en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 553 subscribers, ranking 8 395 in the Technologies & Applications category and 2 164 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 553 subscribers.

According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 5 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.99%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 043 views. Within the first day, a publication typically gains 2 393 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“EEP Communication”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 553
Subscribers
+124 hours
+47 days
+530 days
Posts Archive
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት አመታት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ሽፋንን 100% ለማዳርስ ትሰራለች …///… ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ አጋርነት በማጠናከር 54 በመቶ የሆነውን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት በ2022 ዓ.ም 100% ለማድረስ እየሰራች መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መሾመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የሀገሪቱን የኃይል ዘርፉ ኢንቨስትመንት ማሻሻል እና ማዘመን ላይ ያተኮረ ወርክሾፕ በዛሬው ዕለት አካሂደዋል፡፡ በዘርፉ የፕሮግራም ሁለት ዳይሬክተር አቶ ደስታለም ኃይሉ በወርክሾፑ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በኃይል አማራጭ ላይ እየስራች ያለውን መጠነ ሰፊ ሾል ጠቅሰው የኃይል ተደራሽነት ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራች እንደምትገኝ ገልፀዋል፡፡  በውይይት መድረኩ በዓለም ባንክ እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተወካዮች፣ የስራ ተቋራጮች እና ተበዳሪዎች ፕሮጀክቶችን በጨረታ አሸንፈው የብድር አገልግሎት በሚያገኙባቸው ጉዳዮች ላይ  ለመወያያ የሚሆኑ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡  በዓለም ባንክ የፕሮክዩርመንት ባለሙያ አቶ አማረ አሰፋ ባቀረቡት ሰነድ ባንኩ በኢነርጂ፤ በትምህርት፤ በፆታ፤ በአየር ንብረት ዘርፎች እና መሰል ጉዳዮች ላይ ለተበዳሪዎች የራሱን ፕሮግራም ቀርፆ እንደሚሰራ ገልፀው ተበዳሪዎች ስለባንኩ ማወቅ ያለባቸዉን ጉዳዮች በዝርዝር አስረድተዋል፡፡ እንደ አቶ አማረ ገለፃ ባንኩ በዓለም ላይ በ327 ቢሊዮን ዶላር 1,819 ፕሮጀክቶችን እያስፈፀመ መሆኑን ገልፀው ከእነዚህ ፕሮጀክቶች 41 በመቶዉ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ላይ እንደሚገኙ አስታውሰው ተበዳሪዎች የፋይናንስ አቅርቦትን ከባንኩ ለማግኘት የሚችሉበትን የአሠራርና የተቋሙን ህገ-ደንቦች አብራርተዋል፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፕራይም አንድ ሊያስገነባቸዉ ያሰባቸዉን ስድስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ጨምሮ ተቋሙ በማከፋፈያ ጣቢዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ እየሰራቸው ያለውን የማዘመን እና የማስፋፋት ስራዎችን አስመልክቶ በተወካዩ አቶ ታደሰ ብሩ ቀርቧል፡፡  መድረኩ በዋናነት ፕሮጀክቶች በታለመላቸዉ ጊዜ እና ጥራት ተጠናቀው አገልግሎት ላይ እንዲዉሉ የግዥ ሂደት ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፤ አቅራቢዎች እና ፍላጎቱ ያላቸው ተቋማት በቀረበው ሰነድ ላይ ሀሳባቸውን እንዲሰጡ እና የገበያ ዕድሉን ለማስፋት ያለመ መሆኑን በመድረኩ ተመላክቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው ከ520 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል …///….. የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 527 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረቱን የጣ
+5
ጣቢያው ከ520 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል …///….. የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 527 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረቱን የጣቢያ የኦፕሬሽን ክፍል ሼል አስኪያጅ ተናገሩ። ሼል አስኪያጁ አቶ ተክሉ ጎንፋ እንደተናገሩት ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 488 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 527 ጊጋ ዋት ሰዓት አመንጭቷል። ይህም ከዕቅዱ የ39 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ7 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን በበጀት ዓመቱ በጣቢያው የተከናወኑ የፍተሻና ጥገና ሥራዎች የተርባይኖችን የማመንጨት አቅም ማሳደግ መቻሉን  ሼል አስኪያጁ ተናግረዋል። ከሚያዚያ 1980 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል በማምረት ላይ የሚገኘው የመልካ ዋከና የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 153 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢዉ የነበረውን የኃይል አቅርቦት ችግር አቃሏል ..