en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 679 subscribers, ranking 8 053 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 679 subscribers.

According to the latest data from 05 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 112 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.83%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.95% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 050 views. Within the first day, a publication typically gains 2 501 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 679
Subscribers
-1224 hours
-127 days
+11230 days
Posts Archive
የጨረታ ማስታወቂያ …………/……………. የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር /EEP/DS/01/17 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለተለያዩ አገልግሎት ሊውሉ የሚችሉ ንብረቶችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ለመሸጥ እንደሚከተለው በሎት በመከፋፈል አቅርቧል፤ ሎት-1- 08(ስምንት) ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች፤ቦታ ኮተቤ አካባቢ ብረታ ብረት ፊት ለፊት ከሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ግቢ፤ ሎት-2- ለተቋማችን አገልግሎት የማይሰጡ የብረት፣ የተሽከርካሪና የማሽነሪ ስክራፖች፤(ሞተር እና ቻንሲ ቆራርጦ የሚረከብ) ፤ ቦታ ኮተቤ አከባቢ ብረታ ብረት ፊት ለፊት ከሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ግቢ እና አዳማ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግቢ፤ ሎት-3- የጠጠር ማምረቻ (መፍጫ) ክሬቸር ማሽን፤ቦታ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕራብ አርሲ ዞን መልካ ዋከና ኃ/ማመጫ ጣቢያ ግቢ፤ ሎት-4- ለመልካ ሰዲ የዕንፋሎት ኃ/ማመንጫ ጣቢያ ለመገንባት የመጡ ከፍተኛ መጠን፣ ዓይነትና ዋጋ ያላቸው ዕቃዎችና ማሽነሪዎች፤ ንብረቶቹ የሚገኙበት ቦታ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መልካ ሰዲ ከተማ በፕሮጀክት ጣቢያ ቅጥር ግቢ፤ ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፤ ማሳሰቢያ፡- ውድድሩ የሚከናወነው ሙሉ በሙሉ በኦክሽን ኢትዮጵያ አክሲየን ማህበር በፈጠሩት የማወዳደሪያ ሲስተም መተግበሪያ https://onelink.to/njnamp መሰረት መሆኑን እየገለጽን መስፈርቶቹ ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- 1. በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ሆኖ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ማስረጃ ወይም የታደሠ መታወቂያ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ 2. ስለጨረታው አካሄድ እና ንብረቶች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን ሰነድ የኦክሽን ኢትዮጵያ ፕላትፎርም ላይ ከንብረቶቹ መግለጫ ስር ተያይዞ የሚገኝ ስለሆነ በነጻ አውርደው መመልከት ይችላሉ። 3. ተጫራቾች የጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ከሰባተኛው ቀን ጀምሮ ኦክሽን ኢትዮጵያ አክሲየን ማህበር ጋር ቀጠሮ በማስያዝ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ንብረቶቹ በሚገኙበት የተቋሙ ጣቢያዎች በመገኘት መመልከት ይቻላል፤ 4. ተጫራቾች ለሚያቀርቡት ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ ማቅረብ አለባቸው፡፡ 5. ተወዳዳሪዎች በሎት ሁለት ላይ ለመሳተፍ በብረት አቅላጭ ድርጅትነት የተሰማሩ መሆን ያለባቸው ሲሆን፤ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 6. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ በጨረታ ሰነዱ ላይ በተቀመጠው መሰረት ሲሆን ፣ ለሎት ሁለት ብር 2,000,000.00 (ሁለት ሚሊዮን)፣ ለሎት ሶስት ብር 300,000.00(ሶስት መቶ ሺህ) እና ለሎት አራት ብር 500,000.00(አምስት መቶ ሺህ) በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም ብቻ ሲ.ፒ.ኦ. በማሰራት የኦክሽን ኢትዮጵያ መተግበሪያ ላይ የሚጫረቱበትን ዋጋ ማስገባት ይችላሉ። 7. ጨረታው ከ27/03/2017 እስከ 11/04/2017 ዓ.ም እስከ ጠዋት 4፡00 ድረስ ይካሄዳል ስለሆነም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች የጨረታዉን ሂደት በቀጥታ (online) መከታተል ይችላሉ። 8. ተጫራቾች የኦክሽን ኢትዮጵያን መተግበሪያ ከአፕ ስቶር ወይም ኘሌይ ስቶር (Auction Ethiopia) ብለው በማውረድ ወይም (auction.et) ላይ መመዝገብ እና መጫረት ይችላሉ። 9. በጨረታው አሸናፊ ለምትሆኑ ተጫራቾች ለወደፊት አሸናፊነታችሁ በሚገለፅላችሁ ቀን ጀምሮ የሚቆጠር አምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የአሸነፉችሁበትን ዋጋ ሙሉውን ክፍያ ለወደፊት በምናሳውቃችሁ በተቋማችን ሂሳብ ቁጥር ገቢ በማድረግ የሽያጭ ውል ስምምነት መፈጸም ግዴታ ይኖርባችኋል፤ ሆኖም ግዴታቸውን የማይወጡ ተጫራቾች ለወድድር ያስያዛችሁት የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ. ለተቋማችን ገቢ ይደረጋል፤ 10. ከላይ የተጠቀሰውን እና በጨረታ ሠነዱ ላይ የተቀመጡ መመሪያዎችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ/ሊሰረዝ ይችላል፤ 11. ተቋሙ ጨረታውን ለመቀበል ወይም ላለመቀበል የሚችል ሲሆን በማንኛውም ጊዜ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤ 12. የኦክሽን ኢትዮጵያን መተግበሪያ በተመለከተ የጥሪ ማዕከሉን ለማግኘት በአጭር የስልክ መስመር 9164 ወይም 09-05-11-5511/ 011-666-8828 በመደወል ማግኘት ይችላሉ። 13. ንብረቶቹን በተመለከተ በስልክ ቁጥር 011-558-14-24 ወይም 011-558-06-49 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡ ለበለጠ መረጃ አርብ ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ።ም የወጣዉን አዲስ ዘመን ጋዜጣ መመልከት ይቻላል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ቡድኑ ወደ ድል ተመልሷል ........///....... በ7ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከነማ ጋር ተጫውቶ ሁለት ለባዶ አሸንፏል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሙሉ የበላይነት በወሰ
+4
ቡድኑ ወደ ድል ተመልሷል ........///....... በ7ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከነማ ጋር ተጫውቶ ሁለት ለባዶ አሸንፏል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሙሉ የበላይነት በወሰደበት በዚህ ጨዋታ ማህሌት ምትኩ እና ኢየሩስ ወንድሙ የማሸነፊያ ጎሎቹን ለክለባቸው አስቆጥረዋል። በጨዋታው አንድ ጎል ያስቆጠረችው እና ድንቅ እንቅስቃሴ ያሳየችው ማህሌት ምትኩ ኮከብ ተጫዋች በመሆን ሽልማት ተበርክቶላታል። በ8ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ታህሳስ 02 ቀን 2017 ዓ.ም ከመቻል ጋር የሚጫወት ይሆናል።    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

ተቋሙ ያገለገሉ ንብረቶችን በዲጂታል ሥርዓት ሊያጫርት ነው .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በዲጂታል ሥርዓት ለማጫረት የሚያስችል ስምምነት ከኦክሽን ኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመ። ሥምምነቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  በኩል የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እና በኦክሽን ኢትዮጵያ በኩል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዮሴፍ አንኩ ተፈራርመዋል፡፡ ሥራ አስፈፃሚዋ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንደተናገሩት ስምምነቱ ተቋሙ ያገለገሉ ንብረቶቹን ለማስወገድ የሚያደርገውን የማኑዋል  የጨረታ ሂደት ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር የሚስችለው ነው፡፡ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን ለማስወገድ ተቋሙ የሚያደርገውን አድካሚ ሂደት፣ ጊዜን እና ወጪን ቆጣቢ በሆነ መልኩ በማዘመን  ለማቀላጠፍ  ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ ሀገር በቀል የዲጂታል አጫራች ድርጅቱ ጨረታዎችን በማውጣትና ተደራሽነቱን በማስፋት በአጭር ጊዜ  ተቋሙ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም እንደሚያስገኝ እምነታቸውን ገልፀዋል። የጨረታ ሂደቱ ከሰዎች ድርድር እና ንከኪ የጸዳ፣ ለብልሹ አሰራር የማያጋልጥ እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ ያሉ ተጫራቾች በእኩልነት ለማሳተፍ የሚያስችል እና አገልግሎቱን ለመጠቀም ምንም ዓይነት ወጪ የማያስወጣ በመሆኑ ተመራጭ እንደሆነ ወ/ሮ ስመኝ አስረድተዋል፡፡ የሀገር በቀሉ የዲጂታል አጫራች ድርጅት የኦክሽን ኢትዮጵያ  ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዮሴፍ አንኩ በበኩላቸው ድርጅታቸው  በጨረታ የሚሸጡ  ንብረቶች በዲጂታል ሥርዓት ተደራሽ በማድረግ ተገቢውን ዋጋ እንዲያገኙ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከ32 ሺህ በላይ ተጫራቾችን እና ከ500 በላይ አጫራቾች ድርጅቶችን ይዞ ከ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ባለይ ማገበያየቱን ገልፀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ዕውቅና ተሰጣቸው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በተቋሙ ባላቸው የአመራርነት ሚና እና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ላበረከቱት አስተዋፅኦ የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ በሚል ዕውቅናና ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር በኢነርጂ ዘርፍ ላይ በፈጠራና በአስተዳደር እንዲሁም በልዩ ልዩ ደረጃዎች ተፅዕኖ ለፈጠሩ ሴቶች ዕውቅና ለመስጠት እና በኢነርጂ ዘርፍ ላይ የተሳተፉ ተቋማትና ድርጅቶች ምርታቸውንና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት አውደ ርዕይ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል፡፡ በዕለቱም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤን ጨምሮ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለሆኑ ተጨማሪ ሁለት ሴቶች ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ዕውቅናውን የሰጡት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት የኢነርጂ ዘርፍ ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል፡፡ ዘርፉን ለማሳደግ ብቃት ያለው እና በሁሉም ጾታዎች የተመጣጠነ ባለሙያ እንደሚያስፈልግ ገልፀው ሚኒስቴሩም ሴቶችን ወደ ዘርፉ ለማምጣት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ ማህበሩ በኢነርጂ ዘርፍ ላይ ያለውን የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እና ብቃት ያለው ባለሙያ ለመፍጠር እየሰራ ካለው ሥራ ጎን ለጎን በዘርፉ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ሴቶችን ዕውቅና ለመስጠት የሚያደርገውን ጥረት አመስግነው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለማህበሩ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር ፕሬዚዳንት እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ የሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር ቢሮ ሪዚደንት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሪት አደይ ጌታቸው በበኩላቸው ማህበሩ ባለፉት ሦስት ዓመታት በኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለሆኑ ዘጠኝ ሴቶች ዕውቅና መስጠቱን አስታውሰዋል፡፡ በዛሬው ዕለት በተካሄደው መርሃ ግብር ከቀረቡ አስር ተወዳዳሪዎች መካከል ለሦስት የኢነርጂ ዘርፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች ዕውቅናና ሽልማት መሰጠቱንም ጠቁመዋል፡፡ ዕውቅናዉ ሴት ባለሙያዎች በኢነርጂ ዘርፍ የሚያደርጉትን አስተዋጽዖ ለማስተዋወቅ፣ ለማበረታታት እና ለማክበር እንዲሁም ወጣት ሴቶች በዘርፉ እንዲሰማሩና ለሌሎች ዓርአያ እንዲሆኑ ለማድረግ እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡ በዕለቱ ዕውቅና ከተሰጣቸው መካከል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ማህበሩ ላበረከተላቸው ዕውቅና አመስግነው ዕውቅናው በተቋሙ ባላቸው የአመራርነት ሚና፣ የተቋሙን ሴት ሠራተኞች ጫና ለማቃለል እና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ላበረከቱት አስተዋፅኦ እንደተሰጣቸውም ተናግረዋል:: ዓላማን ለማሳካት ዛሬ ከትላንት የተሻለ እንደሆነ በመገንዘብና ምቹ ሁኔታዎችን በመጠቀም በትጋት መስራት እንደሚጠበቅ የተናገሩት ወ/ሮ ሌንሴ የተሻለ ነገር ለማግኘት ሴቶች ያላቸውን አቅም አሟጠው መጠቀም እንደሚገባቸውም አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር (EWiEN) በኢነርጂ ዘርፍ ያለውን የሥርዓተ-ፆታ ክፍተት ለማመጣጠን በማሰብ በአምስት ሴት ባለሙያዎች የተመሠረተ ለትርፍ ያልተቋቋመና መንግሥታዊ ያልሆነ ማህበር ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር የሚያስችሉ የእድሳት ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው .........//........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር የሚያስችሉ የእድሳት ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የጣቢያው የአስተዳደር፣ ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ተሻገር እንደተናገሩት ጣቢያው ከ37 ዓመት በላይ እድሜ ያስቆጠረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመዝናኛ ሥፍራዎችና የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ላይ እድሳት እየተደረገ ነው። አስር መኖሪያ ቤቶችንና ባለ አንድ ፎቅ የእንግዳ ማረፊያ ቤት ላይ የእድሳት ስራ መጠናቀቁን የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ የቀሪ መኖሪያ ቤቶችን እድሳት ሙሉ በሙሉ በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ አቅደው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። የቤት እድሳት ሥራው ቀለም የመቀባትና የኮርኒስ እንዲሁም ያረጁ የቤት ውስጥ እቃዎችን የግዢ ሂደቱን ጠብቆ የመቀየር ሥራንም የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸዋል። የሠራተኞች ክበብ፣ መናፈሻ፣ የመዋኛ ገንዳ እድሳት፣ የክሊኒክ ጥገና እና የመኪና ማቆሚያ እንዲሁም ጋራዥ ሥራ በራስ አቅም እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተጨማሪም ከሠራተኛ መኖሪያ ቤት እስከ ኃይል ማመንጫ ቤቱ ድረስ ያለውን 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ የጥገና ሥራ ለማካሄድ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። ሠራተኛው የዕረፍት ጊዜውን የሚያሳልፍባቸው የዲ ኤስ ቲቪ፣ የፑል፣ የኳስ ሜዳና እና ሌሎች የመዝናኛ አማራጮች በግቢው ውስጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። የሠራተኞችና የአካባቢው ልጆች የሚማሩበት ከቅድመ መደበኛ እስከ 8ኛ ክፍል የሚያስተምሩ በግልና በመንግስት የሚተዳዱሩ ሁለት ትምህርት ቤቶች በጣቢያው ግቢ ውስጥ መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ተስፋዬ ከ8ኛ ክፍል በላይ ሲሆኑና ወደ ሮቤ ገርጀዳ ሲሄዱ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጡም አብራርተዋል። በተጨማሪም ከመደወላቡ ዩኒቨርስቲና ከበቆጂ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ሠራተኞችና የሠራተኛ ቤተሰቦች የሚማሩበትን ዕድል ተመቻችቷል ብለዋል። ጣቢያው የመምህራንን ማረፊያ፣ የመመላለሻ ትራንስፖርት፣ የመማሪያ ክፍል እና በኃይል ማመንጫ ቤቱና በማከፋፊያ ጣቢያው ተግባር ተኮር ትምህርት የሚማሩበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን ገልጸዋል። ሠራተኞች ወደ በቆጂና አዳባ ገበያ ሄደው የሚያስፈልጋቸውን ነገር እንዲሸምቱ በገበያ ቀናት ጣቢያው የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። የሠራተኛውን ጤና ለመጠበቅ ሙሉ ሕክምናና የላቦራቶሪ አገልግሎት የሚሰጥ ጤና ጣቢያ በጣቢያው መኖሩን ያስታወሱት አቶ ተስፋዬ ከክሊኒኩ አቅም በላይ ሲሆን አሰላ ከሚገኘው ሮሆቦት ሆስፒታል ጋር ባለው ስምምነት መሰረት ሠራተኛውን ሄዶ በነጻ እንዲታከም የትራንስፓርት አገልግሎት መመቻቸቱን ተናግረዋል። ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት በጣቢያው ሠራተኞች መኖሪያ ግቢ ያለውን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍም በዋናው መ/ቤት በኩል በጀት ተይዞ እየተሰራ ነው ብለዋል። እነዚህ ተግባራት የጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ ተፈጥሮላቸው ተረጋግተው ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲያከናውኑ የሚያስችሉ መሆናቸውንም ገልጸዋል። በቀጣይም ለጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ እንዲኖር እና ሙያዊ አቅማቸው እንዲገነባ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። እያንዳንዳቸው 38 ነጥብ 25 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው አራት ተርባይኖች ያሉት የመልካ ዋከና የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 95 ቋሚና 37 ጊዜያዊ ሠራተኞች አሉት።    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ተሸንፏል ........///........ በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ዛሬ በተከናወነ የ6ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ ለባዶ ተረቷል። የንግድ ባንክን ብቸኛ የማሸነፊያ ጎል ብርቱካን ገ/ክርስቶስ በ27ኛው ደቂቃ አስቆጥራለች። በጨዋታ የበላይነት የነበረው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በርካታ ግብ ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን ቢያገኝም በሚያስቆጭ ሁኔታ ዕድሎቹን አምክኗል። በአንፃሩ ንግድ ባንኮች ያገኘውን ብቸኛ ዕድል ወደ ጎል በመቀየር ማሸነፍ ችሏል። በ7ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከነማ ጋር ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም ይጫወታል።    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት .........///....... ቅዳሜ ህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም በአንፎ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በዓለምባንክ፣ በአንፎ፣ በቤቴል፣ በአሸዋሜዳ፣ በዲያስፖራ ሰፈር፣ በፊሊዶሮ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ይቆያል። በተመሳሳይ  እሁድ ህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በቆቃ - አዳማ 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 12፡00 እስከ 1፡00 ሰዓት ድረስ በአዳማ እና በአዋሽ ከተማ ኤሌክትሪክ ይቋረጣል። በተጨማሪም እሁድ ህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በኮተቤ የኃይል ማስተላለፊያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ ስለሆነም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በኮተቤ ብረታብረት ፣ በኪዳነምህረት፣ በአንቆርጫ እና አካባቢው ፣ በላምበረት መናኸሪያ፣ በእስራኤል ኤምባሲ ፣ በቤተመንግስት ፣ በዑራኤል፣ በጃንሜዳ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ ስለሆነ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡    💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ስርቆትን ለመከላከል ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ ሊሰራ ይገባል ........///........ በአፋር ክልል በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል ህብረተሰቡን ባሰተፈ መልኩ እንደሚሰሩ ከክልሉ፣ ከአውሲ ረሱ ዞንና ከተለያዩ ወረዳዎች ከተውጣጡ አመራሮች፣ የፀጥታ አካላት እና የጎሳ መሪዎች ጋር በተካሄደው ውይይት ላይ የተሳተፉ የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ቢልኤ አህመድ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው የስርቆት ወንጀል የብሄራዊ ደህንነት ስጋት እየሆነ መጥቷል። ከዚህ በፊት በስርቆት የወደመውን ንብረት መመለስ ባይቻልም ውድመቱ እንዳይቀጥል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መግባባት ላይ ተደርሶ እየተሰራ እንደሆነ አመልክተዋል። "ስርቆትን መከላከልና የሀገርን ሀብት መጠበቅ ፖሊስ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ማህበረሰብ ኃላፊነት አለበት" ያሉት ኮሚሽነሩ ለዚህም ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት። የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሁሴን መሃመድ በበኩላቸው በመሰረተ ልማቶቹ ላይ እየተፈፀመ የሚገኘውን የስርቆት ወንጀል ለማስቆም በየደረጃው ከሚገኙ የተለያዩ የፀጥታ አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል። ለመሠረተ ልማት ስርቆት ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት እንደ ክልል ቁርጥራጭ ብረቶቹን የሚገዙ ነጋዴዎች በክልሉ እንዳይሰማሩ የሚያደርግ አሰራር መዘርጋቱንም ተናግረዋል። በክልሉ የሚፈጠሩ የስርቆት ችግሮችን ለመፍታት የፀጥታ አካላት ኃላፊነት ወስደው እንደሚሰሩ ገልፀው ይህ ውጤታማ እንዲሆን ማህበረሰቡና ተቋሙ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር ተቀራርቦ መስራት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሙሳ አብዶ እንደተናገሩት የክልሉ ማህበረሰብ አኗኗር የተበታተነ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መሠረተ ልማቱን በቅርበት ለመጠበቅ አስቸጋሪ ሊያደርገው ይችላል። ይሁንና ማህበረሰቡ በኃላፊነት ጥበቃ ማድረግ በሚችልበት ሁኔታ ላይ አመራሩ የግንዛቤ ማስጨመጫዎችን በስፋት መስጠት ይጠበቅበታል ብለዋል። የአውሲ ረሱ ዞን ብልፅግና ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ናስር ሃመዱ በበኩላቸው ማህበረሰቡ መሠረተ ልማቱን በኃላፊነት እንዲጠብቅ፣ ስርቆቱ በሀገር ኢኮኖሚ እና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በሚከናወነው ሥራ ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅዕኖ በማስገንዘብ እንደሚሰራ አስታውቀዋል። ለህብረተሰቡ አገልግሎት በሚሰጡ የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን ለመከላከል ከአማራ ክልል የአጎራባች ወረዳዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም አስረድተዋል። የአጎራባች አካባቢዎችም ከዞኑ ማህበረሰብ ጋር ተቀናጅተው በመስራት የስርቆት ወንጀሎችን በትብብር እንዲከላከሉ አቶ ናስር ጥሪ አቅርበዋል። የስርቆት ድርጊቱ የክልሉ መገለጫ እንዳይሆን የፀጥታ ኃይሉ ህብረተሰቡን በማንቃት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ እና ማህበረሰቡም ከፀጥታ ኃይሉ ጎን እንዲቆም ኃላፊዎቹ አሳስበዋል። እንደ ሥራ ኃላፊዎቹ ገለፃ ውይይቱ ለስርቆት ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎችን በመለየት ጥበቃ የሚደረግበትን አግባብ እና የመረጃ ልውውጡ የሚካሄድበትን ሥርዓት ለመዘርጋት ዕድል ይፈጥራል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አቻ ተለያይቷል .........///....... ድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ባለው የኢትዮጵያ የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከነማ ጋር ነጥብ ተጋርቷል። ትናንት ምሽት አንድ ሰዓት የተከናወነው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ያለምንም ግብ ተጠናቋል። ግብ የሚሆኑ ኳሶችን በተደጋጋሚ ሙከራ በማድረግ ድሬዳዋ ከነማ የተሻለ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአንፃሩ በመልሶ ማጥቃት ጎል ለማግኘት ጥረት ሲያደርግ ተስተውሏል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ ኢድሪሱ አብዱላሂ በርካታ ጎል ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን በማዳን ክለቡን ታድጓል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ14 ነጥብ መቻልን ተከትሎ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በጊዜያዊነት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በ10ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ከስሁል ሽረ ጋር የሚጫወት ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋረጠው ኃይል መልሶ ተገናኝቷል …….///……. ለሦስት ዞኖችና ለጋምቤላ ክልል ኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆነውን የበደሌ መቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የመጠገን ሥራ በስኬት ተጠናቋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት ዛሬ ከረፋዱ 4፡50 ጀምሮ ለሦስት ሰዓት ከ30 ደቂቃ ተቋርጦ የነበረውን መስመር ከበደሌ ከተማ የተንቀሳቀሰው የጥገና ባለሙያዎች ቡድን ወደነበረበት እንዲመለስ አድርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም

በሦስት ዞኖችና ጋምቤላ ክልል ኃይል ተቋርጧል …….///……. ከበደሌ መቱ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት ዛሬ ከረፋዱ 4፡50 ጀምሮ በኢሉባቦር ዞን ያዩ በተባለ አካባቢ ኮንዳክተር ተበጥሷል፡፡ በዚህ የተነሳ በኢሉ አባቦር ዞን፣ በሸካ ዞን እና በቄለም ወለጋ ዞን እንዲሁም በጋምቤላ ክልል ኃይል መቋረጡን ገልፀዋል፡፡ የተበጠሰውን መስመር ለመጠገን ከበደሌ ከተማ የጥገኛ ባለሙያዎች ወደ ሥፍራው መንቀሳቀሳቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመው ችግሩ እስኪፈታ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም