡ ዘፍ 18፡1-25፣ ሮሜ 4፡-3፡፡ አብርሃምም ሥላሴን ወደ ወደ ቤቱ አስገብቶ በሚገባ አስተናገዳቸው፡፡ እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወለደ፡፡ ይስሐቅም 40 ዓመት በሆነው ጊዜ የላባ እኅት የምትሆን በሶርያ ወንዞች መካከል የሚኖር የሶርያውን ሰው የባቱኤልን ልጅ ርብቃን ከእናቱ ሞት በኋላ አግብቶ በእርሷ ከሀዘኑ ተጽናና፡፡ ለ20 ዓመትም ያህል እርሷ መካን ሆና ከኖረች በኋላ በአንድ ቀን ሩካቤ መንታ ልጆችን ፀነሰች፡፡ ይስሐቅም 60 ዓመት በሆነው ጊዜ ርብቃ ሁለት ወንዶች ልጆችን ኤሳውንና ያዕቆብን ወለደች፡፡ እነርሱም በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ ይጣሉ ነበር፡፡ ባደጉም ጊዜ ኤሳው አደን የሚያውቅ ሲሆን ያዕቆብ ከቤት የሚውል ቅምጥል ሆነ፡፡ ይስሐቅም አርጅቶ ነበርና ኤሳው ከዱር አድኖ የሚያመጣለትን ስለሚመገብ ኤሳውን ይወደው ነበር፡፡ ርብቃም ደግሞ ከኤሳው ይልቅ ያዕቆብን ትወደው ስለነበር የምስር ወጥ ትሠራለት ነበር፡፡ አንድ ቀን ኤሳው አደን ውሎ እርቦት ደክሞት ከዱር ሲመጣ ያዕቆብን ከምስር ወጡ እንዲሰጠው ለመነው፡፡ እርሱም ‹‹እልቅናህን ስጠኝና እሺ እሰጥሃለሁ›› አለው፡፡ ኤሳውም ‹‹እኔ በርሃብ ከምሞት በኩር መሆን ምን ይጠቅመኛል? ያውልህ ውሰደው›› አለው፡፡ ያዕቆብም እልቅናውን በመሐላ ካጸናለት በኋላ ዳቦውን ንፍሮውን የምስር ወጡንም በእንጀራ አድርጎ ሰጠው፡፡ ኤሳውም በልቶ ጠጥቶ ሄደ፡፡ ይኸውም ኤሳው የአይሁድ ያዕቆብ የምእመናነ አሕዛብ ምሳሌ ናቸው፡፡ ኤሳው መብሉን ወዶ እልቅናውን እንደሸጠ ሁሉ አይሁድም መሥዋተ ኦሪትን ወደው ብኩርናቸውን ለምእመናነ አሕዛብ አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ ይስሐቅም አርጅቶ ዐይኖቹ ፈዘው የማያይ ከሆነ በኋላ ታላቁ ልጁ ኤሳውን ጠርቶ ወደ በረሃ ሄዶ የሚወደውን ምግብ አድኖ እንዲያመጣለት ላከው፡፡ ኤሳውም ወደ አደን ሲሄድ ርብቃ ታናሹን ልጇን ያዕቆብን ሁለት የበግ ጠቦቶችን አባቱ እንደሚወደው አድርጎ እንዲያዘጋጅና እንዲመረቅ ነገረችው፡፡ እርሷም የኤሳውን ልብስ አለበሰችው፡፡ ወደ አባቱም ገብቶ ምግቡን አቅርቦ

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን ነሐሴ 28-የከበሩ ቅዱሳን አባቶቻችንን የአብርሃም፣ የይስሃቅና የያዕቆብ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ የሁሉ አባት አብርሃም ፍጥረትን በመመርመር አምላኩን ካገኘ በኋላ እግዚአብሔር ተገልጦለት አንድነቱንና ሦስትነቱን አስረድቶታል፡፡ ከዚህም በኋላ አብርሃም እቤት ሄዶ ቤተ ጣዖቱን አቃጠለው፡፡ በዚህም ጊዜ የጣዖት ቤቱ አጋፋሪ የነበረው የሎጥ አባት የሆነው አራን ወደ እሳቱ በመግባት አብሮ ተቃጥሎ በመሞት ሰማዕተ ጣዖት ሆኗል፡፡ ወንድማቸው በዚህ መልኩ ከሞተ በኋላ ሁለቱ የታራ ልጆች አብራምና ናኮር ሚስት አገቡ፡፡ ታራም ልጁን አብርሃምን ከሚስቱ ከሳራ ጋር የአራንን ልጅ ሎጥን ይዞ በመነሣት ወደ ከነዓን ይሄዱ ዘንድ ከከላውዴዎን አወጣቸው፡፡ ካራን በደረሱም ጊዜ ከዚያ እየኖሩ ታራ በ205 ዓመቱ በካራን አገር ሞተ፡፡ እግዚአብሔር ለአብርሃም ተገልጦለት ‹‹አብርሃም አብርሃም›› ብሎ ጠራውና ከዘመዶቹና ከወገኖቹ ተለይቶ በመውጣት ወደ ከነዓን ምድር እንዲሄድ ነገረው፡፡ ዘሩን እንደሚያበዛለትና እንዲባርከው የሚመርቁትን እንደሚባርካቸው፣ የሚረግሙትን ግን እንደሚያጠፋቸው ቃል ገባለት፡፡ አብርሃምም እንደታዘዘው ወደ ከነዓን ሄደ፡፡ አብርሃም መጀመሪያ በካራን ከአባቱ ጋር አብረው 14 ዓመት ተቀመጡ፡፡ ወደ ከነዓንም ከወጣ በኋላ በከነዓን 30 ዘመን ኖረ፡፡ ለአብርሃም 105 ለታራ ደግሞ 205 ሲሆናቸው አብርሃምን አባትህ ሞተ ብለውት ተመልሶ ወደ ካራን መጥቶ አባቱን ቀብሮ ተቀምጦ ሳለ ድጋሚ ወደ ከነዓን ታዞ ሄዷል፡፡ በዚህም ጊዜ ሚስቱን ሣራንና የወንድሙን ልጅ ሎጥን ይዟቸው ወጣ፡፡ በከነዓንም ሳለ ረሀብ ተከሥቶ ወደ ግብፅ ተሰደደ፡፡ በዚያም ስለ ሚስቱ ውበትና ማማር እንዳይገድሉት ፈርቶ ሚስቱን ሣራን እኅቴ ናት ብሎ ሲናገር ‹‹ይህችስ ለንጉሱ ትገባለች›› ብለው ወስደው ለንጉሡ ለፈርዖን ሰጧት፡፡ እግዚአብሔርም በፈርዖን ላይ ጽኑ ደዌን አመጣበት፡፡ ይኸውም ብልቱ አብጦ ትራስ አክሎ ነበር፡፡ እርሱም የአብርሃም ሚስት መሆኗን ካወቀ በኋላ አብርሃምን ጠርቶ ‹‹ለምን ዋሽተህ ይህን በሽታ በኔ ላይ አመጣህብኝ›› ካለው በኋላ ሚስቱን መልሶለት ገንዘብ ሰጥቶት እንዲሸኙት አዘዘ፡፡ አብርሃምም ከሚስቱና ከሎጥ ጋር በቤቴል መኖር ጀመረ፡፡ በወርቅና በብር በከብት ብዛትም እጅግ ባለጸጋ ሆነ፡፡ ሎጥም እንዲሁ ሀብታም ስለሆነ እረኞቻቸው እየተጣሉ ቢያስቸግሯቸው ሁለቱ ተመካክረው በተለያየ ቦታ መኖር ጀመሩ፡፡ አብርሃም በከነዓን ሲቀር ሎጥም ሲያያት ባማረችው በሰዶም ገብቶ ኖረ፡፡ አብርሃም ከሎጥ በመለየቱ ሲያዝን እግዚአብሔር አብርሃምን ‹‹ዘርህን እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደምድር አሸዋ አበዛዋለሁ›› አለው፡፡ የሰማይ ከዋክብት የተባሉት በሃይማኖትም በግብርም መስለውት የሚኖሩትን ሲሆን የምድር አሸዋ የተባሉት ግን አሕዛብ ናቸው፡፡ አምስቱ የሰዶምና የገሞራ ነገሥታት ለአራቱ ለኮሎዶጎሞርን ነገሥታት 12 ዓመት ሲገብሩ ኖረው በ13ኛው ዓመት አንገብርም ብለው ተዋጉ፡፡ አራቱ የኮሎዶጎሞርን ነገሥታት ድል አድርገው ሲመለሱ ሎጥንም አብረው ማርከውት ወሰዱት፡፡ አብርሃምም ይህን ሲሰማ ከዘሮቹ 318 ሰዎችን ይዞ ሄዶ አራቱን የኮሎዶጎሞርን ነገሥታት ድል አድርጎ የተማረከ ወንድሙን ሎጥን መልሶታል፡፡ ይኸውም አብርሃም የጌታችን፣ ሎጥ የሃይማኖት፣ 318ቱ የአብርሃም ሰዎች ሃይማኖትን ያቀኑ የ318ቱ ሊቃውንት ምሳሌ ናቸው፡፡ አራቱ የኮሎዶጎሞርን ነገሥታት የመናፍ*ቃን፣ አምስቱ የሶዶም ነገሥታ ደግሞ የምእመናን ምሳሌ ናቸው፡፡ አብርሃም 318 ሰዎችን ይዞ አሕዛብን ድል አድርጎ የተማረከውን ሎጥን እንደመለሰ ሁሉ ጌታችንም በ318ቱ ሊቃውን ላይ አድሮ ሃይማትኖን መልሷል፡፡ አብርሃምም ከዚህ በኋላ ድል በማድረጉ ደስ ብሎት ለአዳምና ለልጆቹ የመዳን ተስፋን የሰጠውን አምላክ በዐይነ ሥጋ ለማየት ተመኝቶ እግዚአብሔርን ‹‹ልጅህን በዘመኔ ትልከዋለህ? ወይስ ዕለቷን ታሳየኛለህ?