…///…. የቱለፋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሸ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቡልጋ ከተማ እና አካባቢው ለበርካታ ዓመታት ፈተና ሆኖ የቆየውን የኃይል አቀርቦት ችግር ማቃለሉን የቡልጋ ከተማ የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት አስታወቀ። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሸዋየ ማሞ እንደተናገሩት በቡልጋ ከተማ እና አካባቢው ከ256 በላይ ባለሃብቶች በአምራች ኢንደስተሪዎች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዘርፍ መሰማራታቸውንና ከእነዚህ ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት ወደ ምርት ገብተዋል፡፡  በቡልጋ ከተማ እና አካባቢዉ ለሚገኙና ወደ ምርት ለገቡት አምራች ኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦት ተደራሽ በማድረግ ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን አብራርተዋል። በ2012 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሼል የገባው የቱለፋ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ያለውን የኃይል አቅርቦት ችግር እያቃለለ ቢመጣም ቀሪዎቹን ፋብሪካዎች ወደ ምርት ለማስገባት ከተማዉ ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልገው ገልፀዋል።  ከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችና ወደ ከተማዋ እየመጡ ያሉ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎችን አሁን ላይ ባለው የቱለፋ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ብቻ ለማስተናገድ የሚቻል አለመሆኑን አብራርተዋል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በከተማዋ ያለውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ ሼል ቀድሞ እንዲያከናውን የጠየቁት አቶ ሸዋየ ለዚህም ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግና ከተቋሙ ጋር ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የከተማ መስተዳደሩ ለኢንቨስትመንት ያለውን ተመራጭነት ግምት ውስጥ በማስገባት መመስረቱን የገለፁት ኃላፊው በርካታ የአገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስተሮች በተለያዩ ዘርፎች በስፋት እየተስማሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

💡የግንባታ ማሽነሪዎችን በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥር ማንቀሳቀስ የሚኖረው ጉዳት 📌 የኤሌክትሪክ ዥረት (current) የብረት ይዘት ያላቸው ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ቁሶች ላይ በቀላሉ ስለሚተላለፍ እና ከኤሌክትሪክ ጋር በቀጥታ ስለሚገናኝ በማሽነሪዎቹም ሆነ በሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፡፡ በማሽነሪዎቹ እንቅስቃሴ የተነሳ አየሩን ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ሊያደርገው ይችላል፡፡ 📌 ከከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጋር መቀራረብ ከፍተኛ የኤሌክትሮ ማግኔቲክ እንቅስቃሴ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህም የኮሙዩኒኬሽን፣ የመቆጣጠሪያ እና የማንቂያ መሳሪያዎች በአግባቡ እንዳይሰሩ በማድረግ ማሽኖች ያልተጠበቀ ባህርይ እንዲያሳዩና እንዲጎዱ ሊያደርግ ይችላል፡፡ 📌 ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በከፍተኛ ሙቀት፣ በንፋስ እና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ ምክንያቶች ሊረግቡ ስለሚችሉ ከመስመሮቹ ጋር ድንገተኛ መነካካት በመፍጠር አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ 📌 የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እንደ መካከለኛ እና ዝቅተኛ የስርጭት መስመሮች ኃይል በማያስተላልፍ ጎማ ወይም ኢንሱሌተር ስለማይሸፈኑ ኤሌክትሪክ በቀላሉ ወደማሽነሪዎቹ ሊተላለፍ ይችላል፡፡ አደጋ ተከስቶ ማሽነሪውን ለመንቀሳቀስ ቢፈለግ እንኳ የማሽነሪው ጎማዎች እንዲቃጠሉ ስለሚያደርግ በጥቅሉ የማሽነሪዎች ሙሉ ቃጠሎ እና የሰው ህልፈት እንዲከሰት ምክንያት ይሆናል፡፡ 📌 በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚደርስ ጉዳት ኃይል እንዲቋረጥ ከማድረግ ባለፈ የታወቆች መውደቅ በአቅራቢያቸው የሚገኙ ህንፃዎች እንዲጎዱ ሊያደርግ ይችላል፡፡ 📌 ስለሆነም ወደ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹ ቀርቦ ማሽነሪዎችን አለማንቀሳቀስ፣ የግድ ከሥራቸው የሚሰራ ነገር ሲኖር ኃይል መቋረጡን ማረጋገጥ፣ የቅርበትን/የርቀትን መጠን የሚያሳይ ምልክት ማስቀመጥ፣ ማሽነሪዎችን በቀጥታ በሰውነት ላለመንካት መጠንቀቅ እና የአስቸኳይ ጊዜ የጥንቃቄ ርምጃዎችን መተግበር ያስፈልጋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

