ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ውስጥ የተጻፉ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸውና አስገራሚ ታሪካቸው ዓመቱን ሙሉ ምንም ሳይቋረጥ በየቀኑ ይነገርበታል! ለአሥትያየትዎ @abitago
Ko'proq ko'rsatish1 215
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+37 kunlar
+430 kunlar
Postlar arxiv
1 215
ደብረ መድኃኒት አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አንድነት ገዳም!
በዚኽች ዕለት ሐምሌ 26 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ስታስበው የሚውሉት ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ያደረጉት ታላቅ ተአምር ይኽ ነው፦ ‹‹ምንም ሳያስታጉል በየቀኑ ዕጣን የሚያሳርግ ወደ እግዚአብሔር መጸለይን የሚያበዛ ለአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ቤተ ክርስቲያን የሚላላክ አንድ መነኩሴ ነበር፡፡ ከዕለታትም በአንዲት ቀን እንቅልፍ መጥቶበት ተኝቶ ሳለ በዚያች ዕለት ሕልመ ሌሊት አገኘው፡፡ ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ሕልመ ሌሊት እንዳገኘው አይቶ ስለ አቡነ ሰላማ ቤ/ክ ማዕጠንት መታጎል ታላቅ ኀዘን አዘነ፡፡ ያንጊዜም ሰይጣን ከሰይጣን ጋራ ‹‹…ወዳጄ ይህን መነኩሴ ዛሬ ጣልኩት፣ ከአገልግሎቱም አስታጎልኩት አየህን!›› እያለ ሲናገር ሰማው፡፡ ሌላኛውም ሰይጣን መልሶ ‹‹…ወዳጄ መልካም አድርገሃል፣ መጥጠተህ አፌን ሳመኝ›› አለውና ሁለቱም እርስ በእርሳቸው አፍ ለአፍ ሲሳሳሙ ያ መነኩሴ ይህን አይቶና ሰምቶ በመናደድ ድጋሚም በዚህ እንዳይፈተን በማሰብ ስለት ባለው ምላጭ አባለ ዘሩን ቆርጦ ጣለውና የብልቱን ቁራጭ ወደታላቅ ገደል ወረወረውና ለሰይጣን ‹‹ይህን እንካ እንደውሻ ቆጥሬልሃለሁና›› አለው፡፡
ሰይጣኑም ወዲያው በዱር አሞራ ተመስሎ የብልቱን ቁራጭ ጠልፎ ወሰደ፡፡ ነገር ግን የእግዚብሔር ሰው ድንቅ ተአምራትንም የሚያደርግ አባታችን ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ወዲያው ታላቅ የሆነ ነጭ ንስር መስሎ እየበረረ ሔዶ የመነኩሴውን የብልቱን ቁራጭ ከሰይጣን አፍ ቀምቶ ያንን ሰይጣን በሰይፍ ቆረጠውና ወደ አገልጋዩ መነኩሴ ቢሔድ ስለአገልግሎቱ መታጎል እያዘነ አገኘው፡፡ አባታችንም ‹‹…ወዳጄ አገልጋዬ ሆይ! እነሆ የሰውነትህን ብልት እንካ እንደቀድሞው ከሰውነትህ መልሼልሃሁ፤ እግዚአብሔር የፈጠረውን አካል ዳግመኛ አትቁረጥ፣ አስቀድሞም ከነበሩ በኋላም ከሚነሡ ይህንን ፈተና ታግሠው ካላላፉ ጽድቅ የለምና በቤተ ክርስቲያን ክህነትና ማዕረግ አይኖርህምና አካልህን አታጉድል፣ ሳትመረር ፈተናውን ታገሥ እንጂ፡፡ ያለመከራና ያለሥቃይ ጸጋ አትገኝምና…›› እያለ ከመከረው በኋላ ብፁዕና ቅዱስ ማር አቡነ ሰላማ ከመነኩሴው ተሰውሮ ዐረገ፡፡
ከዚህ በኋላ ያ መነኩሴ ፈጽሞ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ እስካረፈበት ዕለት ድረስ ጸሎትን አበዛ፡፡ በሞት ባረፈም ጊዜ በአባታችን ጸሎት መንግሥተ ሰማያትን ወረሰ፡፡›› (ገድለ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገጽ 81-82)
አባታችን ባረፈ ጊዜ በዚህ አስደናቂ ገዳም ላይ ራሱ ጌታችን በአካል ለአባታችን ተገልጦላቸዋል፡፡ አባታችን ማር ሰላማም ቡሩካን በሆኑ እጆቹ ምድሪቱን እንደመሶብ አንሥቶ በሥሉስ ቅዱስ መንበር ፊት አቅርቦ አስባርኳታል፡፡ የገዳሙ አቀማመጥ እጅግ አስገራሚ ነው-ልክ እንደ ግሸን መስቀለኛ ቅርጽ ያለው ሲሆን በአራቱም አቅጣጫ የተለያዩ ምሥጢራት አሉት፡፡ በገዳሙ ምዕራባዊ ክፍል አስደናቂው ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ፣ በስተምሥራቅ የጻድቁ ቅዱስ መካነ መቃብር፣ በስተደቡብ መግቢያ በሩ፣ በስተሰሜን ጻድቁ ከዐለት ላይ ያፈለቋቸው ፈዋሽ ጠበሎች ይገኛሉ፡፡
ለማር አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከሰማይ የወረደላቸው የእጅ መስቀላቸውና ቅዱስ መካነ መቃብራቸው በዚሁ ገዳም ይገኛሉ፡፡ ታላቅ ጻዲቅ፣ መናኝ፣ ሐዋርያ፣ ጳጳስ....የሆነው ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን በድፍን ኢትዮጵያ በአራቱ አቅጣጫ እየዞረ በተአምራቱ ድውያንን እየፈወሰ፣ ሙታንን እያስነሣ፣ ወንጌልን እያስተማረ፣ እያጠመቀ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እየሠራና አገልጋይ የሚሆኑ ቀሳውስትን እየሾመ በሀገራችን ላይ ብርሃንን የፈነጠቀ ለኢትዮጵያ መግለጽ ከሚቻለው በላይ ታላቅ ባለውለታዋ ነው፡፡ ከአቡነ ሰላማ በፊት እኛ ኢትዮጵያውያን ክርስቶስን ከማመን በቀር ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ የመቀበል ልማድ አልነበረንም፡፡ በድንኳን ካለችው ታቦተ ጽዮን በቀርም ታቦታትና አብያተ ክርስቲያናትም ፈጽሞ አልነበሩንም፡፡ ይህን ሁሉ ያገኘነው በማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ነው፡፡ ይሄ ሁሉ ሲታሰብ ከአባ ሰላማ ውለታ አንጻርና እንደሠራላት እጅግ ታላቅ ሥራ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቁን እንደሚገባው መጠን አላከበረችውም ማለት ይቻላል፡፡ ጌታችንም በመጨረሻ ቃልኪዳን ሲሰጠው ‹‹ስለ ትምህርትህና ስለ ስብከትህ ኢትዮጵያን ከጨለማ አውጥተህ በሃይማኖት ስለ አበራሃት ከፍ ያሉ ክብራትንና ማዕረጋትን ፈጽሜ ሰጠሁህ›› ነው ያለው፡፡
የማር አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
1 215
እመቤታችንና ጠባቂዋ የነበረው የ83 ዓመቱ አረጋውያን ዮሴፍ በግብፅ ሳሉ ግብፃውያን እንደ ሕጋቸው ለአማልክቶቻቸው ላሞችን አርደው ሠውላቸው፡፡ በጎሽ፣ በአውራሪስ፣ በነጭ ዝንጀሮ የሚመሰሉ አጋንንትም መጡ፡፡ እመቤታችንም ከሩቅ ሆና ተመልክታቸው እነዚያን አጋንንት በጸሎቷ እንደጢስ በተነቻቸው፡፡ ግብፃውያንም ፈርተው እየጮኹ ሸሹ፡፡ በዚያም ወራት ‹‹ረዳት አማልክቶቻችንን ጠፉብን›› ብለው እያዘኑ ሳለ ዮሴፍን ሲጸልይ አግኝተውት አስረው በምድር ላይ አስተኝተው 40 ግርፋት ገረፉት፡፡ እርሱም በዚህ ጊዜ ‹‹እመቤቴ ሆይ ስለ አንቺና ስለ ልጅሽ ይህ መከራ አግኝቶኛልና እርጂኝ›› ብሎ በኀይል ጮኸ፡፡ እመቤታችንም ድምጹን ስትሰማ የሄሮድስ ጭፍሮች የመጡ መስሏት እጅግ ደነገጠች፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ተገልጦ ካረጋጋት በኋላ ዮሴፍን በኀይል ይደበድቡ የነበሩትን በእሳት ሰይፉ ጨረሳቸው፡፡ ዮሴፍንም በእጆቹ ዳሰሰውና ፈወሰው፡፡ እመቤታችንም ዮሴፍን ባየችው ጊዜ ‹‹ይህ ሁሉ መከራ ያገኘህ በእኔና በልጄ ምክንያት ነው›› ብላው አንገት ለአንገት ተቀቅፈው ተላቀሱ፡፡ መልአኩም ‹‹ይሄ ሀዘናችሁ በደስታችሁ ጊዜ ይረሳል…›› እያለ አረጋጋቸውና ዐረገ፡፡
ጌታችንን በእጆቹ ሥራ እየመገበ እንደ አባት ሆኖ ያሳደገው የአረጋዊው የቅዱስ ዮሴፍ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
1 215
አላቸውና ጊዜው ገና መሆኑን አስረድቶት ሄሮድስን በጦር እንዳይገድለው ከለከለው፡፡ ደማትያኖስም ኃይሉና ጦሩ እጅግ የበረታ ነበር፡፡ ቅዱስ ጊጋርም በዚህ ወቅት ስለ እመቤታችንና ስለልጇ ሰማዕት ሆነ፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ለእመቤታችን ተገልጦ ወደ ግብፅ እንድትሄድ ነገራት፡፡ ዳግመኛም መልአኩ ለገዥው ለደማትያኖስ ተገልጦለት ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ እንዲያሰናብታት ነገረው፡፡ እርሱም አስቀድሞ ‹‹በዙፋኔ ተቀመጪ እኔና ሚስቴ አገልጋይሽ እንሁን እንጂ ከዚህስ አትሄጂም›› ብሎ ግድ ብሏት ነበርና፡፡ ከዚህም በኋላ የአንድ ቀን መንገድ ሸኝቷት እንዲህ አላት፡- ‹‹እመቤቴ ሆይ ሄሮድስ ቢፈልግሽ ወደኔ መልእክት ላኪብኝ ፈጥኜ እመጣለሁ፡፡ የእስራኤል አምላክ ቢፈቅድልኝ ከዛብሎን፣ ከንፍታሌምና ከሐሴቦን ጀምሮ ይሁዳንና ኢየሩሳሌምን ሁሉ አጠፋቸዋለሁ፡፡ ሰውን ብቻ የምገድል አይደለሁ ዛፎቻቸውን ቆመው እንዲታዩ አልፈቅድም፡፡ ሀገሪቱንም ፍርስራሽ አደርጋታለሁ›› አላት፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዳልሆነ አስረድታው መርቃ አሰናበተችውና በበነጋታው ተለያዩ፡፡ ወደ ቤተልሔምም ከደረሱ በኋላ አሁንም መልአኩ አዘዛቸውና በሌሊት ተነሥተው ወደ ግብፅ ተጓዙ፡፡ ሄሮድስም ሀገሪቱን መጥቶ ከበባት፡፡ እነርሱንም ቢያጣ በዚያ ያገኘውን ሁሉ ሰየፈ፡፡ 2 ዓመትና ከዚያ በታች ያሉ ሕፃናትን ሁሉ ሰብስበው እንዲያመጡአቸው አዘዘና 144 ሺህ የቤተልሔም ሕፃናትን ከእናቶቻቸው ላይ እየቀማ ሰየፋቸው፡፡ መላእክትም እጅግ ደንግጠው ይህ ለምን እንዲሆን ፈቀድክ ብለውም አምላካቸውን ጠየቁ፡፡ እንዲህ የሚል ቃልም ከዙፋኑ ወጣ፡- ‹‹ኢየሩሳሌም በሰው ደም እንደምትታጠብ በነቢያት እንዲሁ ተጽፏልና እነዚህ ሕፃናት ለመንግሥተ ሰማያት ቀድመው ተዘጋጁ ናቸው፡፡››
እመቤታችንና እነ ዮሴፍም ግብፅ ደርሰው በዚያ ቢቀመጡም ነገርን ግብፅ አልተመቸቻውም፡፡ ሕዝቡም በሰላም አልተቀበላቸውም፡፡ ወደ ኢትዮጵያ በመጡ ጊዜ ግን ሕዝቡ ሁሉ በሰላም ተቀበላቸው፡፡ ከመንገዱና ከርሃብ ጥሙ ጽናት የተነሣ እጅግ ደክማለችና የኢትዮጵያ ሰዎች እመቤታችንን አይተው እጅግ አዘኑላት፡፡ ‹‹ይህችስ የነገሥታት ዘር ትመሥላለች ነገር ግን አንዳች ችግር አጋጥሟት ተሰዳ ወደ ሀገራችን መጥታለች..›› ብለው እንክብካቤን አደረጉላት፡፡ እግራቸውን አጥበው በክብር ማረፊያዎች ላይ አሳረፏቸው፡፡ መልካም መስተንግዶም አደረጉላቸው፡፡ እመቤታችንም ከድካሟ ካረፈች በኋላ ሀገሪቱን በእጅጉ ወደደቻትና የተወደደ ልጇን ‹‹ይህን ሀገርና ሕዝቧን በመላ ወድጃቸዋልሁና በዚህ እስከ መጨረሻው እንኑር›› አለችው፡፡ ጌታችንም ክብርት እናቱን ‹‹ይህች ቅድስት ሀገር ናት፣ በኋለኛው ዘመን የቅዱሳን መነኮሳት ቦታ ትሆናለች፡፡ በውስጧም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እመሰገንባታለሁ፤ የአንቺም ስም ሳይጠራ አይውልባትም›› አላት፡፡
ከዚህም በኋላ ጌታችን ደመና ጠቅሶ በእርሷ ላይ ተቀመጡ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤልም መጣና እየመራቸው መላ ኢትዮጵያን ጎበኟት፡፡ እመቤታችንም ሀገሪቱንና ሕዝቦቿን ወዳቸዋለች ደስም ተሰኝታባቸዋለችና ጌታችን ለክብርት እናቱ ‹‹ይህችን ቅድስት ሀገር አሥራት አድርጌ ሰጠሁሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም እጅግ ተደስታ ‹‹ልጄ አምላኬ›› ብላ አመሰገነችው፡፡ ከዚህም በኋላ ከአብዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ እየተዘዋወሩ መላዋ ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባረኳት፡፡ ጌታችንም ‹‹በዚህ ቦታ እንዲህ ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል፤ እከሌ የሚባል እንዲህ ዓይነት ቅዱስ ይነሣል…›› እያለ ብዙ ምሥጢራትን ለእናቱ ነገራት፡፡ ከዚህም በኋላ የስደቱ ዘመን ሲያልፍ ሄሮድስም በመጨረሻ ክፉ አሟሟትን ሲሞት መልአኩ ወደ ገሊላ አውራጃ እንዲመለሱ ነገራቸው፡፡ እመቤታችንም ‹‹ከዚህች ሀገርስ ባንሄድ እመርጣለሁ›› ስትል የተወደደ ልጇ ‹‹እናቴ ሆይ ጽድቅንና ፈቃድን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናል›› ብሎ አጽናናትና ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡ የቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
(ምንጭ፡- ገድለ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን፣ ገድለ አቡነ ዮሴፍ አረጋዊ እና ስንክሳር ዘወርሃ ሐምሌ)
1 215
ሰዎችን ቁጥር ባይገልጸውም አውግስጦስና ዮሐንስ አፈወርቅ 12 ናቸው ብለዋል፡፡ በሦስት የትውልድ ቅርን መስለው ሦስት ናቸው የሚሉም አሉ፡፡ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተናገረው በ5 ወር ደርሰው ደብረ ዘይት እግር ሥር ከተሙ፡፡ ተጉዘውም ኢየሩሳሌም ከተማ ገብተው ‹‹የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ የት ነው?›› ብለው ሲጠይቁ ሄሮድስና መላዋ ኢየሩሳሌም ታወኩ፡፡ ሰብዓ ሰገልም በኮከቡ ተመርተው ወደ ቤተልሔም ዋሻ ገብተው ሕፃኑን ከእናቱና ከዮሴፍ ጋር አገኙትና ወድቀው ሰገዱለት፡፡ እጅ መንሻቸውን አቀረቡለት፡፡ መልአኩም ከሄሮድስ እንዲሰወሩ ነግሯቸው በሌላ መንገድ ተመለሱ፡፡ እመቤታችንና ዮሴፍም ሥርዓቱን ሁሉ ፈጽመው ሲጨርሱ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡ የስምዖንም ትንቢት ይፈጸም ዘንድ የሄሮድስ ቁጣ ነደደችና 2 ዓመትና ከዚያ በታች ያሉ ሕፃናት ሁሉ ይገደሉ ዘንድ አዘዘ፡፡ የነቢዩ ኤርሚያስም ትንቢት ተፈጸመችና 144 ሺህ ሕፃናትም ተገደሉ፤ መቃብራቸውም በራማ ሀገር በበለስ ዛፍ ሥር ነው፡፡
መልአኩም ለዮሴፍ ተገልጦለት ‹‹ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሥ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ›› አለው፡፡ እርሱም ወዲያው በሌሊት ተነሥቶ ይዟቸው ሸሸ፡፡ ከናዝሬት ጀምረው የባሕሩን ዳርቻ ይዘው እስከ ፍልስጤም ደረሱ፡፡ በ6ኛው ቀን ደክሟቸው አንድ ዋሻ ውስጥ ገቡ፡፡ እመቤታችንም በጸሎቷ ውኃን አመነጨችና ጠጡ፡፡ ያም ምንጭ ስሙ የማርያም ውኃ ተብሎ እስከዛሬ አለ፡፡ በሌሎችም ቦታዎች እመቤታች ስትጸልይ ውኃ እየፈለቀ በእርሱ ልጇን ገላውን ታጥበዋለች፡፡ ዐሥር ቀን ያህል በይሁዳ ሀገር፣ ዐሥር ቀን ያህል በምድረ በዳ እጅግ አስቸጋሪ ጉዞ ከተጓዙ በኋላ ግብፅ ደረሱ፡፡ ጌታችንም ምድረ ግብፅ በደረሰ ጊዜ በነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት መሠረት የግብፅ ጣዖታት ከመሠረታቸው ተነዋውጠው ምድር አፏን ከፍታ ዋጠቻቸው፡፡ በግብፅ ኤሌዎጶሊዎስ ሀገር ገብተው ዮሴፍ ማረፊያ ሠራ፡፡ በዚያም ባለች ተራራ ሥር ጌታችን ውኃን አፈለቀ፡፡ ይህችውም በእኛና በቅብጥ ሰዎች ዘንድ ሰኔ 8 ቀን የምትታሰበው ዕለት ናት፡፡ ደም ማፍሰስ የለመደ ርጉም ሄሮድስ ሚስቱን ማርያናንም ከገደላት በኋላ ይበቀሉኛል በማለት ከእርሷ የወለዳቸውን የገዛ ልጆቹንም ገደላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በሥጋው ጽኑ መከራ መጣበትና እግዚአብሔር የደዌውን ዘመን አስረዘመበት፡፡ ቢበላ ቢበላ ይጠግብም ይልቁንምረሀብና ጥም ይበዛበታል፣ አንጀቱም ተቋጠረ፣ ሰውነቱም ተልቶ ሰው ሁሉ አልቀርበው አለ፡፡ ማቆ ሲያበቃ በመጨረሻም ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡
የእግዚአብሔርም መልአክ ዮሴፍን ሄሮድስ ስለሞተ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ እስራኤል እንዲመለስ ነገረው፡፡ ተመልሰውም በፍልስጤም አልፈው ድልማጥያ ወደምትባል አንዲት ገር ደርሰው በበረሃ ውስጥ ተቀመጡ፡፡ እመቤታችንም ከነልጇ ረሃቡ ቢጠናባት ትዕማን ወደምትባል አንዲት ከበርቴ ባለሀብት ቤት ሄዳ ቁራሽ እንጀራንና ለልጇም ጥቂት ወተትን ለመነቻት፡፡ ያቺ ክፉ ሴት ግን ልብን በሀዘን የሚሰብር ክፉ ንግግርን ተነጋረቻት፡፡ ጻድቅ ዮሴፍም ‹‹እንግዳን ካለ ይሰጡታል ከሌለ በሰላም ይሸኙታል እንጂ ለምን ክፉ ንግግርን ትናገሪያታለሽ›› እያለ ሲነጋገሩ አሽከሯ ኮቲባ የእመቤቷን ቁጣ ሰምታ መጥታ ጌታችንን ከመሬት ላይ ጥላ እንደ ድንጋይ አንከባለለችው፡፡ እመቤታችንም ደንግጣ እያለቀሰች ልታነሣው ስትል ዮሴፍ ‹‹ተይው አታንሽው ኀይሉን ያሳይ›› አላት፡፡ ያንጊዜም ምድር አፏን ከፍታ ዋጠቻት፣ ገረዷ ኮቲባም በለምጽ ተመታች፡፡ በቤታቸውም ውስጥ በሕይወት የቀረ የለምና ቤተሰቦቿ ጦጣ ሆነው ከተራራ ወደ ተራራ ሸሹ፡፡ እመቤታች፣ ዮሴፍና ሰሎሜም በትዕማን ቤት 6 ወር ከተቀመጡ በኋላ መልአኩ ተገልጦ ከዚያ እንዲወጡ አዘዛቸውና ወጡ፡፡ አርዲስ ወደምትባል ሀገርም ደርሰው የሀገሪቱ ሰዎቸ በሰላም ተቀብለው አስተናገዷቸው፡፡ እመቤታችንም ከገረ ገዥው ሆድ ውስጥ በጸሎቷ እባብ ስላወጣችለትና ከሕመሙ ስላደ በጣም አከበሯቸው፡፡ ዕውሮችን፣ አንካሶችን፣ ለምፃሞችንና አጋንንት ያደሩባቸውን ሁሉ እያመጡላት የልጇን እጆች ይዛ ከሩቅ እያማተበች ፈወሰቻቸው፡፡ ሄሮድስም እንደሚያፈላልጋቸው መልአኩ ሲነግራቸው ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ሀገር እየተዘዋወሩ ታችኛው ግብፅ ንሂሳ ድረስ ደረሱ፡፡ እመቤታችንም በዚያ ያሉ ሕመምተኞችን ፈወሰችላቸው፡፡
ከዚህም በኋላ አሁንም መልአኩ ነግሯቸው ደመናም መጥታ ነጥቃ ወሰደቻቸውና የ38ቱን ወራት መንገድ በአንድ ጊዜ አደረሰቻቸው፡፡ በዚያም ትንሽ ከቆዩ በኋላ ወደ ቤጎር ቆላ ደረሱ፡፡ በዚያም ግብፃውያን እንደ ሕጋቸው ለአማልክቶቻቸው ላሞችን አርደው ሠውላቸው፡፡ በጎሽ፣ በአውራሪስ፣ በነጭ ዝንጀሮ የሚመሰሉ አጋንንትም መጡ፡፡ እመቤታችንም ከሩቅ ሆና ተመልክታቸው እነዚያን አጋንንት በጸሎቷ እንደጢስ በተነቻቸው፡፡ ግብፃውያንም ፈርተው እየጮኹ ሸሹ፡፡ በዚያም ወራት ‹‹ረዳት አማልክቶቻችንን ጠፉብን›› ብለው እያዘኑ ሳለ ዮሴፍን ሲጸልይ አግኝተውት አስረው በምድር ላይ አስተኝተው 40 ግርፋት ገረፉት፡፡ እርሱም በዚህ ጊዜ ‹‹እመቤቴ ሆይ ስለ አንቺና ስለ ልጅሽ ይህ መከራ አግኝቶኛልና እርጂኝ›› ብሎ በኀይል ጮኸ፡፡ እመቤታችንም ድምጹን ስትሰማ የሄሮድስ ጭፍሮች የመጡ መስሏት እጅግ ደነገጠች፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ተገልጦ ካረጋጋት በኋላ ዮሴፍን በኀይል ይደበድቡ የነበሩትን በእሳት ሰይፉ ጨረሳቸው፡፡ ዮሴፍንም በእጆቹ ዳሰሰውና ፈወሰው፡፡ እመቤታችንም ዮሴፍን ባየችው ጊዜ ‹‹ይህ ሁሉ መከራ ያገኘህ በእኔና በልጄ ምክንያት ነው›› ብላው አንገት ለአንገት ተቀቅፈው ተላቀሱ፡፡ መልአኩም ‹‹ይሄ ሀዘናችሁ በደስታችሁ ጊዜ ይረሳል…›› እያለ አረጋጋቸውና ዐረገ፡፡ የሀገሩ ሰዎችም ይወጓቸው ዘንድ ወጡና ክፉ ውሾችን ለቀቁባቸው፡፡ ነገር ግን ውሾቹ በሰው አንደበት እመቤታችንን እያነገሯት ሰግደው የእግሯን ትቢያ ልሰው በመመለስ ባለቤቶቻቸውን መልሰው መናከስ ጀመሩ፣ ብዙዎቹንም ገደሏቸው፡፡ አገራዊ ዮሴፍም ‹‹እመቤቴ ሆይ በዚህ ሀገር ከምንኖርስ በዱር በበረሀ ብንኖር ይሻለናል›› ብሏት ወደለሌላ ትርጓሜዋ የሰላም ሀገር ወደሆነች ዲርዲስ ሀገር ደረሱ፡፡ ሰዎቹም ‹‹ይህችስ የነገሥታት ወገን ትመስላለች በላያችን ላይ ትነግሥብናለች›› ብለው በክፉ ሲነሱባቸው በማግስቱ ደመና ነጥቃ ወስዳ ኤልሳቤጥ በሞት ካረፈችበት በረሀ አደረሰቻቸው፡፡ ዮሐንስ በእናቱ በድን ላይ ሆኖ እያለቀሰ ሳለ ዮሴፍንና ሰሎሜን ባያቸው ጊዜ ደነገጠ፡፡ ጌታችንም አረጋጋው፡፡ እመቤታችንም ስለ ኤልሳቤጥ ሞት እጅግ መሪር የሆነ ልቅሶን ስታለቅስ ልጇ ድንቅ ምሥጢርን ከነገራት በኋላ አረጋጋት፡፡ እመቤታችንም ‹‹እናቱ ሞታበታለችና በዚህም በረሀ ማንም የለመውና ዮሐንስን ከእኛ ጋር እንውሰደው›› ስትለው ጌታችን ‹‹ዕድሉ በዚህ በረሀ ነው›› ብሎ አረጋጋት፡፡ ከዚህም በኋላ ደመና ነጥቃ ወስዳ ወደ ጋዛ ምድር አደረሰቻቸውና በዚያ አተር የሚያበራዩ ሰዎችን አግኝታ እመቤታችን ‹‹ለልጄ አተር ስጡኝ›› አለቻቸው፡፡ እነርሱም ክፉዎች ነበሩና ‹‹ይህ አተር ሳይሆን ድንጋይ ነው›› አሏት፡፡ ሕፃኑ ልጇም ‹‹እናቴ ሆይ እንደቃላቸው ይሁንላቸው ተያቸው›› አላት፡፡ ያንጊዜም አተሩ ድንጋይ ሆነ፣ ይህም እስከዛሬም ድረስ አለ፡፡ ከዚህም በኋላ እመቤታችን ወደ ተወለደችበት ሀገር ወደ ሊባኖስ ተራራ ሄደው በዚያ ያሉ ሰዎችም በሰላም ተቀበሏቸው፡፡ እመቤታችንም ብዙ ተአምራት አደረገችላቸው፡፡ ገዥው ደማትያኖስም ሄሮድስን ሊወጋው ጦሩን አዘጋጅቶ ሳለ ነገር ግን ፈቃደ እግዚአብሔር ከለከለችው፡፡ መልአክም ተገልጦለት በእርሱ ምክንያት ብዙ ሰማዕታት ይሰየፉ ዘንድ
1 215
