ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 698 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 062,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 174

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 698 名订阅者。

根据 01 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 139,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 28.75%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.42% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 513 次浏览,首日通常累积 2 578 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 02 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 698
订阅者
+124 小时
+277 天
+13930 天
帖子存档
photo content

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የዋዜማ መርሐ ግብር በልዩ ድምቀት ተከናውኗል .......///......... ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት የዋዜማ መርሃግብር በድሮን ትርኢት እና በርችት ዝግጅቶች በደመቀ ድባብ ተከናውኗል። የዋዜማ መርሀግብሩ የተለያዩ ህብረ ቀለማዊ ትርኢቶች ቀርበውበታል። በመርሃ ግብሩ ላይ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የቀድሞው ም/ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ታድመዋል። ዛሬ የሀገራት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የግድቡ ምርቃት በይፋ የሚከናወን ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ጳጉሜን -3 የእመርታ ቀን እመርታ ለዘላቂ ከፍታ የወረስነው ዕዳ ብዙ፤ የምንጓዝበት መንገድ ረዥም፤ የሕዝባችንም ፍላጎት ሰፊ ነው፡፡ ቀስ በቀስ በሚደረግ የተለምዶ ጉዞ ወደምንፈልገው የብልጽግና ምዕራ
ጳጉሜን -3 የእመርታ ቀን እመርታ ለዘላቂ ከፍታ የወረስነው ዕዳ ብዙ፤ የምንጓዝበት መንገድ ረዥም፤ የሕዝባችንም ፍላጎት ሰፊ ነው፡፡ ቀስ በቀስ በሚደረግ የተለምዶ ጉዞ ወደምንፈልገው የብልጽግና ምዕራፍ አንደርስም፡፡ ያለን አማራጭ አንዳንድ እርከኖችን መዝለል ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ፈጠራና ፍጥነት ወሳኞች ናቸው፡፡ ከተለመደው መንገድ ወጣ ማለት፣ ከተለመደው ጊዜ በላይ መሥራት፣ ከተለመደው ዋጋ በላይ መክፈል ያስፈልገናል፡፡ ዓላማችን ከአንድ ምዕራፍ ወደ ሌላ ምዕራፍ መሻገር አይደለም፡፡ ከትናንት ዘለን ወደ ነገ መድረስ ነው፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 3 ቀን 2017 ዓ.ም

ጳጉሜን -2 የኅብር ቀን ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ ኢትዮጵያ በብዙ ጸጋዎች የተሞላች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ ጸጋዎቿ የተለያዩ ሳይሆኑ ልዩ ልዩ ናቸው፡፡ የባህል፣ የቋንቋ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔ፣ የእምነት
ጳጉሜን -2 የኅብር ቀን ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ ኢትዮጵያ በብዙ ጸጋዎች የተሞላች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ ጸጋዎቿ የተለያዩ ሳይሆኑ ልዩ ልዩ ናቸው፡፡ የባህል፣ የቋንቋ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔ፣ የእምነት፣ የጾታ፣ የአመለካከት፣ ወዘተ ብዝኃነት ያለንን የጸጋ ብዛት የሚያመለክት ነው፡፡ ብዝኃነት የኢትዮጵያ ታሪኳ እና መልኳ ነው፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም

በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሥር ግንባታ ማከናወን አደገኛ መሆኑን ምን ያህል ያውቃሉ? ከአዲስ ዌስት ወይም ከኮልፌ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ጥቁር አንበሳ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚሄደው መስመር ሥር አደገኛ የህንፃ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ተመልክተናል፡፡  ግንባታው ከአደገኛነቱ ባሻገር በቸልተኝነት የተከናወነ ተግባር ለመሆኑ የምትመለከቱት ምስል አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ግንባታው ከከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ ሥር መከናወኑ እንደ ፈሮ ብረት እና ቆርቆሮ ያሉ ኤሌክትሪክን የመሳብ አቅም ያላቸው የግንባታ ግብዓቶች ኤሌክትሪክን በመሳብ በቀጥታ በሰዎች አካል እና ህይወት ላይ ጉዳት ሊያደርሱ ይችላሉ፡፡ ይህ ግንባታ ትናንት በልደታ፣ በቂርቆስ እና በአራዳ ክፍለከተማ የተወሰኑ አካባቢዎች በተለይም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እና በሜክሲኮ አካባቢ የኃይል መቋረጥ እንዲከሰት ምክንያት ሆኖ ነበር፡፡ አሁን ላይ ግንባታው በሰው ህይወትም ሆነ አካል ላይ ጉዳት ባያደርስም መስመሩ ከሚያሰተላልፈው ከፍተኛ ቮልቴጅ አንፃር አደጋ መድረሱ የሚቀር እንዳልሆነ እናምናለን፡፡ በቀጣይም ከዚህ መስመር ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች በተደጋጋሚ ኃይል እንዲቋረጥባቸው፣ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዳይችሉ የሚያደርግ እና ህብረተሰብን ለእግልት የሚዳርግ በመሆኑ ሊታረም የሚገባው ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ “በቡሃ ላይ ቆሮቆር” እንዲሉ አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል እየተሰራ ባለበት በዚህ ወቅት በቸልተኝነት የሚከናወኑ አደገኛ ግንባታዎች በበዓል ወቅት ህብረተሰቡን ኃይል በማሳጣት የበዓል ድባብን ሊረብሹ ስለሚችሉ የግንባታ ፍቃድ የሰጡ አካላት ውሳኔያቸውን በማጤን ግንባታውን ሊያስቆሙ ይገባል፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ በዚሁ መስመር ሥር የሚከናወኑት የድንጋይ ማውጣት ሥራዎች የአፈር መንሸራተት እያስከተሉ ስለሆነ እንቅስቃሴዎቹ ተገተው የእርምት እርምጃ ካልተወሰደ የኃይል መቋረጥ ሊያመጣ ስለሚችል የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጡት እንጠይቃለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ተቋሙ በደሴ ከተማ የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀመረ ‎……...///…….... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደሴ ከተማ የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀመረ። በግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ ዓሊ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከተማዋን ዕድገትና የህብረተሰቡን ኑሮ ለማሻሻል  እያከናወነ ላለው በጎ ተግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ128 ዓመታት በላይ የተለያዩ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ የህዝብ ተቋም ነው። ተቋሙ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ከመላው ህዝብ ጋር በመሆን ከተስፋ ወደሚጨበጥ ብርሃን የቀየረ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያውያን በላባቸው፣ በደማቸውና ባላቸው አቅም ሁሉ ላደረጉት አበርክቶ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ተቋሙ ከሚያከናውናቸው በርካታ የኃይል መሠረተ ልማቶች ጎን ለጎን በልዩ ልዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝም ነው ያብራሩት። እንደ ኢንጂነር አንዱዓለም ገለፃ ከደሴ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር የተጀመረው የአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ ተቋሙ በመላ ሀገሪቱ የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የሚያከናውነው አካል ነው። የተቋሙ ባለሙያዎች መሟላት የሚገባቸውን የዲዛይን እና መሰል ጉዳዮች ለሥራ አመራሩ እንዳቀረቡ የቤቱን ግንባታ በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለማስረከብ እንደሚሰራ ቃል ገብተዋል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ተቋሙ በአማራ ክልል ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታዎችን እያከናወነ ይገኛል። ተቋሙ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ አካባቢዎች የህብረተሰቡን ፍላጎት ያማከሉ ውጤታማ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱንም አስታውሰዋል። የደሴ ከተማን የኃይል አቅርቦት ለማሻሻል የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እየተገነባ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሙላት ከዚሁ ጎን ለጎን በከተማዋ ለሚኖሩ አረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ኑሮ መሻሻል የቤት ግንባታ መጀመሩ ትልቅ ዕድል ነው ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የተቋሙ የሥራ አመራሮች እና የደሴ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባ ኮማንደር ሰዒድ አሊ በደሴ ከተማ ‎የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አከናውነዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ የተከናወነው በከተማዋ በሚገኘው የቅዳሜ ገበያ አጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በደሴ ባለ 230 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ቅጥር  ግቢ ውስጥ ነው። የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ ፅዱና አረንጓዴ አካባቢን ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት አንድ አካል በመሆኑ በዕለቱ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ዛፎች ተተክለዋል፡፡ በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የከተማው የግብርና ቢሮ፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች፣ በተቋሙ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን እና የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

ጳጉሜ 1፣ የጽናት ቀን ይህ ቀን የሀገራችን ሁሉን አቀፍ ስኬት ለማረጋገጥ በማያቋርጥ ጽናትና ብርታት ለተፋለሙ ጀግኖች ክብር የምንሰጥበት ቀን ነው። በዚህም በቅርቡ በሚመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳ
+1
ጳጉሜ 1፣ የጽናት ቀን ይህ ቀን የሀገራችን ሁሉን አቀፍ ስኬት ለማረጋገጥ በማያቋርጥ ጽናትና ብርታት ለተፋለሙ ጀግኖች ክብር የምንሰጥበት ቀን ነው። በዚህም በቅርቡ በሚመረቀው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብን ጨምሮ ተቋሙ በሚያከናውናቸው ትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ በጽናት ለተሳተፉ የተቋማችን ሠራተኞች እና መሐንዲሶች ክብር እንሰጣለን። የእነርሱ ጽናት እና የማይናወጥ ቁርጠኝነት ሁሉንም ፈተናዎች ተቋቁሞ ታላቅ ህልምን ወደ ተጨባጭ እውነታ ቀይሯል። እነሱ የጽናት ሕያው ምሳሌዎች ናቸው 💧💡 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ማብሰሪያ ነው ….///….. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ማብሰሪያ ነው አሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ሞገስ መኮንን የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅንና ለምርቃት ዝግጁ መሆንን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት ኃይል ከማመንጨት ባሻገር ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው የህዳሴ ግድብ ብዙ ጫናዎችን ተቋቁሞ በቆራጥ የአመራር ውሳኔ ተጠናቋል፡፡ የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ 54 በመቶ ላይ የሚገኘውን የኃይል ተደራሽነት ሽፋን ለማሳደግና የጎረቤት ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር የጎላ ሚና እንዳለውም አብራርተዋል፡፡ ለረጅም ዘመናት በውጫዊ ጫናዎች እና በነበረብን ድህነትና ኋላ ቀርነት ምክንያት ዐባይን መሰል ድንበር ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብታችንን ተጠቅመን የኃይል ፍላጎታችንን ለማሟላት ሳንችል ቆይተናል ብለዋል፡፡ ይህን ችግር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በመቅረፍ በተፈጥሮ ሀብቷ ተጠቅማ ከድህነት ተላቃ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በራስ አቅም፣ ዕውቀትና ገንዘብ ገንብታ ማጠናቀቋን አንስተዋል፡፡ ግድቡ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር በዓሳ ምርት፣ በቱሪዝም፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በኢንዱስትሪ ልማት እና ቀጣናዊ ትስስርንና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ በኩል ጉልህ ሚና እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች በማድረግ የኢትዮጵያን የመልማት አቅሟን መገደብ እንደማይቻል ዐቢይ ማሳያ መሆኑን ያነሱት አቶ ሞገስ የግድብ ግንባታው መጠናቀቅ ኢትዮጵያ ስታራምድ የቆየችውን የጋራ ተጠቃሚነት መርህ በተግባር በማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ተሰሚነቷን እና የመደራደር አቅሟን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድግ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የላብና የደም ጠብታ ያረፈበት የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ማብሰሪያ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ግድቡ ኢትዮጵያ በጽናት ማደግ እንደምትችል ያሳየ ነው ......///........ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን ያሰቡትን እና ያቀዱትን ከግብ ማድረስ እንደሚችሉ ያሳየ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ተናግረዋል። አቶ ሞገስ እንደገለፁት የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዐባይ ግድብ ላይ ለመጠቀም የነበራት የዘመናት ህልም እውን የሆነበት እና የአይቻልም መንፈስ የተሰበረበት ታሪካዊ ድል ነው። ይህ ግድብ ኢትዮጵያ የራሷን ሀብት በአግባቡ የመጠቀም መብቷን እውን ያደረገችበት የሉዓላዊነት መገለጫ መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት። ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ የሚገጥሙ ጫናዎችን ተቋቁማ ለስኬት እንደምትበቃ ያረጋገጠ ነውም ብለዋል። መላው ኢትዮጵያዊያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በጉልበት፣ በዲፕሎማሲ እና በመስዋዕትነት ያፀኑት ታሪካዊ ግድብ ነው መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ከጎረቤት ሀገራት ጋር በፍትሐዊነት መጠቀምን መርህ  አድርጋ እየሰራች መሆኑን የገለፁት አቶ ሞገስ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትም ይህን በመረዳት ተባባሪ ሊሆኑ እንደሚገባ ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

‎ግድቡ በራስ አቅም የመልማት አቅማችን ዐቢይ ማሳያ ነው‎ .....///..... ‎ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በራስ አቅም የመልማት አቅማችን ዐቢይ ማሳያ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። ‎ ‎ተቋሙ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅንና ለምርቃት መዘጋጀትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ‎ ‎መግለጫውን የሰጡት የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምርቃት ዝግጁ ሆኗል። ‎ ‎ግድቡ ከፋይናንስ ምንጩ፣ በሚይዘው የውሃ መጠን፣ በሚሰጠው ትርጉም ከሌሎች የኃይል ማመንጫዎች ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል። ‎ እስካሁን ያለው ‎የግድቡ ግንባታ ወጪ ከ233 ቢሊዮን ብር በላይ መሆኑንና ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት መሸፈኑን የጠቆሙት አቶ ሞገስ ከዚህ ውስጥ 91 በመቶው ከንግድ ባንክ እንዲሁም ቀሪው 23 ቢሊዮን ብሩ ወይም 9 በመቶው በሕብረተሰብ ተሳትፎ የተገኘ መሆኑን ተናግረዋል። ከፋይናንስ ተሳትፎ በተጨማሪ ሕብረተሰቡ በዕውቀት፣ በዲፕሎማሲ፣ በጉልበት እና በሀሳብ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደነበረው አብራርተዋል። ይህም ግድቡ በጫናዎች ሳንበገር በፍትሐዊነት በራሳችን አቅም የመልማትና ብሔራዊ ጥቅማችንን የማስጠበቅ ጽኑ ፍላጎታችንን ለዓለም ያሳየ ነው ብለዋል። አሁን ላይ የግድቡ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለምርቃ ዝግጁ መሆኑን ያወሱት አቶ ሞገስ በህዳሴ ደዴሳ ሆለታ እና በበለስ መስመር በኩል ኃይሉ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እየገባ መሆኑን አብራርተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

‎ተቋሙ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅንና ለምርቃት መዘጋጀትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። ‎ ‎መግለጫውን የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በመስጠት ላይ ናቸው። ‎ ‎ጋዜጣዊ መግለጫው በግድቡ ታሪካዊና ብሔራዊ ጠቀሜታ፣ የግድቡ የቴክኒክ እና የኦፕሬሽን ስኬት፣ ለሀገር ኢኮኖሚና ልማት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ እንዲሁም ተግዳሮቶች እና የወደፊት ዕቅዶች ዙሪያ ትኩረት ያደርጋል። ‎ ‎እኛም በጋዜጣዊ መግለጫው የሚነሱ ኃሳቦችን እየተከታተልን በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የዘንድሮው የመውሊድ በዓል ስናከብር የዘመናት ቁጭ የወለደው እና የአይቻልም
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የዘንድሮው የመውሊድ በዓል ስናከብር የዘመናት ቁጭ የወለደው እና የአይቻልምን መንፈስ በይቻላል የቀየረውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠናቀን በምናከብረው የምረቃ ዋዜማ  ላይ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ  ማድረግ መቻላችን እኛ ኢትዮጵያውያን የምናስበውን ለማሳካት ምንም ዓይነት ፈተና የድል አድራጊ አርበኛ ልጆች መሆናችን ለዓለም ህዝብ ያስመሰከርንበት ነው። በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ በድጋሜ እንኳን ለመውሊድ በዓልና ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማጠናቀቂያ የድል ብስራት ቀን አደረሳችሁ! ኢድ-ሙባረክ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ነሐሴ 29 ቀን 2017 ዓ.ም