‎በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ለኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆኑ ነገሮች፡- ‎•  የኃይል መዋዠቅ (voltage fluctuation)፤ ‎•  ከፍተኛ የኃይል ጭነት (overload)፤ ‎•  በኃይል መሾመሊ ሼር እና አካባቢው የሚኖሩ ዛፎች፤ ‎•  ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ፤ ‎•  ያረጀ እና የተጎዳ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር፤ ‎•  የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት፤ ‎•  መንገድ መቋረጫ ላይ ጭነት የጫኑ መኪኖች መስመሩን ሲነኩት፤ ‎ ‎ ‎ችግሩን ለመከላከል እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች፡- ‎ ‎•  መንገድ የሚሻገሩ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ በመጨመር፤ ‎•  በመስመሩ ሾር ያሉ ዛፎችን በመቁረጥና የአፈር ክምችት በማስወገድ፤ ‎•  ያረጁ መስመሮችን በአዲስ የመተካት (reconductor) ሼል በመስራት፤ ‎•  ከፍተኛ የኃይል ጭነት ያለባቸው መስመሮች በማጥናት ሌላ አጋዥ መስመሮችን በመዘርጋት፤ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ ለመጨመር ጥናት እየተከናወነ ነው፤ …..///…. ትልልቅ ዕቃዎች በተሽከርካሪ ተጭነው የሚያልፉባቸውና መንገድ የሚሻገሩ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ ለመጨመር ጥናት እየተከናወነ መሆኑን የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ማስተባበሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት ተቋሙ በሚያስተዳድራቸው ከ132 እስከ 500 ኪሎ ቮልት የቮልቴጅ መጠን ያላቸው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከመሬት ሊኖራቸው የሚገባ ከፍታ (minimum clearance) እንደቮልቴጅ መጠናቸው የተለያየ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ለባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ቢያንስ 6 ነጥብ 1 ሜትር፣ ለባለ 230 ኪሎ ቮልት 7 ሜትር፣ ለባለ 400 ኪሎ ቮልት 8 ነጥብ 84 ሜትር እንዲሁም ለባለ 500 ኪሎ ቮልት 9 ነጥብ 45 ሜትር ከመሬት ከፍታ ሊኖራቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ሆኖም በግንባታ ግዜ ስታንዳርዱን ጠብቆ ባለመዘርጋት፣ በሙቀት ምክንያት ኮንዳክተር ረዝሞ ሲረግብ፣ መንገድም ይሁን ቤት ሲሰራ አዲስ አፈር በመስመሩ ስር ሲራገፍ እና መሰል ምክንያቶች ከፍታው በሚጠበቀው ልክ ያለመሆን ችግሮች እንደሚስተዋሉ ተናግረዋል፡፡ ይህም በተሸከርካሪዎች ተጭነው በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ስር የሚያቋርጡ ከፍታ ያላቸው ብረት ነክ ዕቃዎች ዓለም አቀፍ አሰራሮችን በጠበቀ መልኩ እንዲያልፉ እንቅፋት የሚፈጥር ከመሆኑ ባሻገር ለኃይል መቆራረጥና ለአዳጋ የሚዳርግ ነው ብለዋል፡፡ በመስመሩ ስር ያሉ ዛፎችን በመቁረጥና የአፈር ክምችት በማስወገድ፣ ያረጁ መስመሮችን በአዲስ በመተካት፣ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ቁመት በመጨመር፣ ዓመታዊ ክትትል በማድረግ እና ችግሩን በጊዜያዊነት ለመከላከል እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል። አሁን ላይ ከጣናነሽ ጀልባ የየብስ ጉዞ ጋር በማያያዝ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከመሬት ያላቸውን ከፍታ በዘመናዊ መሳሪያ በመለካት መረጃዎችን የማደራጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት አቶ ተስፋዬ መንገድ የሚሻገሩ መስመር ላይ ያሉ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ከፍታ ለመጨመር ጥናት እየተከናወነ ነው ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ዘርፉ እንደአዲስ ከተደራጀ በኋላ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ መሻሻል እየታየ ነው፤ ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያካሄደ ባለው ተቋማዊ ለውጥ ዘርፉ እንደአዲስ ከተደራጀ በኋላ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ መሻሻሎች መታየታቸውን የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሼል አስፈፃሚ አስታወቁ። ‎ ‎ዘርፉ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ከሚመለከታቸው የመምሪያና የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ገምግሟል፡፡ መድረኩ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ አበይት ተግባራትን፣ የተመዘገቡ ውጤቶችን፣ የነበሩ ክፍተቶችን እና ሥራዎች ሲመሩበት የነበረውን አግባብ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ለመስጠት ያለመ ነው፡፡ ‎ ‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሼል አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ከዲዛይን ጀምሮ እስከ ፕሮጀክት ትግበራ እና አፈፃፀም ድረስ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ ዘርፉ እንደ አዲስ በአምስት መምሪያዎችንና በሁለት  ቢሮዎች መደራጀቱን ገልፀው ይህም ከዲዛይን ጀምሮ የሚታዩ ችግሮችን በቅርበት በመፍታት እንዲሁም የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን በማጠናከር የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ማሻሻል መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት እና በውጭ የሥራ ተቋራጮች የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቁ የሚያስችሉ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በመስራት የኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲቀላጠፉ በማድረግ ተቋማዊ ለውጡን እያገዘ ነው ብለዋል፡፡ ቀደም ሲል የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ በርካታ ፕሮጀክቶችን ሲያከናውን የቆየ ቢሆንም በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ ክፍተቶች ይስተዋሉበት እንደነበር አቶ ውድነህ አስታውሰዋል፡፡ ሆኖም ዘርፉ ባካሔደው የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታቸው ሲጓተቱ የነበሩ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በማሻሻል መምሪያው ያከናውናቸው ከነበሩ ፕሮጀክቶች ውስጥ ከ90 በመቶ በላይ መጠናቀቃቸውንም አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም ከአላማጣ - ኮምቦልቻ- ለገጣፎ ኃይል ሳይቋረጥ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መሾመር ሽቦ ዝርጋታን በኮንስትራክሸን ማኔጅመንት ወይም ልሾ ኃይል መምሪያ ማከናወን መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡ ዘርፉ ወደፊት የተሟላ ሼል ተቋራጭ ለመሆን ካቀደው ዕቅድ አንፃር ትርፋማ መሆን አለበት ያሉት አቶ ውድነህ በ2017 በጀት ዓመት በፕሮጀክት አፈፃፀም ላይ የተመዘገበውን ስኬት በማጎልበትና ተቋማዊ አቅሙን በማሳደግ ፕሮጀክቶች ትርፋማ የሚሆኑበትን መንገድ ለመፍጠር ይሰራል ብለዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የነበሩ ክፍተቶችን በማረም እንዲሁም የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማጠናከር ዘርፉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከአገር ውጭ በሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ ተሳታፊ ለመሆን የያዘውን ግብ ለማሳካት አመራሩና ሠራተኛው በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ተቋሙ ከ7 ሺ በላይ ለሚሆኑ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት ሰጥቷል፤ ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከለኛ ክሊኒክ በ2017 በጀት ዓመት 7 ሺ 330 ለሚሆኑ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው áˆ¨á‹łá‰ľ ሼል አስኪያጅ አቶ አድማሱ ተኽልቁ እንደገለጹት የተቋሙን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞችን ጤንነት ለማስጠበቅ ከበሽታ መከላከልና ህክምና አገልግሎት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን በጀት ዓመቱ አከናውኗል፡፡ በበጀት ዓመቱ በክሊኒኩ 5 ሺ 132 ወንድ እና 2 ሺ 198 ሴት ሠራተኞች የህክምና አገልግሎቱን ማግኘታቸውን እና ከእነዚህም ውስጥ በላቦራቶሪ አገልግሎት 2 ሺ 485 ያህል ወንድ እና ሴት ሠራተኞች መስተናገዳቸውን አስታውቀዋል፡፡ ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ግልጽ ጨረታ በማውጣትና በማወዳደር ከ 21 የህክምና ተቋሞች ጋር አዲሰ የህክምና አገልግሎት ሰምምነት በመፈራረም ከክሊኒኩ በላይ የሆኑ የጤና ችግሮች ሲያጋጥሙ ሠራተኛኞች ተልከው እንዲገለገሉ መደረጉን አስረድተዋል። በዚህም ከክሊኒኩ አቅም በላይ የሆኑ 5 ሺ 825 ሠራተኞች ወደ ተለያዩ የህክምና ተቋማት መላካቸውን እና 7 ሺ 56 ሠራተኞች ደግሞ በከነማ ፋርማሲ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልፀዋል። ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የክሊኒክ መድኃኒቶችን ከመድኃኒት ፈንድ ኤጀንሲ ግዥ በማከናወን እና ቦታው ድረስ በመሄድ የባለሙያ ድጋፍ መደረጉን የጠቆሙት አቶ አድማሱ ለወላይታ ሶዶ ቁጥር 1 እና 2 ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያዎች የወባ መከላከል እና መቆጣጠር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናና ህክምና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም በዋናው መ/ቤት ክሊኒክ የመድኃኒት መጋዘን ውስጥ የተቀመጡ መድኃኒቶች የመጠቀሚያ ጊዚያቸው ሳያልፍ ለኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲከፋፈል ተደርጓል ብለዋል፡፡ በሰሜን ሪጅን ለስምንት እንዲሁም በምሰራቅ 2 ሪጅን ለአምስት ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች በአቅራቢያቸው ከሚገኙ የጤና ተቋማት ጋር ስምምነት በመፍጠር የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን አስገንዝበዋል፡፡ እንደ አቶ አድማሱ ገለፃ በበጀት ለአጠቃላይ ህክምና ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የኃይል ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ ሥራዎች ማከናወኑን ሪጅኑ ገለፀ ‎.....