ST.GEORGE FC™🇪🇹
Open in Telegram
ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳዲስና ትኩስ መረጃዎች፣ የጨዋታዎች ቀጥታ ስርጭት፣ ኃይላይቶች፣ ቪዲዮዎች እንዲሁም ጊዮርጊሳዊ ታሪኮች በቀጥታ ያገኛሉ! ______________________________ ➢ | ለማንኛዉም አስተያየት፦ @Saintgeorge_fcBot @St_Georgefc @St_Georgefc የቅዱስ ጊዮርጊሳውያን ድምፅ✌️ THE VOICE OF ST.GEORGE FANS
Show more5 398
Subscribers
No data24 hours
-227 days
-7630 days
Posts Archive
5 398
#ወንድማችንን_ታደጉልን🙏
የ 20 አመት ወጣት የሆነው #ኤርሚያስ_ገዛኸኝ ከሁለት ወር በፊት ከሰፈር ጓደኞቹ ጋር ሰባት ሆነው ኑሮን ለማሸነፍ ቤተሰብ ሳያሳውቁ ከባድ እና አስቸጋሪ በሆነው በሊቢያ መንገድ ስደት ጀምረው የነበረ ቢሆንም አብረውት የተጓዙት ለቤተሰብ የደወሉ ሲሆን እሱ ግን ያለበትን ሳናውቅ ሁለት አስጨናቂ ወራትን አሳልፈናል። ክብር ለፈጣሪ ይሁንና ዛሬ በህይወት ስለመኖሩ ማወቅ ብንችልም በአጋቾች እጅ ላይ ወድቆ ነውና ያለው ድጋሚ ወደ ሌላ ጭንቀት ተሸጋግረናል በ 10 ቀናት ውስጥ 840,000 ሺህ ብር መክፈል እንዳለብን አስጠንቅቀውናል። እኛ ደግሞ ይሄን ገንዘብ በዚህ ቀናት ውስጥ ከየትም ማምጣት አንችልምና የኢትዮጵያ ህዝብ ባለው አቅም እንዲያግዘን በፈጣሪ ስም እንማፀናለን🙏እህቶቹ #ህይወት_ገዛኸኝ እና #ሜሮን_ገዛኸኝ
CBE 1000551827511 Hiwot Gezahegn Woldie
5 398
ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ሐሙስ ጠዋት 2.30 በሳሬም ሆቴል ከደጋፊዎች ጋር ለመነጋገር ፕሮግራም ስላዘጋጀ በእለቱ የምትችሉ ደጋፊዎች ማልያችሁን በመልበስ እንድትገኙ በእለቱ የመጠየቅ እድል የምታገኙ ደጋፊዎች የመለማመጂያ ሜዳችንን እንድናጥር እንቅፋት የሆኑብንን የካሳ ጉዳይ ጨርሰው ቦታውን እንዲያስረክቡን እና ካሱ ወደ ከተማችን እንዲመለስልን እናድርግ....
5 398
ውጤት
ሃዋሳ ከተማ 0 - 3 ቅዱስ ጊዮርጊስ
06' አቤል ያለው
34' አቤል ያለው
43' አቤል ያለው(ፍ)
የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኒቨርሲቲ ስታዲየም
ሐሙስ ታህሳስ 04/2016
⚽️ስምንተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ⤵️
5 398
Repost from Ethiopian Premier league Share company
ውጤት
ሃዋሳ ከተማ 0 - 3 ቅዱስ ጊዮርጊስ
06' አቤል ያለው
34' አቤል ያለው
43' አቤል ያለው(ፍ)
የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የኒቨርሲቲ ስታዲየም
ሐሙስ ታህሳስ 04/2016
⚽️ስምንተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ⤵️
5 398
እንኳን ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ 88ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አደረሳችሁ!
88 ዓመታት የድል ጉዞ! ምንግዜም ጊዮርጊስ!
ፀሐይ ባንክ ከአንጋፋው የቅዱስ ዮርጊስ ስፖርት ክለብ ጋር አብሮ በመስራቱ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡
የአሸናፊዎች የቁጠባ ሒሳብ በመክፈት ከልብ ለሚወዱት ክለብዎ እና ለራስዎ ጠቀም ያለ ገቢ ያስገኙ!
አንድ ክለብ! አንድ ቤተሰብ!
ፀሐይ ባንክ
ለሁሉ!
5 398
👉 በፈተና ያልተገደበ - በስኬት የዘለቀ የ88 ዓመታት የድል ጉዞ!
ፋሽስት ለዳግም ወረራ ታጥቆ በመጣበት ወቅት የኢትዮጵያውያን ትግል የመረጃ ምንጭ ሆኖ ሊያገለግል ብቅ ያለ፣ በአርበኝነት መስዋዕትነትን የከፈለ ፣ በስኬት የአሸናፊነት ምልክት ሆኖ የተገኘ፣ የታላቅነት መገለጫ ነው ፤ . . . አርበኛው ቡድን ቅዱስ ጊዮርጊስ !✌️
ገና ከመነሻው በወርሃ ታህሳስ ስምና ውሉ ሲፀና የወደዱትም የተከተሉትም ብዙ መስዋዕትነት ከፍለዋል። ኢትዮጵያዊነትን ስላቀነቀኑ፣ ሰንደቋን ስላነገቡ እስር፣ እንግልትና ስቅላትን ተቀብለዋል። የተነሱበትን መስመር በፅናት ስለጠበቁ ክለባቸው በድል ፣ ሀገራቸው በነፃነት ቀጥለዋል።
በነፃነት ጉዞው ለሀገር አርበኞችን ፣ ለጊዮርጊስ ዘመን ተሻጋሪ ክብርን አጎናፅፈዋል።
እነሆ ጊዮርጊስ በዘመን ጉዞው ለገጠሙት ፈተናዎች ሁሉ እጅ ሳይሰጥ ለ88 ዓመታት ዘልቋል፤ የጠሉና የፈተኑት የሉም፤ እርሱ ግን አሸናፊነት ዛሬም ስሙ ነው።
👉 እንኳን ለዚህ ታላቅ አርበኛ ክለብ 88ኛ አመት በሰላም አደረሣችሁ!
@St_Georgefc
@St_Georgefc
የቅዱስ ጊዮርጊሳውያን ድምፅ✌
THE VOICE OF ST.GEORGE FANS
5 398
✌️ቅ/ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ አርማ✌️
ሸገር ደርቢ
#ቀጣይ ጨዋታ #Next Match
የኢትዮጵያ _ፕሪሚየር _ሊግ _7ኛ ሳምንት ጨዋታ
#Ethiopia_ premier_ League
ኢትዮጵያ ቡና 🆚 ቅዱስ ጊዮርጊስ
📆 ቅዳሜ ህዳር 29/2016
🕗 በ 9:00 ሰዓት
🏟 በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስታዲየም
💛❤️ድል - ለታላቁ ቅዱስ ጊዮርጊስ 💛❤️
#ሼርShare_በማድረግ_መረጃውን_ለደጋፊዎች_ያጋሩ!
Via Saint George SA
#ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️
👉 @SAINTGEORGEFC 👈
👉 @SAINTGEORGEFC 👈
👉 @SAINTGEORGEFC 👈
፩ ክለብ ፩ ቤተሰብ
ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን...✌️
5 398
Repost from ቅ/ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ አርማ
✌️ቅ/ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ አርማ✌️
ሸገር ደርቢ
#ቀጣይ ጨዋታ #Next Match
የኢትዮጵያ _ፕሪሚየር _ሊግ _7ኛ ሳምንት ጨዋታ
#Ethiopia_ premier_ League
ኢትዮጵያ ቡና 🆚 ቅዱስ ጊዮርጊስ
📆 ቅዳሜ ህዳር 29/2016
🕗 በ 9:00 ሰዓት
🏟 በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስታዲየም
💛❤️ድል - ለታላቁ ቅዱስ ጊዮርጊስ 💛❤️
#ሼርShare_በማድረግ_መረጃውን_ለደጋፊዎች_ያጋሩ!
Via Saint George SA
#ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️
👉 @SAINTGEORGEFC 👈
👉 @SAINTGEORGEFC 👈
👉 @SAINTGEORGEFC 👈
፩ ክለብ ፩ ቤተሰብ
ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን...✌️
5 398
የአጋርነት ስምምነቱ ዝርዝር ጉዳዩች በአጭሩ :-
✅የ3 አመት ውል ነው የተፈራረሙት winner .et እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር
✅በመጀመሪያው አመት የ25 ሚሊዮን ብር ክፍያ ነው Winner .et የሚፈፅመው
✅የቀሩትን 2 አመታት ደሞ ቀጣይ በሚደረጉ ስምምነቶች አሁን ከሚከፈለው 25 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ነገር ግን የማይቀንስ ብር ለመክፈል ተስማምተዋል
✅ የሚጨመረው ብር በዋነኝነት የጊዜውን የዋጋ ንረት የቅዱስ ጊዮርጊስን ውጤት እና የዊነር ኢትን የገበያ ትርፍ ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው የሚሆነው
✅ ከ25 ሚሊዮን ብሩ ውጪ በየአመቱ ለ3 አመት የተጫዋቾችን ማልያ የትሬዲንግ ልብሶችን እና ወዘተ አስፈላጊ የስፖርት ትጥቆችን ወጪ ዊነር ኢት ይችላል
✅የ25 ሚሊዮን ብሩ ክፍያ ተቆራርጦ ነው የሚፈፀመው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር በአንድ ዙር አይፈፀሙም
✅winner .et የሚለው ሎጎ የሚለጠፈው የቅዱስ ጊዮርጊስ ዋናው የወንዶች ቡድን ላይ ብቻ ነው ይሄ ማለት winner et ተስፉ ቡድንን የሴቶቹን ቡድንን እና ሌሎች የእርከን ቡድኖቻችንን ስፖንሰር አላረገም ማለት ነው!
5 398
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ዊነር የስፖርት ውርርድ ተቋም ለ 3 አመት በጋራ ለመስራት ውል አስረዋል። ፈረሰኞቹ በመጀመሪያው አመት 25 ሚሊዮን ብር እንደደሚያገኙ ሲታወቅ ዊነር የስፖርት ውርርድ ለቅዱስጊዮርጊስ ለ ጨዋታ እና ለ ልምምድ የሚሆኑ ትጥቆችን ወጪ እንደሚሸፍን ታውቋል።
5 398
👉 ጨዋታው በፈረሰኞቹ አሸናፊነት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ _ፕሪሚየር _ሊግ _5ኛ ሳምንት ጨዋታ
#Ethiopia_ premier_ League
⚽️ ኢትዮጵያ መድን 0 - 3ቅዱስ ጊዮርጊስ ⚽️
⚽️አቤል ያለው 37'(ፍ)
⚽️ ሞሰስ ኦዶ 57'
⚽️አማኑኤል ኤርቦ 81'
📆 ዛሬ ሐሙስ ጥቅምት 22/2016
🕗12:00
🏟 በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስታዲየም
👉 ሊንኩን ተጭነው የቴሌግራም ገፃችን ይቀላቀሉ!!
https://t.me/stgeorge123
#ሼርShare_በማድረግ_መረጃውን_ለደጋፊዎች_ያጋሩ!
5 398
#ቀጣይ ጨዋታ
የኢትዮጵያ _ፕሪሚየር _ሊግ _2ኛ ሳምንት ጨዋታ
#Ethiopia_ premier_ League
⚽️ሀምበርቾ ዱራሜ 🆚 ቅዱስ ጊዮርጊስ ⚽️
5 398
ተጠናቀቀ | ቅዱስ ጊዮርጊስ 4-1 ወልቂጤ ከተማ
20' ዳንኤል ደምሱ (OG) | 30' ስንታየሁ መንግስቱ
57' አማኑኤል አረቦ
75' አቤል ያለው
87' ተገኑ ተሾመ
5 398
ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ቅዱስ ጊዮርጊስ - ወልቂጤ ከነማ
ትልቁ የኢትዮጵያ ሊግ እና ትልቁ የሀገሪቱ ክለብ ነገ ይመለሳሉ🔥
የ2015 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ የ2016 የሻምፒዮንነቱን ጉዞ ነገ አንድ ብሎ ይጀምራል። ታላቁ ክለብ በጣም ውጥረት የበዛበት እና የተጨናነቀ ፕሪሲዝን ዝግጅት ካረገ ቡኃላ በርካታ ተጫዋቾች ሸኝቶ በእነሱም ምትክ ተስፋ ያላቸው ታዳጊዎች እና የውጭ ተጫዋቾች ጨምሮ የአሸናፊነት እና የድል አርማውን አሲዞ ነገ በሽምጥ ሸለቆዋ አዳማ ላይ ጨዋታውን ያረጋል ።