›› ብሎ በጸሎት ጠየቀ፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹ያችንስ ዕለት የማሳይህ አይደለም ይልቁንም ምሳሌዋን ታያለህ እንጂ፣ ዮርዳኖስን ተሻግረህ መልከ ጼዴቅን ታገኛለህ›› ብሎ ምሳሌውን ነገረው፡፡ አብርሃምም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ሲሄድ እጅግ ታላቅ ግርማ ያለውን መልከ ጼዴቅን አይቶ ደነገጠ፡፡ መልከ ጼዴቅም ካበረታው በኋላ ‹‹አንተን ወደዚህ የላከህ እግዚአብሔር እኔን ኅብስተ አኰቴት ጽዋ በረከት ይዤ ወደ አንተ እንድመጣና እንድሰጥህ አዞኛል›› በማለት ከያዘው ኅብስትና ወይን ሰጥቶት ባርኮታል፡፡ አብርሃምም ከያዘው ሁሉ ዓሥራት ሰጥቶታል፡፡ ከዚህም በኋላ አብርሃም በኋለኛው ዘመን አካላወዊ ቃል ከእመቤታችን ተወልዶ ሥጋውን ደሙን በኅብስትና በወይን የሚሰጥ መሆኑን ዐውቆ እጅጉን ተደስቷል፡፡ ይህንንም ጌታችን ወንጌልን ለአይሁድ ሲሰብክላቸው ‹‹አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሴት አደረገ፣ አየም ደስም አለው›› በማለት አስረድቷቸዋል፡፡ ዮሐ 8፡56፡፡ ዮርዳኖስ የጥምቀት ምሳሌ ነው፡፡ አብርሃም ተጠምቀው ልጅነትን ያገኙ ክርስቲያኖች ምሳሌ ሲሆን መልከ ጼዴቅ የቀሳውስት፣ ኅብስተ በረከት ጽዋዓ አኰቴት የሥጋ ወደሙ ምሳሌ ናቸው፡፡ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ካገኘው ሁሉ ከዐሥር አንድ እንደተቀበለው ጌታችንም ከምእመናን ዓሥራተ ጾምን ዐሥራተ ጸሎትን ዐሥራተ ምጽዋትን የመቀበሉ ምሳሌ ነው፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ‹‹ባለጸጋ አደርግሃልሁ›› ቢለው አብርሃም ‹‹ልጅ የለኝ ሀብት ብትሰጠኝ ምን ያደርግልኛል?›› አለው፡፡ እግዚአብሔርም ከአብራክህ የሚወለደው ልጅህ ይወርስሃል ካለው በኋላ ዘሩን እንደሰማይ ከዋክብትና እንደምድር አሸዋ እንደሚያበዛለት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይህን የተነገረውን በማመኑ ጽድቅ ሆኖ ተቆጥሮለታል፡፡ ይኸውም ምሳሌ ነው፣ እስራኤል ልጆቹን በከዋክብት አሕዛብ ልጆቹን ደግሞ በአሸዋ መስሎ አሳይቶታል፡፡ አንድም በሥጋም በሃይማኖትም የሚወልዳቸውን ጻድቃን ልጆቹን በከዋክብት ሲመስላቸው በሥጋ እንጂ በሃይማኖት የማይወልዳቸውን ኃጥአን ልጆቹን ደግሞ በአሸዋ መስሎ አሳይቶታል፡፡ ሥላሴ የገቡባት የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ሁሉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋዋን ለመዋሐድ የማደራቸው ምሳሌ በመሆኑ አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ናት፡፡ ሉቃ 1፡35፡፡ እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል፡፡ ሁለቱ ሰዎች ከአብርሃም ድንኳን ወጥተው ወደ ሰዶም ወደ ገሞራ ሄዱ፣ አብርሃምም ይሸኛቸው ዘንድ አብሯቸው ሄደ፡፡ የሄዱትም ሁለቱ ሰዎች አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዱ ወልድ በአብርሃም ቤት ቀርቷል ይኸውም ከቤተ አብርሃም ሰው እንደሚሆን ለማጠየቅ ነው፡፡ አብርሃምም ተመልሶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ፡፡ እግዚአብሔርም የሚሠራውን ሁሉ ከአብርሃም አይሠውርም ነበርና የሰዶምን የገሞራን ጥፋት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይቅር እንዲላቸው እጅግ አብዝቶ ለመነላቸው፡፡