///….. የኃይል ተደራሽነትን ይበልጥ የሚያጎለብቱ የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ማከናወኑን የሰሜን ምስራቅ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደተናገሩት በሪጅኑ ውስጥ ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች የማስፋፊያ፣የአቅም ማሳደግና የጥገና ሥራዎች ተከናውኗል፡፡ የከሚሴ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅምን ለማሳደግ 50 ኤም ቪ ኤ ፓወር ትራንስፎርመር ተከላ እንዲሁም በኮምቦልቻ 2 እና በጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጂ አይ ኤስ ገጠማ ሥራ የተከናወነ መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ ያስታወቁት፡፡ የኃይል መቋረጥን ከመቀነስ አንፃር በስርቆት እና በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት የደረሰባቸውን ከ13 በላይ የኃይል ማስተላለፊያ ምሶሶዎች (ታዎሮች) ጥገና በማከናወን ወደ አገልግሎት እንዲመለሱ ማድረግ ተችሏል፡፡ አቶ በድሩ እንደገለፁት በአራት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የጥበቃ ማማ እና የስቶር ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ የስራ ከባቢን ለሠራተኞች ምቹ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ የውሃ ችግር የነበረባቸው አራት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውሃ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ የመፈፀም አቅምን ለማጎልበት የሚረዱ በመሰረታዊ ኮምፒውተር፣ በዘመናዊ የአሰራር ስርዓት እና የስራ ደህንነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለ143 ሠራተኞች ተሰጥቷል፡፡ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን በአጠቃላይ ስምንት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በስሩ ይገኛሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን አከናውኗል ‎.....///….. ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፉ በ2017 በጀት ዓመት ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ማከናወኑን የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ‎ ‎ዘርፉ በስሩ ከሚገኙ መምሪያዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡ ‎ ‎የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ እንደገለጹት ግምገማው ዘርፉ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በስሩ የሚገኙ መምሪያዎች በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ተግባራትን እና ያጋጠሙ ችግሮችን የጋራ በማድረግ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለመስጠት ያለመ ነው። ‎ ‎በተጨማሪም መምሪያዎቹ ያሉበትን ደረጃ እንዲያውቁ እና የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የሥራ ክፍሎችን ለማበረታታት የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ‎ ‎በዘርፉ ሥር የሚገኙት የሕግ አገልግሎት፤ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ፣ የሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ እንዲሁም የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያዎች የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸማቸውን በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል። ‎ የተቋሙን ጥቅም ከመጠበቅና ከመከላከል፣ ከገጽታ ግንባታ፣ አሰራሮችን ፈትሾ ከማስተካከል፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማሳደግ፣ ብልሹ አሰራርን ከመከላከልና ከመቆጣጠር እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርን ከማሳደግ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡ በሪፖርቶቹ ተመልክቷል። ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆትን በፈፀሙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከማድረግ ባሻገር ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል የብረት ምሰሶዎቹን ማህበረሰቡን በማሳተፍ በባለቤትነት እንዲጠብቃቸው ለማድረግ በቦርድ አቅጣጫ ተሰጥቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተገልጿል። ‎ከግብዓትና ከሰው ኃይል እጥረት፣ ሥራዎችን ከማዘመን፣ ከአቅም ግንባታ ሥራዎች ጋር በተያያዘ በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ክፍተቶች እንደነበሩም ተነስቷል፡፡ ‌‎አቶ ደጉማ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ በመምሪያዎቹ የተከናወኑ ተግባራት ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። ሁሉም መምሪያዎች በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ የበጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት አለባቸው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ግልፅ፣ አሳታፊና መተግበር የሚችል ዕቅድ በማዘጋጀት ለዘርፉ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9