ነገ ወልቂጤን ስንገጥም የአምናው የውድድር ዘመን የሊጉ ኮኮብ ተጫዋች ቢንያም በላይ ብቻ ሲሆን ጉዳት ላይ የሚገኘው ሌሎቹ ተጫዋቾች በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ💪
ከተጋጣሚያችን ወልቂጤ ከነማዎች ጋር ያለን 🔥🔥🔥የእርስ በእርስ ግንኙነት🔥🔥🔥
በርካታ ግቦችን በሚያስተናግደው በሁለቱ ክለቦች ጨዋታ በእስካሁኖቹ በተደረጉ 7 ጨዋታዎቻች 26 ግቦች የተቆጠሩ ሲሆን ታላቁ ክለባችን ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ7ቱ ጨዋታዎች የ5ቱ ባለድል መሆን ሲችል በድምሩም 18 ግቦችን ሰራተኞቹ ላይ አስቆጥሯል። ይሄም በጫወታ ሲሰላ 2.57 ጎል በየጫወታው ያስቆጥራል ማለት ነው። ይሄ ማለት ሳንጅዬ ብዙ ጎል ለማግባት ከሚቀሉት ክለቦች ውስጥ አንዱ የሆነውን ክለብ ነው ነገ የሚገጥመው ። በአንፃሩ ሰራተኞቹ ደሞ 8 ጎል ማግባት ሲችሉ በየጫወታው በአማካኝ 1.14 ጎል ያስቆጥራሉ። ሆኖም ድል ማረግ የቻለው ግን አንድ ጨዋታ ነው እሱም በጠባብ ውጤት (1 ለ 0) የቀረው 1 ጨዋታ 2-2 በሆነ ውጤት ነው የተጠናቀቀው🔥
በከፍተኛ ውጤት ልዩነት ያለቀው የሁለቱ ጨዋታ 4 ለ 0 በጊዮርጊስ አሸናፊነት የተጠናቀቀው ሲሆን ከፍተኛ ግብም የገባበት ጨዋታ እንዲሁ በጊዮርጊስ 4 ለ 3 አሸናፊነት የተጠናቀቀ ነበር💪
ምርጡ አጥቂ ኦሮ አጎሮ እና ካፕቴን ሀይደር ሸረፋ 3 ግቦችን ወልቂጤ ከነማ ላይ በማግባት ቀዳሚ ሲሆኑ ታላቁ አጥቂያችን ሳላዲን ሰይድ , አማኑኤል ገ/ሚካኤል እና ጌታነህ ከበደ 2 ግብ ወልቂጤ ላይ በማስቆጠር ስማቸው ይጠቀሳል🙌
ነገስ ስንት ግብ እንጠብቅ🙌
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ወልቂጤ ከነማ
ነገ እሁድ
27 / 01 / 2016
አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዮኒቨርስቲ ስታዲየም
#ድል_ለፈረሰኞቹ_Victory_For_Horsemen
5 398
ክለባችን የአራት ተስፈኛ ተጨዋቾች ወደ ዋናው ቡድን አሳደገ።
ከ20 ዓመት በታች ተጫዋች የሆኑት አሮን አንተር፤ አቤሰሎም ዘመንፈስ፤ቢንያም እንዳለና አሸናፊ ሞሼ በዛሬው እለት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በመገኘት ለሶስት ዓመት የሚያቆያቸውን ፊርማ አኑረዋል፡፡
5 398
ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ በዓሉ የሰላም ፣የደስታ ፣የፍቅር፣የመተሳሰብ እንድሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል ።
መልካም የመስቀል በዓል !!
💛❤ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር 💛❤
5 398
☪ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1,498ኛው የነቢዩ መሐመድ ልደት በዓል (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር ፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ ይሆንልን ዘንድ ከልብ እንመኛለን!
ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር
**መልካም በዓል 🕌***
👉 ሊንኩን ተጭነው የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ ።
https://t.me/stgeorge123
#LIKE_COMMENT_SHARE
#ለደጋፊዎች_መረጃ_እንዲደርስ_ሼር_Share_እና_ላይክ_Like_ያድርጉ
