fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 572 مشترک است و جایگاه 8 356 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 162 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 572 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 24 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 24 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 19 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.91% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.83% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 035 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 465 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 25 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 572
مشترکین
+1924 ساعت
+197 روز
+2430 روز
آرشیو پست ها
photo content
+4

የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን የመረጃ አያያዝ ለማዘመን የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው፤ ….//…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን የመረጃ አያያዝ ለማዘመን በተዘረጋው የአሰራር ሥርዓት (EEP POWER DATA MANEGEMENT SYSTEM) ላይ የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠ መሆኑን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለፀ፡፡ በዘርፉ የዕቅድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት የኃይል መረጃ አያያዝ ሥርዓቱ በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ክፍል ከ8 ወር በላይ ጊዜ ወስዶ መልማቱን ተናግረዋል፡፡ እስከ አሁን የኃይል ማመንጫዎች የኦፕሬሽን መረጃ በስልክ፣ በቴሌግራምና በኢሜል በመሰብሰብ ለሚመለከታቸው ኃላፊዎች በኢሜል ሲላክ መቆየቱን የጠቆሙት ወ/ሮ ጥሩወርቅ ይህም ጊዜ ይወስድና ለመረጃ ስህተት ይዳርግ ነበር ብለዋል፡፡ በተቋሙ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ክፍል በራስ ኃይል የለማው የኃይል መረጃ አያያዝ ሥርዓቱ የሁሉም ኃይል ማመንጫ የኦፕሬሽን መረጃዎች ሰርቨር ላይ እንዲቀመጥ በማድረግ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ወቅታዊ መረጃ ለመከታተል እና ግብረ መልስ ለመስጠት የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዶ የአሰራር ሥርዓቱን አጠቃቀም እና የመረጃ አያያዝን አስመልክቶ ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለተላኩ የኦፕሬሽን ሠራተኞች ከጥቅምት ወር ጀምሮ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በዚህም እስከ አሁን ለ18ቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ስልጠና መስጠታቸውንና በቀረው የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደግሞ ቦታው ድረስ በመሄድ ስልጠናውን ለመስጠት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+4

የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታውን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው …….///…….. የመቱ - ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ዝርጋታ ከየካቲት 2017 ዓ.ም. በፊት ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው አሳዬ እንደገለፁት 70 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የማስተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ዝርጋታ በተለያዩ ንዑስ ሥራ ተቋራጮች ተከፋፍሎ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ 174 የብረት ምሰሶዎች ካሉት የማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ውስጥ የ168 ምሰሶዎች ተከላ መጠናቀቁንና የቀሪዎቹን ስድስት ምሶሶች ተከላ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከ36 ኪሎ ሜትር በላይ የመስመር ዝርጋታ መጠናቀቁንና ቀሪውን ሥራ እስከ ጥር 2017 ዓ.ም. ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ የኮንዳክተር ዝርጋታው አፈጻጸም ከ50 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን ፕሮጀክቱን በተያዘው መርሃግብር ለማጠናቀቅ ኮንትራክተሩ ሦስት ተጨማሪ የዝርጋታ ንዑስ ኮንትራክተሮችን በማስገባት ሥራውን እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት ከአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ጋር በተያያዘ የፕሮጀክቱ አበዳሪ ባንክ ያነሳው ጥያቄ በውጭ አማካሪ ድርጅት ተጨማሪ ጥናት ተደርጎበት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ የሚዘረጋበትን አቅጣጫ በመቀየር ለችግሩ መፍትሔ ተሠጥቷል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ ከዓለም ባንክ በተገኘ የ6 ነጥብ 34 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ብድር እና ከ2 መቶ 97 ነጥብ 78 ሚሊዮን ብር በላይ በመንግስት በተመደበ በጀት እየተገነባ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

ተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማቶቹን ለማዘመን በትኩረት እየሠራ ነው፤ ....//.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዳዲስ የሚሠራቸውን እና ነባር የኃይል መሠረተ ልማቶችን ለማዘመን ትኩረት ስጥቶ እየሠራ መሆኑን ገለጸ። በተቋሙ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስኃ ጌታቸው እንደገለጹት ተቋሙ የኃይል ስብጥሩን በጠበቀ መልኩ ተደራሽነቱን የሚያረጋግጡ የኃይል ማመንጫዎችን፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮችን እየገነባና እያስተዳደረ ይገኛል። እነዚህን የኃይል መሠረተ ልማቶችን በማዘመን የኃይል ብክነትን በቀነሰ መልኩ በአገሪቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በዘላቂነት ለማሟላት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። በዚህም አዳዲስ የሚገነቡ የኃይል መሰረተ ልማቶች ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጅ የታገዙ እንዲሁም ዓለምአቀፍ የጥራትና ደህንነት መስፈርቶቹን ያሟሉ እንደሆኑ ጠቁመዋል። ነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጂ አይ ኤስ ብሬከሮችን ቅየራ ጨምሮ ውጤታማነታቸውን የሚጨምር የማዘመንና አቅማቸውን የማሳደግ ሥራም እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ ፍስኃ ረጅም ጊዜ ባገለገሉ ማመንጫ ጣቢያዎች ላይም የመልሶ ግንባታ ሥራ በእቅድ ተይዞ እንደሚከናወን ገልጸዋል። ተቋሙ አሁን ላይ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ቀለበት(ሪንግ) በማድረግ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ጥረት እያደረገ ከመሆኑም ባሻገር የኃይል ብክነትን የሚቀንሱና አሰራሩን የሚያዘምኑ ስማርት ሜትር፣ ሳፕ እና ሳውዝ ክላውድ የሚባሉ ቴክኖሎጂዎችን ሥራ ላይ ማዋሉን ተናግረዋል፡፡ የኃይል መሰረተ ልማቶችን ማዘመን ደህንነታቸውን በማስጠበቅ እና የኃይል መቆራረጥን በመቀነስ የኃይል ፍላጎቱን በማሟላት በኩል ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። የኃይል ፍላጎቱን ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት የታወር ስርቆት፣ የተጋነነ የካሳ ክፍያ፣ የኃይል ማመንጫ ወሰኖችን አልፎ የሚደረግ እርሻ ለተቋሙ ተግዳሮት እንደሆኑበት የጠቆሙት አቶ ፍስኃ የአካበቢው መስተዳድሮች እና ማህበረሰቡ እነዚህ መሰል ችግሮች እንዲቀረፉ በማድረግ በኩል የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የቃል ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ---///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡
የቃል ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ---///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይልድ ኬር የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት የፅሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ከዚህ በታች ከተራ ቁጥር 1 እስከ 17 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ሰራተኛ ምደባ ቢሮ የቃል ፈተና (Interview) የሚሰጥ ስለሆነ ይህንን አውቃችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም

በጣቢያው ተጨማሪ የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው ….....///…..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተጨማሪ የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው የሰው ኃይል አስተዳደርና የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡   ሥራ አስኪያጁ አቶ የበጋእሸት ስርጉ እንደገለጹት የጣቢያው የድጋፍ ሰጭ ሠራተኞች አብዛኞቹ የተቀጠሩት ከአካባቢው ማህበረሰብ በመሆኑ በጣቢያው የመኖሪያ ቤት አልነበራቸውም፡፡ ይህም ሠራተኞቹ ሥራቸውን በቅርበት ሆነው እንዳያከናውኑ ተፅዕኖ ማሳደሩን ተናግረዋል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም 72 የመኖሪያ ቤቶች እና 15 ለጋራ አገልግሎት የሚውሉ በድምሩ 87 ቤቶችን የያዘ ሦስት ባለ አራት ፎቅ ሕንጻዎች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የቤቶቹ ግንባታ መዘግየት ቢያጋጥምም  ቀሪ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ ቤቶቹ ሲጠናቀቁ ሠራተኞች ሥራቸውን በቅርበት ለማከናወን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር የገለጹት ሥራ አስኪያጁ ከቤቶች ግንባታ ጎን ለጎን ጣቢያው ለሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን ለመፍጠር የሚያስችሉ ሌሎች በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ከዋቸሞ የኒቨርስቲ ጋር በመተባበር መምህራንን ጣቢያው ድረስ በማምጣት ሠራተኞች በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው በኤሌክትሪካል እና በኮምፒዩተር ኢንጅነሪንግ የትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እየተደረገ ይገኛል፡፡ የሁለተኛ ዲግሪ ትምርታቸውን መማር ለሚፈልጉም ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ጋር ውይይት መጀመሩንም ገልፀዋል፡፡ የሠራተኛ ቤተሰቦችን ጭምር ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ በቴክኒክና ሙያ ከአንድ መቶ በላይ ሠራተኞችንና የሠራተኛ ቤተሰቦችን አስተምሮ ማስመረቁንም ተናግረዋል፡፡ ለሠራተኞችና ለአካባቢው ማህበረሰብ ልጆች የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ከፍቶ ከ110 በላይ ህጻናት እየተማሩ መሆኑን አውስተው በቀጣይ የትምህርት ዘመን የአንደኛ ክፍል ለመክፈት ከወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ጋር መግባባት ላይ መደረሱንም አስታውቀዋል፡፡ ሠራተኞች ትርፍ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉባቸው የመዝናኛ አማራጮች በጣቢያው ጊቢ መኖራቸውን አውስተው የጊቢውን እንዲሁም ከኃይል ማመንጫው ወደ ስዊች ያርድ የሚወስደውን መንገድ ለማስራት በሂደት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ምቹ የሥራ ከባቢን በመፍጠር የጣቢያው ሠራተኞች ተረጋግተው ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያከናውኑ የሚያደርጉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡ የጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአሁኑ ወቅት 287 ቋሚ ሠራተኞች አሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ........///......... የደብረ ብርሃን ቁጥር አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግና የማሻሻያ ሥራዎችን ለማከናወን እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ አደፍርስ በለጠ እንደገለፁት ከ1970ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ በሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ሊከናወኑ የታቀዱት የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ለደብረ ብርሃን ከተማና ለአካባቢው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ናቸው፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለአዳዲስ ደንበኞች ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ እንዲችል በ33 ኪሎ ቮልት መስመሮች ላይ የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎች መከናወናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም በ15 ኪሎ ቮልት መስመሮች ላይ የዘመናዊ ስዊች ጊር ገጠማ ሥራዎችን ለማከናወን እንቅስቃሴ መጀመሩን የጠቀሱት አቶ አደፍርስ ይህም የጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራዎች ለማዘመን እንደሚያስችል ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ በመቆየቱ ምክንያት በመቆጣጠሪያ ክፍሉ ውስጥ የነበሩት በአየር የሚሰሩት ስዊች ጊሮች በተደጋጋሚ ለብልሽት ስለሚዳረጉ ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ ያጋጥም ነበር። መቆጣጠሪያው በዘመናዊ የጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር መቀየሩ የኃይል መቆራረጥንና በጥገና ሥራዎች ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በመቅረፍ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚረዳም ነው የጠቆሙት። ማከፋፈያ ጣቢያው 31 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ያለው አንድ ባለ 25 እና አንድ ባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች እንዳሉትም ነው የገለፁት። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 132፣  አምስት ባለ 33 እና አራት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። ጣቢያው ከለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ በአስሩ የ132፣ 33 እና 15 ኪሎ ቮልት መስመሮች ለሽዋሮቢት፣ ደብረ ብርሃን ፣ መንዲዳ፣ አንኮበር፣ ሰላድንጋይ እንዲሁም አልዩ አምባ ከተሞች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው የሚገኘው ባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር በ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ለዳሽን ቢራ ፋብሪካ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝም ነው የጠቆሙት። በአሁኑ ወቅት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ውስጥ በሥራ ላይ የሚገኘው ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር ተጨማሪ ኃይል የመሸከም አቅም እንደሌለው የጠቆሙት አቶ አደፍርስ ኃይል የመጫን አቅማቸው ከፍ ባሉ ትራንስፎርመሮች እንዲቀየሩ ጥያቄ መቅረቡንም ነው የተናገሩት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

በምስራቅ ኢትዮጵያ የተቋረጠው ኃይል መልሶ ተገናኝቷል ……..///…….. የድሬዳዋ - ሀረር- ጅግጅጋ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የምስራቅ አንድ ሪጅን የ
በምስራቅ ኢትዮጵያ የተቋረጠው ኃይል መልሶ ተገናኝቷል ……..///…….. የድሬዳዋ - ሀረር- ጅግጅጋ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የምስራቅ አንድ ሪጅን የኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሐመድ እንደገለፁት ለሀረር፣ ጅግጅጋ እና ለሌሎች የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞች ኃይል የተቋረጠው የማስተላለፊያ መስመሩ አንዱ ፌዝ በመበጠሱ ምክንያት ነበር። ችግሩን ለመለየት አስቸጋሪውን የደንገጎን ተራራ በእግር በመጓዝ ፍተሻ መከናወኑን የተናገሩት ዳይሬክተሩ የተበጠሰውን የኃይል ማስተላለፊያ  መስመር በመጠገን አገልግሎቱን ዳግም መመለሱን ገልፀዋል። በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ ደንበኞች በትግዕስት ስለጠበቁ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የጨረታ ማጠናቀቂያ ጊዜ ለማራዘም የወጣ ማስታወቂያ ተቋማችን አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በሽያጭ ለማስወገድ ሕዳር 27/2017 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በቁጥር EEP/DS/01/17 የጨረታ ማስታ
የጨረታ ማጠናቀቂያ ጊዜ ለማራዘም የወጣ ማስታወቂያ ተቋማችን አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በሽያጭ ለማስወገድ ሕዳር 27/2017 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ  በቁጥር EEP/DS/01/17  የጨረታ ማስታወቂያ መውጣቱ ይታወሳል። ይሁንና የጨረታ ሂደቱ በዲጂታል ስርዓት የሚከናወን በመሆኑ ተጫራቾች ንብረቶቹ ያሉበት ቦታ ሄደው ለመመልከት የጊዜ ማነስ ስለገጠማቸው  የጨረታ ጊዜው እንዲራዘም ጥያቄ ቀርቧል። በመሆኑም ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ይጠናቀቅ ተብሎ የነበረው ጨረታ እስከ ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ የተራዘመ መሆኑን እናሳውቃለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ደረጃውን አሻሻለ .......///....... በ10ኛ ሳምንት የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አርባምንጭ ከነማን አንድ ለባዶ ረቷል። የማሸነፊያዋን ብቸኛ ጎል ፀጋነሽ ወራና በ37ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፋለች። በሁለቱም ቡድኖች በኩል ብርቱ ፉክክር በታየበት በዚህ ጨዋታ ኳስን ተቆጣጥሮ ወደ ፊት በመጫወት ረገድ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የተሻለ ነበር። አርባምንጭ ከነማ በአንፃሩ ረጃጅም ኳሶችን በመጠቀም ወደ ጎል ለመድረስ ጥረት ቢያደርግም ሳይሳካለት ቀርቷል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ተጫዋች የሆነችው እፀገነት ብዙነህ የጨዋታው ኮከብ በመሆን ሽልማት ተበርክቶላታል። የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በሊጉ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በ11ኛ ሳምንት መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከነማ  ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጫወት ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ሁለተኛው ዙር የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ የውስጥ ኦዲት ሊጀመር ነው ---///--- ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ የጥራት አስተዳደርና ኦዲት ሠራተኞች በጥራት አስተዳደር ሥርዓት የውስጥ ኦዲት ዙሪያ የገንዛቤ ማሳደግያ ስልጠና ተሰጠ፡፡ ስልጠናው በመጀመሪያው ዙር የታዩ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ በዋናው መ/ቤት በሚገኙ በሁሉም የስራ ክፍሎች የሚጀመረውን የጥራት አስተዳደር ሥርዓት የውስጥ ኦዲት ትግበራ በተሻለ ብቃት እንዲከውኑ ያስችላቸዋል፡፡ ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ተቋሙ የሦስት ዓመት ስትራቴጂካል ዕቅድ ቀርጾ ወደ ትግበራ መግባቱን አስታውሰዋል፡፡ ከስትራቴጂካል ዕቅዱ አንዱ ተቋሙን አይኤስኦ 9001.2015 የጥራት ሥራ አመራር አሰራር ስርዓት (ISO 9001.2015 Quality Management Systems) በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ እውቅና እንዲያገኝ ማስቻል ነው፡፡ ተቋሙ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ እውቅና ማግኘቱ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ይዞ እንደሚመጣ የጠቆሙት ሥራ አስፈጻሚው የስራ ክፍሎቹ ለውስጥ ኦዲት ሥራው መሳካት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የውስጥ አዲቱ የስራ ክፍሎችን ለመተቸት፣ ስህተታቸውን ለማጉላት ሳይሆን በሰራ ክፍሎቻቸው አላሰራ ያሉ አሰራሮችን በመለየት፣ ያሉባቸውን የአሰራር ክፍተቶች በማሻሻል፣ በመሙላት እና መፍትሄ በማስቀመጥ የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እንደሆነ አቶ አንዱዓለም ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ የእቅድ ዝግጅት፣ ክትትል እና ግምገማ ዳሬክተር ወ/ሮ ልደት ዘሪሁን በበኩላቸው የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራው የተቋሙን የአገልግሎት ጥራት ለማሳደግ፣ ወጪዎችን ለመቀነስ እና ምርታማነትን ከፍ ለማድረግ እንዲሁም የስራ ክፍሎቹን ዓሰራር በተቀመጠው የዓሰራር መለኪያ እና መስፈርት መሰረት ስራው መከናወኑን ለመለየት ያስችላል ብለዋል፡፡ ተቋሙ ከ2015 ዓ›ም. ጀምሮ የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ እያከናወነ እንደሚገኝ የተናገሩት ወ/ሮ ልደት ሰልጣኖች ከዚህ በፊት ያገኙትን የተለያዩ ሰልጣናዎች ለመከለስ፣ ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ የተግባር ተሞክሮ እና ልምድ በማካፈል የውስጥ ኦዲት አቅማቸውን ለማሳደግ ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ የውስጥ ኦዲቱ እየተገበረ የሚገኘውን የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ምን ላይ እንደለ ለመፈተሸ እና በቀጣይ በውጭ ለሚካሄደው የኦዲተር ሥራ ያሉብንን ክፍተቶች አርሞ በብቃት ዝገጁ ለመሆን ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡ በዓለም ዓቀፍ እውቅናን ለማገኝት ተቋሙ በቀጣይ በውጭ ድርጅቶች የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ኦዲተሮች እንደሚታይ እና የኦዲተሮቸን ግኝት ተንተርሶ እወቀናው እንደሚሰጠው ተገልጿል፡፡ የሁለተኛው ዙር የውስጥ ኦዲት የጥራት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በዋናው መስሪያ ቤት በሚገኙ የስራ ክፍሎች ለመጀመር ታቅዷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በጣቢያው የቤቶች እድሳት እየተከናወነ ነው .........///......... የጣቢያውን ሠራተኞች መኖሪያ እና የእንግዳ ማረፊያ ቤቶችን እድሳት እያከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ገለጸ። የጣቢያው ሲቪል መሐንዲስ አቶ ምንተስኖት ወዬሳ እንደገለጹት በጣቢያው የሚገኙ ቤቶች ረጅም ዓመት ያገለገሉ በመሆናቸው ከፍተኛ ጉዳት አጋጥሟቸዋል። በጣቢያው 68 የሠራተኛ መኖሪያ እና የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች መኖራቸውን የጠቆሙት አቶ ምንተስኖት በየምዕራፉ አስር ቤቶችን ለማደስ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እስከ አሁን 18 የሠራተኛ መኖሪያና አንድ የእንግዳ ማረፊያ ቤት እድሳት ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ከቤቶቹ እስከ ሦስት ሜትር ድረስ የተተከሉ ዛፎች የሽንት ቤት መስመሮችን የመዝጋትና በሕንጻዎቹ ላይ የመሰንጠቅ አደጋ መፍጠራቸውን የተናገሩት ባለሙያው ዛፎቹን በመቁረጥ የሻወር፣ የሽንት ቤትና የእጅ መታጠቢያ እቃዎችን ሙሉ በሙሉ በመቀየር የእድሳት ሥራው እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተጨማሪም የጣራ መቀየርና መጠገን፣ የመሬት ፕላስቲክ ታይልስ እና የኮርኒስ መቀየር እንዲሁም የኤሌክትሪክ መስመር ዕድሳት፣ የዝገት መከላክያ እና የቀለም ቅብ ሥራዎችም የእድሳቱ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል። የቀሪ ቤቶችን እድሳትን ለማጠናቀቅም ታቅዶ እየተስራ መሆኑን ጠቁመዋል። ለጣቢያው ሠራተኞች ምቹ የመኖሪያ ከባቢን ለመፍጠር ኮሚቴ በማቋቋም ሌሎች ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል። አቶ ምንተስኖት እንዳሉት ከቤቶቹ ዕድሳት ጎን ለጎንም የመኖሪያ ጊቢውን ገፅታ የማስዋብ ሥራም ተጀምሯል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content