en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 686 subscribers, ranking 8 039 in the Technologies & Applications category and 2 170 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 686 subscribers.

According to the latest data from 04 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 132 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.82%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.99% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 208 views. Within the first day, a publication typically gains 2 509 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 686
Subscribers
-424 hours
+57 days
+13230 days
Posts Archive
photo content
+6

የተቋሙ ሴት ሠራተኞች ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አከበሩ …………///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሴት ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በዓለም ለ114ኛ በሀገር አቀፍ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ « ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ» በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብረዋል፡፡ በመርሀግብሩ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሲከበር ሴቶች በሁሉም ዘርፍ አቅማቸውን በማጎልበት ውጤታማ እንዲሆኑ የተጀመረውን ጥረት በማስቀጠል ሊሆን ይገባል፡፡ የሥራ ቦታዎችን  ከጾታ መድልዖ የጸዱ፣ አካታች እና አሳታፊ እንዲሆኑ በሚደረገው ጥረትም የተቋሙ ሴት ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። በተቋሙ  የሴቶች እና ማህበራዊ መመሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በበኩላቸው ሴቶች  የሚያገኙትን ዕድል ሳያባክኑ አሟጠው  በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ የድጋፍ እርምጃዎችን ያመቻቻ ቢሆንም ዕድሉን ከመጠቀም አንጻር ውስንነቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ስለሆነም ተቋሙ ለሴት ሠራተኞች ያስቀመጣቸውን የድጋፍ እርምጃዎች በአግባቡ በመጠቀም የሚጠበቅባቸውን ተቋማዊና ሀገራዊ አስተዋጽኦ ማበርከት አንዳለባቸውም ገልፀዋል፡፡ በበዓሉ ላይ በጡት እና በማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና  እና  ሥነ ግጥም ቀርቧል፡፡ በተመሳሳይ በዓሉ በተቋሙ በአዳማ 1 እና 2፣ በቆቃ፣ በአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም በደሴና በማዕከላዊ ሪጅን 2 በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በምዕራብ ሪጅን ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ኃይል አግኝተዋል ....///... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምዕራብ ሪጅን ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ኃይል ማግኘታቸውን የሪጅኑ የኦፕሬሽንና ጥገና ኃላፊ ገለጹ። ኃላፊው አቶ ታሪኩ ደጉ እንደገለጹት የጊዳ አያና ባለ132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያን ከነቀምቴ ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር በሚያገናኝው ትራንስፎርመር ላይ በደረሰ ችግር የተነሳ ከየካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአምስት ወረዳዎችና አንድ ከተማ አስተዳደር ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል። ኃይል የተቋረጠባቸው ጊዳ፣ ገሊላ፣ ኤበቱ፣ ሀሮ ሊሙ፣ ኪረሙና ሀምሩ ወረዳዎች እንዲሁም ጉትን ከተማ አስተዳደር ናቸው። ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የተጎዳውን የትራንስፎርመር ክፍል በመቀየር ወደ ሥራ ለማስገባት ጥረት ሲደረግ መቆየቱን የገለጹት አቶ ታሪኩ በዛሬው ዕለት የአራት ወረዳዎችንና አንድ አተማ አስተዳደር ኃይል እንዲያገኙ መደረጋቸውን ተናግረዋል። ቀሪ ኃይል ያላገኙ አካባቢዎች በአጭር ጊዜ ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በአደጋው በተከሰተው የኃይል መቋረጥ በትዕግስት ለጠበቁ ነዋሪዎችም ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋማዊ አሰራሮች ሕግን የተከተሉ እንዲሆን መስራት ይገባል ….....