en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 692 subscribers, ranking 8 036 in the Technologies & Applications category and 2 171 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 692 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 143 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 369 views. Within the first day, a publication typically gains 2 511 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 692
Subscribers
-124 hours
+47 days
+14330 days
Posts Archive
photo content
+5

ዓለም አቀፍ የሠራተኞች (የላብ አደሮች) ቀን ! 📌ሜይ ደይ ወይም ሌበር ደይ በሚሉ ስያሜዎች የሚታወቀው ዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን ሚያዚያ 23 ወይም እ.ኤአ. ግንቦት 1 ይከበራል። 📌 በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ የኢንደስትሪ መስፋፋትን ተከትሎ በርካታ የዓለማችን ሀገራት ሠራተኞች እስከ 16 ሰዓታት ድረስ ለመስራት ይገደዱ እንደነበር በታሪክ ድርሳናት ላይ ሰፍሯል፡፡ ይህም በርካቶችን ለከፍተኛ የጤና ጉዳት፣ ለዘላቂ የጤና ቀውስ እና ለሞት ዳርጓል። በዚህ የተነሳ በ1886 የተካሄደው የአሜሪካ የሠራተኞች ማህበራት ንቅናቄ ለላብ አደሮች ቀን መጀመር ምክንያት ሆኗል፡፡ 📌 የላብ አደሮች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ሚያዚያ 23 ወይም እ.ኤአ. ግንቦት 1 ቀን እንዲከበር የተወሰነው እ.ኤ.አ. ግንቦት 4 ቀን 1886 በቺካጎ ሄይማርኬት በነበረው ህዝባዊ ሰልፍ ላይ በፈነዳ ቦንብ የሞቱና የታሰሩ ሰዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። 📌 በውሳኔው መሰረት ዝቅተኛ የክፍያ ወለል እንዲወሰን፣ በቀን 16 ሰአታት መስራትና ሌሎችንም የሠራተኞች የመብት ጥያቄዎች ባነገቡ ማህበራትና ንቅናቄዎች የሥራ ሠዓት በቀን ወደ 8 ሠዓት ዝቅ እንዲል ተደርጓል። ይህም ዛሬ ላለው የሥራ ሰዓት መነሻ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ 📌 በዓለምአቀፍ ደረጃ 3 ነጥብ 62 ቢሊየን ላብ አደሮች እንደሚገኙ ይገመታል። 📌 ዓለምአቀፉ የሠራተኞች (የላብ አደሮች) ቀን “በአምራች ኢንዱስትሪዎች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ የሥራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ” በሚል መሪ ቃል በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ136ኛ ፤ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ ይከበራል፡፡ እንኳን ለዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን አደረሳችሁ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ተጀምረዋል ……..///…… የይርጋለም 2 ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ መጫን ከሚችለው 450 ሜጋ ዋት ኃይል ውስጥ እስከ 410 ሜጋ ዋት የሚሆነውን ለደንበኞችና ለተለያዩ ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ እያቀረበ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ተስፋዬ ኢርባ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው የሚቀርቡለትን የኃይል ጥያቄዎች ለመመለስ የአቅም ማሳደግ ሥራ ማከናወን ያስፈልገዋል፡፡ ጣቢያው በአራት የባለ 400 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመሮች ከወላይታ ሶዶ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ እና ከገናሌ ዳዋ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ባላቸው 13 ወጭ መስመሮች ለጩኮና አለታ ወንዶ ከተሞች፣ ለይርጋለም ኢንዱስትሪ ፓርክ፣ ለዳታ ማይኒንግ  እንዲሁም ለሐዋሳ 2፣ ዲላና ይርጋለም 1 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል፡፡ በጣቢያው ላይ ያሉት የባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመሮች እየሞሉ በመምጣታቸው በ2016 ዓ.ም 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ ቢቀመጥም ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ማስተናገድ እንዳልተቻለ ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ የፕሮግራም 3 ተወካይ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደተናገሩት ይርጋለም 2 ማከፋፈያ ጣቢያን ጨምሮ በወላይታ ሶዶ 2 እና ሱሉልታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማሳደግ ሥራ ለማከናወን የሚያስችሉ ሥራዎች ተጀምረዋል፡፡ ለአቅም ማሳደግ ሥራው የሚያስፈልጉ የትራንስፎርመሮች ግዢ፣ የዲዛይን፣ የሙከራ እና ፍተሻ ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቶ በአሁኑ ወቅት የተወዳዳሪዎችን የጨረታ ሰነድ የመገምገም ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡ በ2011 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የይርጋለም 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በባለ 400/230 ኪሎ ቮልት 500 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እንዲሁም በባለ 230/132/15 ኪሎ ቮልት 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች አሉት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ጣቢያው የኃይል አቅርቦትን  በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጣ ነው ………///……. በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደስራ ያስገባቸው አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የኃይል አቅርቦትን በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጡ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደገለፁት ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ እና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ በርካታ አምራች ድርጅቶች የተሟላ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ የጥገና ባለሙያ ተዳቻ ገናሌ በበኩላቸው ጣቢያው የተገጠመለት ጂ አይ ኤስ  መቆጣጠሪያ እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጣቢያው ኃይል ሳይቆራረጥ ደንበኞች ጋር ለማድረስ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ተናግረዋል። የኃይል መቋረጥ በሚከሰትበት ወቅት በቀላሉ ችግር የደረሰበትን መስመር እና የችግሩን ዓይነት እንዲሁም የችግሩን መጠን በመለየት የተሳካ፣ ፈጣንና ደህንነቱ  የጠበቀ መፍትሔ ለመስጠት እንደረዳቸው ገልፀዋል። የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ500 ኪሎ ቮልት በደዴሳ በኩል በመቀበል  ወደ 400 ኪሎ ቮልት ፤ለውጦ ለአቃቂ፣ ሰበታ እና ሱሉልታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች፣ ለደይሊ ውሃ እና ሀበሻ ሲሚንቶ ኃይል እያቀረበ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

በሪጅኑ በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት 90 በመቶ ቀንሷል ……..///………. የምስራቅ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ በጅግጅጋ ከተማ ሲያካሂድ የቆየውን የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ አጠናቀቀ። የሪጅኑን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ያቀረቡት በሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቁ ሙሉ እንደገለፁት ሪጅኑ አምስት የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸውን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እያስተዳደረ ይገኛል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ1 ሺህ 643 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች እና 719  ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የቁጥጥር እና ጥገና ሥራዎች መከናወናቸውን እንዲሁም በጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ የ33 እና 15 ኪሎ ቮልት የጂ.አይ.ኤስ ስዊችጊር ቅየራ ሥራ መከናወኑንም በሪፖርቱ አንስተዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሪጅኑ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል ከሶማሌ፣ ኦሮሚያ እና ሐረሪ ክልሎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጋቸውን የገለፁት አቶ ወርቁ በዚህም ምክንያት አንድም የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ካለመውደቁም ባሻገር በሪጅኑ ያለው የስርቆት መጠን 90 በመቶ መቀነሱን ጨምረው ጠቅሰዋል። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አብዱላሂ አብሽር በግምገማው ማጠናቀቂያ ላይ እንደተናገሩት ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠና አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። በአራተኛው ሩብ ዓመት የሪጅኑ ዕቅዶች ለማሳካት ሁሉም የሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ጣቢያው የኃይል አቅርቦትን በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጣ ነው ………///……. በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደስራ ያስገባቸው አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የኃይል አቅርቦትን በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጡ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደገለፁት ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ እና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ በርካታ አምራች ድርጅቶች የተሟላ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ የጥገና ባለሙያ ተዳቻ ገናሌ በበኩላቸው ጣቢያው የተገጠመለት ጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጣቢያው ኃይል ሳይቆራረጥ ደንበኞች ጋር ለማድረስ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ተናግረዋል። የኃይል መቋረጥ በሚከሰትበት ወቅት በቀላሉ ችግር የደረሰበትን መስመር እና የችግሩን ዓይነት እንዲሁም የችግሩን መጠን በመለየት የተሳካ፣ ፈጣንና ደህንነቱ የጠበቀ መፍትሔ ለመስጠት እንደረዳቸው ገልፀዋል። የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ500 ኪሎ ቮልት በደዴሳ በኩል በመቀበል ወደ 400 ኪሎ ቮልት ፤ለውጦ ለአቃቂ፣ ሰበታ እና ሱሉልታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች፣ ለደይሊ ውሃ እና ሀበሻ ሲሚንቶ ኃይል እያቀረበ ይገኛል። የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በለገጣፎ ማከፋፈያ የተከሰተው ችግር ሙሉ በሙሉ ተስተካክሏል ………///…….. በለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚገኝ ትራንስፎርመር ገብቶ የሚወጣ አንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ የተነሳ በምስራ
በለገጣፎ ማከፋፈያ የተከሰተው ችግር  ሙሉ በሙሉ ተስተካክሏል ………///…….. በለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚገኝ ትራንስፎርመር ገብቶ የሚወጣ አንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ የተነሳ በምስራቅ አዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ከትራንስፎርመሩ ከሚወጡት ሦስት ፌዞች መካከል በአንደኛው ፌዝ ላይ የገጠመውን ችግር ምሽት 5:00 ሰዓት አካባቢ መልሶ በማገናኘት በመቻሉ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች በሙሉ ኃይል እንዲያገኙ ተደርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም

በለገጣፎ ማከፋፈያ በገጠመ ችግር  የምስራቅ አዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል ………///…….. በለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚገኝ ትራንስፎርመር ገብቶ የሚወጣ አንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ የተነሳ በምስራቅ አዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል። በአንደኛው ፌዝ ላይ የገጠመውን ችግር በለገዳዲ፣ ለገጣፎ እና በየካ አባዶ እና አካባቢው ኃይል እንዲቋረጥ ምክንያት ሆኗል። የገጠመውን ችግር በፍጥነት ለማስተካከል ርብርብ እየተደረገ ሲሆን አንዳንድ አካባቢዎችን መልሶ ማገናኘት ተችሏል። የገጠመን ድንገተኛ ችግር ለማስተካከል የተወሰኑ ሰዓታት የሚፈልግ በመሆኑ ደንበኞች በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም

ስዊች ጊሮች በራስ አቅም መቀየራቸው የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን አስችላል ………///…….. ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ የማከፋፈያ ጣቢያ መቆጣጠሪያዎች ወይም ስዊች ጊሮች በተቋሙ የውስጥ አቅም መቀየራቸው በጣቢያዎቹ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚያስችላቸው በቅየራ ሥራው ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ፡፡ በደቡብ አንድ ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ያለው አማረ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያ መቆጣጠሪያዎችን የማዘመኑ ሥራ በቴክኖሎጂው ዙሪያ ስልጠና የወሰዱ የሪጅን ማስተባበሪያ እና  የሪጅን የጥገና ባለሙያዎችን በማቀናጀት ሲከናወን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ በፊት ከተከናወኑ የማዘመን ሥራዎች የተገኙ የእውቀትና የቴክኖሎጅ ሽግግሮችን በመጠቀም በአሁኑ ወቅት የመቆጣጠሪያ ቅየራ ሥራው በሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች እየተከናወነ ስለመሆኑ አስረድተዋል፡፡ የማዘመን ሥራው በተቋሙ የራስ አቅም መከናወኑ ሠራተኞቹ ቴክኖሎጂውን ተላምደው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ እንዲያከናወኑ ለማድረግ እንደሚያግዝም አመልክተዋል፡፡ የሻሸመኔ ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ምህረቱ ግዛው እና የይርጋለም ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈይሰል ዋቤ በበኩላቸው ከጣቢያዎቹ የብሬከር ቅየራ ሥራ ከኦፕሬሽን ሥራው ጋር በተያያዘ የሚከናወኑ ተግባራትን በአግባቡ ለመፈፀም የሚያስችል እውቀትና ክህሎት እየተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ እቴነሽ አሎንጄ በበኩላቸው በብሬከር ቅየራ ሥራው መሳተፋቸው የኦፕሬሽን ሥራዎችን ለማቀላጠፍ እና ለሚያጋጥሙ ቴክኒካል ችግሮች በቀላሉ መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችል ክህሎትና ግንዛቤ መቅሰማቸውን አስረድተዋል፡፡ በደቡብ አንድ እና ሁለት ሪጅኖች የጥገና ባለሙያ የሆኑት አቶ ዘውዴ ጥላሁን እና አቶ አስቻለው ጴጥሮስ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት በሪጅኖች አቅም እየተከናወነ ላለው ሥራ ከዚህ በፊት ከዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች ጋር በመተባበር ከተከናወነው ሥራ የተገኘው የእርስ በእርስ መማማር እና ልምድ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አበርክቷል፡፡ በራስ አቅም እየተከናወነ ያለው የመቆጣጠሪያዎች ቅየራ ሥራ በቀጣይ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በራስ ባለሙያዎች መስራት እንደሚቻል ማሳያ መሆኑንም ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎቹ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ዘርፉ በስሩ የሚገኙ መምሪያዎች በቅንጅት እንዲሰሩ አሳሰበ ….....///…....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በስር የሚገኙ ሁሉም የሥራ ክፍሎች ሥራዎችን በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዱጉማ ነዳ አሳስበዋል፡፡ በዘርፉ ሥር የሚገኙት የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን፤ የህግ አገልግሎት፤ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ እንዲሁም የሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያዎች ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያከናወኗቸውን ሥራዎች ከሥራ ክፍሎቹ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በዛሬው ዕለት ገምግመዋል፡፡ በመድረኩ ላይ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በየሥራ ክፍሎቹ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የነበሩ ጠንካራ ጎኖች፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች በዝርዝር ቀርበዋል፡፡  በሥራ ክፍሎቹ የቀረበው ሪፖርት እንዳመለከተዉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተከናወኑት ተግባራት የተቋሙን  ገጽታ በመገንባት፣ ተጠያቂነት፤ ግልጽነት እና ፍትሀዊነት በማስፈን ረገድ የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል፡፡ ሥራ አስፈፃሚው በሰጡት የማጠቃለያ አቅጣጫ እንዳመለከቱት ተቋሙ የጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል፣  የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅ እና ገጽታ ለመገንባት በሚያስችል መልኩ ለመቃኘት እንደዚህ ዓይነት የግምገማ መድረኮች ጥቅማቸው የጎላ ነው፡፡ ተቋሙ እያካሄደ ያለዉ ለውጥ ውጤታማ እንዲሆን ከዘርፉ ብዙ እንደሚጠበቅ በመገንዘብ በቀጣይም ለውጡን ውጤታማ ለማድረግ በተቀመጡ ደንቦችና አሰራሮች መሰረት ሥራዎችን ማከናወን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ እንደ አቶ ዱጉማ ገለፃ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የነበሩ መልካም ጎኖችን በማጠናከርና ደካማ ጎኖችን በማሻሻል መምሪያዎች በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል፡፡  ከአሰራር መመሪያዎች ጋር በተያያዘ በሥራ ክፍሎች የተነሱ ሃሳቦችን በግብዓትነት በመውሰድ መመሪያዎችን በማዘጋጀትና በማስፀደቅ ወደ ሥራ ለማስገባት የሥራ ክፍሎች ጋር በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡  ዘርፉ የጀመረውን የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል እና የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የሥራ ክፍሎች የሚበረታቱበት የአሰራር ሥርዓት እንደሚዘረጋ ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ዘርፉ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን እየገመገመ ነው ......///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸሙን መገምገም ጀምሯል። የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ድጉማ ነዳ እንደገለጹት ግምገማው በዘርፉ የተከናወኑ  ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና ያልተከናወኑ ሥራዎቸ ደግሞ በቀሪዎቹ ሦስት ወራት በማጠናቀቅ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ያለመ ነው። ግምገማው በዋነኛነት በዘጠኝ ወራት ውስጥ  የተቋሙን ጥቅምን ለማስጠበቅ፣ የተቋሙን ገጽታ ለመገንባት እና በተቋሙ  ውስጥ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ የተከናወኑ ሥራዎች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። ግምገማው የዘርፉን የቀጣይ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3