en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 696 subscribers, ranking 8 049 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 696 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 141 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 28.59%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.37% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 487 views. Within the first day, a publication typically gains 2 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 696
Subscribers
No data24 hours
+147 days
+14130 days
Posts Archive
ጉዳት ደርሶበት የነበረው የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ተጠግኗል .....///.....… በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቱሉቦሎ አካባቢ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የማስተላለፊያ መስመር እና ለግንኙነት የሚያግዘው ኦፕቲካል ፋይበር (OPGW) ተጠግኖ ወደ ሥራ መግባቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይበር ኦፕቲክስ የኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ገለፀ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ኤርሚያስ ገብረ መድህን እንደገለፁት የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮቹ ለኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መከላከያ ከመስጠት ባለፈ ለቴሌኮሙዩኒኬሽን ሥራዎች እንዲሁም ከኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መረጃዎችን ወደ ብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ለማድረስ ይረዳሉ። ከጊቤ ሁለት - ሰበታ ሁለት ባለው ባለ 400 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ላይ ተዘርግተው በሚገኙ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች በጉዳት ምክንያት አገልግሎቱ ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ ጉዳት በደረሰበት መስመር ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የፋይበር ኦፕቲክስ ተከራይተው ይጠቀሙ እንደነበር አቶ ኤርሚያስ አስታውሰዋል። በደረሰው ጉዳት የተነሳ አገልግሎቱ ተቋርጦ ጥገና ሳይደረግለት መቆየቱን እና የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከሉ ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች ያሉ መረጃዎችን መሰብሰብና መመልከት አለመቻሉን አብራርተዋል፡፡ የተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ መስመሩን ጠግኖ ወደ ሥራ ማስገባቱን ተናግረዋል፡፡ የጥገና ሥራው በጥቂት ቀናት እንዲጠናቀቅ እገዛ ያደረገውን ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አመስግነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ሪጅኑ የእንጨት ምሰሶዎችን በብረት ምሰሶ እየቀየረ ነው ……....///…..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን በስርቆት ምክንያት ወድቀው በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን በብረት ምሰሶዎች እየቀየረ መሆኑን ገለጸ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ደምሴ  እንደገለጹት በሪጅኑ በአዋሽ - አሰላ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈጸመ ስርቆት ምሰሶው ወድቆ ነበር። ሪጅኑ አገልግሎቱ እንዳይቋረጥ ለማድረግ የወደቁ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን በእንጨት በመተካት በጊዜያዊነት አገልግሎቱን ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰዋል። አሁን ላይ የአዋሽ - አሰላን የእንጨት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን በብረት በመቀየር ወንጂ ስኳር ፋብሪካ፣ አሰላ እና አካባቢው የሚገኙ ዞንና ወረዳዎች ከትናንት እኩለ ቀን ጀምሮ ያልተቆራረጠና አስተማማኝ ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን አስረድተዋል። ሪጅኑ በመቶ ቀን ዕቅዱ የአዋሽ - አሰላ የማስተላለፊያ መስመርን ጨምሮ ሌሎች በጊዜያዊ የእንጨት ምሰሶዎች አገልግሎት እየሰጡ ያሉትን የቆቃ - ቢሾፍቱ- ገላን እና ቃሊቲ ባለ 132 ኪሎ ቮልት እንዲሁም አዳማ ሁለት - አዋሽ 7 ኪሎ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመሮች በብረት ምሰሶ ለመቀየር እየሰራ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ሪጅኑ  የተቋረጡትን የመተሀራ - መልካ ጅሎ የባቡር መስመር እና ቃሊቲ - ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመሮች  ወደ ኦፕሬሽን እንዲገቡ ለማድረግ  እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የይርጋለም ቁጥር ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የምሽት ገጽታ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራ
+6
የይርጋለም ቁጥር ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የምሽት ገጽታ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

#EidAlAdha 🕋✨ ለተቋማችን የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የመረዳዳት እንዲሆንላችሁ እ
#EidAlAdha 🕋✨ ለተቋማችን የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የመረዳዳት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦቱ ለከተሞች የኢንዱስትሪ  ዕድገት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው ……….///……… የኃይል አቅርቦት አስተማማኝ መሆንና የተደራሽነቱ መስፋት የከተሞችን ሁለንተናዊ ዕድገት እያፋጠነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን መምሪያ ዳይሬክተር ገለፁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገነባቸውና የሚያስተዳድራቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች  ለኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ በሪጅኑ ውስጥ በሚገኙት በአዳማ ፣ በቢሾፍቱ፣ በሞጆና በዱከም ከተሞች ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለሀገር ኢኮኖሚዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ ኢንዱስትሪዎች ቁጥር እንዲጨምር ምክንያት የሆነው የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝነት ማደግ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አቶ አለማየሁ ገለፃ በሪጅኑ ውስጥ በሚገኙ ከተሞች  አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት መኖር ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል እንዲፈጠር እና  የኑሮ ዘይቤ እንዲስተካከል  መነቃቃትን ፈጥሯል፡፡ ለህብረተሰቡና ለኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ ከፍተኛ አቅም ያላቸው ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ከአዲስ አበባ እስከ መተሃራ ድረስ ተገንብተው አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጡ ነው ብለዋል፡፡ ዱከም ኢስት ኢንዱስትሪ፣ የሱ ብረታብረት፣ ሲ እና ኢ ብራዘርስ ፣ካኖሪያ ጨርቃ ጨርቅ ፣ ጆርጅ ሹዝ እና ወንጂ ስኳር ፋብሪካ በማዕከላዊ 2 ሪጅን ወስጥ ከሚገኙ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንደስትሪዎች መካከል እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ የደንበኞችን እርካታ ከማሳደግ ባለፈ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት  የሪጅኑ የአሰራር ጥንካሬዎች መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎች ለሕግ ቀርበዋል ….....///…...... በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ 27 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ለሕግ ማቅረቡን የቢሾፍቱ የከተማ አስተዳደር ገለፀ። የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ገዛኸኝ ደጀኔ እንደገለፁት ከተማዋ ከፍተኛ የኃይል አቅርቦት የሚፈልጉ በርካታ የብረታ ብረትና ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች መገኛ ናት፡፡ የኃይል መሰረተ ልማቶች በባህሪያቸው ለጥቃት የተጋለጡ በመሆናቸው እና በሚደርስባቸው ጉዳት አገልግሎቱ ቢቋረጥ በከተማዋ ነዋሪዎችና በፋብሪካዎች ላይ ከፍተኛ ኪሳራ የሚያደርስና የከተማዋን ዕድገት የሚያቀጭጭ ነው ብለዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ የቴሌኮሙኒኬሽንና የኤሌክትሪክ አውታሮችን ደህንነት ለመጠበቅ በወጣው አዋጅ መሰረት በአካባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት ተገንዝቦ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በ2017 በጀት ዓመት አስር ወራት ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት በኃይል መሰረተ ልማት ላይ ጉዳት ያደረሱ 27 ተጠርጣሪዎችን ለሕግ መቅረባቸውን ገልፀዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በሠራቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራትና በአጥፊዎች ላይ በሚወስደው የተጠናከረ እርምጃ አሁን ላይ በአካባቢው የነበሩ ችግሮች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መቀረፋቸውን ገልጸዋል። የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን የመጠበቁ ኃላፊነት ለአንድ ተቋም ወይም ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆኑ በቀጣይ ሕዝቡን በማሳተፍ መስራት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስረድተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

በኃይል ዘርፉ ያሉ ችግሮችን የሚያቃልሉ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን እያከናወንኩ ነው - ዩኒቨርስቲው ........///…….. በኢትዮጵያ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ከማድረግ አንጻር ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የጥናትና ምርምር ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የአዳማ ሣይንስና ቴክኒዮሎጅ ዩኒቨርስቲ ገለፀ። በዩኒቨርስቲው የኤሌክትሪካል ምህንድስና እና ኮምፒውቲንግ ኮሌጁ ምክትል ዲን መስፍን መገራ እንደገለጹት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ዓለም አቀፍ መለኪያ እየሆነ መጥቷል፡፡ ዘመኑ ያለ ኤሌክትሪክ ኃይል ምንም ዓይነት አገልግሎት መስጠትም ሆነ ማግኘት የማይታሰብበት በመሆኑ ከተሞችና ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት እና ግብርናን በማዘመን የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ የፋይናንስን አገልግሎቶችን ለማሳለጥ እና መረጃዎችን ለመለዋወጥ እንዲሁም መሠረታዊ የሕዝብ ፍላጎቶችን ተደራሽ ለማድረግ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት አስፈላጊ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያም እንደሀገር ያሉ ሀብቶቿን አሟጣ በመጠቀም ሁሉን አቀፍ ዕድገት ለማስመዝገብ እና የማህበረሰቡን ሕይወት ለማዘመን ታዳሽ ኃይል አቅርቦት ላይ ትኩረት ሰጥታ በርካታ ተግባራትን እያከናወነች እንድምትገኝ አብራርተዋል። እንደ አቶ መስፍን ገለፃ ባለፉት ዓመታት ኃይል በማመንጨት ከሀገር ውስጥ አልፎ የጎረቤት ሀገራትን በማስተሳሰር በኩል የተሻሉ ውጤቶች ቢመዘገቡም ሁሉንም የሀገሪቱን አካባቢ ተደራሽ ከማድረግ አንፃር ያሉ ውስንነቶችን መፍታት ይገባል፡፡ የአዳማ ሳይንስና ቴክኒዮሎጅ ዩኒቨርስቲ በኃይል ዘርፉ ላይ እንደሚሳተፍ የትምህርት ተቋም ቀደም ሲል በአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታ ላይ ከሌሎች አካላት ጋር በመሆን የማማከር ሥራ ላይ መሳተፉን ጠቁመዋል፡፡ ዩኒቨርስቲው ከዋናው ግሪድ ራቅ ባሉ የገጠር አካባቢ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ፀሐይን በመጠቀም በሶላር ኃይል በሚያገኙበት አማራጭ ላይ ሲሰራ መቆየቱን አውስተዋል፡፡ ዩኒቨርስቲው በኃይል ማመንጨትና በስብጥሩ ዙሪያ ያሉ ክፍተቶች በሚሞሉበት ዙሪያ ጥናትና ምርምሮችን እየተሰሩ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ ዘርፉን ይበልጥ ለማዘመን እና የኃይል አማራጮችን በማስፋት እንዲሁም የኃይል ብክነትን በመቀነስ ከግሪድ ውጭ የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ተግባራዊ በሚሆኑበት ዙሪያም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅቶ እንደሚሰራ ገልፀዋል። ዩኒቨርስቲው በቀጣይ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በጥናትና ምርምር እንዲሁም በአቅም ግንባታ ሥራዎች ዙሪያ ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የሁለቱ ተቋማት የኮሙዩኒኬሽን የሥራ ክፍሎች በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ ……...///……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን የሥራ ኃላፊዎች በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ለውይይቱ የመነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት የሁለቱ ተቋማት የአብሮነት ጉዞ አንድ ምዕተ ዓመትን የተሻገረ ነው። ተቋማቱ ወደ ሁለት ከተከፈሉበት ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የኮሙኒኬሽን የሥራ ክፍሎች የተቋማቱን ገጽታ ከመገንባት እና ከመረጃ አሰጣጥ ጋር ተያይዞ በርካታ ሥራዎች ማከናወናቸውን ገልጸዋል። ይሁንና ከቃላት አጠቃቃም እና ተቀናጅቶ ከመስራት አንጻር ክፍተቶች መኖራቸውን ያነሱት አቶ ሞገስ በቀጣይ የጋራ የግንኙነት ጊዜ በማስቀመጥ የታዩ ችግሮችን መቅረፍ እና በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ ተናቦ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዋር አብራር በበኩላቸው ሁለቱ ተቋማት የሚሰሩት ሥራ ተመጋጋቢ በመሆኑ የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማጠናከር እና ችግሮችን በማረም በጋራ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። አላስፈላጊ መሳሳቦችን በማስወገድ የመረጃ ልውውጡን ማዘመን፣ የጋራ የውይይት መድረኮችን መፍጠር እና ችግሮችን በየጊዜው እየለዩ የጋራ መፍትሄ ማስቀመጥ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱ ተቋማት የኮሙዩኒኬሽን የሥራ ክፍሎች እስከ አሁን የነበሩ ችግሮችን በሚቀርፍ መልኩ አብረው መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ኮሚቴ አዋቅረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ተቋሙ የከተማዋን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ አድርጎ እንዲሰራ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቀረበ ........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቢሾፍቱ ከተማን የወደፊት የኃይል ፍላጎት ታሳቢ አድርጎ የኃይል መሰረተ ልማቶችን እንዲገነባ የከተማ አስተዳደሩ ጠየቀ። የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ገዛኸኝ ደጀኔ እንደተናገሩት ከተማው 63 ሺ ሄክታር የሚሸፍን ስፋት ያለው ሲሆን አሁኑ ወቅት በከተማው 2 ሺ 200 አካባቢ ኢንቨስትመንቶች ይገኛሉ። ከዚህ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው የማኑፋክቸሪንግ ኢንደስትሪው መሆኑንና በዘንድሮው በጀት ዓመት ከ250 በላይ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን እንዲሁም ነባሮቹ ትልልቅ የማስፋፊያ ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህም ለአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ የሥራ ዕድልን እየፈጠረ ነው ያሉት ምክትል ከንቲባው ለአብነትም ኢንቨስትመንት በመኖሩ ብቻ በዚህ ዓመት 62 ሺ ለሚሆኑ ወጣቶች በቋሚነት የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰዋል። እንደ ምክትል ከንቲባው ገለፃ ፋብሪካዎቹ የሥራ ዕድል ከመፍጠር በተጨማሪ ከውጭ የሚገባውን ምርት በመተካት፣ የውጭ ምንዛሬን በማዳንና የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር እንዲኖር በማድረግ የጎላ ሚና አላቸው። የብረታ ብረት ፋብሪካዎችን ጨምሮ አብዛኛዎቹ በከተማዋ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ የኃይል አቅርቦት የሚጠይቁ ቢሆንም ተቋሙ ቀደም ብሎ ባከናወነው ሥራ አሁን ላይ የኃይል አቅርቦት ችግር አለመኖሩን አንስተዋል። የከተማ አስተዳደሩ ዘመናዊ የግብርና ሥራን ለማስፋፋት፣ አምራች ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ እና ከተማዋን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ አቅዶ እየሰራ ነው ያሉት አቶ ገዛኸኝ በ5 ዓመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ትልቁ የአየር ማረፊያ በከተማዋ ወደ ግንባታ መግባቱን ገልጸዋል። በዚህም በየዓመቱ ከ110 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ወደ ከተማዋ ይመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅና ይህን ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችና ወደ ከተማዋ እየመጡ ያሉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎችን አሁን ላይ ባለው የኃይል አቅርቦት ለማስተናገድ የሚቻል አለመሆኑን ከማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ውይይት መረዳታቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በከተማዋ በቀጣይ ዓመታት ሊኖር የሚችለውን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ ሥራ ቀድሞ እንዲያከናውን ምክትል ከንቲባው ጠይቀዋል። ለዚህም ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግና ከተቋሙ ጋር ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው .....….///…...... የደጀን-ደብረማርቆስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ሥራ ከ87 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ፕሮጀክቱ አስታወቀ፡፡ በፕሮጀክቱ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራ አስኪያጅ አቶ እንዳለ ላቀው እንዳስታወቁት የመስመር ዝርጋታው የደጀን ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል ነው፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ 48 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው የደጀን-ደብረማርቆስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር 111 የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች አሉት፡፡ በአሁኑ ወቅት የ110 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች የመሠረትና የኮንክሪት ሥራ እንዲሁም የ106 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች የተከላ ሥራ መጠናቀቁን ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰው ቀሪ የመሠረት እና ተከላ ሥራዎች በቅርቡ እንደሚጠናቀቁ ነው የገለፁት፡፡ በ55 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የኮንዳክተር ዝርጋታ መከናወኑን የገለፁት አቶ እንዳለ በቀሪ 56 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ኮንዳክተር ለመዘርጋት ከወዲሁ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ሥራው በራስ አቅም እየተከናወነ በመሆኑ ከፍተኛ ወጪ ማዳን መቻሉን የጠቀሱት አቶ እንዳለ በዝርጋታ ሥራው ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ ሠራተኞች የዕውቀትና ልምድ ሽግግር እንዲያገኙም ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል፡፡ የደጀን- ደብረማርቆስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክት ከ73 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበለት ሲሆን የፋይናንስ ወጪውም ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሸፈን ነው፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱን እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ነው አቶ እንዳለ የጠቆሙት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የምስራቁን ግሪድ የኃይል ፍሰት ለማመጣጠን እየተሰራ ነው ….....///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቁን ግሪድ የኃይል ፍሰት ለማመጣጠን የሚያስችሉ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ማስተባበሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት እስከ ጅቡቲ ያለው የምስራቁ ኮሪደር የኃይል ፍሰት በጣም የተጨናነቀ ነው። ችግሩን ለመቅረፍ የአደጋ ጊዜ የከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን (emergency restoration tower) ወደ ሥራ በማስገባት ቀደም ሲል የተጨናነቁ መስመሮችን አነስተኛ የኃይል ፍሰት ወደሚገኝባቸው መስመሮች በማዘዋወር እና ከአገልግሎት ውጭ የነበሩ መስመሮችን ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። የአደጋ ጊዜ የከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በተለያየ ምክንያት የሚወድቁ የብረት ምሰሶዎችን በአጭር ጊዜ ለመተካት የሚኖራቸው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ወደ ሥራ እንዲገቡ አቅጣጫ መቀመጡን አስረድተዋል። በቢሾፍቱ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ያላለቁ ሥራዎች የነበሩ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በማከፋፈያ ጣቢያ ሰርኪዩቶችን ለማገናኘት የሚያገለግለው የቤይ እጥረት በመኖሩ ምክንያት አገልግሎት ሳይሰጥ የቆየ መስመር መኖሩን አቶ ተስፋዬ አንስተዋል። ከፍተኛ የኃይል ጭነት የሚታይበትን የገላን ቆቃ መስመር ኃይል ለማመጣጠን ከቢሾፍቱ 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል እንዲያገኝ ለማስቻል የአደጋ ጊዜ የብረት ምሰሶዎች ጣቢያው ውስጥ የመትከል ሥራው ዛሬ ይጀመራል ብለዋል። እንደ አቶ ተስፋዬ ገለፃ በአዋሽ 7 በአደጋ ምክንያት የወደቁ ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ለመተካት ጊዜ የሚወስድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የአደጋ ጊዜ የብረት ምሰሶዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በመትከል በመስመር ላይ የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት ታቅዷል። የእውቀት ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ የተከላ ሥራው ከሁሉም ሪጅን በተውጣጡ የጥገና ባለሙያዎች፣ በዋናው መ/ቤት መሐንዲሶች እንዲሁም የሰርቬይና የትራንስሚሽን ዲዚይን ባለሙያዎች እንደሚከናወን ተናግረዋል። ይህም የምስራቁን ግሪድ የኃይል ፍሰት ከማመጣጠን በተጨማሪ ከኢስት የኢንዱስትሪ ዞንና ከገዳ ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ ላለው የኃይል ፍላጎት ለሟሟላት በቂ ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን አቶ ተስፋዬ አብራርተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5