///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ እየተተገበሩ ያሉ አሰራሮች ሕጋዊ ሂደትን ተከትለው መከናወናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ በተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ። ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዱጉማ ነዳ ከተቋሙ የሕግ አገልግሎት መምሪያ ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ውይይቱ ዓላማ በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ ተቋማዊ የለውጥ ሥራዎች ከመደገፍ ባለፈ የተቋሙን የፋይናንስ አቅም በእጅጉ እየተፈታተኑ ባሉት የታወር ስርቆትና የካሳ ክፍያ ጉዳዮች ዙሪያ መምሪያው በምን አግባብ እየሰራ ነው የሚለውን አይቶ ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ያለመ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ ለውይይት መነሻ እንዲሆን አምስት አባላት ያሉት የጥናት ኮሚቴ በማቋቋም በመምሪያው እና በስሩ ባሉ ክፍሎች እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችና የመፍትሔ ሀሳቦች ለማመላከት የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት መሰራቱን ተናግረዋል። መምሪያው ቅንጅታዊ አሰራርንና ሙያዊ ብቃትን በማሳደግና አሰራሮች ሕግን የተከተሉ መሆናቸውን በመቆጣጠር ተቋሙን በመጠበቅና በመከላከል በኩል ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር ደረጃ የሚሰራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶች ከብክነት በፀዳ መልኩ በውጤታማነት ለመፈፀም የመምሪያው ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ በሕግ አገልግሎት መምሪያና በሥሩ በሚገኙ የሥራ ክፍሎችን የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመለየት እና የመፍትሔ ሀሳቦችን  ለማመላከት የተሰራው የዳሰሳ ጥናትም ለውይይቱ ተሳታፊዎች ቀርቧል፡፡ በመምሪያው ውስጥ ከሠራተኛ አቅም ግንባታ፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ፣ ከመፈጸም አቅምና ከግብዓት አቅርቦት ጋር ያሉ ችግሮች እንዲሁም ከሌሎች የተቋሙ የሥራ ክፍሎች ጋር ያለውን ግንኙነት በተመለከተ በጥናቱ ተዳሷል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም ጥናቱ ራሳቸውን እንዲያዩና በሥራ ክፍሎች መካከል እርስ በእርስ የመማማር ዕድልን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። መምሪያው ተቋሙን የሚመጥን ሥራ ለመስራት ያስችለው ዘንድ ሊፈቱና ሊታዩ ይገባሉ ያሏቸውን ሀሳቦችና አስተያየቶች አንስተው መሰል ጥናቶችና ወይይቶች በየጊዜው የሚደረጉበት አሠራር እንዲዘረጋም ጠይቀዋል፡፡ የሕግ አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ መስከረም በቀለ በበኩላቸው ከተሳታፊዎች የተነሱ እንዲሁም በጥናቱ የተለዩ ችግሮችን እንደ ግብዓት በመውሰድ በተቋማዊ ለውጡ የሕግ ክፍል ሊኖረው የሚችለውን ሚና እንዲወጣ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ከታወር ስርቆትና ከካሳ ክፍያ ጋር ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች፣ ከፍትህና አስተዳደር አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም አብራርተዋል፡፡ የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ በፍርድ ቤት ባሉ ጉዳዮች ዙሪያም መረጃና ማስረጃ በማጠናከር የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅና ለመከላከል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጠቆሙት ዳይሬክተሯ ተቋማዊ አሰራሮችን በመፈተሸ በሕግ እንዲደገፉ ብሎም ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን መምሪያው በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

ጣቢያው የጥገና ሥራዎቹን ቢያሳካም ኃይል የማምረት አፈፃፀሙ ከዕቅዱ ያነሰ ነበር …….///……. የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2017 ግማሽ በጀት ዓመት በቅድመ መከላከል፣ በትንበያ እና የገጠሙ ችግሮችን በማስተካከል ከዕቅዱ በላይ ቢያከናውንም ኃይል በማምረት ረገድ የያዘውን ዕቅድ ማሳካት እንዳልቻለ አስታወቀ፡፡ የጣቢያ ኃላፊው አቶ መለሰ ሲሎ እንደገለፁት ጣቢያው በግማሽ ዓመቱ በቅድመ መከላከል፣ በትንበያ እና የገጠሙ ችግሮችን በማስተካከል 141 ጥገናዎች ለማከናወን አቅዶ 150 ጥገናዎችን በማከናወን የ106 ነጥብ 21 በመቶ አፈፃፀም አስመዝግቧል፡፡ በንፋስ ተርባይኖችና በስዊችያርድ 152 የፍተሻ ሥራዎችን ለማከናወን የያዘውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካቱን ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ ይሁንና በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ለማምረት ካቀደው 249 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ውስጥ ማምረት የቻለው 184 ነጥብ 26 ጊጋ ዋት ሠዓት ብቻ መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡ እንደ ኃላፊው ገለጻ የኃይል ማምረት አፈፃፀሙ ከዕቅዱ አንፃር ዝቅ ያለ ቢሆንም የንፋስ ተርባይኖች የሚቆሙበትን ጊዜ በመቀነስ እና አስተማማኝ የጥገና ሥራዎችን በመስራት በተለዋዋጭ የንፋስ ሁኔታዎች ውስጥ ያልተቋረጠ ኃይል ማምረት ተችሏል፡፡ የጣቢያው የጥገና ባለሙያዎች ቴክኖሎጂን በቀላሉ መላመዳቸውና የሥራ ተነሳሽነታቸው ከፍ ያለ መሆኑ ለበጥገና ሥራ ለተመዘገበው ውጤት አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡ የተቋም ሀብት ዕቅድ ሶፍትዌር ወይም ERP፣ የሳፕ ጥገና ሞጁልና የኃይል አስተዳደር ሥርዓቶች እና ሌሎች የለውጥ መሳሪያዎች በጣቢያው መተግበራቸው ለጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራዎች ጉልህ ድርሻ እንደነበራቸው ገልፀዋል፡፡ ኃላፊው እንደተናገሩት የጥገና ሥራዎች በዕቅድ መተግበራቸው የሥራ ጊዜን ውጤታማ በማድረግ እና የመሳሪያዎችን የህይወት ዘመን በማራዘም በጣቢያው የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖር አስችሏል፡፡   💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ማከፋፈያ ጣቢያው ለአግልግሎት ዝግጁ ተደርጓል .......///…..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የበቆጂ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አሰኪያጁ አቶ እንዳልካቸው ጃምቦ እንደገለጹት በማከፋፈፈያ ጣቢው የፍተሻ እና የሙከራ ሥራዎች ላለፉት ሦስት ወራት ሲከናወኑ ቆይተዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን ከመልካ ዋከና ወደ ቆቃ ከሚሄደው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ጋር በማገናኘት የፍተሻና የሙከራ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡ የፍተሻና የሙከራ ሥራው መጠናቀቁን ተከትሎ አስር ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ለደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መደረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ለበቆጂና እና በ120 ኪሎ ሜትር ዙሪያ መለስ ውስጥ ለሚገኙ ከተሞች እና ወረዳዎች አስተማማኝ የኃይል ለማቅረብና የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማፋጠን እንደሚያግዝ ጠቁመዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ላለፉት አስራ ዘጠኝ ወራት ሲከናወን ቆይቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት አራት ታወሮች ወድቀዋል ………///……… ከባህርዳር - ወልዲያ - ኮምቦልቻ በተዘረጋው ባለ 400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት አራት የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች መውደቃቸውን ፕሮጀክቱ አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የባህርዳር - ወልዲያ - ኮምቦልቻ ፕሮጀክ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ኪሮስ እንዳስታወቁት ስርቆቱ የተፈፀመው መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም በደቡብ ጎንደር ደብረታቦር ከተማ አቅራቢያ ጉና ወረዳ ነው። በተፈፀመው ስርቆት አራት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በሙሉ መውደቃቸውን ያረጋገጡት ሥራ አስኪያጁ በስርቆቱ 129 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኪሳራ በተቋሙ ላይ ደርሷል ብለዋል። በስርቆትና በፀጥታ መደፍረስ ሲፈተን የቆየውን ፕሮጀክት በማጠናቀቅ ከግሪድ ጋር ለማገናኘት ተቋሙ ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ በሚገኝበት ወቅት ችግሩ መፈጠሩ እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 87 በመቶ ቢደርስም በፕሮጀክቱ ላይ የሚፈፀሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆቶች ለሥራው እንቅፋት መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል። ስለሆነም ቀሪ የፕሮጀክቱን ሥራዎች በአጭር ጊዜ አጠናቆ አገልግሎት ለማስጀመር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለችግሩ ልዩ ትኩረት ሊሰጡት እንደሚገባ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ከፕሮጀክቱ የዕውቀትና ቴክኖሎጅ ሽግግር እየተገኘ ነው ………///……… ከደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እየተገኘበት መሆኑን በፕሮጀክቱ የሳይት ሁለት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አርጋዉ ታዲ እንዳስታወቁት በደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሳይት ሁለት በሚከናወኑ የማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ላይ 80 የውጭ ሀገር ዜጎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ከግንባታ ሥራዎቹ የዕውቀት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ በሥራው ላይ እየተሳተፉ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ከውጭ ሀገር ዜጎች ጋር በማቀናጀት እንዲሰሩ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ ይህም ወደፊት የሚከናወኑ ሥራዎችን በራስ ኃይል ለማከናወን የሚያስችል አቅም ለመፍጠርና የሥራ ባህልን ለማሳደግ እንደሚያግዝ ነው አቶ አርጋው ያስታወቁት፡፡ በባዮክሰን ኢንጂነሪንግ አማካሪ ሲቪል መሃንዲስ አቶ አብርሃም ደሳለኝ በበኩላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራዎች መሳተፋቸው ብቁ ሠራተኞችን ለማፍራት ያግዛል ብለዋል፡፡ በሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሲቪል መሐንዲስ የሆኑት አቶ መኮንን ጥላሁን በበኩላቸው እንደተናገሩት ከውጭ ሀገር ዜጎች ጋር መስራቱ ክህሎትን ለማዳበር፣ ቴክኖሎጂና ልምድ ለመቅሰም ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ በሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ በረዳት ፎርማንነት እየሰራ የሚገኘው አሳየኸኝ አሻግሬ እንደገለፀው ወደ ፕሮጀክቱ ከመቀላቀሉ በፊት ከሹፍርና ውጭ ከግንባታ ሥራዎች ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ዕውቀትና  ልምድ አልነበረውም፡፡ ይሁንና ፕሮጀክቱን በተቀላቀለ በአንድ አመት ከስድስት ወር ውስጥ የተለያዩ ሙያዎች ባለቤት እንደሆነና ለዚህ ደግሞ ከውጭ ዜጎች ጋር አብሮ መስራቱ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚወስድ ተናግሯል፡፡ በሳይት ሁለት በሚከናወኑ የሽግዳንና ቲርጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ከሳውላ ቲርጋ በሚዘረጋው የማስተላለፊያ መስመር ላይ ከአንድ ሺህ በላይ ሠራተኞች እየተሳተፉ መሆናቸውን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

በማስፋፊያ ሥራ ተጨማሪ 310 ሜጋ ዋት ኃይል ማግኘት ተችሏል ……….///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት አምስት ዓመታት በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በተከናወኑ የአቅም ማሳደግና የማዘመን ሥራዎች ተጨማሪ 310 ሜጋ ዋት ኃይል ማግኘት መቻሉን በተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ  አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳስታወቁት ከከተሞችና ከኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት ከአዳዲስ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎች በተጨማሪ በነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ፣ የማስፋፊያ እና ማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ዕድሜ፣ የኃይል ጭነት ከመጠን በላይ መሆን እና በጣቢያዎች ላይ በሚከሰቱ ድንገተኛ ችግሮች በዕቃዎች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ለአቅም ማሳደግ እና ማሻሻያ ሥራዎች መከናወን ምክንያት እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡ ሥራው በስዊች ጊሮች፣ ትራንስርመሮች፣ ቮልቴጁን በሚያመጣጥኑ ሸንት ሪያክተሮች እና በሌሎች ዋና ዋና የማከፋፈያ ጣቢያ አካላት ላይ እንደሚከናወንም ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ ባለፉት አምስት ዓመታት በነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 22 የሚሆኑ ፓወር ትራንስፎርመሮችን በመትከል 310 ሜጋ ዋት ተጨማሪ ኃይል ማግኘት ተችሏል፡፡ የጣቢያዎቹን የመቆጣጠሪያ ብሬከሮች (swichgear) አቅም የማሳደግና የማዘመን ሥራዎች በመሰራታቸው ትራንስፎርመሮቹ በተሻለ አቅም እንዲሰሩ ማድረግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡ በ75 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ለማከናወን ከታቀደው የመቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ሥራዎች እስከ አሁን የ25ቱ መጠናቀቁን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ በተያዘው ዓመት የአስር ጣቢያዎችን ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነውም ብለዋል፡፡ ቦሌ ለሚ፣ ሻሸመኔ፣ ጂግጂጋ፣ በደሌ፣ ሐረር II እና III፣ ወልቂጤ፣ ደብረ ታቦር፣ ጊንጭ፣  ደብረ ብርሃን፣ ድሬዳዋ II እና III፣ አሸጎዳ፣ ገላን፣ ሆሳዕና፣ ባህርዳር II፣ ጌዶ እና ጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማሳደግ፣ ማስፋፊያ እና የማዘመን ሥራዎች ከተከናወኑባቸው  መካከል ተጠቃሾች ናቸው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ለሠራተኞች የሥራ ላይ ደህንነት ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ……..///……… በግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞችን ጤንነትና ደህንነት ለመጠበቅ ለሥራ ላይ ደህንነት ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ሳይት ሁለት አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ ሃይሰን ሄቪ ኢንደስትሪ ኮርፖሬሽን የሳይት ሁለት የሥራ ቦታ ደህንነትና የሠራተኛ ጤንነት ቁጥጥር ሥራ አስኪያጅ አቶ ባህሩ በቀለ እንዳስታወቁት የቲርጋና ሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከከተማ ርቆ የሚገኝ በመሆኑ የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል እና የሠራተኞችን ጤንነት ለማረጋገጥ በሳይቱ የሥራ ላይ ደህንነት የሥራ ክፍል በማቋቋም ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በግንባታ ሥራ ላይ የሚሳተፉ ሠራተኞች ለተለያዩ አደጋዎች ተጋላጭ በመሆናቸው በሥራ ላይ የሚደርሱ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ሠራተኛው ሥራ ከመጀመሩ በፊት ስለ አደጋ አጋላጭ ሁኔታዎች፣ ስለአደጋ መከላከያ መንገዶች፣ ሠራተኞች በስራ ቦታቸው ላይ ስለሚኖራቸው እንቅስቃሴ እንዲሁም ከደህንነት መሳሪያዎች አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የግንዛቤ ማስጨበጫ በየጊዜው እንደሚሰጥ አመልክተዋል፡፡ በሥራው ላይ አደጋ ቢያጋጥም ለተጎጂዎቹ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት በሥራ ቦታዎች ላይ የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ ክፍል  መዘጋጀቱንና ከአቅም በላይ ከሆነ ደግሞ ወደ ህክምና ተቋማት የሚላኩበት አሰራር መዘርጋቱን ሥራ አስኪያጁ አንስተዋል፡፡ የሥራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ መንገዶችን በማያከብር ሠራተኛ ላይ እስከ ሥራ ማሰናበት የሚደርስ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድም አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ ባህሩ ገለፃ ሠራተኛው የሥራ ላይ ደህንነት ጉዳይን ባህል በማድረጉ እና አስፈላጊው ክትትልና ቁጥጥር በመደረጉ እስከ አሁን ምንም አይነት አደጋ አላጋጠመም፡ በሽግዳን ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ ላይ በአናፂነትና በረዳት ፎርማን እየሰሩ የሚገኙት  ጃኪ አይቾሚ እና አሳየኸኝ አሻግሬ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ የሥራ ቦታ ለአደጋ እንዳይጋለጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎች እንደሚቀርብላቸው ተናግረዋል፡፡  የሚሰጣቸውን የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎችን በአግባቡ በመተግበር ደህንነታቸውን ጠብቀው እየሠሩ እንደሆነም አረጋግጠዋል፡፡ በደቡባዊ የኤሌክትሪክ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በሳይት ሁለት በሚከናወኑ የግንባታ ሥራዎች ላይ ከአንድ ሺ በላይ ሠራተኞች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም