en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 680 subscribers, ranking 8 053 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 680 subscribers.

According to the latest data from 05 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 112 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.83%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.95% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 050 views. Within the first day, a publication typically gains 2 501 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 680
Subscribers
-1224 hours
-127 days
+11230 days
Posts Archive
የፕሮጀክቱ ግንባታ 78 ነጥብ 2 በመቶ ደርሷል ……...///………. የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ 78 ነጥብ 2 መድረሱን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ፈቃዱ አብርሃም እንደገለጹት 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከዴንማርክ መንግሥት በተገኘ ብድር እና ዕርዳታ ከ146 ሚሊዮን ዩሮ በላይ በጀት ግንባታው የተጀመረው ታህሳስ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ነው። ፕሮጀክቱ እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 46 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 የንፋስ ተርባይኖች ሲኖሩት የ22 ተርባይኖች ተከላ መጠናቀቁንና የ20ዎቹ ተርባይኖች የቅድመ ፍተሻ ሥራ መከናወኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማመንጫው የባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የሲቪል ሥራ ከ95 በመቶ በላይ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ ከ60 በመቶ ደርሷል። እያንዳንዱን ተርባይን የሚያገናኙ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በሥራ ተቋራጩ ምክንያት መዘግየት አፈጻጸሙም 54 በመቶ ላይ እንደሚገኝና አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 78 ነጥብ 2 መድረሱን አስታውቀዋል። የግንባታው ሥራ ተቋራጭ ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒዌብል ኢነርጂ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ኤድዋርዶ ጎንዛሌዝ እንደገለጹት ኩባንያቸው በኢትዮጵያ መሰል ፕሮጀክት ሲገነባ የመጀመሪያው ቢሆንም በሰሜን አፍሪካ ጨምሮ በበርካታ የዓለም ሀገራት የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት ልምድ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም መልካም በሚባል ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑንና ቀሪ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑንም አስረድተዋል። የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የአፈፃፀም ክትትልና ቁጥጥር ተወካይ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሰሎሞን ተረፈ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ የንፋስ ኃይል ማመንጫውን 29 የንፋስ ማማዎች ተከላ ፣ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፍያ ጣቢያ፣ 38 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የባለ 33 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ ከእያንዳንዱ የንፋስ ማማዎች ኃይል ተቀብሎ ወደ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚያስገባው የባለ 33 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ከሚዘረጋው 38 ኪሎ ሜትር ውስጥ የ25 ኪሎ ሜትሩ ሥራ መጠናቀቁን ተወካይ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ ያለቁ የንፋስ ማማዎችን በማገናኘት በአጭር ጊዜ ኃይል በማምረት ወደ ግሪድ ለማስገባት የማጠናቀቅያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች እየቀነሱ ነው ……….///….…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል በተሰራው ሥራ ውጤት እየተገኘ መሆኑን በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለጹት በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈጸሙ የስርቆት ወንጀሎች በሀገር ደረጃ ለመከላከል በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅጣጫ ተሰጥቶበታል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትም ለክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ለሚመለከታቸው የፀጥታ ዘርፍ ተቋማት ኃላፊዎች በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት የሀገሪቱ ብሔራዊ የደህንነት አጀንዳ መሆኑን የማስገንዘብ ሥራ መስራቱን ተናግረዋል። ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀል የሚፈፀምባቸው እና ትኩረት የሚሹ  21 መስመሮች መለየታቸውንና ተቋሙ ከብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር ጠንካራ የመረጃ ልውውጥ ስርዓት መዘርጋቱን ገልፀዋል፡፡ የሥራ ክፍሉ ባለፉት ስድስት ወራት ከተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ጋር በመሆን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከሚገኙ የክልል፣ ዞንና ወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች፣ የኀገር ሽማግሌዎችና አባገዳዎች በኃይል ማስተላለፊያ መሰረተ ልማቶች ስርቆት ዙሪያ  ሰባት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ማካሄዱን ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አቶ ዋለ ገለፃ በውይይት መድረኮቹ በተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ የቁጥጥር ሥርዓቱ ከመጠናከሩም በላይ የየአካባቢው ማህበረሰብ በመሰረተ ልማቶቹ ላይ ያለው የእኔነት ስሜት እያደገ መጥቷል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራት በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የተፈፀመው ስርቆት ካለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ጊዜያት ጋር ሲነፃፀር እየቀነሰ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም የታየውን መሻሻል አጠናክሮ ለማስቀጠል እና የየአካባቢው ማህበረሰብ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅ የሚያግዙ ስልቶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክፍሉ አደረጃጀቱን በማጠናከር በሁሉም ቋንቋዎች የግንዛቤ ፈጠራ ሥራውን አጠናክሮ ለማስቀጠል እየሰራ ነው ያሉት አቶ ዋለ ከረጅም ጊዜ ዕቅድ አንጻር የጎረቤት ሀገራትን ልምድ ታሳቢ በማድረግ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለመተግበር እየሰራ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ለጣቢያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በእሳት አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ ……….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከማዕከላዊ 3 ሪጅን ለተውጣጡ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በእሳት አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ስልጠና መስጠቱን የሪጅኑ ጥገናና ኦፕሬሽን ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ታደሰ ገብሬ እንደተናገሩት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር ከሪጅኑ ለተውጣጡ ከ30 በላይ የጣቢያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በመሠረታዊ የእሳት እና ድንገተኛ አደጋ መከላከል ዙሪያ ለሁለተኛ ጊዜ ስልጠና ተሰጥቷል። ሥልጠናው በተግባርና በንድፈ ሀሳብ ተደግፎ መሰጠቱን የጠቆሙት ኃላፊው የሥልጠናው ዓላማ በሪጅኑ ውስጥ ባሉ ማከፋፈያ እና የማስተላለፊያ መስመር ጣቢያዎች ላይ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ የሚከሰቱ የእሳት አደጋዎችን አስቀድሞ ለመከላከል ያለመ ነው ብለዋል። የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የእሳት አደጋን አስቀድሞ መከላከል በሚቻልባቸውና ሲከሰትም መተግበር ስላለባቸው የደህንነት ማስጠበቂያ ሥራዎች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንደተፈጠረላቸውም ተናግረዋል። ስልጠናው ሪጅኖች ከሚያከናውኗቸው ሥራዎች ጋር በተያያዘ ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊ በመሆኑ በቀጣይ በሁሉም የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ባለሙያዎች እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡   ለሰልጣኞች የምስክር ወረቀት የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የስልጠና ማዕከል ኃላፊ ኮማንደር አለማየሁ ጦፋ ሰልጣኞች ባገኙት እውቀት የሥራ ቦታቸውን ደህንነት በማስጠበቅ ድንገተኛ የእሳት አደጋዎች ሊከላከሉ እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የኃይል ምርት አፈጻጸምን ማሳደግ ተችሏል …….///……... በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በራስ አቅም የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የግማሽ በጀት ዓመቱን የኃይል ምርት አፈፃፀም ማሳደጋቸውን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የዕቅድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በተለያዩ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በርካታ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም ተከናውነዋል፡፡ በተከዜ እና በጢስ አባይ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በብልሽት ምክንያት የቆሙ ተርባይኖችን እንዲሁም በግልገል ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኖዝል ጫፍ ጥገና በራስ አቅም በማከናወን የጣቢያዎቹን የኃይል ምርት ማሻሻል መቻሉን ጠቁመዋል። እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለፃ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች ላይ ተጽዕኖ በማያሳድር እና የግድቦችን ደህንነት ለመጠበቅ እንዲያስችል የሞሉ ግድቦችን ውሃ የማስተንፈስ እንዲሁም የኃይል ማመንጨት ሂደቱን የሚያስተጓጉሉ የተንሳፋፊ ሳሮችን የመከላከል ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ለኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የመለዋወጫ ዕቃዎችን ለማቅረብ ከቮይት ሃይድሮ፣ ኤመርሰን ኮንትሮል እና ዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ እንዲሁም ዲራክ አውቶሜሽን ከተባሉ የውጭና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ጋር የማዕቀፍ ግዥ ውል በመፈራረም ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ ከጥገና ሥራዎቹ ጎን ለጎን የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውንም ነው ወ/ሮ ጥሩወርቅ የተናገሩት፡፡ በጣቢያዎቹ የጥገና አስተዳደርን ለማዘመን የሚያግዙ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ጨምሮ የተሽከርካሪ አስተዳደር፣ የሥራ ፍሰትን የመቆጣጠር እና የጤናና ደህንነት አሰራሮች ተግባራዊ መደረጋቸው ጠቅሰዋል። በጣቢያዎቹ በራስ ኃይል የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የኃይል ምርት አፈጻጸሙን በማሳደጋቸው ባለፉት ስድስት ወራት 13 ሺህ 504 ነጥብ 2 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል እንዲመነጭ አስችሏል። ይህም የዕቅዱን 15 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን ነው ወ/ሮ ጥሩወርቅ ያብራሩት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ጣቢያው የደበኞችን የኃይል ጥያቄ እየመለሰ ነው …..….///……….. የወልቂጤ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ከደንበኞች የሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎችን እየመለሰ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙጀረብ የኑስ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው ካለው 360 ሜጋ ዋት ኃይል ውስጥ 102 ሜጋ ዋት ኃይሉ ደንበኞችን ሲጠብቅ ቆይቷል፡፡ ጣቢያው ያለውን አቅም ለመጠቀም ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራው ሥራ አሁን ላይ እስከ 80 ሜጋ ዋት ኃይል የሚጠቀሙ ተጨማሪ ደንበኞችን ማግኘት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ ከኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች መካከል የቢተን ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ድርጅት ሱፐርቫይዘር ሚስተር  ጂየን ሊየን በበኩላቸው ከጣቢያው የጠየቁትን ኃይል በአጭር ጊዜ በማግኘታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ለሰጣቸው ፈጣን ምላሽ እና ላደረገላቸው ትብብር አመስግነው በቀጣይም በመካከላቸው የሚኖረውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+6

የማከፋፈያ ጣቢያውን ግንባታ እስከ መጪው ሐምሌ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን እስከ መጪው ሐምሌ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡   ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት የማከፋፈያ ጣቢያው ከቆቃ-ገላን ከተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ላይ በመቀጠል 14 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እና እያንዳንዳቸው ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው አራት ትራንስፎርመሮች እንዲኖሩት ተደርጎ እየተገነባ ነው፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ለማስቀመጥ የሚያግዙ ከ290 በላይ የመሠረት ቁፋሮና የኮንክሪት ሙሌት እንዲሁም የአራት ትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ ግንባታዎች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የሲቪል ሥራዎች ስለተጠናቀቁ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በመርሀ ግብሩ መሰረት ሳይት ከደረሱ ቀሪ የተከላ ሥራዎች በተያዘው እቅድ መሰረት እንደሚከናወን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑ ስለመሆናቸውም ጠቅሰዋል፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻፀም 48 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን የጠቆሙት አቶ ቴዎድሮስ ቀሪ የመንገድ፣ የመቆጣጠሪያ ክፍሉ ግንባታ እና የፍሳሽ ማስወገጃ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሚካኒካል ሥራዎችን የማካካሻ እቅድ በማውጣት ፕሮጀክቱን እስከ መጭው ሐምሌ 2017 ዓ.ም ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ባለስልጣን ለሚያስገነባው ስማርት ሲቲ በተለያዩ ምዕራፎች እንዲቀርብለት ከሚፈልገው 575 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ውስጥ ፕሮጀክቱ በመጀመሪያው ምዕራፍ 252 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የማከፋፈያ ጣቢያውን ጨምሮ 2 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ላለው የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ የሚያስፈልገው ወጪ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን እየተሸፈነ ነው። ፕሮጀክቱ ለ181 ዜጎች ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድሎች ፈጥሯል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም

አራተኛው የህብረት ስምምነት ድርድር ተጀመረ ……///….… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኞች ማህበርና በተቋሙ ሥራ አመራር መካከል የህብረት ስምምነቱን ለማሻሻል ድርድር መጀመሩን የህብረት ስምምነቱ ኮሚቴ ሰብሳቢ ገለፁ፡፡ ሰብሳቢው አቶ ደረጄ አጥናፌ እንደገለፁት የተቋሙንና የሠራተኛውን ጥቅምና መብት ባስጠበቀ መልኩ ሥራዎች እንዲሰሩ እና የኢንዱስትሪ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ በኩል የህብረት ስምምነቱ ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡ በሥራ ላይ ያለውን የህብረት ስምምነት ለማሻሻል አንቀፆችን ለመለየት ከተቋሙ ሥራ አመራር እና ከመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ተወካዮች የተውጣጣ ቡድን ድርድር መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ በድርድሩ በሥራ ላይ ባለው የህብረት ስምምነት ላይ የቅሬታ እና የአለመግባባት ምንጮች ሆነው አላሰራ ያሉ ጉዳዮች ካሉ በጥንቃቄ ታይተው እንደሚስተካከሉ ጠቁመዋል፡፡ ለቀጣይ ሶስት ዓመታት እንዲያገለግል እየተዘጋጀ ባለው የህብረት ስምምነት ላይ ሀሳብ አለኝ የሚል የሥራ ክፍል በሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት በኩል ሀሳቡን ሊያቀርብ እንዲሚችልም ሰብሳቢው ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀ መንበር እና የህብረት ስምምነት ድርድር ኮሚቴ አባል አቶ ዳንኤል ገ/ሚካኤል በበኩላቸው የህብረት ስምምነቱ የተቋሙን እና የሠራተኛውን መብት እና ጥቅም ያስጠበቀ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ግብዓቶችን በዘርፍ ተወካዮች እና በደብዳቤ መሰበሰቡን የገለጹት አቶ ዳንኤል በሦስተኛው ህብረት ስምምነት ያልተካቱቱ፣ በስራ ሂደትም እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮች በድርድሩ ሊታዩ ይችላሉ ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 19  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ባለፉት አስር ቀናት ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ለስርቆት ተዳርጓል ……..///…… ባለፉት አስር ቀናት ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦ.ፒ.ጂ ደብሊው ፋይበር መስመር ለስርቆት መዳረጋቸውን የአዋሽ - ወልዲያ - ሃራ ገበያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ቢሮ አስታወቀ። በቢሮው የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተክለወይን ብርሃነአሰፋ እንደተናገሩት ባለፉት አስር ቀናት ከመተሃራ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ ድረስ በቡድን በተደራጀ ሁኔታ 78 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ዝርፊያ ተፈጽሟል። ከባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ ሁለት ድረስ ደግሞ 2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ በዘራፊዎች መወሰዱንም ነው አቶ ተክለወይን የጠቆሙት። በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በዱዱብ እና ዶሆ ቀበሌዎች ሁለት ጊዜ እንዲሁም በዱለሳ ወረዳ በቡሩቱሊ እና ኢስኪለሊ ቀበሌዎች አንድ ጊዜ በተፈፀመ የስርቆት ወንጀል ሳቢያ ከ758 ሺህ ዶላር በላይ እና በብር ከ6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱን ተናግረዋል። የስርቆት ወንጀሉ የተፈፀመው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ወደ ሥራ እስኪገባ ድረስ በ33 እና 15 ኪሎ ቮልት በጊዜያዊነት ኃይል ይዞ እንዲቆይ ለማድረግ ከሥራ ተቋራጩ ጋር ምክክሮች እየተደረጉ ባሉበት ወቅት መሆኑ እንዳሳዘናቸውም ገልፀዋል። እንደ ሳይት ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ዝርፊያ ተፈፅሞባቸው በአይሱዙ መኪና ተጭነው ሲጓዝ የነበረ የኮንዳክተር ሽቦ በአዳማ ከተማ ላይ እንዲሁም በዱለሳ ወረዳ መቁረጫ ሴጌቶ ይዘው የተገኙ ሁለት ተጠርጣሪዎች ተይዘው ክስ ለመመስረት ማስረጃ እየተደራጀ ይገኛል። በኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ዙሪያ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከቀበሌ አመራሮች እንዲሁም ከፀጥታ ዘርፍ አካላት ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ ከ2 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ በዘራፊዎች መወሰዱን አብራርተዋል። በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ ላይ የተፈፀመው የስርቆት ወንጀል  እጅግ አስደንጋጭ ነው። በበጀት ዓመቱ በኦፕሬሽን ላይ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ይፈፀሙ የነበሩ የስርቆት ወንጀሎች መቀነሳቸውን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይሁን እንጂ በግንባታ ላይ ባሉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ስርቆቱ መቀጠሉን ተናግረዋል። በአዋሽ- ወልዲያ-ሃራ ገቢያ ላይ የተፈፀመው ዝርፊያ በሀገር ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና የሚያሳድር ከመሆኑም ባሻገር ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን ገልፀዋል። በጉዳዩ ላይ የገቢረሱ ዞን አስተዳደርን ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 19  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

🌍 Exploring Ethiopia's Diverse Energy Capacity 🌍 Ethiopia is expanding its energy sources to meet growing demand, advancing solar, wind, geothermal, and hydropower for a sustainable future. 🔹 Key Highlights: ✅ Hydropower – A major contributor to Ethiopia’s electricity supply ✅ Solar & wind energy – Unlocking new renewable opportunities ✅ Geothermal potential – Tapping into Ethiopia’s natural resources With a growing demand for electricity, Ethiopia is harnessing its rich renewable energy resources to strengthen its power sector. Watch the full video now: 👉 https://youtu.be/QqPeoay756Y Subscribe for more updates: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia "Empowering Ethiopia with Diverse Energy Solutions!" #Ethiopia #RenewableEnergy #SustainableDevelopment #Hydropower #SolarEnergy #WindPower #GeothermalEnergy #CleanEnergy #AfricaRising #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ዩትዩብ | ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ቲክቶክ | ድረ - ገፅ

የተቋሙ ሠራተኞች በመንግስት ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ዙሪያ ተወያዩ ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "ከቃል ወደ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ውይይቱ ሠራተኛው በጉባዔው በተቀመጡ ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ግንዛቤ በመጨበጥ ለተግባራዊነቱ እንዲሰራ ለማድረግ ነው። ፓርቲው መንግስትን የሚመራ እንደመሆኑ መጠን ሠራተኞችም የፓርቲውን ውሳኔዎችና ያስቀመጣቸውን የትኩረት አቅጣጫዎች በመረዳት  ሥራቸውን በዚሁ አግባብ ማከናወን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በመድረኩ ላይ በፓርቲው ሁለተኛ ጉባዔ በተቀመጡ ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የተዘጋጀ ሰነድ በንባብ ቀርቧል። ጠንካራ የፓርቲ ግንባታ፣ የብሔራዊነት ገዥ ትርክት ግንባታን ማጠናከር፣ ውጤታማ የሰላም ግንባታ ሥራ መስራት፣ የፍትህ ዘርፍ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የሀገር ግንባታን ማጠናከር እና የኢኮኖሚ ልማትን ማፋጠን የሚሉት በጉባዔው ከተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች መካከል መሆናቸው በሰነዱ ላይ ተመልክቷል። በተጨማሪም ማህበራዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በውጤታማነት ማስቀጠል፣ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራዎች መስራት፣ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ውጤታማነትን ማረጋገጥ እና ጠንካራ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ሥራዎችን መስራት የሚሉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች በፓርቲው መቀመጣቸውም ተገልጿል። በውይይቱ ላይ ከሠላም፣ ከተቋም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥ፣ ከልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ከፍትህ ሥርዓቱ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች በተሳታፊዎች ቀርበዋል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስ እና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በሰጡት ምላሽ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በመንግስት ፖሊሲና የፖለቲካ አቅጣጫዎች የሚመሩ መሆናቸውን ገልፀዋል። መንግስት የግጭት መንስዔዎችን ከምንጩ ለማድረቅና የሀገሪቱን ሀብት በፍትሐዊነት ለመጠቀም በትኩረት እየሰራ መሆኑን አቶ ደመረ ጠቅሰዋል። የሰላም ጉዳይ ለመንግስት ብቻ የተተወ ባለመሆኑ ሁላችንም ሰላምን ለማጽናት የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ነው ያሉት። በተቋሙ የትራንስሚሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ በበኩላቸው ገዢ ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት የጋራ መግባባት መፍጠር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል። መንግስት ከሰላም እጦት ጋር የተያያዙ ችግሮችን አካታች በሆነ መልኩ ለመፍታት ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የኢንጂነሪንግ እና ግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው ውይይት የተደረገበት ሰነድ የፓርቲ ብቻ ሳይሆን የመንግስት ሰነድ በመሆኑ፣ እንደዜጋ ማወቅና  በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት መፈፀም ስለሚጠበቅብን ነው ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 18  ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6