es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 572 suscriptores, ocupando la posición 8 384 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 165 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 572 suscriptores.

Según los últimos datos del 23 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 0, y en las últimas 24 horas de -2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.89%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.48% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 026 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 408 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 24 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 572
Suscriptores
-224 horas
-37 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
photo content
+2

ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ፈጥሯል  ….....///…..… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ ሁለትና ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 50 ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን የጣቢያዎቹ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው አበበ እንደገለፁት ጣቢያዎቹ እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ኖሯቸው  ከ60 ዓመት በፊት በ60 ሚሊዮን ብር ተገንብተው አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ናቸው። ጣቢያው በሁለት ማህበራት የተደራጁ 50 የሚሆኑ የአካባቢው ወጣቶችን በጥበቃ ሥራ ላይ በማሰማራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ይህም የጣቢያውን ደህንነት በአግባቡ ለማስጠበቅ ከማገዙም ባለፈ የአካባቢው ማህበረሰብ በጣቢያው ላይ ያለውን የባለቤትነት ስሜት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል። የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አቶ ወርቁ ቱፋ እንደገለፁት በማህበራቸው የታቀፉት 25 ሰዎች በጣቢያው ሥራ ከመጀመራቸው በፊት አባላቱ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር ትልቅ ፈተና ነበር። በማህበር ተደራጅተው በጣቢያው በተፈጠረላቸው የሥራ ዕድል ለሁለት ዓመት አካባቢ መስራታቸውን የጠቆሙት አቶ ወርቁ በዚህም ራሳቸውን ጨምሮ አራት ቤተሰቦቻቸውን ለማስተዳደር የሚያስችል ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እንደረዳቸው ተናግረዋል፡፡ ሌላኛው የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መጋቢ ሃምሳ አለቃ በቀለ ገዳ በበኩላቸው ከሠራዊት ተመላሽና እና የተሰው አባላትን ቤተሰብ ይዞ የፅዳትና ጥበቃ አገልግሎት የሚሰጥ ማህበር እንዳላቸው ጠቁመዋል። በጣቢያው ሥራ ከመጀመራቸው በፊት ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር ይቸገሩ የነበሩት መጋቢ ሃምሳ አለቃ በቀለ፤ ጣቢያው በፈጠረላቸው የሥራ ዕድል ከአካባቢያቸው ሳይርቁ ሰባት ቤተሰባቸውን እያስተዳደሩና ልጆቻቸውን እያስተማሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጣቢያዎቹ ለ25 የማህበሩ አባላት በጥበቃ አገልግሎት የሥራ ዕድል  በመፍጠራቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ነው ……..///……. የቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ መሆኑ አስታወቀ። የማመንጫ ጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ያፌት ተስፋዬ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው የምስራቁን የሀገራችን ክፍል ከዋናው ግሪድ ጋር የሚያገናኝ ነው። እንደ አቶ ያፌት ገለጻ ጣቢያው ከመልካ ዋከና፤  ከአዳማ ንፋስ ኃይል ማመንጫ እና ከቃሊቲ ኃይል በመቀበል ለሁርሶ፣ ለአዳማ እና ለቃሊቲ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚሰጥ በመሆኑ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የማመንጫ ጣቢያው በዕቅድ ላይ የተመሰረተ የጥገናና የፍተሻ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ጣቢያው ሲመሰረት ሰው የማይቆጣጠረው የነበረ ቢሆንም ዕድሜው እየገፋ ሲሄድ ግን የሠው ኃይል በመፈለጉ የማመንጫ ጣቢያው ያሉትን የኦፕሬሽን አና የጥገና ሠራተኞች በመመደብ ጭምር የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ከመስጠቱ ጋር ተያይዞ የማዘመንና የማስፉፊያ ሥራ የሚያስፈልገው መሆኑንም ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ……..///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን  አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንዳስታወቁት በሪጅኑ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው ስምንት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና 1 ሺ 180 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመሮች አሉ። በሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ከ2016 በጀት ዓመት ጀምሮ በአምስት የማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማዘመን ሥራዎችን ለማከናወን ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አብራርተዋል። በዚህም በወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ በ 33 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያ ወይም ብሬከር  እና በሆሳዕና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ዘመናዊ የጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ ቅየራ ቅየራ መከናወኑን ተናግረዋል። በወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ የባለ 15 ኪሎ ቮልት እንዲሁም በሀላባና ሳውላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን በዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች ለመቀየር እየተሰራ መሆኑንም አቶ ምትኩ ጠቁመዋል። ከመቆጣጠሪያ ቅየራው በተጨማሪ በብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አማካይነት በነባሮቹ የወላይታ ሶዶ ሁለተኛ እና አርባምንጭ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማስፋፊያ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አብራርተዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከማስፋፊያ ሥራው ጎን ለጎን በፕሮጀክቱ አርባ ምንጭ 2ኛን ጨምሮ ሽግዳንና ቲርጋ ላይ የሚገነቡ ሦስት አዳዲስ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ እንዲሁም የ424 ኪሎ ሜትር የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ እየተከናወነ ነው። ይህም በሪጅኑ ያለውን የኃይል ተደራሽነት በዘላቂነት ለማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይም የተጠናከረ የፍተሻ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አቶ ምትኩ ገልጸዋል። በሪጅኑ የተጠናከረ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች እንደሚከናወኑ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ለዚህም የባለሙያዎችን አቅም ለመገንባት በማዕከል እንዲሁም በሪጅኑ አቅም የተለያዩ አጫጭርና የሥራ ላይ ሥልጠናዎች እንደሚሰጡ አብራርተዋል። በኃይል መሠረተ ልማቱ ውስጥ የሚተከሉ ዛፎችና የሚገነቡ ቤቶች እንዲሁም የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት ለሪጅኑ ፈተና እንደሆኑበትም ጠቅሰዋል። ችግሩን ለመከላከል የሚመለከታቸው የጸጥታና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ህብረተሰቡ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የትውውቅ መርሃግብር አካሄዱ ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች የተሳተፉበት የተቋማቱ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የእርስ በእርስ ትውውቅ የትውውቅ መርሃ ግብር አካሄደ፡፡ በተቋማቱ የተደረገውን ሪፎርም ተከትሎ የተመደቡ የሥራ ኃላፊዎችን እርስ በእርስ ለማስተዋወቅ ትናንት ምሽት በተዘጋጀ መርሃግብር ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት በመተጋገዝና ተቀራርቦ በመሥራት በዘርፉ የሚነሳውን ችግር በጋራ መፍታት ይቻላል፡፡ ግንኙነቱ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን እርካታ በሚያሳድጉ ጉዳዮች ላይ ጌዜ ሳይጠብቁ ለመነጋገር ዕድል የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ  ገረመው በበኩላቸው የሁለቱ ተቋማት ግንኙነት ኃይል ከመሸጥና ከመግዛት ያለፈ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ እንደዚህ ዓይነት የግንኙነት መድረኮች የበለጠ የሚያቀራርቡ እና ፈጣን መፍትሔ ለመስጠት የሚያግዙ በመሆናቸው በመደበኛ አሰራሮች ታግዘው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

ጣቢያው ኃይል የማስተላለፍ ታሪካዊ ሚናውን እየተወጣ ነው ……..///…...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቃሊቲ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል በማስተላለፍ የነበረውን ታሪካዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ እጅጉ ማሬ እንደገለጹት ማከፋፈያ ጣቢያው በሁለት ትራንስፎርመሮች በባለ 132 ኪሎ ቮልት ሦስት ገቢ መስመሮች ከቆቃ የመነጨውን ኃይል ተቀብሎ ለአቃቂ፣ ለጎፋ እና በጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች ኃይል ለማስተላለፍ በ1950 ዎቹ የተገነባ ነው። ጣቢያው የትራንስፎርመሮችን ቁጥር በማሳደግ ከቆቃ በተጨማሪ  በ 230 ኪሎ ቮልት ከመልካ ዋከና የኃይል ማመንጪ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ ለገፈርሳ፣ ለኮተቤ፣ ለአዲስ ሴንተር እና ለሰበታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በባለ 132 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ኃይል ሲሰጥ እንደነበረም ጠቁመዋል። የኃይል ማመንጫዎች በየጊዜው እያደጉ መምጣታቸውን ተከትሎ የትራንስፎርመሮቹ ቁጥር በመጨመር  የመጫን አቅማቸውን ከ63 ሜጋ ቮልት አምፔር ወደ 125 ሜጋ ቮልት አምፔር ከፍ መድረጉንም ተናግረዋል። እንደ አቶ እጅጉ ገለጻ ጣቢያው አሁን ላይ በ 230 ኪሎ ቮልት አራት ገቢ መስመሮች፣  በ 132 ኪሎ ቮልት አስር፣ በ 45 ኪሎ ቮልት አንድ፣ በ 33 ኪሎ ቮልት አራት እንዲሁም በ 15 ኪሎ ቮልት አምስት ወጪ መስመሮች ሲኖሩት በአዲስ አበባ ዙሪያ ላሉት አብዛኞቹ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እየሰጠ ይገኛል ብለዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው ታሪካዊ ሚናውን መወጣት በሚያስችል መልኩ የኃይል ፍላጎቱን ታሳቢ ያደረገ የአቅም ማሳደግ እና የማዘመን ሥራዎችን ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ስለመሆኑም ተናግረዋል። የቃሊቲ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ በአሁኑ ወቅት 510 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በጣቢያዎቹ የኃይል ምርቱን አስተማማኝነት የሚጨምሩ የጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል ….....///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ 2 እና 3 የውሃ ኃይል ማመንጫዎችን የኃይል ምርት አስተማማኝነት የሚጨምሩ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸው ተገለጸ። የጣቢያዎቹ የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሮቤል አበበ  እንደገለጹት በማመንጫ ጣቢያዎቹ የቅድመ መከላከል፣ የትንበያ እና የፍተሻ ጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም በማከናወን ዩኒቶቹ የአቅማቸውን ከ95 በመቶ በላይ ኃይል እያመረቱ ይገኛል። የአዋሽ ሦስት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ብሬከርን በመቀየር ቆሞ የነበረው ተርባይን እንዲሰራ በማድረግ የኃይል ምርቱን አስተማማኝነቱን ማስጠበቅ መቻሉን ገልፀዋል። በአዋሽ ሁለት ጣቢያ ከአሁን ቀደም የነበሩ መቆጣጠሪያ ብሬከሮች ረጅም ጊዜ ያገለገሉና የተለያዬ ጉዳት የደረሰባቸው እንደነበሩ የጠቆሙት አቶ ሮቤል ከአዋሽ 7 ኪሎ ዲዝል ጣቢያ የነበረን ብሬከር በማምጣት ተከላ ተጠናቆ የሙከራና የፍተሻ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በተጨማሪም ለአካባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ባለ 15 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያ ብሬከሮችን ሙሉ በሙሉ በአዲስ በመቀየር ወደ አገልግሎት ማስገባት መቻሉንም አብራርተዋል። የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸው ጣቢያዎቹ ለረጅም ዓመት አስተማማኝ ኃይል እንዲያመርቱ ከማስቻሉም በላይ ጊዜንና ወጪን በመቆጠብ የሠራተኞች ቡድናዊ ስሜት እንዲጠነክር እና እርስ በእርስ ልምድ በመለዋወጥ አቅማቸውን የሚያጎለብቱበትን ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል። የአዋሽ 2 እና 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው አበበ በበኩላቸው ጣቢያዎቹ 64 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ኖሯቸው ከ60 ዓመት በፊት ኦፕሬሽን ቢጀምሩም ዛሬም ከ56 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እያመነጩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ጣቢያዎቹ የተሰሩት የቆቃ ኃይል ማመንጫ ግድብን ተከትለው በመሆኑ ከቆቃ በሚለቀቀው የውሃ መጠን የበጀት ዓመቱን የኃይል ምረት እቅድ ለማሳካት እየሰራ ነው። ተርባይኖች እንዳይቆሙ ዕቃዎች ላይ ማሻሽያ በመስራት በራስ አቅም በርካታ የጥገና ሥራዎችን እየተሰሩ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ጌታቸው ጣቢያዎቹ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የመልሶ ግንባታ ሥራ የሚፈልጉ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። የጥገና ሥራዎችን በአግባቡ ለማከናወን ባለሙያዎቹ አጫጭር የሥራ ላይ ሥልጠናዎች እንዲያገኙ በማድረግ የእርስ በእርስ መማማሪያ ሥርዓት መዘርጋቱም ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የማከፋፈያ ጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት ተጠናቋል ……....///…….... የመቱ ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ አሸናፊ ሙሉብርሃን እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው ከዓለም  ባንክ በተገኘ 7 ሚሊዮን ዶላር ብድር  እና ተቋሙ በመደበው አንድ ቢሊየን ብር  ለማሻና ለአካባቢው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በማድረጉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን የኃይል ትስስር ለማሳለጥ ህዳር 2012 ዓ.ም ነበር ግንባታው የተጀመረው። የማከፋፈያ ጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራ ትናንት በስኬት ተጠናቆ በዛሬው ዕለት ትራንስፎርመሩን ሥራ የማስጀመር ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 50 ሜጋ ቮልት አምፔር የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እንዲሁም ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት ተናግረዋል፡፡ አካባቢው በተፈጥሮ ሀብት የታደለ ቢሆንም ለረጅም ጊዜ የመብራት አቅርቦት ባለመኖሩ ነዋሪዎቹ የሀብቱ ተጠቃሚ ሳይሆኑ ቆይቷል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ሥራ መጀመር የማሻ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ በማድረግ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን እንደሚያነቃቃ አስረድተዋል። የመቱ ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታውን ሲኖ ሃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን በአማካሪነት ደግሞ ኢ. ኤል. ሲ. ELC የተባለ የጣሊያን ኩባንያ ተሳትፎበታል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+3

ግድቡ በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ኃይል ለማሳካት የሚያስችል ውሃ ይዟል ……...///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቆቃ የውሃ  ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ በ2017 በጀት ዓመት ለማመንጨት የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል የውሃ መጠን መያዙን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሞርካ ኃይሌ እንደገለጹት ከአባ ሳሙኤል ቀጥሎ በ1952 ዓ.ም ሥራ የጀመረው የቆቃ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላለፉት 65 ዓመታት አስተማማኝ ኃይል እያመረተ ይገኛል። ማመንጫ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት 134 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት አቅዶ በ9 ወራት ውስጥ 119 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል ማምረቱን ጠቁመዋል። ከግድቡ የሚለቀቀው ውሃ በሕብረተሰቡ ላይ የጎርፍ አደጋ እንዳይደርስ እንዲሁም ከማመንጫው በታችኛው ተፋሰስ ለሚገኙ ሰፋፊ የእርሻ ልማቶች የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን ለመልቀቅ በግድቡ የሚገኘው ውሃ በውሃና ኢነርጅ ሚኒስቴር እና በአዋሽ ተፋሰስ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግበት ገልጸዋል። አሁን ላይ በግድቡ ያለው የውሃ መጠን ከባህር ጠለል በላይ 1586 ነጥብ 68 ሜትር ሲሆን ባለፈው በጀት ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ከባህር ጠለል በላይ 1587 ነጥብ 01 ሜትር እንደነበር አውስተዋል። በግድቡ ውስጥ የሚገኘው የውሃ መጠን ጣቢያው በቀሪ ወራት ያለምንም የውሃ እጥረት ኃይል እንዲያመነጭና ዓመታዊ ዕቅዱን እንዲያሳካ የሚያስችለው መሆኑን አቶ ሞርካ ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ዕቅዱን ለማሳካት ከውሃ አስተዳደር ሥራው ጎን ለጎን ሣምንታዊና ወርሃዊ የጥገና ሥራዎች በዕቅድ ተይዘው በመከናወን ላይ ናቸው። ጣቢያው ከ65 ዓመታት በኋላም ሲገነባ ከተቀመጠለት 110 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ አማካይ ዓመታዊ የኃይል ምርት እያመረተ መሆኑን ገልፀው ለዚህም የኦፕሬሽንና የጥገና ክፍሉ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። ከ25 ዓመት በፊት በኤሌክትሮ ሜካኒካል ክፍሉ ላይ የመልሶ ግንባታ ሥራ መከናወኑን የጠቆሙት አቶ ሞርካ አሁንም ጣቢያው ረጅም ዓመት ከማገልገሉ ጋር ተያይዞ በተለያዩ ክፍሎች ላይ የመልሶ ግንባታ ሥራ እንደሚያስፈልገው አመልክተዋል። የግድቡን ደህንነት ለመጠበቅና የእምቦጭ አረምን ለመከላከል ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ በዕቅድ ተይዞ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የቆቃ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በሦስት ተርባይን 43 ነጥብ 2 ሜጋ ዋት የማምረት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል:: ኢድ ሙባረክ!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል:: ኢድ ሙባረክ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ.ም

የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ 65 በመቶ ደርሷል ……..///………. የደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የንባታ አጠቃላይ አፈፃፀም 65 በመቶ ላይ መድረሱን በፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ሱፐርቫይዘር ተናገሩ። ሱፐርቫይዘሩ አቶ ተመስገን ጥላሁን እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ ከወላይታ ሶዶ 2ኛ እና በግንባታ ላይ ከሚገኘው የሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሁለት ገቢ መስመሮች ኃይል ተቀብሎ በአስር ባለ 33 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ለደንበኞች ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ ይገኛል። ማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት የባለ 125 አውቶ ትራንስፎርመሮች፣ ሁለት ባለ 63 እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች የተከላና ገጠማ ሥራዎች እንዲሁም ዘይት የመሙላት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች መትከያ፣ የፕሮቴክሽንና ሌሎች የኮሙዩኒኬሽኝ ገመዶች የሚዘረጉበት የመሠረት ሥራ እንዲሁም የ230 እና 132 ኪሎ ቮልት የሲዊች ያርድ የስቲል ስትራክቸር ተከላ ሥራዎች ሲጠናቀቁ የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የስቲል ስትራክቸር ሥራ ደግሞ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚኙ አቶ ተመስገን አስታውቀዋል። የመቆጣጠሪያ ቤቱ የግንባታ ሥራ 80 በመቶ የደረሰ  ሲሆን የኦፕሬተሮች የመኖሪያ ቤቶች የግንባታ ሥራ እየተፋጠነ እንደሆነም ተናግረዋል። የመቆጣጠሪያ ክፍሉንና የፕሮቴክሽን ፓናሎች ገጠማና ገመድ ዝርጋታ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን፣ የፍተሻና ሙከራ እንዲሁም ሌሎች የተጀመሩ ቀሪ ሥራዎችን በቀጣዮቹ ስምንት ወራት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማብቃት ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነ ሱፐርቫይዘሩ አስረድተዋል። እንደ ሱፐርቫይዘሩ ገለፃ የፕሮጀክቱ  የሲቪል ሥራ 68 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ 40 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ አፈፃፀሙ ደግሞ ከ65 በመቶ በላይ ደርሷል። በአካባቢው ያለውን ግሪድ ስርዓት ለማጠናከር የማከፋፈያ ጣቢያውን ከአርባ ምንጭ 1ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር ለማገናኘት የሚያስችል የማስፋፊያ ሥራ በነባሩ ላይ  መጀመሩንም ጠቁመዋል። ከ37 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተከናወነ የሚገኘው የአርባ ምንጭ 2ኛ  ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በከተማዋ አካባቢ ሊገነባ ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንደስትሪ ፓርክ እና በ120 ኪሎ ሜትር ውስጥ ለሚገኙ አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 19 ቀን 2017 ዓ.ም