EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 572 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 356,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 572 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 24,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.83% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 035 次浏览,首日通常累积 2 465 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 572
订阅者
+1924 小时
+197 天
+2430 天
帖子存档
15 572
አራተኛው የህብረት ስምምነት ድርድር ተጀመረ
……///….…
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኞች ማህበርና በተቋሙ ሥራ አመራር መካከል የህብረት ስምምነቱን ለማሻሻል ድርድር መጀመሩን የህብረት ስምምነቱ ኮሚቴ ሰብሳቢ ገለፁ፡፡
ሰብሳቢው አቶ ደረጄ አጥናፌ እንደገለፁት የተቋሙንና የሠራተኛውን ጥቅምና መብት ባስጠበቀ መልኩ ሥራዎች እንዲሰሩ እና የኢንዱስትሪ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ በኩል የህብረት ስምምነቱ ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡
በሥራ ላይ ያለውን የህብረት ስምምነት ለማሻሻል አንቀፆችን ለመለየት ከተቋሙ ሥራ አመራር እና ከመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ተወካዮች የተውጣጣ ቡድን ድርድር መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
በድርድሩ በሥራ ላይ ባለው የህብረት ስምምነት ላይ የቅሬታ እና የአለመግባባት ምንጮች ሆነው አላሰራ ያሉ ጉዳዮች ካሉ በጥንቃቄ ታይተው እንደሚስተካከሉ ጠቁመዋል፡፡
ለቀጣይ ሶስት ዓመታት እንዲያገለግል እየተዘጋጀ ባለው የህብረት ስምምነት ላይ ሀሳብ አለኝ የሚል የሥራ ክፍል በሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት በኩል ሀሳቡን ሊያቀርብ እንዲሚችልም ሰብሳቢው ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀ መንበር እና የህብረት ስምምነት ድርድር ኮሚቴ አባል አቶ ዳንኤል ገ/ሚካኤል በበኩላቸው የህብረት ስምምነቱ የተቋሙን እና የሠራተኛውን መብት እና ጥቅም ያስጠበቀ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ግብዓቶችን በዘርፍ ተወካዮች እና በደብዳቤ መሰበሰቡን የገለጹት አቶ ዳንኤል በሦስተኛው ህብረት ስምምነት ያልተካቱቱ፣ በስራ ሂደትም እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮች በድርድሩ ሊታዩ ይችላሉ ብለዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
ባለፉት አስር ቀናት ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ለስርቆት ተዳርጓል
……..///……
ባለፉት አስር ቀናት ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦ.ፒ.ጂ ደብሊው ፋይበር መስመር ለስርቆት መዳረጋቸውን የአዋሽ - ወልዲያ - ሃራ ገበያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ተክለወይን ብርሃነአሰፋ እንደተናገሩት ባለፉት አስር ቀናት ከመተሃራ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ ድረስ በቡድን በተደራጀ ሁኔታ 78 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ዝርፊያ ተፈጽሟል።
ከባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ ሁለት ድረስ ደግሞ 2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ በዘራፊዎች መወሰዱንም ነው አቶ ተክለወይን የጠቆሙት።
በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በዱዱብ እና ዶሆ ቀበሌዎች ሁለት ጊዜ እንዲሁም በዱለሳ ወረዳ በቡሩቱሊ እና ኢስኪለሊ ቀበሌዎች አንድ ጊዜ በተፈፀመ የስርቆት ወንጀል ሳቢያ ከ758 ሺህ ዶላር በላይ እና በብር ከ6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱን ተናግረዋል።
የስርቆት ወንጀሉ የተፈፀመው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ወደ ሥራ እስኪገባ ድረስ በ33 እና 15 ኪሎ ቮልት በጊዜያዊነት ኃይል ይዞ እንዲቆይ ለማድረግ ከሥራ ተቋራጩ ጋር ምክክሮች እየተደረጉ ባሉበት ወቅት መሆኑ እንዳሳዘናቸውም ገልፀዋል።
እንደ ሳይት ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ዝርፊያ ተፈፅሞባቸው በአይሱዙ መኪና ተጭነው ሲጓዝ የነበረ የኮንዳክተር ሽቦ በአዳማ ከተማ ላይ እንዲሁም በዱለሳ ወረዳ መቁረጫ ሴጌቶ ይዘው የተገኙ ሁለት ተጠርጣሪዎች ተይዘው ክስ ለመመስረት ማስረጃ እየተደራጀ ይገኛል።
በኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ዙሪያ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከቀበሌ አመራሮች እንዲሁም ከፀጥታ ዘርፍ አካላት ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ ከ2 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ በዘራፊዎች መወሰዱን አብራርተዋል።
በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደተናገሩት በፕሮጀክቱ ላይ የተፈፀመው የስርቆት ወንጀል እጅግ አስደንጋጭ ነው።
በበጀት ዓመቱ በኦፕሬሽን ላይ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ይፈፀሙ የነበሩ የስርቆት ወንጀሎች መቀነሳቸውን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይሁን እንጂ በግንባታ ላይ ባሉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ስርቆቱ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በአዋሽ- ወልዲያ-ሃራ ገቢያ ላይ የተፈፀመው ዝርፊያ በሀገር ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና የሚያሳድር ከመሆኑም ባሻገር ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ላይ እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን ገልፀዋል።
በጉዳዩ ላይ የገቢረሱ ዞን አስተዳደርን ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
🌍 Exploring Ethiopia's Diverse Energy Capacity 🌍
Ethiopia is expanding its energy sources to meet growing demand, advancing solar, wind, geothermal, and hydropower for a sustainable future.
🔹 Key Highlights:
✅ Hydropower – A major contributor to Ethiopia’s electricity supply
✅ Solar & wind energy – Unlocking new renewable opportunities
✅ Geothermal potential – Tapping into Ethiopia’s natural resources
With a growing demand for electricity, Ethiopia is harnessing its rich renewable energy resources to strengthen its power sector.
Watch the full video now: 👉 https://youtu.be/QqPeoay756Y
Subscribe for more updates: https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
"Empowering Ethiopia with Diverse Energy Solutions!"
#Ethiopia #RenewableEnergy #SustainableDevelopment #Hydropower #SolarEnergy #WindPower #GeothermalEnergy #CleanEnergy #AfricaRising #EEP
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
ዩትዩብ | ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ቲክቶክ | ድረ - ገፅ
15 572
የተቋሙ ሠራተኞች በመንግስት ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ዙሪያ ተወያዩ
........///........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "ከቃል ወደ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ውይይቱ ሠራተኛው በጉባዔው በተቀመጡ ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ግንዛቤ በመጨበጥ ለተግባራዊነቱ እንዲሰራ ለማድረግ ነው።
ፓርቲው መንግስትን የሚመራ እንደመሆኑ መጠን ሠራተኞችም የፓርቲውን ውሳኔዎችና ያስቀመጣቸውን የትኩረት አቅጣጫዎች በመረዳት ሥራቸውን በዚሁ አግባብ ማከናወን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
በመድረኩ ላይ በፓርቲው ሁለተኛ ጉባዔ በተቀመጡ ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የተዘጋጀ ሰነድ በንባብ ቀርቧል።
ጠንካራ የፓርቲ ግንባታ፣ የብሔራዊነት ገዥ ትርክት ግንባታን ማጠናከር፣ ውጤታማ የሰላም ግንባታ ሥራ መስራት፣ የፍትህ ዘርፍ ውጤታማነትን ማሳደግ፣ የሀገር ግንባታን ማጠናከር እና የኢኮኖሚ ልማትን ማፋጠን የሚሉት በጉባዔው ከተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች መካከል መሆናቸው በሰነዱ ላይ ተመልክቷል።
በተጨማሪም ማህበራዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በውጤታማነት ማስቀጠል፣ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራዎች መስራት፣ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ውጤታማነትን ማረጋገጥ እና ጠንካራ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ሥራዎችን መስራት የሚሉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች በፓርቲው መቀመጣቸውም ተገልጿል።
በውይይቱ ላይ ከሠላም፣ ከተቋም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥ፣ ከልማትና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ከፍትህ ሥርዓቱ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች በተሳታፊዎች ቀርበዋል።
በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስ እና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በሰጡት ምላሽ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በመንግስት ፖሊሲና የፖለቲካ አቅጣጫዎች የሚመሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።
መንግስት የግጭት መንስዔዎችን ከምንጩ ለማድረቅና የሀገሪቱን ሀብት በፍትሐዊነት ለመጠቀም በትኩረት እየሰራ መሆኑን አቶ ደመረ ጠቅሰዋል።
የሰላም ጉዳይ ለመንግስት ብቻ የተተወ ባለመሆኑ ሁላችንም ሰላምን ለማጽናት የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ነው ያሉት።
በተቋሙ የትራንስሚሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ በበኩላቸው ገዢ ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት የጋራ መግባባት መፍጠር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
መንግስት ከሰላም እጦት ጋር የተያያዙ ችግሮችን አካታች በሆነ መልኩ ለመፍታት ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
የኢንጂነሪንግ እና ግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው ውይይት የተደረገበት ሰነድ የፓርቲ ብቻ ሳይሆን የመንግስት ሰነድ በመሆኑ፣ እንደዜጋ ማወቅና በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት መፈፀም ስለሚጠበቅብን ነው ብለዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
በውሃ ