ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 560 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 160

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 560 名订阅者。

根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 32,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.03%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.88% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 052 次浏览,首日通常累积 2 472 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 560
订阅者
-524 小时
+167
+3230
帖子存档
photo content
+2

በበጀት ዓመቱ በ25 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ይከናወናሉ ……...///………. በ2017 በጀት ዓመት በ25 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎች እንደሚከናወኑ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ በሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ጌታሁን እንደገለፁት በሦስት ዓመት ውስጥ የ75 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግ ዕቅድ ተይዟል። የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራው በማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩትን መቆጣጠሪያዎች በሌላ ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ መሳሪያ በመቀየር አቅማቸውን ለማሳደግ ያለመ መሆኑንም ነው የጠቆሙት። የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራው በ2016 በጀት ዓመት እንደተጀመረ የገለፁት አቶ ፀጋዬ በበጀት ዓመቱ በ25 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ሦስት ወራት በጋሸና፣ ድሬዳዋና ጌዶ እንዲሁም አሸጎዳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች መከናወናቸውን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በተቋሙ ባለሙያዎች በተከናወነው ሥራ ከ3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉን አስታውቀዋል። በቀጣይም በደቡብ አንድ ሪጅን ስር በሚገኙት የዲላ፣ ሻሸመኔ እና ይርጋለም ቁጥር አንድ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተመሳሳይ ሥራዎችን ለማከናወን እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ጠቁመዋል። ተቋሙ የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎችን በራሱ ለማከናወን ከሁሉም ሪጅኖች የተውጣጡ 20 ባለሙያዎች በውጭ ሀገር ሥልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ፀጋዬ ገለፃ በጣቢያዎቹ እየተከናወነ የሚገኘው የማሻሻያ ሥራ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግና ለማዘመን የሚያግዝ ነው። የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ወይም ስዊችጊር ገጠማ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እየተከናወነ መሆኑ በ15 እና 33 ኪሎ ቮልት መስመሮች በሚከሰቱ ተደጋጋሚ ችግሮች ሳቢያ ይፈጠር የነበረውን የኃይል መቆራረጥና የጥገና ጊዜን ለመቀነስ አወንታዊ ሚና እንዳላቸውም ነው ሥራ አስኪያጁ የገለፁት። በአሁኑ ወቅት ለ50 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚሆኑ ዘመናዊ የጂ.አይ.ኤስ ስዊችጊር ዕቃዎች መረከባቸውን የጠቀሱት አቶ ፀጋዬ ቀሪ 25 ስዊችጊሮች በምርት ሂደት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ከዓለም ባንክ እና ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 24 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ወጪ እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የውስጥ ኮሙዩኒኬሽንን በማጠናከር በሠራተኛው ዘንድ የእኔነት ስሜትን ለመፍጠር ይሰራል ……...//……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኮሙኒኬሽን ሥራዎችን በማጠናከር በተቋሙ ሠራተኞች ዘንድ የእኔነት ስሜትን ለማጎልበት እየተሠራ መሆኑን የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መመሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለጹት ሠራተኞች ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት በውል ተገንዝበው በእኔነት ስሜት ለተቋማዊ ስኬት እንዲሰሩ የሚያደርጉ የውስጥ ኮሙዩኒኬሽን ሥራዎችን በዕቅድ እየተከናወኑ ነው። በተቋሙ ውስጥ ባሉ የኤሌክትሮኒክስ ማሳያ ቦርዶች፣ በውስጥ ሕትመቶችና በአጭር መልዕክት ማስተላለፊያ ነፃ የተቋሙ ቁጥር አማካኝነት የተቋሙን አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ የሚያሳዩ እና ለሠራተኞች በቂ ግንዛቤ የሚፈጥሩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚህም የሥራ ክፍሎች አፈጻጸማቸውን የሚያጎለብቱበት፣ በአንድ ሥራ ሂደት የሚመዘገብ የሠራተኛ ውጤት ለአጠቃላይ ተቋማዊ ስኬትና ለውጥ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ግንዛቤ የሚያገኙበት እና የሥራ ክፍሎች ከሚያከናውኗቸው ሥራዎች እርስ በእርስ ልምድ የሚወስዱበት አሰራር እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡ ከሥራ ክብደቱ ጋር ተያይዞ የዘገባ ድግግሞሹ ካልተለያየ በስተቀር ሁሉም የሥራ ክፍሎች የዘገባ ሽፋን እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም በማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በራስ አቅም እየተከናወኑ ያሉ ትልልቅ የጥገና ሥራዎችን ሽፋን እንዲያገኙ እየተደረጉ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሞገስ ይሄም ከተቋም ባሻገር እንደ ሀገር ያለውን ጠቀሜታ በማህበረሰቡና በባለድርሻ አካላት ዘንድ እንዲታወቅ በማድረግ የተቋሙን ገጽታ የመገንባት ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። በቀጣይም በሠራተኛው ዘንድ የሚነሱ ችግሮች የሚፈቱባቸው፣ ስለተቋሙ ይበልጥ የሚገነዘቡባቸው እና የእኔነት ስሜትን የሚፈጥሩ መድረኮችን ለመፍጠር መታቀዱን አቶ ሞገስ ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በማከፋፈያ ጣቢያው ለአካባቢው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ሥራዎች ሊከናወኑ ነው ……..///…..... የዲላ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግና የማሻሻያ ሥራዎችን ለማከናወን እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ዘካሪያስ መኩሪያ እንደገለፁት ከ1996 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ በሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ሊከናወኑ የታቀዱት የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ለዲላ ከተማና አካባቢው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ናቸው፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 12 ሜጋ ዋት ኃይል የመሸከም አቅም ያለው አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር እንዲሁም ሁለት ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና ሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ጣቢያው ከይርጋለም ቁጥር 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ በአምስቱ የ33 እና 15 ኪሎ ቮልት መስመሮች ለዲላ፣ ጎሎልቻ፣ ጓንጓ፣ ይርጋጨፌ፣ ሱሉሞ፣ ቡሌና ቀባዶ እንዲሁም ወናጎ ከተሞች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ አቶ ዘካሪያስ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በአሁኑ ወቅት ማከፋፈያ ጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት መስመሮች ለአዳዲስ ደንበኞች ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ አቅም የለውም። ይህን ተከትሎ በጣቢያው የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎችን ለማከናወን እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ጌታሁን እንደገለፁት የጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የዘመናዊ ስዊች ጊር ገጠማ እንዲሁም ነባሩን ትራንስፎርመር የመቀየር ሥራ ይሰራል። የአቅም ማሻሻያ ሥራው በዋናነት በ15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ እንደሚከናወን ያነሱት አቶ ፀጋዬ ይህም የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራዎች ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ለማዘመን እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ የ15 ኪሎ ቮልት የጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር ዕቃዎች ተጓጉዘው ጣቢያው ላይ መድረሳቸውንና በቀጣይም የሲቪል፣ የጊዜያዊ መቆጣጠሪያ ክፍልና የገጠማ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ጨምረው ገልፀዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ ተጨማሪ ባለ 30 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንፎርመር በጣቢያው ለማስቀመጥ ዕቅድ መያዙንም ነው አቶ ፀጋዬ የተናገሩት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የጣቢያውን የኮንክሪት ሙሌት ሥራ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …....///....... የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ መሰረት የኮንክሪት ሙሌት ሥራን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ እንደገለጹት የኮንክሪት ሙሊት ሥራውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ከመከላክያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት ጋር ስምምነት በመፈጸም ወደ ሥራ ተገብቷል። በዚህም እስከአሁን የአንድ ትራንስፎርመር፣ የ62 ኮለሞች እና 173 ፓዶች የኮንክሪት ሙሌት ሥራ መጠናቀቁን አብራርተዋል። የቀሪ 73 ፓዶችና የሦስት ትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ መሠረት የኮንክሪት ሙሌት ሥራዎች በቀጣይ ቀናት በማጠናቀቅ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራውን ለመጀመር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የመከላክያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት 1 ሺ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት ለማቅረብና የሁለት ወራት ርዝማኔ ያለው ከተቋሙ ጋር ስምምነት ፈጥሮ የኮንክሪት ሙሌት ሥራው መጀመሩን ከአሁን ቀደም መዘገባችን ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

በአመራር ሥርዓተ ልማት ላይ ያተኮረ ወርክሾፕ ተካሄደ ........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት ስልጠናና ልማት መምሪያ ከአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመቀናጀት ያዘጋጀው የአመራር ሥርዓተ ልማት ሰነድ ለውይይት ቀረበ። የተቋሙ የሰው ሀብት ስልጠናና ልማት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) እንደገለፁት ወርክሾፑ የተዘጋጀው ከተቋሙ የሥራ መሪዎች እና ባለሙያዎች በሰነዱ ላይ ተጨማሪ ግብአት ለመሰብሰብ ነው። የአመራር ልማት ሰነዱ ዘጠኝ ዋና ዋና ክፍሎች ያሉት እንዳሉት የገለፁት ዳይሬክተሩ የኮርፖሬት ስትራቴጂ ትንተና፣ የብቃት ወይም ኮምፒተንሲ ልየታ እና የሞጁል ዝግጅቶችን አካቷል ብለዋል፡፡ የአመራር ልማቱ ከአፍሪካ የአመራር ልቀት አካዳሚ ጋር በመሆን ተግባራዊ ሲደረግ ከላይ እስከ ታች የተናበበ ስትራቴጂያዊ አመራር ለመፍጠር እንደሚያስችል ተናግረዋል። የአመራር ሥርዓተ ልማት ሰባት የብቃት ፕሮግራሞች ያሉት ሲሆን ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የ18 ወራት ጊዜ እንደሚወስድ ተገልጿል። 14 ሞጁሎችን ያካተተው ይህ ሰነድ የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ስልጠናዎችን በማካተት ለተቋሙ የሥራ መሪዎች የሚሰጥ ይሆናል። በወርክሾፑ ላይ የተቋሙ የሥራ መሪዎች እና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን የሥራ አመራር ስርዓተ ልማት ሰነዱን የሚያዳብሩ ግብአቶች አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ስርቆትን የመከላከል ሥራ ሀገራዊ ትኩረት ይሻል .......///........ በኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ሀገራዊ ትኩረት የሚሻ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ዘርፍ የደቡብ አንድ ሪጅን ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች በኃይል መሰረተ ልማቶች ስርቆት ዙሪያ ተቋሙ ከሚመለከታቸው የመስተዳደር አካላት ጋር በቅርበት እንዲሰራ ጠይቀዋል። የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በሰጡት ማብራሪያ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል አማራጭ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለመጠቀም የሚያስችል ጥናት ተጠንቷል። ጥናቱ ከስርቆት ጋር የተያያዙ ችግሮችን እንዴት መፍታት ይገባል ለሚለው ጥያቄ ቴክኒካዊ መፍትሔ ማስቀመጡን አቶ ሞገስ ገልፀዋል። የመፍትሔ ሀሳቡ የስርቆት ወንጀሎች በተደጋጋሚ በሚፈፀምባቸው መስመሮች በንዝረት አማካይነት ጥቆማ መስጠት የሚችሉ መሳሪያዎችን መግጠምን ጨምሮ በድሮም በመታገዝ ክትትል ማድረግ የሚቻልባቸው አማራጮችን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነም ነው ያብራሩት። ከክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ የመስተዳድር አካላትና የፀጥታ መዋቅሩ የመፍትሄው አካል እንዲሆኑ ለማድረግ ውይይቶች መጀመራቸውንና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ ስለመሆኑ ተናግረዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ በመሠረተ ልማቶቹ ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎችን ከምንጩ ለማድረቅ የህግ ማዕቀፎችን እስከ ማሻሻል የሚያደርሱ ሀሳቦች በጥናቱ ተካተዋል። አገልግሎቱ በችግሩ ዙሪያ ትኩረት መስጠቱ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት የብሔራዊ የደህንነት አጀንዳ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል ብለዋል። በኃይል ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ሀገራዊ ትኩረት በማግኘቱ በአጭር ጊዜ ሒደት ለውጥ እንደሚመጣ እምነታቸውን ገልፀዋል። እንደ ተቋም የኃይል መሠረተ ልማት ደህንነትን የሚከታተል የሥራ ክፍል መቋቋሙን ገልፀው የሥራ ክፍሉ በየሪጅኖቹ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን በመከታተል አፋጣኝ የመፍትሔ እርምጃዎች እንዲወሰዱ የሚያደርግ ነው ብለዋል። የሪጅን መምሪያዎች በመሰረተ ልማቶቹ አቅራቢያ የሚገኙ በመሆናቸው  ከሚመለከታቸው የዞንና ወረዳ የመስተዳድርነና የፀጥታ አካላት ጋር እያደረጉት ያለውን ግንኙነት አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው አሳስበዋል። የተቋሙ የኮሙዩኒኬሽን መምሪያ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች በሚያስተላልፋቸው መልዕክቶች የህብረተሰቡን አመለካከት በመቅረፅ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ ስርቆቶችን ለማስቀረት እየሰራ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በሰሜን ሪጅን ባለፉት ሦስት ወራት 500 የሚሆኑ የታወር አካላት ተሰርቀዋል ..........///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሰሜን ሪጅን በሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በተፈጸመ ስርቆት 500 የሚሆኑ የተለያየ መጠን ያላቸው የታወር ብረቶች መሰረቃቸውን ሪጅኑ አስታወቁ፡፡ በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ፋይበር ኦፕቲክስ ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ህንፃ አረጋዊ እንዳስታወቁት በሪጅኑ ሥር ከሚገኙ 11 የማስተላለፊያ መስመሮች ባለፉት ሦስት ወራት በአራቱ ላይ የኢንስፔክሽን ሥራ ተከናውኗል፡፡ የኢንስፔክሽን ሥራ በተከናወነባቸው በአላማጣ - መሆኒ- መቐለ፣ መቐለ - ተከዜ፣ ተከዜ - አክሱም - ሽሬ እና መቐለ - አድዋ - አክሱም ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ስርቆት ተፈጽሞባቸው መገኘቱን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ በመስመሮቹ ላይ በሚገኙ 41 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት 500 የታወር አካላት በዘራፊዎች ተፈትተው መወሰዳቸውን ነው የተናገሩት፡፡ በሪጅኑ ያለው የስርቆት መጠን ከሌሎች ሪጅኖች ጋር ሲነፃፀር የተሻለ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ህንፃ በአሁኑ ጊዜ መጠኑ ከቦታ ቦታ ቢለያይም ስርቆት የማይፈጸምበት መስመርና አካባቢ እንደሌለ አስታውቀዋል፡፡ የኢንስፔክሽን ሥራ ያልተከናወነባቸው ሌሎች መስመሮች ለስርቆት ተጋላጭ እንደሚሆኑም ስጋታቸውን ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ህንፃ ገለፃ በሪጅኑ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት መደበኛ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎችን ከማከናወን ይልቅ ሪጅኑ በአስቸኳይ የጥገና ሥራዎች ላይ እንዲጠመድ እያደረገው ይገኛል፡፡ ስርቆቱ በሪጅኑ ያለውን የመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት እያባባሰው እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ ምንም እንኳን ባለፉት ሦስት ወራት በሪጅኑ የተፈፀመው የስርቆት መጠን ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር የጨመረ ቢሆንም በስርቆቱ ምክንያት የተቋረጠ ኃይል አለመኖሩን አቶ ህንፃ አረጋግጠዋል፡፡ ስርቆትን ለመከላከል ሪጅኑ ለህብረተሰቡ በተለያዩ መንገዶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በስርቆት ተጠርጥረውና እጅ ከፈንጅ በሚያዙ ተጠርጣሪዎቹ ላይ አስተማሪ ቅጣት ባለመሰጠቱ ስርቆትን ለመከላከል እየተከናወነ ያለው ሥራ መፍትሔ ሊያመጣ አልቻለም ብለዋል፡፡ በሰሜን ሪጅን 2 ሺ 32 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች እና 1 ሺ 50 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የማስተላለፊያ መስመር ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ከሁለት ሳምንት በኋላ መስመሩ ዳግም ተገናኝቷል ………///………. በስርቆት ምክንያት ላለፉት ሁለት ሳምንታት አገልግሎቱ ተስተጓጉሎ የነበረው የቆቃ-ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ማምሻውን አገልግሎት መስጠት ጀመረ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት የተቋረጠውን መስመር መልሶ ለማገናኘት ከፍተኛ ርብርብ ሲደረግ ቆይቷል። ከሪጅኑ በተጨማሪ የሦስት ሪጅኖች ባለሙያዎችን በቅንጅት በማሳተፍ የተከናወነው የጥገና ሥራ የምስራቅ ኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ከፈረቃ ወጥተው ኃይል እንዲያገኙ ማስቻሉን ዳይሬከረተሩ ገልፀዋል። በጥገና ሥራው ላይ የተሳተፉ ሁሉንም ባለሙያዎችና የአዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አስተዳደርን አመስግነዋል። የአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ተደጋጋሚ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት ከሚፈፀምባቸው አካባቢዎች መካከል አንዱ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሎየር 1ኛ የስራ መደብ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ነሐሴ 23 ቀን 2016 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተ
+1
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሎየር 1ኛ የስራ መደብ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ነሐሴ 23 ቀን 2016 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና መውሰዳችሁ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት የጽሁፍ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ከዚህ በላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ጥቅምት 18 እና 19 ቀን 2017 ዓ.ም በወጣላችሁ ፕሮግራም መሰረት ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት የሰራተኛ ምደባ ቢሮ መሰብሰቢያ አዳራሽ የቃል መጠይቅ (Interview) የሚሰጥ በመሆኑ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

በሪጅኑ የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የመጫን አቅማቸው ከ70 በመቶ በላይ ደርሷል .........///........ በደቡብ አንድ ሪጅን የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኤሌክትሪክ የመጫን አቅማቸው ከ70 በመቶ በላይ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ከደቡብ አንድ ሪጅን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጆች ጋር በኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም እያጋጠሙ በሚገኙ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ በሐዋሳ ከተማ ውይይት አካሂዷል። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ያለው አማረ እንደገለፁት በሪጅኑ ከ132 እስከ 400 ኪሎ ቮልት ኃይል የመጫን አቅም ያላቸው 12 የማከፋፈያ ጣቢያዎች ይገኛሉ። በአስራ ሁለቱ የማከፋፈያ ጣቢያዎች የተለያየ አቅም ያላቸው 23 ትራንስፎርመሮች እንደሚገኙ  የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ጣቢያዎቹ በአሁኑ ወቅት ኃይል የማቅረብ አቅማቸው ከ70 በመቶ በላይ መድረሱን ተናግረዋል። አስራ ሁለቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች 1 ሺህ 910 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ቢኖራቸውም በአሁኑ ሰዓት 1 ሺህ 710 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረቡ እንደሚገኙ ገልፀዋል። የሻኪሶ፣ ሻሸመኔ፣ ሀዋሳ ቁጥር 1፣ ይርጋዓለም ቁጥር 1 እና ቡኩሉ ጉማ እንዲሁም ያዶት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ በመሆናቸው የማሻሻያ ሥራዎች እንደሚያስፈልጋቸው አቶ ያለው ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በተያዘው በጀት ዓመት በሪጅኑ በሦስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የ15/33 ኪሎ ቮልት የጂ.አይ.ኤስ ብሬከር ቅየራ ሥራ ይከናወናል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጆቹ በበኩላቸው አንዳንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማነስ ችግር እየገጠማቸው በመሆኑ የተበላሹ ትራንስፎርመሮች እና ብሬከሮችን በወቅቱ እንዲጠገኑና እንዲቀየሩ ጠይቀዋል። ለኦፕሬሽን ሥራ አስፈላጊ የሆነው የተሽከርካሪ አቅርቦት፣ የሥራ ላይ መሳሪያዎች አቅርቦት እና የሰው ኃይል እጥረት በሥራቸው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ እንዲሟላላቸው ጥሪ አቅርበዋል። ጣቢያዎቹ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ምቹ የሥራ ከባቢ ከመፍጠር ጀምሮ እየተስተዋሉ ለሚገኙ ችግሮች መፍትሔ እንዲሰጥ አሳስበዋል። በተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ በሪጅኑ በሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎች የታዩ ችግሮችን ለመፍታት ዘርፉ ጥረት ያደርጋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1