እመቤታችንም በመልአኩ ብስራት ጌታችንን ስትፀንስ ያንጊዜ ዕድሜዋ 14 ዓመት ከ11 ወር ነበር፡፡ አረጋዊ ዮሴፍም ከ3 ወር በኋላ ሥራውን ጨርሶ ወደ ቤት ሲመለስ ደንግልን ፀንሳ አገኛትና እጅግ ደነገጠ፡፡ በራሱም ላይ ትቢያን ነስንሶ በምድር ላይ ወደቆ መራራ ልቅሶን አለቀሰ፡፡ ‹‹ማርያም ሆይ ካህናቱ ስለ አንቺ ቢመረምሩኝ ምን እመልሳለሁ? በፈጣሪዬ በእግዚአብሔር ፊትስ እንዴት እቆማለሁ? ከሚያገኘኝ ስድብም የተነሣ ወዮልኝ፡፡ የእስራኤል ልጅ ሆይ ከማን ፀንስሽ? ክብርሽንስ የደፈረ ማን ነው?...›› እያለ ጠየቃት፡፡ ድንግልም ‹‹እኔ ንጹሕ እንደሆንኩ እግዚአብሔር ያውቃል፤ ይህን ያደረገው እግዚአብሔር ነው…›› እያለች ሁኔታውን በደንብ አስረዳችው፡፡ እርሱም የሚያደርገው ግራ ገብቶት ሳለ ይገልጥለት ዘንድ በልቅሶ ወደ እግዚአብሔር አመለከተ፡፡ እመቤታችንም ‹‹ጌታዬ ሆይ ይህን ምሥጢር ለአገልጋይህ ለዮሴፍ ግለጥለት…›› ብላ ጸለየች፡፡ ወዲያውም እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ ለዮሴፍ በሕልም ተነጋገረው፡፡ በማኅፃኗ ያለው በግብረ መንፈስ ቅዱስ ነውና አትፍራ… ሕዝቡንም ሁሉ ከኃጢአታቸው ያድናቸዋል…›› እያለ አስረዳው፡፡ ከእንቅልፉም ነቅቶ እጅግ ደንግጦ ወደ እመቤታችን ቢሄድ ስትጸልይ አገኛትና ሰገደላት፡፡ ከዚህም በኋላ በናዝሬት ከሚኖሩ ከካህናት ወገን የሆነ አንድ ካህን አረጋዊ ዮሴፍን ሰላምታ ይሰጠው ዘንድ ወደ ቤቱ መጥቶ ‹‹ምነው ወደ ቤተ መውደስ አልመጣህም?›› ቢለው ዮሴፍም ‹‹ከመንገድ የመጣሁት ገና ትናንት ነውና አረፍ ልበል ብዬ ነው›› አለው፡፡ እንዲህ ሲጨዋወቱ ያም ካህን ወደ ንጽሕት ደንግል አይኖቹን አንሥቶ ተመለከተና እንደፀነሰች ዐወቀ፡፡ ወዲያው ሮጦ በፍጥነት ወደ ካህናቱ በመሄድ ‹‹ስለ እርሱ ምስክር የሆናችሁለት ዮሴፍ እነሆ በደለ፣ ኃጢአትንም ሠራ፣ ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የወሰዳትን፣ እናንተም ጠባቂዋ ያደረጋችሁት ድንግል ማርያምን ዐወቃት ፀነሰችም›› ብሎ ነገራቸው፡፡
እነርሱም ወፈ ዮሴፍ መልእክተኞች ልከው ‹‹ማርያም ይዘሃት ና›› ብለው ላኩበት፡፡ የሴፍም አምጥቷት ሁሉም ቢመለከቷት ፀንሳች፡፡ ወደ ካህናቱም ሁሉ መልአክተኞችን ልከው ሁሉም ካህናት ተሰበሰቡና ዮሴፍንና ድንግል ማርያምን በአደባባይ አቆሟቸው፡፡ እመቤታችንንም ‹‹በእስራኤል ደናግል ላይ ለምን ስድብን አደረግሽ?›› እያሉ ወቀሷት፡፡ በሙሴም ሕግ መሠረት ሆድን የሚሰነጥቅ ማየ ዘለፋ አጠጧትና የሚያደርጋትን ለማየት ተሰበሰቡ፡፡ ነገር ግን ማየ ዘለፋው እንኳንስ በእርሷ ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይቅርና ፊቷን እንደ ሚያዝያ ጨረቃ አደመቀው፡፡ የመንፈስ ቅዱስን ሥራ የማያምኑትን ብዙዎችን ግን አቃጠላቸው፡፡ እነርሱም የድንግልን ንጽሕናዋን ባዩ ጊዜ እጅግ ተደነቁ፡፡ ዮሴፍንና እመቤታችንንም ‹‹እግዚአብሔር ካልፈረደባችሁ እኛ አንፈርድባችሁ በሰላም ወደ ቤታችሁ ሂዱ›› ብለው አሰናበቷቸው፡፡ በአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ መሠረት ሄሮድስ በሀገረ ይሁዳ ሰው ሁሉ በየወገኑ፣ በየሀገሩ፣ በየአባቱ ይቆጠር ዘንድ አዘዘ፡፡ አይሁድም ለመቆጠር ብቻ ሳይሆን ሄሮድስን አይወዱትም ነበርና ከቄሣር ጋር ያጣሉት ዘንድ ተሰበሰቡ፡፡ እመቤታችንም የመውለጃዋ ወቅት ደርሶ ነበርና አረጋዊ ዮሴፍ ወደ ቤተልሄም ወስዳትና ከአንዲት የእረኞች ዋሻ ውስጥ ይዟት ገባና በዚያ አደሩ፡፡ በዚያም ከብቶች የሚያድሩበት የፈረሰ ግንብ ነበረ፡፡ ይህም በኬብሮን ትይዩ ሲሆን አቀድሞ የእሴይ ቤት ነበርና ዳዊት በዚህ ቤት ተወልዷል፣ በዚያም በሳሙኤል እጅ የመንግሥት ቅባት ተቀብቶበታል፡፡ ቦታው በባቢሎን ስደት ጊዜ ፈርሶ የፈረሰው ግንብ ከሩቅ ለሚመጡ ነጋዴዎች ማደሪያ ሆኖ ነበር፡፡ በአጠገቡም ዋሻ ነበርና ጌታችን በታኅሣሥ ወር በመንፈቀ ሌሊት ማክሰኞ ቀን በዚያ ዋሻ ተወለደ፡፡ ጌታችንም በተወለደ ጊዜ ዋሻው በእጅጉ ስላበራ ዮሴፍ ደንግጦና ተንቀጥቅጦ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ እመቤታችንም ስትወልድ እንደሴቶች ሁሉ ልማድ ሕማም አላገኛትም፡፡ መልአኩም ለእረኞቹ አብስሯቸው ወደ ዋሻው ሄደው የተወለደውን ሕፃን ከእናቱና ከዮሴፍ ጋር አገኙት፡፡ ከእረኞቹም አንዱ የቤተልሔሙና በኋላም በይሁዳ የተተካው ማትያስ ነበር፡፡ እረኞቹም የበግ ጠቦትና የላም ወተትን፣ ማርንና ቅቤን አምጥተው እጅ መንሻ አቀረቡ፡፡ የሕፃኑንም መለኮታዊ እግር ስመው ከሁሉም በፊት አስቀደመው ሰገዱለት፡፡ ለእመቤታችንና ከዮሴፍም ከሰገዱ በኋላ ተመልሰው ሄደው በይሁዳ ሀገር ሁሉ ዜናውን ተናገሩ፡፡
ሰሎሜም እመቤታችን በድንግልና የበኩር ልጇን እንደወለደች ስትሰማ መጀመሪያ ‹‹በዓይኖቼ ካላየሁ በእጆቼም ካልዳሰስኩ አላምንም›› ብላ ወደ ዋሻው ሄደች፡፡ ወደ እመቤታችንም ቀርባ ሰውነቷን ዳሰሰች፡፡ ወዲያውም መለኮታዊ እሳት የወጣበትን ሰውነቷን ዳሥሣለችና እጆቿ ተቃጠሉ፤ ደረቁም፡፡ ወዲያውም በታላቅ ቃል እየጮኸችና እያለቀሰች ‹‹የአምላክ እናት ሆይ ይቅር በይኝ የሃይማኖቴ ጉድለት ታላቅ መከራ አመጣብኝ›› እያለች በእመቤታችን ፊት መሪር ልቅሶን አለቀሰች፡፡ ድንግል ማርያምም ወደ ልጇ ማለደችላት፡፡ በዚህም ጊዜ መልአክ መጥቶ ሰሎሜን ‹‹እግዚአብሔር ይቅር ብሎሻል፣ ወደ ሕፃኑ ሂጂና በተቃጠሉ እጆቺሽ ያዥውና ታቀፊው ተድኛለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ትታቀፈው ዘንድ ሕፃኑን ልጇን ሰጠቻት፡፡ ሰሎሜም በታቀፈችው ጊዜ እጇ ወዲያው ዳነላትና የእመቤታችንን ደንግልናዋን አምና ሰገደችላት፡፡ ሰሎሜም ያየችውንና የሆነውን ሁሉ ለኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ሁሉ ለማውራት እጅግ ተቻኩላ ከዋሻው ወጥታ ስትሄድ ከሰማይ ድምጽ መጣላትና ያየችውን ተአምር ሕፃኑ ወደ ቤተ መቅደስ እስኪገባ ድረስ ለማንም እንዳትናገር አስጠነቀቃት፡፡
ጌታቸንም እንደ አይሁድ ልማድ በ8ኛ ቀኑ ግዝረትን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ፈጽሞ በ40ኛውም ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ ጌታችን ከመወለዱ ከ277 ዓመት በፊት በንጉሥ በጥሊሞስ ትእዛዝ 72ቱ ሊቃውንት መጻሕፍቶቻቸውን ከዮናናውያን ቋንቋ ወደ ጽርዕ ቋንቋ ሲተረጉሙ የ123 ዓመቱ ስምዖን አንዱ ነበር፡፡ ትንቢተ ኢሳይያስን የተረጎመው እርሱ ነበርና ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንደምትወልድ ይህንንም ሳያይ እንዳይሞት እግዚአብሔር ቃል ገብቶለት ነበር፡፡ ወደ መቅደስም ሲመጣ መልአኩ ለስምዖን ተገልጦለት ሲጠብቀው የኖረው ተስፋው ዕውን ሆኖ ዛሬ መሢሑን በክንዶቹ እንደሚታቀፈው ነገረው፡፡ በቤተ መቅደስም ጌታችንን አገኘውና ታቅፎ ‹‹ጌታ ሆይ ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና ባሪያህን ሰላም አሰናብተው›› አለው፡፡ ለእመቤታችንም ‹‹ጦርና ሰይፍ በልብሽ ውስጥ ይገባል›› ብሎ በልጇ ምክንያት የሚደርስባትን መከራ በትንቢት ነገራት፡፡ ‹‹ጦርና ሰይፍ›› ያለውም የክርስቶስን መከራ ነው፡፡ በሕማሙና በመቸንከሩ ልቧ መሪር በሆነ የኀዘን ጦር ተወግቷልና አንጀቷም በተሳለ የሰይፍ ኀዘን ተነዋውቷልና፡፡ ልጇ የተቀበላቸው መከራዎችንም እንደ እርሱ በልቡናዋ እመቤታችንም ተቀብላቸዋለችና ስለዚህም የሰማዕታት እናት ትባላለች፡፡ ከሰብዓ ሰገል አንዱ ዘሮአስተር የሚባለው ስለ ኮከብ መውጣትና ስለ ክርስቶስ ትንቢት ተናግሮ ነበርና ከዚያ ጊዜ ጀምሮ የጥበብ ሰዎች መጻሕፍትን ተምረው በትንቢቱም ታምነው ይኖሩ ነበር፡፡ ስለዚህም በየዓመቱ ሁሉም አንድ ቀን ከፍ ባለ ተራራ ላይ ይሰበሰቡና ኮከቡን ይመለከቱታል፡፡ ክርስቶስም በተወለደ ጊዜ አዲስ ኮከብ በሕፃን መልክ ታያቸው፡፡ በላዩም የመስቀል ምልክት አለው፡፡ ‹‹የአሕዛብ ተስፋቸውና መስፍናቸው፣ የአይሁድ ንጉሣቸው ወደ ምድር ወረደ›› የሚል ቃልም ሰሙ፡፡ ‹‹እጅ ለመንሳትና ለመስገድም ፈጥናችሁ ሂዱ›› አላቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የጥበብ
1 215
ጌታችን ለአቡነ ሰላማ የገባላቸው ልዩ ቃልኪዳን፡- ‹‹አባታችን አባ ሰላማ በጸሎት ላይ ሳለ ጌታችን ወደ እርሱ መጥቶ ‹እንደ ወዳጄ እንደ አብርሃምና እንደ ወዳጄ እንደ ዳዊት ልቡናዬ የሚፈልገውን የምትፈጽምልኝ ታማኝ አገልጋይ ወዳጄ ሆይ! የለመንከኝን ሁሉ አደረኩልህ፡፡ ከዛሬ ወዲህ ከእኔ ጋር ትኖራለህ፣ እኔ ካለሁበት ቦታ ከፍ ባለ ዙፋን ትቀመጣለህ፣ በዓሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል ላይ በዕለተ ምጽዓት ትፈርዳለህ፡፡ መታሰቢያህን ያደረገ፣ ስምህን የጠራ፣ አንተን አምኖ ስምህን ጠርቶ ጸሎት የጸለየ፣ በቤተ ክርስቲያንህም የተማጸነ፣ ወደ ሥራውም ተግባር ለመሄድ በቤተ ክርስቲያንህ ቅጽር ሲያልፍ የቤተ ክርስቲያንን ቅጽር የተሳለመውን እኔ እስከ ዓሥራ አምስት ትውልድ እምርልሃለሁ፡፡ በመታሰቢያህ ቀን ስለ ስምህ ብሎ የታመመውን የጠየቀ፣ ያዘነውን ያጽናና፣ የተራቆተውን ያለበሰ፣ የተራበውን ያበላ፣ የተጠማውን ያጠጣ፣ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈውን ያጻፈውን ገበታውን የተሳለመውን ያነበበውን የተረጎመውን እስከ ዓሥራ አምስት ትውልድ እምርልሃለሁ፡፡ በመታሰቢያህ ቀንም በስምህ ለቤተ ክርስቲያንህ ሣር የገዘጎዘውን እንጨትም ለፍም የሰጠውን እስከ ዓሥራ አምስት ትውልድ እምርልሃለሁ፡፡ ከሩቅም ከቅርብም ለመሳለም ወደ ቤተ ክርስቲያንህ የሄደውን ወደ መቃብሬ ወደ ኢየሩሳሌም እንደሄደ አደርግለታለሁ፣ ከገሀነመ እሳትም አድነዋለሁ፣ ሲኦልንም አያያትም፡፡ የገድልህና የተአምርህ የቃልኪዳንህ መጽሐፍ ባለበት ቦታ፣ ስምህ በተጠራበት ቦታ፣ መታሰቢያህም በተደረገበት ቦታ እኔ ከአንተ ጋር እኖራለሁ፣ ርኩሳን መናፍስት ክፉዎች አጋንንት አይቀርቡም፣ በዚያም ጠባቂ መላእክትን አኖራለሁ፣ እኔም ከዚያ ቦታ አልለይም፡፡ የገድልህን መጽሐፍ ቆሞ የሰማ ሰማንያ ዓመት የሠራው ኃጢአቱ ይሠረይለታል፣ ተቀምጦም የሰማ ቢኖር የአርባ ዓመት ኃጢአቱ ይሠረይለታል፡፡›››
የአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
አቡነ ዮሴፍ አረጋዊ፡- የእመቤታችን ጠባቂ የነበረው ጻድቁ ዮሴፍ ዘሩ ከዳዊት ወገን ሲሆን ሀገሩ ናዝሬት ነው፡፡ በተወለደ ጊዜ መልአክ መጥቶ ለወላጆቹ ‹‹የተመረጠና ታማኝ አገልጋይ ይሆናል›› ብሎ ነግሯቸዋል፡፡ አናጺም ነጋዴም የነበረ ሲሆን ሦስት ሴቶችና ወንዶች ልጆች ነበሩት፡፡ በትዳር ዓለም ሆኖ 40 ዓመት ኖሯል፡፡ 83 ዓመት ሲሆነው እመቤታችንን ለመጠበቅ ከአረጋውያን ሽማግሌዎች መካከል ዕጣ ወጥቶለት ተመረጠ፡፡ እመቤታችንን ከቤተ መቅደስ ሊወስድ ሲል መልኳ እየተለዋወጠ ቢመለከት በዚህች ሕፃን ምክንያት ይገድሉኛል ብሎ ስለፈራና ስለደነገጠ ‹‹እምቢ አልወስድም›› አለ፡፡ ይህን ጊዜ መልአኩ ተገልጦለት ‹‹ሕፃኗን ተረከብና ወስደህ ጠብቃት›› ብሎት ወደቤቱ ወስዷታል፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ መለኮትን መውለዷን የአምላክ እናት መሆኗን አላወቀም ነበር፡፡ አረጋዊው ዮሴፍ ይህ እጅግ ድንቅ ምሥጢር ግልጽ የሆነለት ጌታችንን በድንግልና ወልዳ በበረት ግርግም ስታስተኛው ነው፡፡ መላእክት እንደ ቅጠል እረግፈው ሲያመሰግኑት፣ እንስሳት እስትንፋሳቸውን ሲገብሩለት፣ ሰብዓ ሰገል ለአምላክነቱ እጅ መንሻን ሲሰጡት ሲመለከት ያን ጊዜ ነው አምላክን መውለዷን ያወቀው፡፡ እነዚህን ምልክቶች እስካየበት ጊዜ ድረስ የአምላክ እናት መሆኗን አላወቃትም ነበር፡፡ በወንጌልም ‹‹የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም›› ተብሎ የተነገረው ለዚህ ነው፡፡ ማቴ 1፡24፡፡ ሄሮድስ ጌታችንን ያገኘ መስሎት 144 ሺህ የቤቴልሔም ሕፃናትን በሰይፍ ሲፈጅ መልአኩ ለዮሴፍ ተገልጦለት ‹‹እናቱንና ሕፃኑን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ›› (ማቴ 2፡13) ብሎ በነገረው መሠረት አረጋዊ ዮሴፍ ታማኝ አገልጋይ በመሆን ብዙ ዘመን ከእመቤታችንና ከጌታችን ጋር በረሃ ለበረሃ ሲንከራተት ኖሯል፡፡ ይህም ጻድቅ አረጋዊ እመቤታችንና የተወደደ ልጇን መድኃኔዓለምን በእጆቹ ሥራ ይመግባቸው ነበር፡፡ ሁለቱንም ከሄሮድስ ለማዳን ብዙ ሰማዕትንት የተቀበለ ነው፡፡ ጌታችንንም ተሸክሞ ሲሰደድ ይመረኮዛት የነበረችው የምርኩዝ በትሩ የተባረከች ሆና ለምልማለች፡፡ ጌታችን በዚህች አረጋዊ ዮሴፍ በትር ብዙ አስደናቂ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ዛሬም ድረስ በግብፅ ደብረ ቁስቋም ትገኛለች፡፡ አረጋዊ ዮሴፍ በ114 ዓመቱ ታሞ ሊያርፍ ሲል ጌታችን ተገልጦለት ‹‹ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ?›› ቢለው ‹‹በሞትኩ ጊዜ ሥጋዬን በምድር አታስቀርብኝ›› አለው፡፡ ጌታችንም ‹‹እሺ እንዳልክ ይሁንልህ›› ብሎት ሌላም ትልቅ ቃልኪዳን ከገባለት በኋላ በዚህች ዕለት በክብር እንዲያርፍ አድርጎት ሥጋውን ብሔረ ብፁዓን አስገብቶለታል፡፡
የዮሴፍ አረጋዊን ገድል ስናስብ ጌታችን ከቅድስት ድንግል እናቱ፣ ከአረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ወደ ግብፅ በመሰደዱን ከእመቤታችን ጋር የደረሰበትን መከራ እናስባለንና ከመነሻው ጀምሮ እንየው፡፡ እመቤታችን በቤተ መቅደስ ሳለች ከአባቷ የሚመጣላትን የትረፈረፈ ሀብት ለድኆችና ጦም አዳሪዎች ትመጸውት ነበር፡፡ 7 ዓመት በሆናት ጊዜ ግን ወላጆቿ ዐረፉና እነርሱ የተውላትን ወርቅና ብዙ ገንዘብ ለእግዚአብሔርና ለጦም አዳሪዎች ሰጠች እንጂ ምንም አልወሰደችም፡፡ ካህናቱ እንደ በባሕላቸው መሠረት በቤተ መቅደስ በብፅዓት ያደገን ሰው (ሴትም ይሁን ወንድ) ለአካለ መጠን ሲደርስ በቤተ መቅደስ እያገለገለ እንዲኖር ወይም ከካህናቱ ወገን መርጦ እንዲያገባና ሀብት ሰጥተው እንዲሸኙት ሁለት ምርጫ ይሰጡታል፡፡ እመቤታችንም 12 ዓመት በሆናት ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ይህንኑ ምርጫ ሲያቀርብላት እመቤታችንም በልቧ የሰው ልጅ ሀሳብ የላትምና ‹‹እኔስ በእግዚአብሔር ቤት እያገለገልኩ መኖርን እመርጣለሁ›› አለችው፡፡ ካህናቱም ‹‹ስለእርሷ ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ እግዚአብሔር የሚነግርህን በጸሎት ጠይቅ›› አሉትና እርሱም የክህነት ልብሱን ለብሶ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ ገብቶ በጸሎት ሲጠይቅ እግዚአብሔር መልአኩን ልኮለት ሚስቶች የሌሏቸውን የዳዊት ወገን የሆኑ ወንዶችን ሰብስቦ በበትራቸው ላይ ስማቸውን ጽፎ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ እንዲያገባው ነገረው፡፡ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስም በአዋጅ አስነግሮ 1985 ብሮችን ሰብስቦ ሲጸልይባቸው ቢያደር በአረጋዊ ዮሴፍ በትር ላይ ምልክት ታየ፡፡ በትሩንም ሲሰጠው ነጭ ርግብ መጥታ በዮሴፍ ላይ አረፈች፡፡ እርሱም ድንግልን እንዲወስዳት ሲነገረው አለቀሰ፡፡ ‹‹ይቅር በሉኝ እኔ ሽማግሌ ነኝና ልጆችም አሉኝ፤ ዕድሜዬም 83 ዓመት ነውና›› እያለ አለቀሰ፡፡ ዘካርያስም ‹‹ይህ ሥራ ከእኛ ዘንድ አይደለም፣ እግዚአብሔር አዞናል እንጂ፡፡ እነሆ እርሷን ትጠብቃት ዘንድ ሰጥቶሃልና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እምቢ አትበል፤ ትእዛዙን አንቀበልም ያሉትን ፈጣሪህ እግዚአብሔር እንዴት እንዳደረጋቸው አስብ…›› እያለ አጽናናው፡፡ አገራዊ ዮሴፍም እየፈራ ድንግል ማርያምን ወደቤቱ ወሰዳት፡፡ እቤቱ ወስዶም ልጆቹና ቤተሰቦቹ ይጠብቋት ዘንድ አደራ ሰጥቷቸው ወደ ንግድ ሄደ፡፡ እመቤታንም ወደ ዮሴፍ ቤት በገባች ጊዜ ልጆቹ እናታቸው በልጅነታቸው ሞታባቸዋልችና የሙት ልጆች ሆነው አገኘቻቸው፡፡ ዮሴፍ አስቀድሞ ማርያም የምትባል ሚስት አግብቶ ነበር፡፡ ከእርሷም 3 ሴቶችና 4 ወንዶች ልጆች ነበሩት፡፡ እነርም ስምዖን፣ ያዕቆብ፣ ይሁዳና ዮሳ ናቸው፡፡ ማቴዎስና ማርቆስም ይህንን በወንጌላቸው ጽፈውታል፡፡
1 215
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአቡነ ሰላማ ከሁሉም የሚበልጥ ክብር እንደሰጣቸው፡- ‹‹ብፁዕ አባታችን አባ ሰላማ ጌታችንን ‹ጌታዬ ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! እስቲ በሰማይ ቤት ያለውን ክብሬን አሳየኝ› አለው፡፡ ጌታችንም መልሶ ‹እሺ ይሁንልህ መጥተህ ከጨረቃና ከፀሐይ ሰባት እጅ የሚበልጥ ክብርህን እይ፣ ከጻድቃንና ከሰማዕታት ክብር ያንተ ክብር ይበልጣል፣ በክብር የሚመስልህ የለም፣ እኔ ፈጣሪህ የእሳት ፈረሶች የሚሆኑ መላእክት በኪሩቤል ላይ እንደምቀመጥ አንተም ከእነርሱ በላይ ትሆናለህ፡፡ ስለ ትምህርትህና ስለ ስብከትህ ኢትዮጵያን ከጨለማ አውጥተህ በሃይማኖት ስለ አበራሃት ከፍ ያሉ ክብራትንና ማዕረጋትን ፈጽሜ ሰጠሁህ፣ አንተንም ከቅዱሳን በላይ ብርሃን አደረግሁህ፣ የቅዱሳን ፀሐይና ብርሃናቸውም አደረግሁህ፣ ከእናቴ ከድንግል ማርያም በታች ትቀመጣለህ› አለው፡፡ ዳግመኛም ‹እኔም ፊቴን አሳየሁህ፣ እኔንም አይተህ መረዳት ቻልክ፡፡ ከነቢያትና ከሐዋርያት ስለእኔ መረዳት የቻለ አልነበረም፡፡ ሙሴም አየኝ ስለ እኔ መረዳት ግን ተሳነው፣ ኢሳይያስም አየኝ ስለ እኔ ግን መረዳት አልቻለም፣ አንተም ታማኝ አገልጋዬና ወዳጄ የልቡናዬን ፈቃድ የምትፈጽም ሆይ ፊቴን አይተህ ስለ ስብከትህና ስለ ንጹሕ ልቡናህ ስለ እኔ መረዳት ቻልክ፣ ወንጌል ልበ ንጹሖች ንዑዳን ክቡራን ናቸው እነርሱ እግዚአብሔርን ያዩታልና እንዳለ ዛሬም ሰላማ ሆይ! ክብርና ሞገስን ሰጥቼሃለሁ ደስ ይበልህ› አለው፡፡››
ንስሐ ያልገቡና ከኃጢአት ሳይነጹ ሰዎች ሥጋ ወደሙን ቢቀበሉ እንዳልተቀበሉ ይሆንባቸዋል፡- ብፁዕ አባታችን አባ ሰላማ ለሕዝቡ እንዲህ ብለው አስተማሩ፡- ‹‹እውነት እላችኋለሁ ሰንበትን የሻረ ስርየት የለውም፣ ዳግመኛም ሰንበትን አክብሩ፣ ዓሥርቱ ቃላተ ኦሪትን አክብሩ፣ ስድስቱ የወንጌል ቃላትንም አክብሩ፣ ለሁሉም መልካምን አድርጉ፣ ከኃጢአት ንጹሕ ያልሆኑት ሰዎች ሳይገባቸው ሥጋውና ደሙን እንዳይቀበሉ ከልክሏቸው፣ በድፍረት ሥጋውና ደሙን ቢቀበሉ መላእክት የጌታችንን ሥጋውንና ደሙን በድፍረት ከሚቀበሉ ሰዎች አፍ ነጥቀው የጌታችንን ሥጋ በብርሃን ጉጠት ወስደው ሃይማኖታቸው ለቀና መልካም ሥራ ላላቸው ያቀብሏቸዋል፡፡ ሥጋውና ደሙን በድፍረት የሚቀበል የጌታችንን ሥጋና ደም አላወቀምና ለራሱ ፍዳውንና መቅሰፍቱን በላ፡፡››
አጋንንት ጥርጣሬንና ክህደትን ክፉውንም ሁሉ እንደሚያመጡብን፡- ‹‹ብፁዕና ቅዱስ አባታችን ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ደብረ መድኃኒት በምትባል ዋሻው ውስጥ የወንጌልን ጸሎት እየጸለየ ሳለ አጋንንት ወደ እርሱ ተሰብስበው መጡ፡፡ በሜዳም ላይ ወቅኒ አሉ፣ ይህም ማለት የአጋንንት አምልኮ ቤታቸው ማለት ነው፡፡ እርስ በእርሳቸውም ሁሉን ገዛን፣ ሁሉን አሸነፍን፡፡ ነገር ግን በጉልበታችንና በኃይላችን እናሸንፈው ዘንድ የማይቻለን አንድ ጠላታችን ቀረን፡፡ እስቲ የምናስትበትን መንገድ እንፈልግ እናስብ ተባባሉ፡፡ ከእነርሱም መካከል ሰባቱ አጋንንት ‹እኛ በጥበባችን እናሸንፈዋለን› አሉ፡፡ አንደኛውም ‹እኔ ጉሮሮውን አሳብጨ በረሃብና በጥም ይሞታል› አለ፡፡ ሁለተኛውም ‹ወደ ፈጣሪው ምልጃና ጸሎት እንዳያደርግ አንደበቱን አስረዋለሁ› አለ፡፡ ሦስተኛውም ‹ወደ ፈጣሪው እንዳይሰግድ በጉልበቱ ላይ ከባድ ቁርጥማትን አመጣበታለሁ› አለ፡፡ አራተኛውም ‹በልቡናው አድሬ ትዝብትንና ትዕቢትን፣ ጥርጣሬና ክሕደትን አመጣበታለሁ› አለ፡፡ አምስተኛውም ‹እኔ በራሱ ላይ አድሬ ስንፍናንና መኝታን፣ ማንቀላፋትን አመጣበታልሁ› አለ፡፡ ስድስተኛውም ‹እኔ በብልቱ አድሬ በእርሱ ላይ ዝሙትን አመጣበታለሁ› አለ፡፡ ሰባተኛውም ‹እኔ ስስትንና ሀሜትን ሳቅን አመጣበታለሁ› አለ፡፡ እነዚህም አጋንንት ሰባቱም እንዲህ ባሉ ጊዜ ሌሎቹ አጋንንት ደግሞ ‹እንደዚህ ባለው ሥራ ጠላታችንን ድል ብታደርጉ በእኛ ላይ መኳንንትና መሳፍንት ገዥ ትሆናላችሁ፣ እኛም ተገዥ ባሮች እንሆናችኋለን፣ ባታሸንፉት ግን ከእኛ በታች የምትገዙ ባሮች እናደርጋችኋለን› አሉ፡፡ ይህንንም ከተማከሩ በኋላ ከሀገሩ ሰዎች አንዱን ሰው አርደው ሥጋውን በሉ፣ ደሙንም ጠጡና ከምሽት እስከ ጠዋት ድረስ ተጫወቱ፡፡ ከዚህም በኋላ እነዚያ ክፉ አጋንንት በሙሉ ተሰብስበው አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ወዳለበት ሄደው ይዋጉት ዘንድ እነዚያን ሰባቱን አጋንንት ሸኙዋቸው፡፡ እነዚያም አጋንንት እንደሙሽራ ሚዜዎች እየዘለሉ ሄዱ፡፡ ብፁዕና ቅዱስ አባታችን አባ ሰላማም የሰይጣናትን ምክር ያስቱትና ይገድሉትም ዘንድ እንደመከሩ በመንፈስ ቅዱስ ዐወቀ፡፡ እነዚያም አጋንንት እርሱ ወዳለበት በደረሱ ጊዜ በመስቀል ምልክት በእርሱ ላይ አማተበ፡፡ የመስቀሉም ምልክት አጥር ሆነባቸውና ከዚያ ሳያልፉ ቀሩ፡፡ ብፁዕ አባታችንም ወደ እግዚአብሔር እየተማጸነ ፈጽሞ ጸለየ፡፡ በዚያን ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ ከሰማይ ወርዶ በእሳት መብረቅ መታቸውና ወደ ሲኦል አሰጠማቸው፡፡››
‹‹ወንድሞች ሆይ! ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ ‹ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ› እንዳለ እንዲሁ በአባታችን በአባ ሰላማ ላይ የተደረገውን በዐይነ ኅሊና ተመልክታችሁ በዕዝነ ልቡና ስሙ፡፡ በትግራይም ሀገር ከእግዚአብሔር ሕግ የሚያስቱ በሰውም አድረው ክፉ ነገርን የሚያሳስቡ ራስንና ሰውነትን የሚያሳምሙ አጋንንት ነበሩ፡፡ በእግርም አድረው ያስነክሷቸዋል፤ በምላስም አድረው መልካም ነገርን እንዳይናገሩ ያኮላትፏቸዋል፤ በጉሮሮአቸውም አድረው ጉሮሮአቸውን ይዘጋሉ፡፡ ሰውነታቸውንም ታማሚ ያደርጓቸዋል፡፡ መልካም ቀይ የሆነውንም ነጭ ያደርጋሉ፡፡ በእጅ አድረው ያሳምሟቸዋል፤ ለመግደልም ያፋጥኗቸዋል፤ በልብም አድረው የሃይማኖትን ነገር እንዳይሰሙ ያደነቁሯቸዋል፤ በእራሳቸውም ላይ አድረው ጸሎት እንዳያደርጉና ሃይማኖትን እንዳይማሩ ይከለክሏቸዋል፤ በብልታቸውም አድረው ትዕግስትንና ንጽሕናን እንዳይዙ ዝሙትን ያመጣሉ፤ በሆዳቸውም አድረው ለሞት እስኪያደርሳቸው ድረስ ቁርጠት ያመጡባቸዋል፤ በኩላሊትም አድረው ያጎሳቁሏቸዋል፤ ለመቅሰፍትም ያደርሷቸዋል፤ በአንገታቸውም አድረው አንገታቸውን ያሳንቋቸዋል፤ በጭናቸውና በደረታቸውም አድረው ዝሙትን ያመጡባቸዋል፤ በአፋቸውና በከንፈራቸው አድረው ሐሰትንና ክሕደትን ያመጡባቸዋል፤ በገንዘባቸውም አድረው በእነርሱ ላይ ስንፍናንና ውድቀትን ስስትንም ያመጣሉ፤ በአንጀታቸውም አድረው አጽዋማትን እንዳይጾሙ ረሃብን ያመጡባቸዋል፤ በኅሊናቸውም አድረው አምልኮተ ጣኦትንና አጋንንትን መሳብ ያሳስቧቸዋል፤ በጎን አጥንቶቻቸውም አድረው ይወጉዋቸዋል፣ ይሰብሯቸዋል፤ በዐይኖቻቸውም አድረው ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዳያዩ መታወርንና የዐይን በሽታንም በእነርሱ ላይ ያመጡባቸዋል፤ በጥርሶቻቸውም አድረው በከንቱ ነገር እንዲስቁ ያደርጓቸዋል፤ በውስጥ እግራቸውም አድረው ወደሌቦች ይወስዷቸዋል፤ በውስጥ ኅሊናቸውም አድረው በወንድማቸው ላይ መጣላትንና ቂም መያዝን በቀልን ያመጣሉ፤ በአፋቸውም ላይ አድረው ሱስ የሚያሲዙትን ዕፅዋት እንዲበሉ፣ እንዲጠጡ፣ እንዲያሸቱና እንዲያጤሱ ያደርጓቸዋል፡፡ ይህም የተገኘው እስማኤላውያን ከሆኑ ከአማሌቅና ከኔባል መስጊድ ነው፡፡››
1 215
ፍሬምናጦስ አጠናክሮ ያልተጠመቀውን ሁሉ አጥምቆአል፡፡
ፍሬምናጦስም ወደ እስክንድሪያ ለመሄድ አስቦ ሳለ እንደተኛ እመቤታችን ድንግል ማርያም ተገልጣለት ‹‹ዲቁናና ቅስናን መቀበል ይገባሃል፣ ለጵጵስና ተዘጋጅ፣ እግዚአብሔር ይህችን ከፍ ያለችውን ማዕረግ ሰጥተሃልና የልጄ ወዳጅ ሆይ በጸሎትህና በልመናህ በስብከትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ፣ በእጅህ ጥምቀትንና ሥጋ ወደሙን ይቀበላሉ›› አለችው፡፡ ጌታችንም እንዲሁ ተገልጦለት ‹‹ወደ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አትናቴዎስ ሄደህ ከፍ ያችውን ማዕረግ ተቀብለህ የኢትዮጵያን ሰዎች አጥምቅልኝ፣ ነቢዩ ዳዊት ስለ እነርሱ ‹ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች› ብሎ ተናግሯልና›› አለው፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ሰላማ ቅዱሳኑን ነገሥታት አብርሃንና አጽብሓን አግኝቶ ከእነርሱም ጋር ተማክሮ ወደ እስክንድሪያ ሄዶ በቅዱስ አትናቴዎስ እጅ በአገራችን ላይ የመጀመሪያው ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ታኅሳስ 18 ቀን ተሾመ፡፡ ስሙንም ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አለው፡፡ ሰላማ ማለት እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያስታርቅ ማለት ነው፡፡ ከሣቴ ብርሃን ማለትም ሃይማኖትን ገልጦ የሚያስተምር ማለት ነው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስም ከሾመው በኋላ ታቦትና በጣም ብዙ ንዋያተ ቅድሳትንና መገልገያ ዕቃዎችን ሰጥቶ መርቆ በሰላም ወደ ኢትዮጵያ ላከው፡፡
ቅዱሳን የሆኑ ሁለቱ ነገሥታትም መምጣቱን በሰሙ ጊዜ ‹‹ኢትዮጵያ ሰዎች ሁላችሁ እስከ 40 ቀን ተሰብሰቡ›› ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ በደብረ ሲናም ሄደው ተገኛኙትና ከዚያች ቀን ጀምሮ ሕዝቡም ሁሉ እስከ 40 ቀን ድረስ ተጠመቁ፡፡ በዚያችም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያች በደብረ ሲና አገር ላይ ወረደና ሕዝቡን ሁሉ ባረኮ ተመልሶ ሲያርግ ከአባ ሰላማ በቀር ያየው አልነበረም፡፡ ወደ አክሱምም ሄደው ነገሥታቱም የአድባራት ሁሉ የበላይ የምትሆን የቅድስት ጽዮንን ቤተ ክርስቲያን በወርቅና በዕንቊ ሠሩና አባ ሰላማ ባርኮ ቀደሳት፡፡ ታቦተ ጽዮንም ከድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት አብርሃና አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ተገኘች፡፡ አባታችንም በእመቤታችንም በዓለ ዕረፍት ቀን ጥር 21 ቀን በውስጧ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቀድስ ሚካኤልና ገብርኤል በግራ በቀኝ እየተራዱት እርሱም ከምድር ሦስት ክንድ ከፍ ብሎ ሥርዓተ ቅዳሴውን ፈጽሞ ለነገሥታቱና ለሕዝቡም ሁሉ አቆረባቸው፡፡ የዚያን ዕለትም እጅግ ታላቅ በዓልን አደረጉ፡፡ ከዚያም ሌሎችን እየሾመ ወደ ሌላ አገር ካሰማራ በኋላ እርሱም በየሀገሩ በአራቱም አቅጣጫ እየዞረ እያጠመቀና እያስተማረ አብያተ ክርስቲያናትንም እየሠራ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች ታላቅ ብርሃን ሆነ፡፡ በየቀኑም እስከ ማታ ድረስ የሚጠመቀው ሕዝብ የሦስት ገበያ ሕዝብ ይሆናል፡፡ በመሸም ጊዜ እንደ ኢያሱ ፀሐይን እያቆመ ሕዝቡን ያጠምቅ ነበር፡፡ መድኃኔዓለምም በየጊዜው በአካል እየተገለጠለት አገልግሎቱን ያፋጥንለት ይባርከውና ቃልኪዳን ይሰጠው ነበር፡፡
አባታችንም በድፍን ኢትዮጵያ በአራቱ አቅጣጫ እየዞረ በተአምራቱ ድውያንን እየፈወሰ፣ ሙታንን እያስነሣ፣ ወንጌልን እያስተማረ፣ እያጠመቀ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እየሠራና አገልጋይ የሚሆኑ ቀሳውስትን እየሾመ በሀገራችን ላይ ብርሃንን የፈነጠቀ ለኢትዮጵያ መግለጽ ከሚቻለው በላይ ታላቅ ባለውለታዋ ነው፡፡ ከአቡነ ሰላማ በፊት እኛ ኢትዮጵያውያን ክርስቶስን ከማመን በቀር ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ የመቀበል ልማድ አልነበረንም፡፡ በድንኳን ካለችው ታቦተ ጽዮን በቀርም ታቦታትና አብያተ ክርስቲያናትም አልነበሩንም፡፡ ይሄ ሁሉ ሲታሰብ ከአባ ሰላማ ውለታ አንጻርና እንደሠራላት እጅግ ታላቅ ሥራ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቁን እንደሚገባው መጠን አላከበረችውም ማለት ይቻላል፡፡ ጌታችንም በመጨረሻ ቃልኪዳን ሲሰጠው ‹‹ስለ ትምህርትህና ስለ ስብከትህ ኢትዮጵያን ከጨለማ አውጥተህ በሃይማኖት ስለ አበራሃት ከፍ ያሉ ክብራትንና ማዕረጋትን ፈጽሜ ሰጠሁህ›› ነው ያለው፡፡ ‹‹ነቢያትና ሐዋርያት ፊቴን አይተው ስለእኔ መረዳት ያቻሉትን አንተ ግን ፊቴን አይተህ ስለ እኔ እንድትረዳ አደረግሁህ፣ ለቅዱሳንም ሁሉ ብርሃናቸው አድርጌሃለሁ›› ተብሎ በጌታችን አንደበት የተነገረለትን ቅዱስ፣ ጻዲቅ፣ መናኝ፣ ሐዋርያ፣ ጳጳስ… ቤተ ክርስቲያናችን አሁን እያከበረችው ባለው መልኩ ብቻ አልነበረም ማከበርና መዘከር የነበረባት፡፡ በተንቤን ምድር ብቻ በብሕትውናና በጽሙና ሲቀመጥ ቋጥኝ ፈልፍሎ በሠራው ቤተ ክርስቲያን ላይ የብርሃን መሰላል ተተክሎለት በእርሱም ወደ ሰማይ ወጥቶ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥሉስ ቅዱስን መንበር አጥኗል፡፡ የተንቤንንም ምድር ቡሩካን በሆኑ እጆቹ አንሥቶ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ መንበር ፊት አቅርቦ አስባርኳታል፡፡ መልአክም ሰማያዊ መናና ኅብስት እያመጣ ይመግበው ነበር፡፡ ወንጌልንም ካዳረሰ በኋላ በዋሻ ገብቶ በበዓት ተወስኖ ሰውነቱን በመከራ ይቀጣል፡፡ በጎጃም ክፍለ ሀገር በሞጣ ዓባይ በኩል በምትገኝ ቦታ እያስተማረና ሐዋርያዊ ተልዕኮውን እየተወጣ ሳለ ጊዜው መሽቶ ፀሐይ ልትጠልቅ ስትል እንደ ኢያሱ ገዝቶ ያቆማት ሲሆን ጌታችን ግዝቱን እንዲፈታ ከነገረው በኋላ ነው ግዝቱን አንስቶላት የጠለቀችው፡፡ በታዘዘውም መሠረት ከጎጃም ወደ ትግራይ ሲሄድ የዓባይን ባሕር በመጠምጠሚያው ለሁለት ክፍሎ ከእርሱም ጋር የነበሩትን አሻግሯቸዋል፡፡ በደመናም ተጭኖ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሄዶ አይሁድ ቀብረው በደፈኑት በክርስቶስ መስቀል ላይ ጸሎት አድርጎ ሰግዷል፡፡ ከጌታችንና ከእመቤታችንም መካነ መቃብር አፈር ዘግኖ ወደ ሀገራችን በማምጣት በሚያንጻቸው አብያተ ክርስቲያናት ላይ ነስንሶታል፡፡ አባታችን አባ ሰላማ ሐምሌ 26 ቀን ሲያርፍ ነፍሱን መላእክት ያይደሉ ራሱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ተቀብሎ ከእርሱ ጋር አሳርጓታል፡፡ መላእክትም ሥጋውን ከጌታችንና ከእመቤታችን መቃብር አድርሰው ወደ ደብረ መድኃኒት የመለሱት ሲሆን በመቃብሩም ላይ ብርሃን ወርዶ ለሁሉም ታይቷል፡፡ ነገሥታቱም ከዐረፈ በኋላ ወደ ደብረ መድኃኒት መጥተው ለመካነ መቃብሩ ሲሰግዱ አባ ሰላማም ተገልጦላቸው ከነሠራዊታቸው ባርኳቸዋል፡፡
ጌታችን ለአቡነ ሰላማ የተገለጠበት ልዩ ሁኔታ፡-
ጌታችን ራሱ ሠራዒ ካህን ሆኖ ለአቡነ ሰላማና ለሁለቱ ቅዱሳን ነገሥታት ሥጋ ወደሙን እንዳቀበላቸው፡- ‹‹አባታችን አባ ሰላማ ከተራራ ላይ ወጥቶ በዚያን ደብረ ምሥጢርና ደብረ ምሥራቅ በምትባል ደብር በምስራቋ በኩል ሁለት የውኃ ምንጮችን ቆፈረ፡፡ በክረምትና በበጋ፣ በፀደይና በመፀውም ቢሆን ከውስጧ ውኃ እንዳይታጣ በመስቀል ምልክት አማትቦ ባረካት፡፡ ዳግመኛም በዚያ ደብር ቤተ ክርስቲያንን ይሠራ ዘንድ ፈጽሞ ጸለየ፡፡ በዚያች ደብረ መድኃኒት በምዕራቧ በኩል በግራና በቀኝ መላእክት እየተራዱት በእግዚአብሔር ፈቃድ ቤተ ክርስቲያንን ሠራ፡፡ ሥራውንም በፈጸመ ጊዜ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በዚያች ደብር ላይ ወርዶ እርሱ ራሱ በሥጋውና በደሙ ላይ ሠራዒ ካህን ሆኖ ለብፁዕና ቅዱስ አባታችን ለአባ ሰላማና ለከበሩ ነገሥታት ለአብርሃና አጽብሓ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው፡፡››
1 215
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን
ሐምሌ 26-ጌታችንን በእጆቹ ሥራ እየመገበ ያሳደገው አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ዐረፈ፡፡
+ ጌታችን ‹‹ስለ ትምህርትህና ስለ ስብከትህ ኢትዮጵያን ከጨለማ አውጥተህ በሃይማኖት ስለ አበራሃት…›› ብሎ ቃልኪዳን የሰጣቸው አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ዕረፍታቸው ነው፡፡ ከአቡነ ሰላማ በፊት እኛ ኢትዮጵያውያን ክርስቶስን ከማመን በቀር ሥጋ ወደሙ የመቀበል ልማድ ያልነበረን ሲሆን በድንኳን ካለችው ታቦተ ጽዮን በቀርም ታቦታትና አብያተ ክርስቲያናትም አልነበሩንም፡፡ አቡነ ሰላማ እኛን ኢትዮጵያንን የክርስቶስ ተካፋዮች ያደረገን የመጀመሪያው አባታችን ነው፡፡
+ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ሃሌሉያ ዕረፍታቸው ነው፡፡
አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ሃሌሉያ፡- የትውልድ ሀገራቸው ተንቤን ነው፡፡ አባታቸው ይስሐለነ እግዚእ እናታቸው ትቀድሰነ ማርያም ይባላሉ፡፡ አቡነ አቢየ እግዚእ አጎታቸው ናቸው፡፡ እናታቸው እሳቸውን ፀንሳ ሳለ ቡራኬ ለመቀበል ወደ ወንድሟ ስትሄድ አቡነ አቢየ እግዚእ መሬት ላይ ወድቀው ሰግደውላታል፡፡ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም ‹‹ለዚህች ሴት እንዴት ሰገዱላት?›› ብለው ቢጠይቋቸው አቡነ አቢየ እግዚእ ስለ አቡነ ሳሙኤል ክብርና ጽድቅ ትንቢት ነግረዋቸዋል፡፡
አቡነ ሳሙኤል ሲወለዱ እናታቸው ለአቡነ አቢየ እግዚእ ሰጠቻቸው፣ እርሳቸውም በሃይማኖት በመግባር ኮትኩተው ሁሉን አስተምረው አሳደጓቸው፡፡ አባታችን የጻድቃንና የሰማዕታትን ታሪክ እያነበቡ ያዝኑና ያለቅሱ ነበር፡፡ እንደ እነርሱ በሆንኩም እያሉ ይመኙ ነበር፡፡ አቡነ አቢየ እግዚእ ሀሳባቸውን በመንፈስ ተረድተውላቸው ነበርና መርቀው ባርከው አሰናበቷቸው፡፡ አቡነ ሳሙኤልም በሕፃንነታቸው መንነው ወደ አቡነ እንጦንዮስ ገዳም ገብተው በ14 ዓመታቸው መነኮሱ፡፡
ከየት እንደመጣ የማይታወቅና መላ አካሉ እንደበረዶ ነጭ የሆነ አንበሳ መጥቶ እየመራቸው አሁን ደብረ ሃሌሉያ እየተባለ ወደሚጠራው ገዳማቸው ሄደው በዓታቸውን አጽንተው ገዳሙን መሠረቱት፡፡ አቡነ ሳሙኤል ዘሀለሎም እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ ጻድቁ የጌታችን መከራ በማሰብ ከተወለዱ ጀምሮ ተላጭተውት የማያውቁትን ፀጉራቸውን ከትልቅ ዛፍ ላይ እያሠሩ ይጸልዩ ነበር፡፡ እንዲሁ አድርገው ዛፍ ላይ ራሳቸውን ሰቅለው 40 ቀንና 40 ሌሊት ሲጸልዩ በመጨረሻ የታሠሩበት ፀጉራቸው ተነቅሎ ከመሬት ላይ ወደቁ፡፡ ደማቸውም እንደ ውኃ ፈሰሰ፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን አስከትሎ ተገልጦላቸው እጃቸውን ይዞ አንሥቷቸዋል፡፡ ‹‹ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ?›› ቢላቸው ስለ ሀገራችን ሰላም ይልቁንም በዚህ በቆረቆሩት ገዳማቸው የሚኖሩትን ልጆቻቸውን እንዲጠብቅላቸው ለመኑት፡፡ ጌታችንም በገዳማቸው ውስጥ በፍጹም ሕማም፣ ደዌና ተስቦ በሽታ እንደማይገባ ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ለመንግሥተ ሰማያትም ያልታጨ ሰው በዚህ ገዳም ገብቶ አይቀበርም፡፡ ጻድቁ ከዛፉ ላይ ወድቀው ሳለ ጌታችንን እጨብጣለሁ ብለው የዘረጓት እጃቸው እያበራች ኖራለች፡፡ እንደ መብረቅም እየጮኸች ለገዳሙ እንደ ደወል ታገለግል ነበር፡፡ በመጨረሻም ሊያርፉ ሲሉ ልጆቻቸውን ሰብስበው ባርከዋቸዋል፡፡ ያ አቡነ ሳሙኤል የባረኩበት ቡራኬም በመጽሐፈ ግንዘት ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ዛሬም ድረስ ሰው ሲሞት ‹‹ቡራኬ ዘአቡነ ሳሙኤል›› ብሎ ካህኑ ይደግማል፡፡ እንደ አለመታደል ሆኖ በከተማ አካባቢ ግን እየተደረገ አይደለም፡፡ አቡነ ሳሙኤል ብዙዎችን ያመነኮሱ ሲሆን እንደነ አቡነ ተጠምቀ መድኅን፣ አቡነ ዘኢየሱስ፣ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ያሉ ሌሎችንም በርካታ መነኮሳትን አፍርተዋል፡፡
አባታችንን ያመነኮሷቸው አባት አቡነ እንጦንዮስ ሊጠይቋቸው ወደ ደብረ ሃሌሉያ ሄደው ሲመለሱ እንዲላላካቸው አንድ ትንሽ ልጅ ትተውላቸው ተመለሱ፡፡ አቡነ ሳሙኤልም በጥበብ መንፈሳዊ ኮትኩተው አሳደጉት፡፡ አንድ ቀን ምግባቸው የሚሆን የእንጨት ፍሬዎችን ለመልቀም ከበዓታቸው ሲወጡ ልጃቸው እንዳይደክምባቸው በማሰብ በገዳማቸው ትተውት ለመሄድ አሰቡ፡፡ ብቻውን ስለሆነ አስፈሪ አራዊት እንዳያስደነግጡት በማሰብ ጉድጓድ ቆፍረው በዚያ አኑረውት ሄዱ፡፡ ርቀው ሄደው የእንጨቶችን ፍሬ ሲለቅሙ በጫካው እሳት ተስቶ ገዳማቸውንም ሙሉ በሙሉ አቃጠለው፡፡ ጻድቁ ስለ ልጃቸው ወደ ፈጣሪያቸው ጸልየው ካበቁ በኋላ ወደ ገዳማቸው ቢሄዱ የልጃቸው የራስ ፀጉር እንኳን ሳትቃጠል በሰላም አገኝተውታል፡፡ ያ ልጅም በኋላ አቡነ ገብረ መስቀል የተባለው ገድለኛ አባት ነው፡፡
የአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ሃሌሉያ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን፡- ቅዱስ አባታችን አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በኋላ በ245 ዓ.ም በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ኅዳር 26 ቀን ሲወለዱ ታላቅ ብርሃን ከሰማይ ወርዶ ለ7 ቀናት አብርቷል፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ወደ ምድር ወርደው ጻደቁ በመወለዳቸው ታላቅ ደስታን አድርገዋል፡፡ አባታችን በተወለዱ ጊዜ ‹‹ለአብ ስግለት ለወልድ ስግደት ለመንፈስ ቅዱስ ስግደት ይገባል፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጡኝ ቅድመ ዓለም ለነበሩ ዛሬም ላሉ ዓለምን አሳልፈው ለሚኖሩ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል ብለው ዳግመኛም አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ብለው ፈጣሪያቸውን በአንድነት በሦስትነት አመስግነዋል፡፡ ቅዱስ አባታችን በሌላኛው ስማቸው ፍሬምናጦስ እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ በ40 ቀናቸው ጌታ በተጠመቀበት በዮርዳኖስ ያጠመቋቸውና ስመ ክርስትና የሰጧቸው ሊቀ ጳጳስ ‹‹ይህ ሕፃን ለኢትዮጵያውን ሁሉ ብርሃን ይሆንላቸዋል›› በማለት ትንቢት ተናግረዋል፡፡ አቡነ ሰላማ በሊቀ ጳጳሱ በቅዱስ አትናቴዎስ በሚገባ ተምረው ካደጉ በኋላ በ257 ዓ.ም ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ ስሙ ሜርጵዮስ ከሚባል ከአንድ ነጋዴ ጋር መጡ፡፡ ከእነሱም ጋር አድስዮስ የሚባል ልጅ ነበር፡፡ ወደ ሀገራችንም ሊመጡ የቻሉት እንዴት ነው? ቢሉ መጀመሪያ ለሰባት ወር በአንድ ሌላ አገር ኖረው ወደ ኢየሩሳሌም ሊመለሱ ሲሉ የበረሃ ሽፍቶች ሜርጵዮስንና ሌሎች መንገደኞችን ገደሏቸውና ሁለቱን ልጆች ማርከው ወስደው ስሙ አልአሜዳ ለሚባል ለአክሱም ንጉሥ ሰጡት፡፡ እርሱም አድስዮስን የቤተክርስቲያን የአልባሳትና የዕቃ ቤት ጠባቂ አድርጎ ሲሾመው ፍሬምናጦስን ደግሞ የቤተ ክርስቲያንና የሕግ ጠባቂ አደረገው-የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓቷንና አገልግሎቷን ጠንቅቆ ያውቅ ነበርና፡፡
እርሱም በአክሱምም በተጋድሎና በትጋት ኖረ፡፡ ቅዳሜና እሁድ የዛፍ ቅጠሎችን ከመመገብ በቀር ሌላ ምግብ አይቀምስም ነበር፡፡ በየቀኑም አምስት ሺህ ስግደትን ይሰግድ ነበር፡፡ በእርሱም የተጋድሎ ዘመን ደጋግ የሆኑ ነገሥታት አብርሃና አጽብሓ ነገሡ፡፡ እነርሱም ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍሬምናጦስን በጣም ይወዱት ነበር፡፡ አንድ ቀን ፍሬምናጦስ የአክሱሙን ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ሚናስን ‹‹ግዝረትና እምነት በእናንተ ዘንድ አለ ነገር ግን ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ መቀበል በእናንተ ዘንድ የለም›› አለው፡፡ ቅዱስ ሚናስም ‹‹ግዝረትንስ አባቶቻችን ሌዋውያን አመጡ፣ በክርስቶስ ማመንን ሕንኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት ጃንደረባ አመጣልን፡፡ ስለ ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ ሐዋርያ ወደ እኛ አልተላከም ነገር ግን ያልከውን ሁሉ የሚያደርግልን የሚባርከንና የሚቀድሰን ጳጳስን ታመጣልን ዘንድ ሊቀ ጳጳሱ ወዳለበት ወደ እስክንድሪያ አገር አንተ ሂድ›› አለው፡፡ ጥምቀትስ በጃንደረባው በኩል አገራችን ገብቶ ነበር ነገር ግን ገና ስላልተጠናከና ብዙ ሕዝብም አልተጠመቀም ነበርና አባታችን
1 215
ሐምሌ 25 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ታስበው የሚውሉት ጻድቁ አቡነ ሕፃን ሞአ በሕይወተ ሥጋ ሳሉ ዘወትር ዓርብ ዓርብ ወደ ሲኦል ወርደው እልፍ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጡ ሲሆን በሥራው ሁሉ እንደ በላኤ ሰብዕ የሆነውን ሰውም እንዲሁ ከሲኦል አውጥተውታል። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አንድ ጊዜ በሕፃን ልጅ አምሳል አንድ ጊዜ በሽማግሌ አምሳል እንዲሁም በቀራንዮ እንደተሰቀለ ሆኖ ይገለጥላቸው የነበረ ሲሆን ሲቀድሱ በበግ አምሳልም እየተገለጠላቸው ይሠዉት እንደነበር በገድላቸው ላይ ተጽፎ እናገኘዋለን።
አባታችን ሕፃን ሞአ ገና ሲወለዱ የወላጆቻቸውን ቤት በብርሃን የሞሉ፣ ስለ ጽድቅ ብለው ከበሬ ጋር በመታረስ ሰማዕትነትን የተቀበሉ፤ በደመና ተጭነው ወደ ኢየሩሳሌም ይሔዱ የነበሩ፤ ሌሊት ሌሊት በባሕር ውስጥ እየገቡ ይጸልዩ የነበሩ፣ እሾህ ያለው የብረት መታጠቂያ ታጥቀው ሲሰግዱ በዕንባቸው ምድርን ያርሱ የነበሩ፤ ተቀምጠው ጥቂት ያንቀላፉ ነበር እንጂ በጎናቸው ተኝነተው የማያዉቁ፣ ሰይጣን በዘንዶ ተመስሎ ሊበላቸው ቢመጣ አማትበው ከሁለት የከፈሉ፣ ምድር፣ ባሕር፣ እንስሳት፣ አዕዋፋት፣ ዕፅዋት ሁሉ በሰው ቋንቋ ያናግሯቸው የነበሩ፣ የከበሩ ዘጠኙ ቅዱሳን በትግራይ ሳለ ተገልጠውላቸው ምሥጢር ያለው መልእክት የነገሯቸው፤ አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ተገልጣ የወርቅ መስቀል ስጦታ የሰጠቻቸው፤ መንፈስ ቅዱስ በጎልማሳ ሰው አምሳል የተገለጠላቸውና የባረካቸው፤ በሕይወተ ሥጋ ሳሉ መልአክ የሲኦልን በር ከፍላቶቸው እልፍ ነፍሳትን ያወጡ፤ ጌታችን ተገልጦላቸው ራሱ በክቡራት እጆቹ ያቈረባቸው በኋላም ታላቅ የምሕረት ቃልኪዳን የገባላቸው ሲሆን አባታችን በዚህ ዘመን በትውልዱ ዘንድ እንደሚገባቸው መጠን ያልታወቁ እጅግ ታላቅ ጻድቅ ናቸው። አሁን ግን ገድላቸው ታትሞ ሕዝበ ክርስቲያኑ ዘንድ ደርሶ ጻድቁ በስፋት የሚታወቁበት ጊዜ ስለደረሰ በእጅጉ ደስታ ይሰማናል።
ከዝክረ ቅዱሳን አገልግሎታችን ውስጥ አንዱ ገድለ ቅዱሳንን ማሳተምና ለገዳማቱ ማስረከብ እንደሆነ ይታወቃል። በዚኹ መሠረት የአቡነ ሕፃን ሞዐን ገድል እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ አሳትመን ለገዳሙ ስለአስረከብን ልዑል እግዚአብሔርንና ጻድቁ አቡነ ሕፃን ሞዐን እናመሰግናለን!!! ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!!!
1 215
‹‹ከወዴት ነህ? ከዚህ በረሃ ውስጥስ እንዴት ጠፋህ?›› አለው፡፡ ወጣቱ እስላምም የሆነውን ነገረው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም ‹‹ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ›› አለውና በአየር ላይ እየበረረ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች በውስጧ አስገባውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ ይህም ወጣት በኋላ አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሰማዕትነት ተቀብሏል፡፡ ገዳምም ገብቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ እንደገና ወደ አገሩ ተመልሶ ብዙዎችን ወደ ክርስትና አምጥቷል፡፡ በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም ቤተ ክርስቲያን አሠርቶ አበ ምኔትም ሆኖ ብዙ መነኮሳትን አፍርቷል፡፡
የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
1 215
ሲመለስ ወንዙ ወዲያው ደረቀ፡፡ እነርሱም ወንዙ የደረቀው በዱማድዮስ ምክንያት መሆኑን ዐውቀው ከእግሩ ሥር ወድቀው ይቅርታ ሲጠይቁት በጸሎቱ የወንዙን ውኃ እንደቀድሞው መልሶላቸዋል፡፡ በዚህም ሲያከብሩት ቢመለከት ጊዜ ውዳሴ ከንቱ መጣብኝ ብሎ ከዚያ ወጥቶ በመሄድ በሌላ ቦታ በዓት ሰርቶ መኖር ጀመረ፡፡ የከሃዲው ንጉሥ የዋልጦስ ጭፍሮች ቤተ ክርስቲያንን ሊያፈርሱ ሲሄዱ የቅዱስ ዱማድዮስን በዓት አግኝተው እርሱንና ደቀ መዝሙሩን ከውጭ ሆነው በድንጋይ ወገሯቸው፡፡ በበዓታቸውም ላይ የወደቀው የድንጋዩም መጠን ኮረብታ ሆነ፡፡ ቅዱስ ዱማድዮስና ደቀ መዝሙሩም በዚያው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላም በዚሁ በሐምሌ 25 ቀን አንድ ነጋዴ በዚያ ሲያልፍ ግመሉ የቅዱሳኑ ዐፅም ያለበት ቦታ ላይ ወድቆ በዚያው ዐፅማቸው ተገኝቶ ሊጣ ቻለ፡፡ ከሥጋውም ብዙ ተአምራት ተገለጡ፡፡
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ ድንቅ ተአምር ያደረገበትና ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ልደቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡
ታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርቆሬዎስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ‹‹መርቆሬዎስ›› ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ወላጆቹ አስሊጥ ከምትባል ሀገር ቢሆኑም እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡ አያቱና አባቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ስለነበር አንድ ቀን እንደልማዳቸው አውሬ ሲያድኑ ከገጸ ከለባት ወገን የሆኑ ሁለት ወንዶች አግኝተዋቸው የመርቆሬዎስን አያት በሉት፡፡ አባቱንም ሊበሉት ሲሉ የታዘዘ መልአክ ከለከላቸው፡፡ ዙሪያቸውንም በእሳት አጥሮ ከበባቸው፡፡ እነርሱም በተቸገሩ ጊዜ ለመርቆሬዎስ አባት ሰገዱለት፡፡ በዚያን ጊዜም እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደበጎች የዋሆች ሆነው አብረውት ወደ መንደር ገቡ፡፡
ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተወለደና ስሙ ፒሉፓዴር ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸውም በእርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት ኖሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፡፡ አባቱን ኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፡፡ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባትና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜናቸውን ሲሰማ ወታደሮቹን ልኮ በፊቱ አቆማቸው፡፡ እግዚአብሔርም የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው አራዊት አደረጋቸውና ንጉሡን እጅግ አስፈሩት፡፡ ንጉሡም የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የአራዊት ተፈጥሮአቸውን ያርቅለት ዘንድ ለመነው፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት በለመነ ጊዜ ተፈጥሮአቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ፡፡
ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ገዥና የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የውሻ ፊት ያላቸውም አብረው ያገለግሉት ስለነበር ሁሉም ይፈራው ነበር፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ከላከው በኋላ ሳይመለስ ስለቀረ ሚስቱን ሊያገባት አሰበ፡፡ የመርቆሬዎስ አባትም የመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ገዢ በነበረው ንጉሥ ተይዞ ቢማረክም ገዥው ክርስቲያን መሆኑን አይቶ አከበረው፡፡ ቆይቶም በሀገሩ ላይ ሾመው፡፡ ሚስቱም ጠፍታ ከሀገሯ ወጥታ ሄዳ ስለነበር ከባሏ ተገናኝተው በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡ መርቆሬዎስም አባቱና እናቱ ከሞቱ በኋላ ንጉሡ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው፡፡
መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብሮት ነበር፡፡ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በጦሩ መሀል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ›› አለው፡፡ መልአኩም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና ‹‹ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው›› አለው፡፡
ጦርነቱን ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት ‹‹ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት እረሳህ?›› አለው፡፡ ከጦርነቱም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፡፡ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ ‹‹ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፣ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም›› አለው፡፡ ንጉሡም ተናዶ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡
ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የአገሩ ሰዎች እንዳይነሱበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጵዶቅያና የእስያ ክፍል ወደሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ንጉሡ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ኅዳር 25 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፡፡ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፡፡ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡
ከብዙ ተአምራቱም አንዱ የቂሳርያውን ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስን እረድቶ ከሃዲውን ዑልያኖስን የገደለበት ነው፡፡ ዑልያኖስ ነግሦ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖታትን ማምለክና ክርስቲያኖችን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ የቂሳርያው ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም አስተምሮ ሊመልሰው ወደ ንጉሡ ቢመጣ ክብር ይግባውና ዑልያኖስ ጌታችንን ሰድቦ ባስልዮስንም አሰረው፡፡ ባስልዮስም በእሥር ቤት ሳለ በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ጸለየ፡፡ ሥዕሉም ወዲያው ተሰወረው፡፡ ያንጊዜም ወደ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ዘንድ ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለውና ወዲያው ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡ ከጦሩም አንገት ደም ይንጠፋጠፍ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ከሃዲውን ንጉሥ እንደገደለው ዐውቆ ‹‹የክርስቶስ ምስክር ጌታዬ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?›› አለው፡፡ ሥዕሉም ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አደረገ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡
ሌላው ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በተአምሩ ከእስልምና እምነት መልሶ ክርስቲያን ያደረገው አንድ እስላም ሰው አለ፡፡ ይኸውም የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራችበት በምስር አገር የሚኖር ከመሳፍንት ወገን የሆነ ወጣት ነበረ፡፡ ከብዙ ሰዎችም ጋር ሆኖ ወደ መሐመድ መቃብር ለመሄድ እንዳሰበ ለአባቱ ሲነግረው ስንቅ ሰንቀው በሰላም ወደ መካ መዲና ሸኙት፡፡
መካ ደርሰውም ሥራቸውም ፈጽመው ወደቤታቸው እየተመለሱ ሰባት ቀን ተጓዙ፡፡ በሌሊትም ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ ግዳጁ ያ እስላም ወጣት ከግመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ፡፡ እነርሱም አብሯቸው የሚጓ መስላቸው ስለነበር ባልንጀሮቹም በበረሃው ውስጥ ትተውት ሄዱ፡፡ እርሱም ወዴት እንደሚሄድ ስላላወቀ አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ እጅግ ደነገጠ፡፡ በዚያም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ ቅዱስ መርቆሬዎስን እንዲያድነው በመለመን ተሳለ፡፡ ወዲያውም ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሱ መጣና
1 215
+ + +
ሰማዕታቱ ቅድስት ቴክላ እና ቅድስት ሙጊ፡- ቅድስት ቴክላና ቅድስት ሙጊ ከምትባል ቅድስት ጋር አንድ ላይ ሰማዕትነት የተቀበሉ ከእስክንድርያና ከባሕያራ አውራጃ ቀራቁስ ከሚባል መንደር የተገኙ ናቸው፡፡ ሁለቱም በቀራቁስ መንደር ውስጥ እግዚአብሔርን በምትፈራ በአንዲት ሴት ቤት አደጉ፡፡ አንድ ቀን በባሕር ዳርቻ ሲያልፉ መኰንኑ የክርስቲያን ወገኖችን ሲያሠቃያቸው አዩት፡፡ የእግዚአብሔርም መልአክ ተገለጠላቸውና ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም መከራን ለሚታገሡ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጀላቸውን ክብራቸውን አሳያቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅድስት ቴክላና ቅድስት ሙጊ በመርከብ ተሳፍረው ወደ እስክንድርያ ተጓዙ፡፡ በመኰንኑም ፊት ቆመው ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን መሰከሩ፡፡ እርሱም ጽኑ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮች አሠቃያቸው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በሚያለቅሱ ሁለት ሴቶች አምሳል ከቅድስት አልሳቤጥ ጋር ተገለጠችላቸውና አጽናናቻቸው፡፡ በመጨረሻም መኰንኑ በመጀመሪያ የቅድስት ሙጊን ራስ በሰይፍ ከቆረጠ በኋላ ቅድስት ቴክላ ወደ ሌላ ቦታ ላካትና በዚያም ጽኑ ሥቃይን ተሠቃይታ አንገቷን ተሰይፋ የሰማዕትነት ተጋድሎዋን ፈጽማለች፡፡
+ + +
ሰማዕቷ ቅድስት ኢላርያ፡- የቅድስት ኢላርያ ወላጆቿ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ በጾም በጾሎት መጋደል የጀመረችው ገና በሕፃንነቷ ነው፡፡ 11 ዓመት በሆናት ጊዜ ራሷ ቆማ ስትጸልይ ጌታችን ታላቅ ብርሃን ገለጠላት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሩፋኤልም ተገልጦላት የጌታችንን አምላክነት በከሃድያኑ ፊት መስክራ የሰማዕታት የክብር አክሊል እንድትቀዳጅ ነገራት፡፡ በተነገራትም መሠረት ደስ ተሰኝታ ያላትን ንብረት መጽውታ ‹ጣው እና ሰርስና› ወደሚባሉ ሀገሮች ሄዳ በከሃዲው መኮንን ፊት መሰከረች፡፡ ጌታችን ሳኑሲ ለመባል ጻድቅ ሰው ስለ ቅድስት ኢላርያ ነገረውና ሳኑሲም በእርሷ ጽናት ደስ ተሰኝቶ አጽናናት፡፡ መኮንኑም ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ሥቃዮች አሠቃያት፡፡ ሥጋዋን ሰነጣጥቆ በእሳት በጋሉ የብረት ችንካሮች ቸነከራት፡፡ ከዚህም በኋላ ከ500 ባልነጀራሞች ሰማዕታት ጋር አሠራት፡፡ በመርከብ ውስጥ ጭነው ሲወስዷቸው ድንገት አንድ ዓሣ አንበሪ መጥቶ ከእናቱ ዕቅፍ አንዱን ልጅ ነጥቆ ወሰደው፡፡ እናቱም እጅግ ባለቀሰች ጊዜ ቅድስት ኢላርያ አይታት ራራችላትና ወደ ጌታችን ለመነችላት፡፡ ወዲያውም ዓሣ አንበሪው ነጥቆ የወሰደውን ልጅ ምንም ጉዳት ሳያደርስበት መልሶ ለእናቱ ሰጣት፡፡
ከዚህም በኋላ መኮንኑ የቅድስት ኢላርያን ሰውነቷን ማሠቃየቱን ቀጠለ፡፡ ሁሉንም የእግሯንና የእጇን ጥፍሮቿን ነቀላቸው፡፡ ምላሷን አስቆረጠው፡፡ በብረት ችንካር ቸነከራት፡፡ በብረት አልጋ ላይ አስተኝቶ ከታች እሳት አነደዱበት፡፡ ነገር ግን ይህ ሁሉ መከራ ከደረሰባት በኋላ ጌታችን ፍጹም ጤነኛ አደረጋት፡፡ መኮንኑም እርሷን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራሷን በሰይፍ አስቆረጣትና የሰማዕትነት ፍጸሜዋ ሆነ፡፡
+ + +
ሰማዕቱ ቅዱስ አበከረዙን፡- ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ወንበዴ የነበረ ነው፡፡ አበከረዙንም ከሌሎች ሁለት ወንበዴ ጓደኞቹ ጋር የአንድን መነኩሴ ንብረት ለመስረቅ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሄዱ፡፡ መነኩሴውንም ቆሞ ለጸሎት እየተጋ ስላገኙት ጨርሶ እስኪተኛ ድረስ ጠበቁት፡፡ እርሱ ግን ሲጸልይ አደረ እንጂ አልተኛም ነበር፡፡ እነርሱም ታላቅ ፍርሃት አደረባቸውና ደነገጡ፡፡ በነጋም ጊዜ ሽማግሌው መነኩሴ ወደ ሽፍቶቹ ሲመጣ ሲያዩት ከእግሩ በታች በመስገድ ይቅር እንዲላቸው ለመኑት፡፡ ሰይፎቻቸውንም መዝው በፊቱ ጥለው ደቀመዝሙሮቹ ያደርጋቸው ዘንድ ለመኑትና አስተምሮ አመነኮሳቸው፡፡
ቅዱስ አበከረዙን በጽኑ ተጋድሎ ሳለ አንድ ጻድቅ ወደ እርሱ መጥቶ ሰማዕት እንደሚሆን ትንቢት ነገረው፡፡ ከ7 ዓመት በኋላ ሰይጣን በክርስቲያኖች ላይ መከራን አመጣ፡፡ ቅዱስ አበከረዙንም ከመንፈሳዊ አባቱ ቡራኬ ተቀብሎና ተሰናብቶ ከገዳም በመውጣት ወደ ምስክርነት አደባባይ ወጣ፡፡ ኒቅዮስ ወደምትባል ሀገርም ሄዶ ከሃዲውን ንጉሥ መክስምያኖስን አገኘውና በፊቱ የጌታቸንን ክብር መሰከረ፡፡ ንጉሡም ሥጋውን በመጋዝ ቆራርጦ በቁስሉ መጣጣና ጨው ጨመረበት፡፡ ወደ እስክንድርያም ሲወስዱት በመርከብ ምሰሶ ላይ 5 ጊዜ ሰቀሉት፡፡ በጋን ውስጥ ከተው ወደ ባሕር ውስጥም ጣሉት ነገር ግን የታዘዘ መልአክ መጥቶ ገምኑዲ ወደምትባል ከተማ እንዲሄድ ነገረው፡፡ ወደ ትውልድ ሀገሩም በመሄድ አበከረዙን ስለሚባል ሰው ሲጠይቅ ማንም አላወቀውም ነበር፡፡ አንዲት ሕፃን ልጅ አውቃው ስሙን ከጠራችው በኋላ ሰገደችለት፡፡ ሕዝቡንም ከደዌያቸው ፈወሳቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ አበከረዙን ወደ ገምኑዲ ከተማ ሄዶ ከወታደሮቹ ጨፍሮች አንዱን ‹‹እኔ ክርስቲያን ነኝና በዚህች ከተማ አስረህ ጎትተኝ›› አለው፡፡ እርሱም ወደመኮንኑ እስኪያደርሰው ድረስ አሥሮ እየጎተተ ወሰደው፡፡ መኮንኑም በእንጨት ላይ ዘቅዝቆ ሰቀለውና ደም በአፍና በአፍንጫው እየፈሰሰ ለ10 ቀን ቆየ፡፡ በብረት በትር ደብድበው የጀርባውን አጥንት ሰበሩት፡፡ ነገር ግን ጌታችን ፈጽሞ ፈወሰው፡፡ የጭፍሮች አለቃ የሆነው የአንዱ ልጁ ከሞተች ከ12 ቀናት በኋላ አበከረዙን ከሞት አስነሣት በሲኦል ያየችውን ሁሉ ለሕዝቡ መሰከረች፡፡ መኮንኑም ማሠቃየት ቢሰለቸው ወደ እስክንድርያ ላከው፡፡ ጌታችንም ለአበከረዙን ተገለጠለትና አጽናናው ሰማዕትነቱንም በዚያ እንደሚፈጽም ነገረው፡፡ ጌታችን እንደነገረውም በእስክንድርያ ብዙ ከተሠቃየ በኋላ በዚህች ዕለት አንገቱን ተሰይፎ ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ጌታችን ስሙን ለሚጠራ ቃልኪዳን ገብቶለታል፡፡ የታዘዘ መልአክም መኑፍ በሚባል ሀገር ለሚገኝ ለአንድ ቄስ ተገልጦ የቅዱስ አበከረዙንን ሥጋ ያለበትን ከነገረው በኋላ ወስዶ በክብር እንዲያስቀምጠው አዘዘው፡፡ ከሥጋውም ብዙ አስደናቂ ተአምራት ተገለጡ፡፡
+ + +
ሰማዕቱ ቅዱስ ዱማድዮስ፡- የከዋክብትን ጥበብ እየተማረ በፋርስ ሀገር አደገ፡፡ ክርስትናን መማር ሽቶ አጋልዮስ የሚባለውን ቄስ አገኘውና ከእርሱ ሃይማኖትን ተማረ፡፡ ወደ ሶርያ ሀገር ሄዶ በዚያ ተጠምቆ መነኮሰና በጽኑ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ ነገር ግን ጽኑ ተጋድሎውን ያዩ መነኮሳት ቀኑበትና ከዚያ ሊያባርሩት ወደዱ፡፡ ሀሳባቸውን ካወቀ በኋላ ወደ ሰርጊስ ገዳም ሄደና በዚያም ከአንድ ሽማግሌ ቄስ ጋር በመቀመጥ ዲቁና ተሹሞ ማገልገል ጀመረ፡፡ በቅዳሴም ጊዜ በመሥዋዕቱ ላይ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ሲወርስ ዱማድዮስ ያያል፡፡ ነገር ግን ሥጋዊ ርግብ እንደሆነች እያሰበ ርግቧ ጽዋውን እንዳትደፋው በማለት ያባርራት ዘንድ እጁን ይሰነዝራል፡፡ ሽማግሌው መነኩሴ ግን እርግቧን አያያትም ነበር፡፡ ቅዳሴውም ካበቃ በኋላ ቄሱ ለምን እጁን ወደ መሥዋዕቱ እንደሚዘረጋና እንደሚደነግጥ ዱማድዮስን ጠየቀው፡፡ ዱማድዮስም ያየውን ሲነግረው ቄሱም ‹‹ሌላ ጊዜ ስታያት ለእኔ ንገረኝ›› አለው፡፡
ዱማድዮስም ሌላ ቀን ርግቧን ባያት ጊዜ ‹‹አባቴ ሆይ ርግቧ መጣች›› አለው ነገር ግን አሁንም ግን ቄሱ አላያትም፡፡ ቄሱም ይህ ምሥጢር ይገለጥለት ዘንድ ወደ ጌታችን አጥብቆ ጸለየ ነገር ግን እንዳይታበይ በርግቧ የተመሰለ መንፈስ ቅዱስ መሆኑን ለዱማድዮስ አልነገረውም፡፡ ቄሱም ዱማድዮስን ወስዶ ቅስና አሾመው፡፡ የቅዱስ ዱማድዮስ ዜናው እስከ ሊቀ ጳጳሳቱ በተሰማ ጊዜ ከዚያ በመሸሽ ወደ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ሄደ፡፡ በዚያም ሣር እየበላ ኖረ፡፡ ብዙ ተአምራቶችንም ይሠራ ነበር፡፡ ዕውራንን ያበራል፣ ድዳዎች እንዲናገሩ ያደርጋል፣ አንድ ቀን ወደ ወንዝ ውኃ ሊቀዳ ቢወርድ ሴቶች ቢዘባበቱበት አዝኖ
