uz
Feedback
ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

Kanalga Telegram’da o‘tish

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ውስጥ የተጻፉ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸውና አስገራሚ ታሪካቸው ዓመቱን ሙሉ ምንም ሳይቋረጥ በየቀኑ ይነገርበታል! ለአሥትያየትዎ @abitago

Ko'proq ko'rsatish
1 210
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-47 kun
-630 kun
Postlar arxiv
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን መስከረም 9-ከቅዱስ ፋሲለደስ ጋር ዐሥራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ሰባት (14737) አማኞች በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ + ‹‹ተጋድሎውን በዛፍ ላይ ሆኖ የፈጸመ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘ ንጉሥ ያሳይ ዕረፍቱ ነው›› በማለት ስንክሳሩ በስም የገለጸው ጻድቁ ንጉሥ ያሳይ ዐረፈ፡፡ + አባ ቢሶራ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ + ዳግመኛም በዚህች ዕለት የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በሮም አገር ታላቅ ተአምር ያደረገባት ዕለት ናት፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በሮም አገር ያደረገው ታላቅ ተአምር፡- ይኸውም በሮም አገር ፍሩምያ በምትባል ከተማ የተደረገ ተአምር ነው፡፡ በዚህች ከተማ ውስጥ የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ነበረች፡፡ በዚህችም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገናናው መልአክ ብዙ አስደናቂ ተአምራትን ሲሠራ ኖረ፡፡ በዚህም ምክንያት ዮናናውያን ሰዎች ሰይጣናዊ ቅናት ቀንተው በአካባቢው የሚወርደውን የወንዝ ውኃ አቅጣጫውን መልሰው ቤተ ክርስቲያኗን የሚጠባቃትን መጋቢውንም ጭምር በውኃው ሊያሰጥሟት ተነሡ፡፡ በዚህም ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ለቤተ ክርስቲያኑ መጋቢ ለናርጢኖስ ተገለጠለትና ‹‹አይዞህ ጽና አትፍራ›› አለው፡፡ ይህንንም ብሎ በእጁ ላይ ባለው በትር ዐለቱን መታው፡፡ ዐለቱም ተሰንጥቆ እንደበር ሆነ፡፡ የዚያ ወንዝ ውኃም በውስጡ አልፎ ሄደ፡፡ ይህንንም ያዩ ሁሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ገናናውን መልአክ ቅዱስ ሚካኤልንም አከበሩት፡፡ ከዚያች ቀን እስከዛሬ የወንዙ ውኃ በዚያች በተሰነጠቀች ዐለት ውስጥ አልፎ ሲሄድ ያዩታል፣ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ግን ከቶ አይቀርብም፡፡ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ አይለየን፡፡ +++ አባ ቢሶራ፡- ይኸውም አባ ቢሶራ በግብጽ አገር መጺል የምትባል ከተማ ኤጲስ ቆጶስ ሲሆን ዲዮቅልጥያኖስ የክርስቲያኖችን ደም እንደ ውኃ ሲያፈስ አባ ቢሶራም በጌታችን ስም ሰማዕት ይሆን ዘንድ ወደደ፡፡ ሕዝቡን ሁሉ ጠርቶ በሃይማኖት እንዲጸኑ ከመከራቸው በኋላ ወደ ከሃዲዎች ዘንድ ሄዶ የጌታችንን ክብር መስክሮ ለመሞት እንደወሰነ ነገራቸው፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ታላቁም ታናሹም እያለቀሱ ‹‹ከእኛ ተለይተህ ወደ ሞት አትሄድም፣ እኛንስ እንደሙት ልጆች ለምን ትተወናለህ?›› እያሉ ለመኑት፡፡ ነገር ግን አባ ቢሶራ ሰማዕትነት ዕጣ ክፍሉ መሆኑን ነግሯቸው በሃይማኖት እስከመጨረሻ እንዲጸኑ ከመከራቸው በኋላ ተሰናብቷቸው ወደ ሰማዕትነት ሄደ፡፡ ሕዝቡም መሪር ልቅሶን እያለቀሱ ሸኙት፡፡ ሌሎች ሦስት ኤጲስ ቆጶሳትም ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ ተከትለውት ሄዱ፡፡ አባ ቢሶራ እና ሦስት ኤጲስ ቆጶሳትም የክርስቲያኖችን ደም ያፈስ በነበረው መኮንን ፊቱ ቆመው የጌታችንን አምላክነት መሰከሩ፡፡ መኮንኑም ይዞ ጽኑ ሥቃይ አደረሰባቸው፡፡ ይልቁንም ኤጲስቆጶሳት መሆናቸውን ሲያውቅ ሥቃይን አበዛባቸው፡፡ ነገር ግን ጌታችን እያጸናቸው መከራውን በትዕግስት ተቀበሉ፡፡ በመጨረሻም በዚህች ዕለት አባ ቢሶራና ሦስት ኤጲስ ቆጶሳት (ቢስኮስ፣ ፊናቢክስ እና ቴዎድሮስ) አንገታቸውን ተሰይፈው ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን! + + + ዳግመኛም በዚህች ዕለት ከቅዱስ ፋሲለደስ ጋር ዐሥራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ሰባት (14737) አማኞች በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ (ከሰማዕቱ የዕረፍት ዕለት ጋር መስከረም ዓሥራ አንድን ቀን እንመለከተዋለን፡፡ ) የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

ሙሴ ሰው ከወዳጁ ጋር እንደሚነጋገር ከእግዚአብሐር ጋር 570 ጊዜ ቃል በቃል ተነጋግሯል፡፡ 40 ቀን 40 ሌሊት ከጾመ በኋላ ዓሥሩን ትእዛዛት የተጻፉባቸውን ጽላት ተቀበለ፡፡ እስራኤላውያን ባዩት ጊዜ እንዳይሞቱ ፊቱን እስኪሸፍንላቸው ድረስ ፊቱ እንደ ፀሐይ የሚያበራበት ጊዜም ነበር፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሴ 120 ዓመት በሆነው ጊዜ እግዚአብሔር ሕዝቡን ለአገልጋዩ ለነዌ ልጅ ለኢያሱ እንዲያስረክበው ስላዘዘው ለኢያሱ አስረክቦታል፡፡ ሙሴም እግዚአብሔር እንዳዘዘው በምስክሩ ድንኳን ውስጥ የሚሠራውን ሁሉ ሠርቶ ካዘጋጀ በኋላ በተራራ ውስጥ ዐረፈ፡፡ በዚያም በመልእክት እጅ በሥውር ተቀበረ፡፡ የእስራኤል ልጆችም ወስደው እንዳያመልኩት እግዚአብሔር የሙሴን ሥጋ ሰወረ፡፡ ሰይጣንም የሙሴን ሥጋ ለእስራኤል ሊገልጥላቸው በወደደ ጊዜ ሐዋርያው ይሁዳ በጻፈው መጽሐፉ ላይ እንደመሰከረ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ገሠጸው፣ ከዚህም ሥራ ከለከለው፡፡ የእስራኤልም ልጆች ለሙሴ 40 ቀን አልቅሰውለታል፡፡ ጌታችን ስለ ሙሴ ሲናገር ከእስራኤል ልጆች ውስጥ እንደ ሙሴ ያለ ደግ የዋህ ቅን ነቢይ እንደማይነሣ መስክሮለታል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን! + + + የመጥምቁ ዮሐንስ አባት የበራክዩ ልጅ ካህኑ ዘካርያስ፡- የበራክዩ ልጅ ካህኑና ነቢዩ ዘካርያስ- ይህም ነቢይ ዘካርያስ በንጉሥ ሄሮድስ እጅ መስከረም 8 ቀን በሰማዕትነት ያረፈ ሲሆን የመጥምቁ ዮሐንስ አባት ነው፡፡ ስለ ልጁ ዮሐንስ መወለድ ቅዱስ ገብርኤል ባበሰረው ጊዜ አምኖ ባለመቀበሉ ልጁ ዮሐንስ እስኪወለድ ድረስ ዲዳ ሆኗል፡፡ ልጁ በተወለደም ጊዜ ‹‹ስሙን ዮሐንስ በሉት›› ብሎ በእጁ ሲጽፍ አንደበቱ ተከፍቶለታል፡፡ እርሱና ሚስቱ በእግዚአብሔር ሕግ ያለነቀፋ የጸኑ ደጎች እንደሆኑ ቅዱስ ወንጌል ይመሰክርላቸዋል፡፡ ‹‹በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ›› ተብሎ ነው በወንጌል ጽድቃቸው የተነገረላቸው፡፡ ሉቃ 1፡5-6፡፡ ንጉሥ ሄሮድስ ጌታችንን የሚያገኝ መስሎት 144 ሺህ ቤቴልሔም ሕፃናትን በግፍ ሲጨፈጭፍ እመቤታችን ልጇን ጌታችንን ይዛ ወደ ግብጽ ስትሰደድ ዮሐንስንም እናቱ ቅድስት አልሳቤጥ ይዛው ወደ ሲና በረሃ ገባች፡፡ ኤልሳቤጥ ከመሄዷ በፊት ግን ከባሏ ከዘካርያስ ጋር ሲሰነባበቱ የሚሆነውንም ሁሉ እርሱ ቀድሞ ያውቅ ነበርና ‹‹ሕፃኑን ልጄን ሲያጡ እኔን ይገድሉኛል፣ አንቺ ግን ወደ በረሃው ይዘሽው ሂጂና በዚያ ሸሽጊው›› ብሎ መክሯታል፡፡ ኤልሳቤጥም ከሄደች በኋላ የርጉም ሄሮድስ ጭፍሮች ዮሐንስን ባጡት ጊዜ ወደ ዘካርያስ መጥተው ‹‹ልጅህን ወዴት አድርሰኸው ነው? ወዴትስ ደበቅኸው? አሁን ከደበቅህበት አምጥተህ ፈጥነህ አስረክበን›› በማለት የፍጥኝ አስረው አሠቃዩት፡፡ ሄሮድስም ዘካርያስ ዘንድ ሄዶ ሕፃኑን ልጅ ዮሐንስን ካልሰጠው እንደሚገድለው ነገረው፡፡ ካህኑ ዘካርያስም የንጉሡን ዛቻ ባለመፍራት አገልግሎቱን ቀጠለ፡፡ በመጨረሻም ንጉሡም ወታደሮቹን ልኮ በቤተ መቅደሱና በመሠዊያው መካከል አስገደለው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የቅዱስ ዘካርያስን ሥጋውን ሰወረው፣ ደሙ ግን እንደ ድንጋይ ሆነች፡፡ ሕዝቡም እንደ ልማዳቸው ለጸሎት በመጡ ጊዜ ከካህናት አንዱ ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ የረጋ የዘካርያስን ደም አገኘ፡፡ ከመሠዊያውም እንዲህ የሚል ድምፅ ተሰማ፡- ‹‹እነሆ የበራክዩ ልጅ ዘካርያስ ተገደለ፣ የሚበቀልም እስኪመጣ ድረስ ደሙ ስትጮህ ትኖራለች›› የሚል ድምፅ ተሰማ፡፡ ይህንንም አንዳንዶች በማሳሳት ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ስለሆነው ስለ በራክዩ ልጅ ነቢዩ ዘካርያስ የተነገረ ነው ይላሉ ግን አይደለም፡፡ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው የበራክዩ ልጅ ነቢዩ ዘካርያስ የእርጅና ዘመኑ ደርሶ ኡረት በሚባል አገር ሞተ፡፡ ሥጋውም ያለጥፋት በዚያ ተገኝቶ ቤተ ክርስቲያን ሠርተውለታል፡፡ የዚህኛው የካህኑና የመጥምቁ አባት ዘካርያስ ግን ሥጋው አልተገኘም፡፡ ስለመገደሉ የደሙ ድምፅ ምስክር ሆነ እንጂ፡፡ ጌታችንም ለተረገሙ አይሁድ ስለእርሱ ሲናገር ‹‹የገደላችሁት የዘካርያስ ደም በላያችሁ ይደርሳል›› ብሏቸዋል፡፡ የዘካርያስም ደም እስከ ሰባት ዓመት ድረስ እየፈላ ደሙ ሲካሰሳቸው ከኖረ ገዥው ጥጦስ ገዳዮቹን በሰይፍ ሲገድላቸው ደሙ መፍላቱን አቁሟል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን መስከረም 8-ግብጻዊው ዕብራዊውን ሲገድለው አይቶት ለወገኑ ተበቅሎ ግብጻዊውን ገድሎ ወደ ምድያም አገር ማለትም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የካህኑን የዮቶርን ልጅ አግብቶ ሁለት ልጆችን ወለዶ በኢትዮጵያ 40 ዓመት ከኖረ በኃላ የዮቶርን በጎች እየተበቀ ሳለ እግዚአብሔር በቁጥቋጦ ውስጥ በታላቅ ራእይ ተገልጦለት እስራኤልን ከግብጽ እንዲያወጣ ነግሮት ሄዶ በ10 መቅሰፍታት እስራኤላውያንን ነጻ ያወጣቸው ሊቀ ነቢያት ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡ + የመጥምቁ ዮሐንስ አባት የበራክዩ ልጅ ካህኑ ዘካርያስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ + ከሃዲው መኮንን በእጅጉ ካሠቃየው በኋላ አንገቱን በሰይፍ የሰየፈው ሰማዕቱ ቅዱስ ሉክዮስ ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡ + ሰማዕቱ ቅዱስ ዲማድዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ + ምግቡ የአጋዘን ወተት የሆነ በዕረፍቱም ጊዜ ብዙ ተአምራትን ያደረገ የከበረ ገዳማዊ ቂርቆስ ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ዲማድዮስ፡- ይኸውም በሃይማኖትና በምግባር ያጌጠ ስለነበር ጌታችን ተገልጦለት ሄዶ በስሙ ሰማዕት ይሆን ዘንድ አዘዘው፡፡ ከደቡባዊ ግብጽ ተነሥቶ እናት አባቱን ትቶ ወጥቶ ወደ አትሪብ በመሄድ በከሃዲው መኮንን ፊት ስለ ጌታችን መሰከረ፡፡ ከሃዲውም ገዥ ጽኑ ሥቃይ ካደረሰበት በኋላ ወደ እስክንድርያ ላከው፡፡ የእስክንድርያም መኮንን ሉክያኖስ በተራው አሠቃየው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ዲማድዮስ ተገልጦለት አረጋጋው፡፡ በኋላም መኮንኑ ዲማድዮስን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕትነቱ ፍጻሜ ሆነ፡፡ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን! + + + ሊቀ ነቢያት ሙሴ፡- የፈርዖን ሴት ልጅ ‹‹ከውኃ አውጥቼዋለሁና›› ስትል ሕፃኑን ሙሴ ብላ ጠርታዋለች፡፡ ዘጸ 2፡10፡፡ እስራኤላውን በግብፅ ባርነት እየተገዙ ባለበት ወቅት ፈርዖን እስራኤላውያን ወንድ ልጅ ሲወልዱ እንዲገደል በአዋጅ አስነገረ፡፡ የሙሴም እናት ልጇ በፈርዖን ትእዛዝ መሠረት እንዳይገደልባት ስለ ፈርዖን ትእዛዝ ፍራቻ ልጇን በቅርጫት አድርጋ ወንዝ ውስጥ ጣለችው፡፡ ተርሙት የምትባለው የፈርዖን ሴት ልጅ በወንዝ ገላዋን ልትታጠብ ወርዳ ሳለ በዚያ ቅርጫት አግኝታ ብትከፍተው የሚያሳሳ ውብ ልጅ አገኘት፡፡ ‹‹ይህንንስ አሳድገዋለሁ›› ብላ ወደ ቤቷ ወሰደችውና ሙሴ በንጉሡ በፈርዖን ቤት አደገ፡፡ የሙሴም እናት ተንከባካቢ ሞግዚቱ ሆና ተጥሎ የተገኘውን ልጇን እንድታሳድግ ከፈርዖን ሴት ልጅ ጋር በድብቅ ተስማምታ በንጉሡ ቤት ገባች፡፡ እናቱም ልጇን ሙሴ የፈርዖን ልጅ እንዳይባል ሃይማኖቱን፣ ማንነቱን፣ ታሪኩን፣ ባሕሉን ጠንቅቃ እያስተማረች አሳደገችው፡፡ ሙሴ 40 ዓመት በሆነው ጊዜ አንዱ ግብፃዊ ዕብራዊውን ሲገድለው አይቶት ለወገኑ ተበቅሎ ግብፃዊውን ገደለው፡፡ በማግስቱ ደግሞ ሁለት ዕብራውያን እርስ በእርሳቸው ሲጣሉ አያቸው፡፡ ሊያስታርቃቸው ፈልጎ ወደ እነርሱ ጠጋ ቢል አንደኛው ዐመፀኛ ዕብራዊ ‹‹ትናንት ግብፃዊውን እንደገደልከው ልትገድለን ትሻለህን?›› አለው፡፡ ሙሴም ‹‹በድብቅ አደረኩት ያልኩት ለካ ታውቆብኛል›› ብሎ ፈርዖንን ፈርቶ ወደ ምድያም አገር ሸሽቶ ሄደ፡፡ የምድያም አገር ካህን የሆነውን የዮቶርን (በሌላ ስሙ ራጉኤል ይባላል) ሴት ልጁን ሲፓራን አግብቶ 40 ዓመት በምድያም ተቀምጦ ሁለት ልጆችንም ወለደ፡፡ ይህችውም ምድያም የተባለች አገር ቅድስት ኢትዮጵያ ናት፡፡ የዚህም ምስክሩ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ዘጸ 2፡1-25፣ ኦሪት ዘኁልቅ 12፡1-12፡፡ ሕዝበ እስራኤል ከግብፅ ሳይወጡ በኋለኛውም ዘመን ጌታችን ከመወለዱም ከብዙ ዘመን በፊት በቅድስት አገር ኢትዮጵያ ውስጥ እግዚአብሔርን የሚያገለግል ካህን እንደነበረ መጽሐፍ ቅዱስ የሚመሰክረው ሐቅ ነው፡፡ ሙሴ በምድያም አገር ማለትም በኢትዮጵያ በዱር ሆኖ የኢትዮጵያዊውን ካሁን የዮቶርን በጎች እየጠበቀ ሳለ በቁጥቋጦ ውስጥ ታላቅ ራእይ አየ፡፡ ነበልባል ከሐመልማል ጋር ሐመልማልም ከነበልባል ጋር ተዋሕዶ ነበልባሉ ሐመልማሉን ሳያቃጥለው፣ ሐመልማሉም ነበልባሉን ሳያጠፋው ተመልክቷል፡፡ ይህንንም ምሥጢር ለመረዳት ጠጋ ሲል ከቁጥቋጦው ውስጥ እግዚአብሔር ድምፅ አውጥቶ ጠራው፡፡ የቆመባት ስፍራ የተቀደሰች ስለሆነች ጫማውንም ከእግሩ እንዲያወልቅ ነገረው፡፡ ዘጸ 3፡5፣ ሐዋ 7፡30-34፡፡ ለጊዜው ሐመልማል የእስራኤል፣ ነበልባሉ ደግሞ የመከራቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐመልማሉ ነበልባሉን ያለመጥፋቱ እስራኤልም መከራውን ግብር ገብተን ቀኖና ይዘን እናርቀው ያለማለታቸው ምሳሌ ሲሆን ነበልባሉ ሐመልማሉን ሳያቃጥል ማየቱ የግብጽ መከራ እስራኤልን ጨርሶ ያለማጥፋቱ ምሳሌ ነው፡፡ ፍጻሜው ግን ሙሴ ያየው የነበልባልና የሐመልማል ተዋሕዶ የመለኮትና የትስብእት ተዋሕዶ ምሳሌ ነው፡፡ ነበልባሉ ሐመልማሉን እንዳላቃጠለው ሁሉ ሐመልማሉም ነበልባሉን እንዳላጠፋው ሁሉ መለኮት ምልአቱን ስፋቱን ርቀቱን ሳይተው ሥጋም ግዙፍነቱን ሳይተው የመዋሐዳቸው አንድ አካል አንድ ባሕርይ የመሆናቸው ምሳሌ ነው፡፡ እንዲሁም ነበልባሉ የጌታችን ምሳሌ ሲሆን ሐመልማሉ ደግሞ የእመቤታችን ምሳሌ ነው፡፡ ይኸውም ነበልባሉ ሐመልማሉን እንዳላቃጠለው ሁሉ እሳተ መለኮት ጌታችንም 9 ወር ከ5 ቀን በማኅፀኗ ባደረ ጊዜ እመቤታችንን ባሕርየ መለኮቱ አላቃጠላትም፤ ሐመልማሉም ነበልባሉን እንዳላጠፋው ሁሉ ጌታችንም ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ቢሆንም ባሕርየ መለኮቱ አልተለወጠም፡፡ ይህንንም ቅዱስ ኤፍሬም በሐሙስ ምስጋናው ላይ እንዲህ ሲል ገልጾታል፡- ‹‹መለወጥ የሌለባት ድንግል ማርያም ሙሴ በበረሐ በነደ እሳት ጫፎቿ ሳይቃጠሉ ያያት ዕፅን ትመስላለች፣ የአብ ቃል በእርሷ ሰው ሆኗልና እሳተ መለኮቱ አላቃጠላትምና፤ ከወለደችው በኋላ ድንግልንናዋ አልተለወጠምና፤ ሰውም ቢሆን መለኮቱ አልተለወጠም በእውነት አምላክ ነውና፣ በእውነት አምላክ የሆነ እርሱ መጥቶ አዳነን፡፡›› የደማስቆው ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስም ‹‹ዕፀ ጳጦስ የአምላክ እናት አምሳል ነበረች፤ ሙሴ ወደ እርሷ በተጠጋ ጊዜ እግዚአብሔር ‹አንተ የቆምክባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውልቅ› አለው፡፡ እንግዲህ ሙሴ የወላዲተ አምላክን ምሳሌ ያየባት መሬት የተቀደሰች ከሆነች ምሳሌዋ ራሷ ምን ያህል የተቀደሰች ትሆን? እርሷ ቅድስት ብቻ ሳትሆን ቅድስተ ቅዱሳን ናት›› በማለት ስለ እመቤታችን አስተምሯል፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝበ እስራኤልን ከግብፅ ባርነት እንዲያወጣቸው ላከው፡፡ ሙሴም ወደ ግብፅ አገር ሄዶ 10 የተለያዩ መቅሰፍቶች አመጣ፡፡ መጀመሪያ ውኃውን ወደ ደምንት ለወጠው፡፡ 10ኛው የበኩር ልጆቻቸው ሞቱ፡፡ በተአምራቱም ሕዝቡን ይዞ ከግብፅ ወጣ፡፡ የኤርትራን ባሕር በበትሩ ለሁለት ከፍሎ አሻገራቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ሕዝበ እስራኤልን በምድረ በዳ 40 ዓመት ሙሉ መና ከሰማይ እያወረደ መገባቸው፣ ከአለትም ላይ ውኃ እያፈለቀ አጠጣቸው፡፡ እራኤል ግን እጅግ ክፉዎች ነበሩና በክፋ ይነሱበት ነበር፡፡ በድንጋይ ሊወግሩት ያሉበት ጊዜም ነበር፡፡ እርሱ ግን ፍጹም በመታገስ በኃጢአታቸው እንዳይሞቱ ወደ እግዚአብሔር ይማልድላቸው ነበር፡፡

ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፡፡በጣም ብዙ ድርሳናትን ደርሰዋል፡፡100 ዓመት በሆናቸው ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ከ10 ቀን በኋላ በሞት እንደሚያርፉ ነገራቸው፡፡ ሕዝቡንም ጠርተው በሃይማኖት እንዲጸኑ ከመከሯቸውና ከተሰናበቷቸው በኋላ መስከረም 7 ቀን በሰላም ዐርፈዋል፡፡ይኸውም ዕረፍታቸው የተከናወነው ኤጲፋንዮስ ባረፈ በ2ኛ ዓመቱ ዮሐንስ አፈወርቅ ባረፈ በዓመቱ ነው፡፡ጌታችን የብርሃን ሰረገላ ሰጥቷቸዋል፡፡ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣በጸሎታቸው ይማረን፡፡ + + + + + + + + + + + + + + + ሰማዕታቱ ቅድስት ራፊቃ እና አራት ልጆቿ፡- ለቅድስት ራፊቃ እና ለአራት ልጆቿ ማለትም ለአጋቶን፣ ለጴጥሮስ፣ ለዮሐንስና ለአሞን ጌታችን ለሁሉም በራእይ ተገልጦላቸው በስሙ መስክረው ሰማዕት እንሚሆኑ ነገራቸው፡፡አስቀድሞም ታላቁ አጋቶን በአገሩ ተሹሞ በሥልጣን ሆኖ ነበር። የጌታችንንም የሰማዕትነት ጥሪ ተቀብለው ከላይኛው ግብጽ ከቁስ አውራጃ ተነሥተው በከሃዲው መኮንን በዲዮናስዮስ ፊት ስለ ጌታችን አምላክነት መሰከሩ፡፡መኮንኑም ብዙ ሥቃዮችን አደረሰባቸው፡፡ጌታችንም በተአምራት ከመከራቸው ሲያድናቸው ያየ ብዙ ሰዎች ሲያምኑ መኮንኑ እጅግ ተቆጥቶ ጽኑ ሥቃይ አደረሰባቸው፡፡ማሠቃየትም በሰለቸው ጊዜ ወደ እስክንድርያው ገዥ አርማንዮስ ዘንድ ላካቸው፡፡ከሃዲው አርማንዮስም ሥጋቸውን ቆራርጦ በመንኮራኩር ውስጥ ጨመራቸው፡፡ነገር ግን ጌታችን ጤነኛ አድርጎ ፈወሳቸው፡፡ዳግመኛም ዘቅዝቀውም ሰቀሏቸው፡፡ አሁንም ጌታችን አዳናቸው፡፡በተአምራተቸውም ብዙዎች በጌታችን አመኑ፡፡በመጨረሻም ራሶቻቸውንም በሰይፍ ቆርጠው ሥጋቸውን ወደ ባሕር ጣሉት፡፡ቅድስት ራፊቃና አራት ልጆቿም ሰማዕትነታቸውን በዚሁ ፈጸሙ፡፡የታዘዘ መልአክም መጥቶ ለአንዱ ባለጸጋ የቅዱሳኑን ሥጋ ያለበትን ነግሮት እንዲያወጣውና በክብር እንዲያስቀምጠው አዘዘው፡፡ባለጸጋውም የቅዱሳኑን ሥጋቸውን ከባሕሩ አወጥቶ የመከራ ዘመን እስኪያልፍ በክብር አኖረው፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ተአምራት ተገልጠው ታዩ፡፡ የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣በጸሎታቸው ይማረን፡፡ + + + + + + + + + + + + + + + + ዳግመኛም በዚኽች ዕለት እመቤታችን ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክን የወለደቻት ቅድስት ሐና ልደቷ ነው፡፡ሐና ማለት ‹‹ጸጋ›› ማለት ነው፡፡አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እናት ናት፡፡እርሷም ከኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሜልኪ ልጅ ለሆነ ለማጣት ልጁ ናት፡፡የቅድስት ሐና አባት ማጣትና እናቷ ሄርሜላ ከእርሷ በተጨማሪ ሶፍያና ማርያም የሚባሉ ሌሎች ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ቅድስት ሐና ከይሁዳ ነገድ የሆነውን ጻድቅ ኢያቄምን አግብታ ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደች፣ ድንግል ማርያምም መድኃኔዓለም ክርስቶስን ወለደች፡፡ሶፍያ ኤልሳቤጥን ወለደች፣ ኤልሳቤጥም መጥምቁ ዮሐንስን ወለደች፡፡ከሦስቱም ታናሽ የሆነችው ‹‹ማርያም›› የተባለችው የማጣትና የሄርሜላ ልጅ ደግሞ ሰሎሜን ወለደቻት፡፡ይኽችም ታላቅ እናት ቅድስት ሐና አምላክን በድንግልና ሆና በሥጋ ለወለደችው ለቅድስት ድንግል ማርያም ወላጇ ትሆን ዘንድ የተገባት ሆናለችና ከሴቶች ሁሉ እንደምትበልጥና እንደምትከብር እንረዳ፡፡ ለዓለም ሁሉ ድኅነት የተደረገባትን ልዩ ስጦታ የሆነች ድንግል ማርያምን እርሷ አስገኘቻት፡፡ለክብር ባለቤት ለጌታችን ለአምላችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ አያቱ ሆናለችና ምን ያህል ክብርት እንደሆነችና እግዚአብሔር የመረጣት ንጽሕት ቅድስት እንደሆነች በዚህ ይታወቃል፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን መስከረም 7-የብርሃን እናቱ የሆነች ድንግል ወላዲተ አምላክን የወለደቻት ቅድስት ሐና ልደቷ ነው፡፡ + በ451 ዓ.ም በጉባዔ ኬልቄዶን ላይ ተገኝቶ ልዮንን የረታውና ያወገዘው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ በዓለ ልደቱና ዕረፍቱ ነው፡፡ + በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው ደብዳቤ በመጻፍ ብቻ በንጉሡ ልጅ ላይ ያደረውን ሰይጣን ያስወጡትና በሀገርም ላይ የመጣውን የጠላትን ጦር በመርታት ድል ያደርጉ የነበሩት አቡነ ሳዊርያኖስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ + ቅድስት ራፊቃ እና 4 ልጆቿ ቁልቁል ተሰቅለውና አንገታቸውን በመሰየፍ ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጸሙ፡፡ + ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ከቅዱስ ፋሲለደስ ጋር ማኅበርተኞቹ የሆኑ ሁለት ሺህ ሰባት ሰዎችም በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ + የመጥምቁ ዮሐንስ እናት የቅድስት ኤልሳቤጥም የመታሰቢያዋ በዓል ነው፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን፡፡ + + + + + + + + + + + + + + + ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ፡- ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት 25ኛው ነው፡፡ስለ ቀናች ሃይማኖት ታላቅ ተጋድሎን ከፈጸመ በኋላ በተሰደደበት በደሴተ ጋግራ መስክረም 7 ቀን ዐርፏል፡፡ንጉሡ መርቅያኖስ በጠራው ጉባዔ በጠሩት ጊዜ በቦታው ሲገኝ 636 ጉባኤተኞች ተሰብስበው ደረሰ፡፡‹‹ምን ጉድለት ተገኝቶ ነው ይህ ሁሉ የተጠራው?›› ሲላቸው ‹‹በንጉሡ ትእዛዝ ተጠርተን ነው›› አሉት፡፡ቅዱስ ዲዮስቆሮስም ‹‹ይህ ጉባኤ ስለ ጌታችን ክብር ቢሆን ኖሮ እኔ ተቀምጨ እግዚአብሔር በሰጠኝ በአንደበቴ እናገር ነበር ነገር ግን የጉኤው መሰብሰብ በንጉሡ ትእዛዝ ከሆነ ንጉሡ እንዳሻው ይምራው›› አላቸው፡፡ከዚህም በኋላ የክርስቶስን ባሕርይ ለሁለት የሚከፍለው የክህደትን ቃል በውስጡ የያዘውን የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ልዮን የላከውን ደብዳቤ ቀደደው፡፡ለጉባኤውም ርትእት የሆነች ሃይማኖትን ገለጸ፡፡የተዋሕዶንም ምሥጢር በነፍስና በሥጋ እንዲሁም በእሳትና ብረት እየመሰለ አስዳ፡፡ጌታችን ሰው እንደመሆኑ ወደ ሠርግ ቤት ተጠርቶ ሄደ፣ አምላክ እንደመሆኑ ውኃውን ለውጦ ወይን አደረገው›› እያለም በብዙ ምሳሌዎች ሲያስረዳቸው ከጉባኤው ሊከራከረው የደፈረ ማንም አልነበረው፡፡ነገር ግን ክፉዎች ጉባኤውን በከሃዲው በልዮን ምክር ወዳዘጋጀው ንጉሡ መርቅያንና ወደ ሚስቱ ንግሥት ብርክያል መልዕክት ልከው ከዲዮስቆሮስ በቀር እነርሱ ያዘዙትን ሃይማኖትንና ትእዛዝ የሚቃወም እንደሌለ በመናገር ነገር ሠሩበት፡፡ነገር ግን በጉባኤው ውስጥ ንስጥሮስን ያወገዙ አባቶችም ነበሩበት፡፡ንጉሡም ቅዱስ ዲዮስቆሮስን አስጠርቶት ከሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት ጋር እስከ ማታ ድረስ ሲከራከሩ ዋሉ፡፡ቅዱስ ዲዮስቆሮስ እንዳልተመለሰላቸው ባዩ ጊዜ ንግሥቲቷና ንጉሡ በእርሱ ተቆጥተው ክፉኛ አስደበደቡት፡፡ጽሕሙን ነጭተው ጥርሱንም አስወለቁት፡፡ ቅዱስ ዲዮስቆሮስም የተነጨ ጽሕሙንና የወለቀ ጥርሱን ሰብስቦ ወደ እስክንድርያ በመላክ ‹‹እነሆ የቀናች ሃይማኖት ፍሬ ይህ ነው›› አላቸው፡፡ለጉበኤው የተሰበሰቡ ኤጲስ ቆጶሳትም በቅዱስ ዲዮስቆሮስ ላይ የደረሰውን ዐይተው ፈሩና ከከሃዲው ንጉሥ መርቅያኖስ ጋር ተስማሙ፡፡ክብር ይግባውና ‹‹ለክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርያት አሉት›› ብለው በንጉሡ መዝገብ ላይ በእጆቻቸው ጽፈው ፈረሙ፡፡ቅዱስ ዲዮስቆሮስም እነርሱ የጻፉለትን መዝገብ እንዲልኩለት ሲጠይቃቸው ላኩለት እርሱም ጽፎ የሚፈርምበት መስሎአቸው ነበርና፡፡እርሱ ግን አባቶቻችን ሐዋርያት ካስተማሯት ከቀናች ሃይማኖት በኒቅያ የተሰበሰቡ ሃይማኖታቸው የቀና የ318 ኤጲስ ቆጶሳት አባቶቻችን ከሠሯት ሕግ የሚወጣውን ሁሉ በደብዳቤው ግርጌ ጽፎ አወገዘ፡፡መና*ፍቁ ንጉሥም ይህን ጊዜ እጅግ ተናዶ ጋግራ ወደምትባል ደሴት እንዲያግዙት አዘዘ፡፡የሀገረ ቃው ኤጲስ ቆጶስ አባ መቃርስ አብሮት ተሰደደ፡፡ሌሎቹ ግን ሸሹ። ከዚህም በኋላ እነዚያ የካዱ 636 ኤጲስ ቆጶሳት ተቀምጠው በኬልቄዶን ለራሳቸው መመሪያ የሚሆናቸውን ሥርዓት ሠሩ፡፡በጋግራ ደሴት ያለው ኤጲስ ቆጶስም ከንጉሡ ጋር የተባበረ ነበርና አቡነ ዲዮስቆሮስ ላይ ብዙ መከራ አደረሰበት፡፡የደሴቱ ሰዎች ግን በቅዱስ ዲዮስቆሮስ እጅ የሚፈጸሙ ተአምራትን እያዩ እጅግ ያከብሩት ነበር፡፡ከዚህም በኋላ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ አባ መቃርስን ወደ እስክንድርያ ሄዶ ሰማዕት እንደሚሆን ትንቢት ነገረውና ከነጋዴዎች ጋር ላከው፡፡እንደተናገረውም አባ መቃርስ በእስክንደርያ ሰማዕት ሆኖ ዐረፈ፡፡አቡነ ዲዮስቆሮስ ግን በዚያቹ በጋግራ ደሴት ሰማዕትነቱን ፈጽሞ በክብር ዐርፏል፡፡ምእመናንም ሥጋውን በዚያው አኖሩት፡፡የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ + + + + + + + + + + + + + + + አቡነ ሳዊርያኖስ፡- የግሪክ አቴናን ፍልስፍናና ጥበብ ጠንቅቀው የተማሩ ናቸው፡፡ምግባር ሃይማኖታቸው የሰመረ፣ ትሩፋት ተጋድሏቸው የቀና ነው፡፡ብሉይን ከሐዲስም አጠናቀው ተምረዋል፡፡ወላጆቻቸው ያወረሷቸውን እጅግ የተትረፈረፈ ንብረት ሸጠውና ለጦም አዳሪዎች መጽውተው ለድኆች ማደሪያና ለእንግዶች ማሪፊያ ቤት ሠርተው ነዳያንን ይንከባከቡ ጀመር፡፡ይህንንም የጽድቅ ሥራቸውን የሮሜው ጻድቁ ንጉሥ አኖሬዎስ ሲሰማ እጅግ ደስ ተደስቶ አስመጥቶ ከእርሱ ጋር በቤተ መንግሥቱ አማካሪና አባቱ አድርጎ አኖራቸው፡፡ከንጉሡም ጋር አብረው ሁልጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ሌሊቱን በሙሉ ለጸሎት ቆመው ያድራሉ፡ጻድቁ የገብላው አገር ንጉሥ ሴት ልጁን ሰይጣን ይዟት ሳለ ደብዳቤ በመጻፍ ልከው በልጅቷ ላይ ያደረውን ሰይጣን በደብዳቤአቸው ብቻ አስወጥተውታል፡፡አቡነ ሳዊርያኖስ ደብዳቤ በመጻፍ ብቻ በሀገር ላይ የመጣ የጠላትንም ጦር እያሸበሩ ድል ያደርጉ ነበር፡፡ይኸውም የቍስጥንጥንያው ንጉሥ አርቃዴዎስና አኖርዮስ በገብላ አገር ኤጲስቆጶስነት ከሾሟቸው በኋላ የፋርስ ሰዎች እነዚህን ደጋግ ነገሥታት ሊወጓቸው ሽተው በኃይል በመጡባቸው ጊዜ ወደ አባ ሳዊርያኖስ መልአክትን ላኩ፡፡አባታችንም ለቅዱሳን ነገሥታቱ ‹‹እኛ የክርስቶስ ከሆንን መንግሥታችንም የክርስቶስ ነው፣ እንዲህም ከሆነ የጦር መሣርያ የጦር ሠራዊትም አንሻም…››ብለው ደብዳቤ ጽፈው እንደላኩ ነገሥታቱ ያለ ምንም ጦርነት የፋርስን ሀገር ሰዎች አሸንፈው ወደ ሀገራቸው መልሰዋቸዋል፡፡አቡነ ሳዊርያኖስ በገብላ አገር ኤጲስቆጶስነት ከተሾሙ በኋላ የሙሴን ሕግ በማወቁ የሚመካ አንድ ስሙ ስቅጣር የሚባል አይሁዳዊ ወደ እርሳቸው መጥቶ ተከራከራቸው፡፡የጻድቁንም ቃላቸውን ሊሰማቸው አልቻለም ነበር፡፡በዚህም ጊዜ ጌታችን ለአቡነ ሳዊርያኖስ ተለጠላቸውና ‹‹እኔ ካከበርኳቸው ወገኖች ይሆናል›› በማለት እንደሚያምን ነገራቸው፡፡ያም አይሁዳዊ ወደቤቱ በገባ ጊዜ ወገኖቹ አይሁድ ሲኦል ውስጥ ሆነው ሲሠቃዩ በራእይ ተመለከተ፡፡‹‹ከሃዲዎች ዘመዶችህን እነሆ እይ›› የሚል ድምንም ሰማ፡፡በማግሥቱም ይህ አይሁዳዊ ወደ አቡነ ሳዊርያኖስ መጥቶ ከእግራቸው ሥር ወድቆ እንዲያስተምሩትና የክርስቶስ ወገን እንዲያደርጉት ለመናቸው፡፡እርሳቸውም አስተምረው ከሀገሩ ሰዎች ጋር አንድ ላይ አጠመቋቸው፡፡የቀሩት ብዙ አይሁድም በጌታችን አምነው ተጠመቁ፡፡አቡነ ሳዊርያኖስ ሥራየኛ ጠንቋዮችን ሁሉ እያሳመኑ አስተምረው አስጠምቀዋቸዋል፡፡አቡነ ሳዊርያኖስ ስለ ዮሐንስ አፈወርቅ ስደትና እንግልት ያለችበት ድረስ ሄደው ንግሥት አውዶክስያን ቢመክሯትና ቢገሥጹዋትም በክፋቷ ጸንታ አልሰማቸው ብትል ተመልሰው ወደ አገራቸው ሄደዋል፡፡አቡነ ሳዊርያኖስ ተአምራታቸው

ሰማዕትነቱን በዚሁ ፈጽሟል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡ + + + + + የአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ የሥጋ ፍልሰት፦ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ ትውልዳቸው ከካህናቱ ወገን አክሱም ነው አባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው አመተ ማርያም ይባላሉ። ለመምህር ሰጥተዋቸው ሲማሩ አድገው በኋላም ወላጆቻቸው በሞት ሲለዩአቸው ደብረ በንኰል ገዳም ገብተው ሥርዓተ ምንኩስናን ከአበው እያጠኑ ለትልቁም ለትንሹም በትሕትና እየታዘዙ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየሰበሩ በትኅርምት በጽሞና በጸሎት ይኖሩ ነበር። ሰይጣን በውዳሴ ከንቱ ጾር ቢመጣባቸው ከማሕበረ መነኰሳቱ ተለይተው በተባሕትዎ ለመኖር ሽተው ወጥተው ሲሔዱ ተከዜ ደረሱ።ወንዙ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትምህርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉ ሳይበላሽ ተሻግረዋል። ዋልድባ ሲደርሱ ጌታ እዚህ ተቀመጥ ስላላቸው ገዳም መሥርተው ሥርዓተ ምንኩስናን እያስተማሩ ተቀመጡ። ዛሬ በዋልድባ የሚያመሰግኑበት ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያምን ከተከዜ ወዲህ ያመጡ እሳቸው ናቸው። ይህንን እየጸለዩ ሲሔዱ ክንድ ከስንዝር መሬት ለቀው ይታዩ ነበር። አንድ ቀንም ይህንን ጸሎት ደግመው ውኃውን ቢባርኩት ኅብስተ ሕይወት ሆነላቸው ከነ ደቀ መዛሙርቶቻቸው ተመግበውታል።እመቤታችንም የፍቅር መግለጫ ዕጣን፣ ወርቅ፣ እንቁ ሰጥታቸዋለች። "ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ አንድ አድርጎ የደገመውን አንተ ከገባህበት መካነ ሕይወት አስገባዋለሁ" ብላ ቃልኪዳን ሰጥታቸዋለች።ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታን በስብሐተ መላእክት ተገልጦ "በስምህ የተማጸነውን በጎ የሰራውን፣ዜና ገድልህን የጻፈውን፣ያስጻፈውን፣ ያነበበ፣ የተማረ፣ ያስተማረ፣ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ምሬልሃለሁ።በዚህ ቦታ በዋልድባ የሚሰበሰቡ ልጆችህን ከእዳ ከፍዳ እሰውርልሃለሁ" አላቸው። እንኪያስ ቦታዋን ባርክልኝ ብለው እንደ መሶብ አንስተው አስባርከዋታል ጌታችንም "እህል አይብቀልብሽ ኃጢአት አይሻገርብሽ" ብሎ ቃል ኪዳን ገባላት ለገዳመ ዋሊ። አባታችን አቡነ ሳሙኤል በበዓታቸው ውስጥ ጸንተው ሲኖሩ ታህሣሥ 12 ቀን ያረፉ ሲሆን ዛሬ መስከረም 6 ግን ፍልሰተ አጽማቸው የተከናወነበት ዕለት ነው።ከአባታቸው ከአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት): አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን መስከረም 6-ታላቁ ነቢይ የአሞጽ ልጅ ቅዱስ ኢሳይያስ ዕረፍቱ ነው፡፡ + የዋልድባው የአቡነ ሳሙኤል ዐፅማቸው  የፈለሰበት ዕለት ነው፡፡ + ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሰማዕቷ ቅድስት ሰብልትንያ ሰማዕትነቷን በድል ፈጸመች፡፡ ሰማዕቷ ቅድስት ሰብልትንያ፡- ይህችውም ቅድስት ሰብልትንያ በ9 ዓመቷ የከሃዲው ንጉሥ የዲዮቅልጥያኖስ ጭፍሮች ይዘው እጅና እግሯን አሥረው ከሚነድ እሳት ውስጥ ጨመሯት ነገር ግን ጌታችን ፍጹም ጤነኛ አድርጎ አዳናት፡፡ ዳግመኛም ይዘው እያሠዋዩአት ሳለ በሥቃይ ውስጥ ሆና ውኃ ጥም እጅግ በጠናባት ጊዜ ጌታችንን በጸሎት ጠይቃ ውኃ አፍልቃ ከጠጣች በኋላ ጌታችንን አመስግናና ነፍሷን አደራ ሰጥታ ራሷን ከእሳቱ ውስጥ ወርውራ ምስክርነቷን በክብርና በድል ፈጽማለች፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን፡፡ + + + + + ነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ፡- ኢሳይያስ ማለት ‹‹እግዚአብሔር ደኅንነት ነው›› ማለት ነው፡፡አባቱ አሞጽ ይባላል ሆኖም ‹‹ነቢዩ አሞጽ›› ሳይሆን ሌላኛው አሞጽ ነው፡፡2ኛ ነገ 19፡1፣ ኢሳ 1፡1፡፡ይህ ታላቅ ነቢይ ለይሁዳ በነገሠ በ5ቱ ነገሥታት ዘመን አስተምሯል፤ ትንቢት ተናግሯል፡፡እነዚህም ዖዝያን፣ ኢዮአታም፣ አካዝ፣ ሕዝቅያስና ምናሴ ናቸው፡፡በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመነ መንግሥት የቤተ መንግሥት አማካሪ ነበር፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በመጀመሪያ ነቢይ እንዲሆን የተጠራው ዖዝያን በሞተበት ዓመት ነው፡፡አስቀድሞ የነበረው ንጉሡ አዛርያስ ሀብተ ክህነት ሳይኖረው ሊያጥን ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ እያየ ነቢዩ ኢሳይያስ ወዳጁ ስለሆነ ሳይገሥጸው ቀረ።ነገር ግን እግዚአብሔርም ስለድፍረቱ ዖዝያንን በለምጽ አነደደው፡፡እግዚአብሔርም በዖዝያን ፈንታ ኢዮአታምን አነገሠወው፡፡ኢሳይያስም ባለሠገሠጹ ከንፈሩ ላይ ለምጽ ወጣበት፡፡ኑሮውም ከሰው ተለይቶ በጨለማ ቤት ሆነ፡፡ሀብተ ትንቢቱንም ተቀማ፡፡ነገር ግን ነቢዩ ከልቡ ተጸጽቶ በጾም በጸሎት ተወስኖ ንስሓ ስለገባ እግዚአብሔር ንስሃውን ተቀበለው፡፡ንስሓውንም እንደተቀበለው ያውቀው ዘንድ እግዚአብሔር በረዥም ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ ኪሩቤል ዙፋኑን ተሸክመውት፣ 24ቱ ካህናተ ሰማይ "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ" እያሉ ሲያመሰግኑት ተገለጠለት፡፡ኢሳ 6፡1፡፡መልአኩንም ልኮ ከለምፁ ፈወሰው፡፡ሀብተ ትንቢቱም መለሰለት፡፡ንስሓን የሚቀበል የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁን፡፡በንጉሡ በአካዝ ዘመነ መንግሥት የሶርያና የሰማርያ ሠራዊት ወደ ይሁዳ በዘመቱ ጊዜ ነቢዩ ኢሳይያስ አካዝን በእግዚአብሔር እንዲታመን እንዳይደነግጥ መከረው፡፡አካዝ ግን ጠላቶቹን እንዲቋቋምለት ለማድረግ ለአሦር ንጉሥ ግብር ይልክለት ነበር፡፡ኢሳ 7፡1-17፣ 8፡1-114፣ 2ኛ ዜና መ 28፡16-21፡፡የአሦርም መንግሥት እየተስፋፋ ሲሄድ የይሁዳ አለቆች ለእርዳታ ወደ ግብፅ ተመለከቱ፡፡ነቢዩ ኢሳይያስም ይህንን ሲያይ እግዚአብሔርን ከመማጸን ይልቅ ወደ ውጭ መመልከታቸው በእግዚአብሔር አለማመን መሆኑን ገልጾ ተናገረ፡፡የአሦር ንጉሥም የይሁዳን ከተሞች በእጁ አድርጎ በኢየሩሳሌም ላይ ዛቻ ሲናገር ኢሳይያስ ስለ አሦራውያንና ስለ ንጉሣቸው ሰናክሬም መሸነፍ ተነበየ፡፡በትንቢቱም መሠረት የአሦር ሠራዊት በአንዲት ሌሊት ቸነፈር ተመቷል፡፡2ኛ ነገ 18፣ 19፡፡2ኛ ዜና 32፡16-21፣ ኢሳ 36፡፡ይኸውም የፋርሱ ንጉሥ ሰናክሬም ኢየሩሳሌምን ከቦ ሳለ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ቃል ተናገረ፡፡ጻድቁ ንጉሥ ሕዝቅያስም ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ ዘንድ ለነቢዩ ኢሳይያስ መልእክት ላከበት፡፡ኢሳይያስም በጸሎት እግዚአብሔርን ከጠየቀ በኋላ በጸሎቱ ያገኘውን መልስ ለንጉሥ ሕዝቅያስ ‹‹አትፍራ በሰይፍ እንዲወድቅ አደርገዋለሁ ብሎሃል›› አለው፡፡በዚያችም ሌሊት እግዚአብሔር የላከው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ወደ ሰናክሬም ሰፈር መጥቶ ከፋስ ሠራዊት 185,000 (መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ) ሠራዊቶቹን በአንዲት ሌሊት ገደላቸው፡፡ከዚህም በኋላ ሕዝቅያስ ታሞ ለሞት በደረሰ ጊዜ ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ እርሱ መጥቶ ‹‹እግዚአብሔር ‹ትሞታለህ እንጂ አትድንም› ብሏልና ቤትህን አዘጋጅ››› አለው፡፡ሕዝቅያስም ማቅ ለብሶ አመድ ነስንሶ በእጅጉ ሲያለቅስ እግዚአብሔር ዳግመኛ ነቢዩን ወደ ንጉሡ ላከው፡፡ ‹‹የአባትህ የዳዊት ፈጣሪ እግዚአብሔር ጸሎትህን ሰማሁ፣ ዕንባህንም አየሁ፣ እነሆ በዘመንህ ላይ 15 ዓመት ጨመርኩልህ›› ብለህ ነገረው አለው፡፡ነቢዩ ኢሳይያስም ሄዶ ለንጉሥ ሕዝቅያስ ነገረው፡፡ነቢዩ ኢሳይያስ ዳግመኛም በአካዝ ዘመን እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ፡- ‹‹እናንተ የዳዊት ቤት ሆይ! ስሙ፣ በውኑ ሰውን ማድከማችሁ ቀላል ነውን? አምላኬን ደግሞ የምታደክሙ፤ ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ! ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፡፡›› ኢሳ 7፡13-14፡፡ነቢዩ ዳግመኛም ክብር ይባውና ስለጌታችንም መከራ ትንቢትን ሲናገር እንዲህ አለ፡- ‹‹የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፡፡ መልክና ውበት የለውም፣ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም፡፡የተናቀ ከሰውም የተጠላ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፣ እኛም አላከበርነውም፡፡በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው፡፡እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፣ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፣ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን፡፡እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ፡፡ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፣ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፣ እንዲሁ አፉን አልከፈተም፡፡በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገንበትም ነበር፡፡እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፣ ዕድሜውም ይረዝማል፣ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል፡፡ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል. ኃጢአታቸውን ይሰከማል፡፡ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፣ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፣ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና፣ እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፣ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ፡፡››ትንቢተ ኢሳይያስ 53፡1-12፡፡ነቢዩ ይህንን የመድኃኔዓለምን መከራ ሞቱን በትንቢት የተናገረውና ያስተማረው ከጌታችን ልደት ከ913 ዓመት በፊት ነው፡፡ነቢዩ ኢሳይያስ ዳግመኛም ስለ እስራኤል መማረክና ከምርኮም ስለ መመለሳቸው ትንቢትን ተናገሯል፡፡እንዲሁም በሕዝቅያስ ልጅ በንጉሥ ምናሴ ላይ ትንቢትን ተናገረ፡፡ጣዖትን ስለማቆሙና ስለማምለኩ ገሠጸው፡፡ስለዚህም ንጉሥ ምናሴ ተቆጥቶ ነቢዩ ኢሳይያስን በእንጨትመሰንጠቂያ መጋዝ ከእግሮቹ መሀል ጀምሮ እስከ ጭንቅላቱ ድረስ ለሁለት ሰንጥቆ ገድሎታል፡፡ነቢዩም

አቡነ አሮንን ከንጉሡ ጋር ለማጣላት አንድ መሠሪ ሰው ወደ ንጉሥ ሰይፈ አርዕድ ሔዶ ‹‹ንጉሥ ሆይ! ስለ አንተ የማይጸልይ፣ ለመንግሥትህ ክብር የማይሰጥ፣ ነገሥታትን የሚሰድብ፣ አንተንም ከአባትህ ጋር የሚቃወም እንደዚሁም በአንተ ላይ ዘለፋና መርገምን የሚናገር አንድ መነኩሴ አለ…›› ብሎ ነገር ሠራ፡፡ ንጉሡም ይህን ሲሰማ እጅግ ተበሳጨና ‹‹ምን ላድርግ?›› አለው፡፡ ያም ነገረ ሠሪ ሰው ‹‹…ከመነኮሳት ልጆቹ ጋር ከደብሩ አስወጥተህ ሥጋቸውን ወደሚያቀልጥ የፀሐይ ሐሩር ወዳለበት የውኃ ጥም ወደበዛበት በረሃ በግዞት ወስደህ በትናቸው፣ በዚያ እንደ አንበጣ ይረግፋሉ፣ አይተርፉም›› አለው፡፡ ንጉሡም ጭፍሮቹን ልኮ አቡነ አሮንን ከ700 ልጆቻቸው ጋር ከመቄት አስመጣቸው፡፡ አቡነ አሮንንም ‹‹…ስለእኛ ለምን አትጸልይም? ለምንስ ትረግመናለህ? ለምን ትዘልፈናለህ?›› አላው፡፡ አቡነ አሮንም ‹‹እንደሥራህ፣ እንደ አካሔድህ እንጸልይልሃለን›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹ልጄንና ወንድሜንስ ለምን በድፍረት አመነኮስካቸው?›› አለው፡፡ አባታችንም ‹‹አንተም ወደ እኔ ብትመጣ ባመነኮስኩህ ነበር›› ሲለው ንጉሡ በአደባባይ ሊናገሩት የማይገባ ታላቅ ስድብን ከሰደበው በኋላ ‹‹ልጄንና ወንድሜን አምጣ…›› እያለ በንዴት በዱላ አስደበደባቸው፤ የአባታችንንና የልጆቻቸውን ቆብ በማውለቅና ልብሳቸውን በመግፈፍ ራቁታቸውን በአደባባይ በሕዝብ ፊት አቆሟቸው፣ ብዙ ግርፋትንም ገረፏቸው፡፡ ንጉሡም አቡነ አሮንን ‹‹ኀፍረትህና ጉስቁልናህ በሁሉ ፊት እንደተገለጠ ተመልከት›› ሲለው አባታችንም ‹‹ከአንተ የሌለ በእኔ ፍጥረት ውስጥ ምን አለ? እኔም እንደ አንተ፣ አንተም እንደእኔ አይደለህምን? የአንተም አካል የእኔ አካል አይደለምን?› አለው፡፡ ንጉሡም ወዲያው ለተራቡ አንበሶች ሰጣቸው ነገር ግን አንበሶቹ ከአባታችን እግር ሥር እየተንከባለሉ እግሩን ይልሱ ጀመር፡፡ የንጉሡ ሠራዊትም ይህን አይተው ፈሩ፣ ደነገጡ፡፡ ንጉሳቸውንም ‹‹አናብስትን ከሚያሰግድ፣ በመንገድም ላይ በበረሃ ውስጥ ስናመጣው ውኃን ከጭንጫ ላይ ካፈለቀ ከእንዲህ ዓይነት ጻድቅ ሰው ጋር አትጣላ›› እያሉ መከሩት፡፡ አቡነ አሮን መጻሕፍትን ተምረው ጨርሰው በዲቁና እያገለገሉ ሳለ ፍሕም ከቤተልሔም ጭረው ወደ ቤተ መቅደስ ሲወስዱ በጣታቸው ላይ ፍሕሟ ተጣብቃ አቃጠለቻቸው፡፡ አቡነ አሮንም በዚህ ጊዜ ‹‹የምድሩ እሳት እንዲህ ከሆነ የሰማዩ እሳትማ ከዚህ የበለጠ ምንኛ ይከፋ!...›› በማለት ከነገሥታት ወላጆቻው ተለይተው ዓለምን ንቀው ወደ ሳይንት አገር በመሔድ በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል እጅ መነኮሱ፡፡ አቡነ አሮን በዓለም ላይ ነግሠው መኖር የሚችሉ የንጉሥ ገብረ መስቀል ልጅ መሆናቸውን ልብ ይሏል፡፡ የአቡነ አሮን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን።

አባቶች ‹‹በቶሎ ወደዚህ ና ፣በዚህ አንተ የብዙዎች አባት ትሆናለህ›› ብለው ወደ አቡነ መልክአ ክርስቶስ መልእክት ላኩበት፡፡ አባታችንም ከዳውንት ወደ ግሸቅ መሔጃ መንገዱ ላይ መንኳክ ማርያም ደርሶ አደረ፤ ጸሎት አድርሶ ቦታዋን ቢባርካት ጠበል ፈለቀ፤የገዳም ሥርዓትንም ሠራላት፡፡ ዛሬም ድረስ አባታችን ያፈለቀው ጠበል ብዙ ተኣምራት እያደረገ ምስክር ሆኖ በቦታው ላይ አለ፡፡አቡነ መልክአ ክርስቶስ የእመቤታችንን ታቦት ይዞ በሽሎ የሚባል ወንዝ ሲደርስ እንደ ሱራፌል ቀንና ሌሊት ሳያስታጉሉ የሚያመሰግኑ ሥዉራን ቅዱሳን በደብሩ እንዳሉ አስተዋለ፡፡ እመቤታችን እየመራችው በደብሩ አናት አድርሳው ‹‹ይህ ቦታህ ይሁን፣ ስሙም ግሸቅ ይባል፣ ታቦቴንም በቀኝህ አኑር›› አለችው፡፡ዳግመኛም ‹‹ልጄ ገዳመ አስቄጥስን፣ገዳመ ሲሐትን እንደባረከ ይህን ገዳምህንም ይባርክልህ፤ ማህበረ መቃርስ ወማኅበረ ጳኩሚስ፣ ማኅበረ ሖር ወአባ አብሎ፣ ደብረ ኮኖብዮስ እና ሌሎችንም እንድባረከ ይባርክልህ፤ ከአንተ የሚወለዱ አንዱስ እንኳን አይጠፋም፤ በገዳምህ የተቀበረ አይጠፋም›› አለችው፡፡አባታችንም ገዳሙን ግሸቅ ካደረገ በኋላ ገዳማዊ አንድነቱ እየጠነከረ በመምጣቱ በደብሩ ዙሪያ የነበሩ ክፉዎች ‹‹ቦታችንን ሊቀሙን ነው›› ብለው በማሰብ ክፋትን ማድረግ ጀመሩ፡፡ በድንግልና ራሳቸውን ጠብቀው ከዓለም የተለዩ ደናግል መነኰሳት ሴቶቹን በማየት እንዲፈተኑ ተንኮል አስበው መነኰሳት አባቶች ውኃ ከሚቀዱበት ማይ ዘአጋም ከተባለ ምንጭ ሴቶች ልጆቻቸውን መላክ ጀመሩ፡፡መነኰሳቱም በዚህ አዝነው ውኃ ሳይቀዱ በመመለስ ለአቡነ መልክአ ክርስቶስ የሆነውን ሲነሩት ‹‹ልጆቼ ይህን ቦታ እመቤታችን ነች የሰጠችኝ፣ ‹አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የፈቀዱልህ ቦታህ ነው፣ ለአንተና ለልጆችህ ለዘለዓለም ማደርያ ርስትህ ይሁን፣ወገን የሌላቸው ታማሚዎች ስምህን በመዘከር ከመከራ ይዳኑ› ብላ ተናግራ ሰጥታኛለች፤ እግዚአብሔር ለኛ ካለው ያድርገው ለእነርሱ ካለው ይሁን ብሎ ሱባኤ ይዞ እናትና ልጅን ለመነ፡፡ የአካባቢው ሰዎችም እግዚአብሔርን አሳዝነዋልና ከእነርሱ ውስጥ ብዙዎች በሕማም በደዌ ተመቱ፤ ብዙ ሰው መሞት ሲጀምር ቀሪዎቹ ከገዳሙ ክልል ሸሽተው ወጡ፡፡በዚህም ጊዜ የአቡነ መልክአ ክርስቶስ ዝና በመላው ኢትዮጵያ ደረሰ፡፡ዳግመኛም አባታችን ‹‹…የኤርትራን ባሕር ከፍለህ ሕዝብህን ያሻገርኽ፣እንዳይርባቸው በበረሓ መና ያወረድኽ፣ እንዳይጠሙ ከዓለት ውኃ ያፈለቅኽ አምላክ ሆይ! ዛሬም አንተ ነኽና ውኃ አፍልቅልኝ›› ብሎ ቢማጸን በግሸቅ ተራራ ላይ ውኃ ፈለቀለት፡፡ በገዳሙ የነበሩ ሁሉ ከእርሷ ተጠምቀው ጠጥተው ተፈወሱ፡፡ የጎንደሩ ንጉስ አድያም ሰገድ ኢያሱ ሙያተኞችን ልኮ በግንብ አሰራት፡፡የአጼ ኢያሱ ልጅ ልዑል ሰገድ ተክለ ሃይማኖትም ውኃ የሚቀዱበት በቅሎ ሰጥቷቸዋል፡፡ማኅደረ ክርስቶስ የሚባል ክፉ ጠላት በብዙ ፈተና የሚያሠቃየው የአቡነ መልክአ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር በደብሩ ነበር፡፡ አቡነ መልክአ ክርስቶስም በጸሎቱ ክፉ ጠላትን ድል አደረገለት፡፡ ‹‹ልጄ አይዞህ አትፍራ ጽና›› ይለው ያበረታው ነበር፡፡ ከዚኽም በኋላ በጎንደር ዙሪያ ብዙ መነኰሳት ሰማዕት በሚሆኑበት ዘመን ማኅደረ ክርስቶስ ለአባታችን በራእይ ያየውን ነገረው፤ ‹‹አንተ ሰማዕት ለመሆን ሒድ፣ አቡነ መልክአ ክርስቶስ ግን አይሔድም፣ብዙ ሥራ ከፊቱ አለ፣ ብዙዎችን ወደ መንግስተ ሰማያት ይጠራልና›› ተብያለው በማለት የተነገረውን መልእክት አስረዳው፡፡ አባታችንም ‹‹የነብያትን መንገድ ያቀና ሰማዕታትን በፈተና ሁሉ ያጸና አምላክ መንገድህን ያቅናልህ ያስፈጸምህ›› ብሎ ልጁን መረቀውና ሰማዕትነት ወደ ሚቀበልበት ቦታ ሰደደው፡፡ ማኅደረ ክርስቶስም ወደ ንጉሥ ወታደሮች ዘንድ ቀርቦ ስለ ሃይማኖቱ መስክሮ አንገቱን በሰይፍ ተቆርጦ የክብር አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ አንገቱንም በሰይፍ ከቆረጡት በኋላ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ራስ የሰማዕቱ ማኅደረ ክርስቶስ ራስ መዝሙረ ዳዊት መኃልየ ሰሎሞን ውዳሴ ማርያም ዘመረች፡፡የአቡነ መልክአ ክርስቶስ የዕረፍቱ ቀን በደረሰ ጊዜ በጽኑ ደዌ ታመመ፡፡ ከመረጣቸው ጋር ቃልኪዳን ያደረገ መድኀኔዓለም ለአቡነ መልክአ ክርስቶስም እንዲሁ አደረገ፡፡ ‹‹…ድካምህን ተቀብያለሁ፣ በእጅህ የመነኰሱ፣ በመስቀልህ የተባረኩ፣ ከሩቅ አንተን ብለው ደጅህ የመጡ፣በስምህ መታሰቢያህን የሚያደርጉትን ሁሉ የልባቸውን በጎ መሻት እፈጽምላቸዋለሁ፤በደላቸውን ሳልመለከት ጸጋ በረከትን እሰጣቸዋለሁ፤የወዳጆችህን ትውልድ እስከ 15 ትውልድ እምርልሃለሁ›› ብሎ ቃልኪዳን ከገባላቸው በኋላ መስከረም 5 ቀን በዕለተ ቀዳሚት በ86 ዓመታቸው ነፍሳቸው ከሥጋው ተለየች፡፡ከመቃብራቸውም ላይ ሕሙማን የሚፈወሱበት ድንቅ ድንቅ ተኣምራትን የሚያድርግ ጠበል ፈለቀ፡፡አቡነ መልክአ ክርስቶስ ለአገልግሎት ሲጓዙ በመንገድ ላይ ከሞተ 900 ዓመት የሞላውን ሰው ዐፅም አግኝነተው ወደ እግዚአብሔር ጸልየው በመስቀላቸው ባርከው ከሞት አስነሥተውታል፣ ከሞት የተነሣውም ሰው ኢአማኒ ስለነበር ጻድቁ አጥምቀው ለክርስቶስ መንግሥት አብቅተውታል፡፡ጻድቁ አቡነ መልክአ ክርስቶስ ያደረጉት ታላቅ ተአምር ይኽ ነው፡- ለጻድቁ እንደ ሰው እየተላላከ ከበሸሎ ወንዝ ውኃ እየቀዳ ወደ ገዳማቸው የሚያመጣላቸው አንድ አህያ ነበራቸው፡፡ አህያውም ሰው ሳይጭነው ባዶ እንስራ ወደ ወንዙ ወስዶ በተአምር ውኃው በእንስራ ሲሞላለት ሳያጋድል ይዞ ሩቅ መንገድ ተጉዞ ከአባታችን ገዳም ይደርሳል፡፡ ነገር ግን በአንደኛም ቀን ይህንን አገልጋይ አህያቸውን ጅብ በላባቸው፡፡ አቡነ መልክአ ክርስቶስም በአህያቸው ፈንታ ጅቡን 7 ዓመት ውኃ አስቀድተውታል፡፡ቅዱሳኑ አቡነ መልክአ ክርስቶስ እና አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ በአንድ ዘመን አብረው የኖሩ ሲሆን ኹለቱ ቅዱሳን የቅርብ ወዳጆችም ነበሩ፡፡ገድላቸው እንደሚናገረው አቡነ መልክአ ክርስቶስ ከግራኝ አህመድ የ15 ዓመት ጥፋት በኋላ የቅዱስ ያሬድን የቅዳሴ ዜማ ትምህርት ጠብቆ ለትውልድ በማበርከት እጅግ የጎላ ድርሻ አላቸው፡፡አቡነ መልክአ ክርስቶስ ዐቢይ ጾም ሲገባ ብዙ ጊዜ ብቻውን ሱባኤ ይይዛል፡፡በዐቢይ ጾም ወቅት ከዕለታት በአንደኛው ቀን በግሸቅ ማርያም ሳለ ክፉ ጠላት በከባድ ረኀብ ፈተነው፡፡ አባታችንም በዚህ አዝኖ ሲጨነቅ ክብርት እመቤታችን ተገጻለት ‹‹ሰላም ለአንተ ይሁን ወዳጄ መልክአ ክርስቶስ›› አለችው፤ ዳግመኛም ‹‹ስለምን ትተክዛለህ? አይዞህ ጽና…›› ብላ በልጇ ቸርነት ሰማያዊ ኅብስት መገበችው፡፡ አባታችንም ይህን ምሥጢር ለልጁ ለአባ ሚካኤል ከነገረው በኋላ ‹‹እስከምሞት ድረስ ይህን ለማንም አትንገር፣ በኋላ ግን እንደፈቃድህ›› አለው፡፡ቅዱሳን ከውዳሴ ከንቱ ለመሸሽ ሲሉ በሕይወት እያሉ በጎ ሥራቸውን መደበቅ ልማዳቸው ነው፡፡የአቡነ መልክአ ክርስቶስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

እየሰበሰበች በሥውር ደብቃ ያኖረችውን አንዲት ሴትም አብረው ከሰማዕታቱ ጋር ቀበሯት፡፡ የቅድስት ሶፍያና የልጆቿም የዕረፍታቸው ቀን መስከረም 5 ነው፡፡ የሰማዕታቱ የቅድስት ሶፍያንና የልጆቿ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን! + + + + + አቡነ አሮን ዘመቄት፡- የመቄቱ አቡነ አሮን ወላጅ አባታቸው የላስታው ጻድቁ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ናቸው፡፡ እናታቸው አመተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የላስታ ነገሥታት የዘር ሐረጋቸው ከንጉሥ ሰሎሞን ዘር ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡ ከ10ኛው እስከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253 ዓ.ም ገደማ) በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪያ ‹‹የዛጉዌ ሥርወ መንግሥት›› ወይም ‹‹የላስታ መንግሥት›› በመባል ይታወቃል፡፡ የንጉሥ ሰሎሞን ዘር የሆነው መራ ክርስቶስ 3 ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም ጠንጠውድም፣ ግርማ ስዩምና ዣን ስዩም ናቸው፡፡ጠንጠውድም ገብረ መስቀልን ወለደ፣ ገብረ መስቀልም አቡነ አሮንን ወለደ፣ግርማ ስዩም ይምርሐነ ክርስቶስን ወለደ፣ ዣን ስዩም ደግሞ ገብረ ማርያምንና ላሊበላን ወለደ፡፡ ገብረ ማርያምም ነዓኲቶ ለአብን ወለደ፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ነገሥታት እንደ መልከጼዴቅ (ዘፍ14፡18) ክህነትን ከንግሥና፣ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሕዝብንም በቅድስናና በንጽሕና አገልግለው አልፈዋል፡፡አቡነ አሮን ግን ገና በ7 ዓመታቸው ነው ዓለምን ፍጹም ንቀው በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል እጅ የመነኮሱት፡፡ በ16 ዓመታቸውም ዋልድባ ገዳም ገብተዋል፡፡ ነሐሴ 5 ቀን ገና ሲወለዱ ሙት አስነሥተዋል፡፡ በሀገራችን እየተዘዋወሩ ወንጌልን ሲሰብኩ የሸዋው ንጉሥ አንኮበር ድረስ ጠርቷቸው ሲሔዱ አዋሽ ወንዝ ሞልቶባቸው አገኙት፡፡ ሲሻገሩም ዳዊታቸውን ወሰደባቸው፡፡ ‹‹ልጆቼን አመነኮስክብኝ›› በሚል ሰበብ ንጉሡ 7 ዓመት በግዞት አስሮ አስቀመጣቸው፡፡ነገር ግን ከ7 ዓመት በኋላ አቡነ አሮን ተመልሰው በአዋሽ ወንዝ ሲመጡ መልአክ መጣና ‹‹መቋሚያህን ወደ ወንዙ ላክ›› አላቸው፡፡ መቋሚያቸውንም ቢልኩ ከ7 ዓመት በፊት ወደ ወንዙ ገብቶባቸው የነበረውን ዳዊታቸውን ይዘው አወጡ፡፡ ዳዊቱም በውኃው አልራሰም ነበር፣ ይልቁንም አቧራውን አራግፈው ፈጣሪያቸውን አመስግነው ዳዊታቸውን ይዘው ሄደዋል፡፡ ያ ዳዊታቸው ዛሬም ድረስ በጋይንት አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ይገኛል፡፡ሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ ውስጥ የሚገኘው እጅግ አስደናቂ ገዳማቸው ፍልፍል ዋሻ ሲሆን ጣራው ክፍት ነው፣ ክፍት በሆነው ጣራ በኩል ፀሐይ ሲገባ ስለሚያቃጥል ጥላ ይይዛሉ ነገር ግን የጻድቁ ግዝት ስላለበት ዝናብ ወደ መቅደሱ ፈጽሞ አይገባም፡፡ እጅግ አስደናቂ ነው፡፡ አቡነ አሮን በዋድላ ሜዳ አልፈው ሲሄዱ በዚያችም ሜዳ ላይ እንደ ኢያሱ ፀሐይን በቃላቸው ገዝተው አቁመዋታል፡፡ ከታች ጋይንት ተነሥተው መንገድ ሲሄዱ በሰንበት ቀን በሬ ጠምዶ ሲያርስ የነበረን ገበሬ ‹‹ለምን በሰንበት ታርሳለህ?›› ቢሉት ‹‹ምቀኛ መነኩሴ›› ብሎ በጅራፉ ቢገርፋቸው በሬዎቹ ግን ፈጽሞ አልንቀሳቀስ ብለው ቆመዋል፡፡በዚህ የተናደደው ገበሬም አቡነ አሮንን መሬት ላይ ጥሎ ገረፋቸው፡፡እሳቸውም ተነሥተው ሲሄዱ ዛፎች ተነቅለው እየተከተሏቸው፣ ቃልም አውጥተው በሰው አንደበት አመስግነዋቸዋል፡፡የአቡነ አሮን መንክራዊ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን! + + + አቡነ መልክአ ክርስቶስ:-የአቡነ መልክአ ክርስቶስ አባት ጣዕመ ክርስቶስ:-እናታቸው አውጋንያ ይባላሉ፡፡ እነርሱም ልጅ አልነበራቸውምና የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ዘወትር ወደ እግዚአብሔር ይማጸኑ ነበር ነገር ግን ‹‹የተባረከ ፍሬ የማትሰጠን ከሆነ ልጅ አትስጠን›› እያሉም ይጸልዩ ነበር፡፡ጣዕመ ክርስቶስና አውጋንያ እግዚአብሔርን የሚፈሩ፣ ሕጉን ዘወትር የሚጠብቁ፣ለተቸገሩ የሚራሩ ናቸው፡፡ የተራቡትን በመመገብ የታረዙትን በማልበስ የበረቱ በመሆናቸው ዘወትር ከቤታቸው ድኆች አይጠፉም ነበር፡፡ የቅዱሳኑን ልመና የተቀበለ አምላክ የእነርሱንም ልመናቸውን ሰምቶ የተባረከ ልጅ አቡነ መልክአ ክርስቶስን ሰጣቸው፡፡ አባታችን በምድረ ኢትዮጵያ ሳርካ በሚባል ቦታ ሰኔ 26 ተፀንሶ መጋቢት 27 ቀን ተወለደ፡፡ዕድሜውም ለትምህርት ደርሶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲማር ከዕለታት በአንድ ቀን ከሕፃናት ጋር ሲጫወት እመቤታችን ተገልጻለት ‹‹ልጄ ከእንግዲህ አንተ የምትጫወተው ከቅዱሳን መላእክት፣ ከጻድቃንና ከሰማዕታት ጋር ይሁን›› አለችው፡፡ እርሱም ዘወትር ጸሎትን መጸለይ ጀመረ፡፡መንፈስ ቅዱስ ስለገለጠለት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ወድያው አጠናቀቀ፡፡ከዚኽም በኋላ አቡነ መልክአ ክርስቶስ ገና በለጋ ዕድሜው ስለ ጌታችን መስክሮ ሰማዕት ይሆን ዘንድ በመመኘት በዘመኑ ሰማዕታት ሰማዕትነትን ከሚቀበሉባቸው ቦታዎች ቢሔድም ሰማዕትነት ለእርሱ አልተፈቀደለትም ነበር፡፡ወደ ወግዳ እና ምድረ ሰርማት የሚባሉ ቦታዎች ቢሔድም የተመኘውን ሳያገኝ ቀረ፣ በዚኽም ጊዜ ቃል ከሰማይ ወደ እርሱ መጣና ‹‹ወዳጄ መልክአ ክርስቶስ ሆይ! ሰማዕትነት ክፍልህ አይደለም ይልቁንም እንደ አብርሃም የብዙሃን አባት የሕፃናትና የደካሞች መጠጊያ ትሆናለህ›› አለው፡፡ከዚኽም በኋላ ጻድቁ በመንዝ፣ በጎንደር፣ በመቄት፣ በዳውንት፣ በላስታ፣በዋድላና በሌሎቹም ቦታዎች ተዘዋውሮ የከበረች ወንጌልን በመስበክ ድዉያንን በመፈወስ ብዙ አገልግሏል፡፡ መንዝ ሪቅ በሚባል ቦታ አቅም የሌላቸውን በዕድሜም የገፉትን እናቶችንና አባቶችን ውኃ በመቅዳት ምግብ በማብሰል ዕንጨት በመሸከም አገለገላቸው፡፡ እንግዶች ሲመጡ እግራቸውን አጥቦ ያሳርፋቸዋል፡፡ሥራዎችን በሚሠራ ጊዜም ከአንደበቱ ጸሎት አይቋረጥም ነበር፡፡ በእንዲህ ያለ ምግባር ዐሥር ዓመት ካገለገለ በኋላ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ደቀ መዝሙር ከሆነው ከአቡነ አኖሬዎስ ቤተ ክርስትያን ደብረ ጽጋጃ አባ ጴጥሮስ በተባለ መምህር እጅ መነኰሰ፡፡አባ ጴጥሮስም አቡነ መልክአ ክርስቶስን ካመነኰሰው በኋላ ወደ ቀደመ ቦታው ሔዶ በዚያ ያሉትን በክህነቱ እንዲያገለግላቸው እንዲያመነኵሳቸው መስቀል ሰጥቶ ሸኘው፡፡ እርሱም ተጨማሪ 12 ዓመት አገልግሏቸው በአጠቃላይ 22 ዓመት ሲሞላው የእግዚአብሔር ጸጋ የበዛላት ወለተ ጽዮን ስታርፍ ፍትሐት አድርሶ ከቀበራት በኋላ ወደ ሌላ ቦታ በመሔድ የእግዚአብሔር መልአክ እየመራው ዳውንት ደረሰ፡፡ በዳውንት አጽፍት ሚካኤል ዘጠኝ ዓመት አገልግሎ ብዙዎችን አመነኰሰ፡፡ ከዚያም ወደ ሌላ ቦታ እንዲሔድ እግዚአብሔር ነግሮት ለሔድ ጉዞ ሲጀምር ድንጋዮች ዕፅዋቶች ከነበሩበት ተነሥተው ይከተሉት ጀመር፣ እርሱ ግን በሥልጣኑ በቦታቸው እንዲወሰኑ አዘዛቸው፡፡ ወደ ዋድላ በመሔድ በሰለልኩላ በየጭራ በሐዲስ አምባ እና በደብረ ዳሪት አቡነ አሮን ተመላልሶ ወንጌልን ሰበከ ድዉያንን ፈወሰ ብዙዎችንም አመነኰሰ፡፡ከዚኽም በኋላ ዐብይ ጾምን ወደ ጎንደር ሔዶ ሱባኤውን በዚያ ከቆየ በኋላ ወደ ሰለልኩላ ተመለሰ፡፡ የቅድስት ድንግል ማርያምና የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት አብሮ ይዞ ስለነበር ሀገሩ እንዲባረክ በሰላልኩላ የቅዱስ ሚካኤልን ቤተ ክርስትያን ሠርቶ ታቦተ ሚካኤልን አስገብቶ አከበረ፡፡ ዛሬም ድረስ በዋድላ ሰለልኩላ ሚካኤል በሰለልኩላ ቅዳሴ መገኛነቱ በብዙዎች ዘንድ ይታወቃል፡፡ አባታችንም ጥቂት ጊዜ በሰለልኩላ ሚካኤል እንደቆየ እመቤታችን ‹‹…ይህ ስፍራህ አይደለምና ወደ ደብረ አብ ደብረ ወልድ ደብረ መንፈስ ቅዱስ ሒድ›› አለችው፡፡በተነገረው ቦታም ተወስነው የሚጸልዩ ሦስት ደገኛ መነኰሳት

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን መስከረም 5-ቤተ መቅደሳቸው ጣራው ክፍት ሆኖ ዝናብ ግን ፈጽሞ የማያስገባው የመቄቱ አቡነ አሮን መንክራዊ ዕረፍታቸው ነው፡፡ እርሳቸውም ዳዊታቸውን አዋሽ ወንዝ ወስዶባቸው ሳለ ከ7 ዓመት በኋላ መልሰው ከወንዙ ውስጥ አቧራውን አራግፈው የተቀበሉ ናቸው፡፡ + አስቀድማ አረማዊት የነበረችውና በኋላ በጌታችን አምና ከሁለት ልጆቿ ጋር ሰማዕትነቷን በድል የፈጸመችው ቅድስት ሶፍያ ዕረፍቷ ነው፡፡ + ዳግመኛም በዚህች ዕለት እግዚአብሔርን የሚወድ ሃይማኖቱ ቀና ደግና ጻዲቅ ንጉሥ ዐፄ ልብነ ድንግል ዕረፍቱ ነው፡፡ + የሚያገለግላቸውን አህያ ጅብ ቢበላባቸው በአህያቸው ፋንታ ጅቡን ለ7 አመት ውሃ እየቀዳ እንዲያገለግላቸው ያደረጉት የአቡነ መልክአ ክርስቶስ ዕረፍታቸው ነው። + ሰማዕቱ ቅዱስ ማማስ ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ማማስ፡- ይኽንንም ቅዱስ ወላጆቹ ቴዎዶስዮስና ታውፍና በከሃዲው ዑልያኖስ ዘመን ሰማዕት ሆነው ሲያርፉ አንዲት ክርስቲያን ሴት ወስዳ አሳደገችው፡፡ እርሷም እናትና አባቱ ዐርፈዋልና ስሙን ማማስ አለችው፡፡ ማማስ ማለት የሙት ልጅ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ማማስ 18 ዓመት በሆነው ጊዜ ክርስቲያን መሆኑን ሲያውቅ ከሃዲው ገዥ ይዞ ልዩ ልዩ በሆኑ ጽኑ ማሠቃያዎች አሠቃየው፡፡ በአንገቱም ላይ ትልቅ ድንጋይ አስሮ ወደ ባሕር ጣለው፣ ነገር ግን ጌታችን መልአኩን ልኮ አዳነው፡፡ ከዚኽም በኋላ ቅዱስ ማማስ በዋሻ ውስጥ የጎሽ ወተት እየጠጣ በመንፈሳዊ ተጋድሎ ተቀመጠ፡፡ ሁለተኛም ከሃዲዎች ይዘውት በሚነድ እሳት ውስጥ ጨመሩት፣ አሁንም ጌታችን ከሚነደው እቶን እሳት አዳነው፡፡ዳግመኛም ተነጣጥቀው እንዲበሉት ለተራቡ አንበሶች ቢሰጡትም ጌታችን ከመከራው ሁሉ ያድነው ስለነበር አሁንም እንደ ነቢዩ ዳንኤል ከአንበሶቹ አፍ አዳነው፡፡ ይልቁንም አንበሶቹ ቅዱስ ማማስን በላያቸው ላይ አውጥተው ተሸከሙት፡፡ ከብዙ ጽኑ ሥቃዮችም በኋላ በመጨረሻ ሕዋሳቶቹ እስኪለያዩና የሆድ ዕቃው እስኪፈስ ድረስ መሬት ላይ ጎተቱትና ምስክርነቱን በዚሁ ፈጽሞ የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ዕረፍቱም መስከረም 5 ነው፡፡ ታላቁ ሊቅ ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ‹‹ተአምኆ ቅዱሳን የቅዱሳን ሰላምታ›› በሚለው ድርሰቱ ላይ ይኽን ታላቅ ሰማዕት ‹‹አንበሳ ለሚሰግድለትና የእሳት ነበልባልን ላቀዘቀዘ የወልድ ምስክር ለሆነ ለማማስ ሰላምታ ይገባል›› በማለት አመስግኖታል፡፡በዚህ ታላቅ ሰማዕት በቅዱስ ማማስ ስም የተጠሩ አንድ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አሉ፡፡አቡነ ማማስ ይባላሉ፡፡ እርሳቸውም የታላቁ አባት የአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ረድእ የነበሩ ሲሆን ያመነኮሷቸውም እሳቸው ናቸው፡፡ የአቡነ አሞኒ ሦስተኛ ልጅ ናቸው፡፡ ትውልዳቸው ወሎ አምሐራ ሳይንት ነው፡፡ አቡነ ማማስ በተለያዩ ቦታዎች ሰባት ገዳማትን ያቀኑ ሲሆን ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቃሉ፡፡በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረው በስብከተ ወንጌል ብዙ አገልግለዋል፡፡ በስማቸው የተሠራው አስደናቂ ገዳም በትግራይ አጋሜ አውራጃ ይገኛል፡፡ኤርትራ አካለ ጉዛይ ውስጥም አቡነ ማማስ የሚባል ትልቅ ገዳም አላቸው፡፡ትግራይ ውስጥ ከእዳጋ አርቢ ወደ ጥንታዊቷ ውቅሮ ማርያም ገዳም በሚወስደው መንገድ ላይ ነበለት ከምትባለው ትንሽ የገጠር ከተማ በስተሰሜን አቅጣጫ በሚገኘው አስደናቂ ገዳማቸው ውስጥ ለየት ያለ የማኅሌት ሥርዓት ይካሄድበታል፡፡ የማኅሌቱ ድምጽ እጅግ የተለየ ሲሆን ማኅሌቱን ቅዱሳን መላእክት እንደሚሳተፉበት በቦታው ላይ ያሉ ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ በማኅሌቱም ወቅት ከዋሻው ጣራ ላይ ልዩ ጣዕም ያለውና ፈውስ የሚሰጥ ልዩ ጠበል ይፈልቃል፡፡ ስለትንሳኤ የሚናገረው ተአምረ ማርያም ላይ ስለዚህ ታላቅ ቦታ እንደተጻፈ አባቶች ያስረዳሉ፡፡ ጻድቁን በመጀመሪያ ወደዚህ ታላቅ ቦታ እየመራ ያመጣቸው የታዘዘ መልአክ ነው፡፡ ገዳሙ ሁለት ቤተ መቅደስ ያለው ሲሆን ቀድሞ በመነኩሴ ብቻ ይገለገል ነበር፡፡የአቡነ ማማስ መካነ መቃብራቸው ካለበት ተራራ ላይ የበቀለ የተለየ የዕፅ ተክል አለ፡፡ ይኽንንም ተክል የአካባቢው ነዋሪ ለእምነትነት በመጠቀም ከተለያዩ ሕመሞች ይፈወስበታል፡፡ የአቡነ ማማስ የዕረፍታቸው ዕለት ጥር 21 ቀን ቢሆንም የአካባቢው ነዋሪ ተአምራት ባደረጉበት ዕለት ታኅሣሥ 30 ቀን በገዳማቸው በደማቅ ሁኔታ ያከብራቸዋል፡፡ የልደት በዓላቸውም ነሐሴ 7 ነው፡፡ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን! + + + + + ሰማዕቷ ቅድስት ሶፍያ፡- ቅድስት ሶፍያ የተባለች ይህችም ንጽሕት ከሁለት ልጆቿ ጋር ሰማዕት የሆነች ናት፡፡ አስቀድማ አረማዊት የነበረች ናት፡፡ ወላጆቿም ጣዖታትን የሚያመልኩ ናቸው፡፡ እርሷም መርምራ በልቧ አስተውላ የወላጆቿ እምነት ከንቱ መሆኑን ዐወቀች፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ መኖፌ ኤጲስ ቆጶስ ዘንድ ሄዳ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነች፡፡ እርሱም ሃይማኖትን ካስተማራት በኋላ ከሁለት ልጆቿ ጋር አጠመቃት፡፡የሀገሯ ሰዎችም ‹‹ለአማልክት መስገድን ትታ ክርስቲያን ሆናለች›› ብለው ለገዥው ለከላድያኖስ ወነጀሏት፡፡ ገዥውም ወደ እርሱ አቅርቦ መረመራት፡፡እርሷም በክርስቶስ ማመኗን ለከሃዲው ገዥ በድፍረት ተናገረች፡፡ ሊያባብላትም ሞክሮ አልሆንለት ቢል ከልጆቿ ጋር ጽኑ ሥቃይን አሠቃያት፡፡ እርሷ ግን በሥቃይ ውስጥ ሳሉ ልጆቿን ታጽናናቸውና ታበረታቸው ነበር፡፡ ‹‹ልጆቼ ሆይ ጠንክሩ፣ጨክኑም፤ እኔ የአንጌቤንዋን እመቤት ሶፍያን እመስላታለሁ፣ እናንተም ጲስጢስ፣አላጲስ፣ አጋጲስ የተባሉ ልጆቿን ምሰሉ›› ስትላቸው እነርሱም ‹‹እናታችን ሆይ ፍለጋሽን እንከተላለንና ስለ እኛ አትፍሪ›› አሏት፡፡ በዚህም ጊዜ ተቃቅፈው እየተሳሳሙ ተላቀሱ፡፡ገዥውም ይህንን አይቶ ልጆቹ እንዲፈሩ በማለት እናታቸውን በፊታቸው አሠቃያት፡፡ ልጆቹም የታዘዘ መልአክ መጥቶ እናታቸውን ሲሰውራት ተመለከቱ፡፡ በሥቃይም ውስጥ ሆና በክርስቶስ ማመኗን ስትናገር ገዥው ምላሷን ከሥሮ አስቆረጠው፣ ነገር ግን መናገሯን አላቋረጠችም ነበር፡፡በመጨረሻም አንገቷን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ገዥው ልጆቿን እሺ ይሉት ዘንድ ቢያባብላቸውም እነርሱ ግን እመቢ አሉት፡፡ በየተራ እያከታተለ ራሳቸውን አስቆረጠው፡፡በመቃብራቸውም ላይ እጅግ አስገራሚ ተአምራት ተፈጸሙ፡፡ደገኛው ንጉሥ ታላቁ ቈስጠንጢኖስ የእነዚህን ቅዱሳት ዜና ትሩፋታቸውን በሰማ ጊዜ ሥጋቸውን ወደ ቍስጥንጥንያ አፍልሶ ወሰደው፡፡ እርሱም ዜናቸውን ከመስማቱ በፊት ታላቅና ሰፊ ቤት በዕንቁና በወርቅ አስውቦ አሠርቶ በላይዋም ላይ ‹‹ይህቺ ቤት የንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ናት›› ብሎ ጽሑፍ አስቀረጸባት፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔር መልአክ ወርዶ ያችን ጽሕፈት ደምስሶ በመቀየር ‹‹ይህች ቤት የሶፍያ ናት›› ብሎ ይጽፋል፡፡ ንጉሡም በተደጋጋሚ እየቀየረ ስሙን ቢጽፈውም መልአኩ በየጊዜው ስሙን በሶፍያ ስም ስለቀየረበት ሠራተኞቹም ሆኑ ንጉሡ የሚያደርጉትን አጡ፡፡አንድ ቀን የንጉሡ ልጅ ሲጫወት መልአኩ ተገለጠለትና ቤቷ የሶፍያ መሆኗን ለአባቱ እንዲነግረው አዘዘው፡፡ ልጁም መልአኩን ‹‹ለአባቴ ነግሬው እስክመጣ ትጠብቀኛለህ?›› ሲለው መልአኩም ‹‹አዎ›› አለው፡፡ ንጉሡም ልጁን የላከው መልአክ መሆኑን ዐውቆ መልአኩ ልጁ እስኪመለስ እንደሚጠብቀው ሲያውቅ መልአኩ ከዚያ እንዳይሄድ ብሎ የገዛ ልጁን ገደለው፡፡ መልአኩም ልጁ እስኪመጣ እየጠበቀው በዚያ ቦታ ኖረ፡፡ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስም የቅድስት ሶፍያንና የልጆቿን ሥጋ አስመጥቶ በዚያች ቤት ውስጥ በታላቅ ክብር አኖረው። አስክሬናቸውን ከወደቀበት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት - Telegram kanali @sinksarr statistikasi va tahlili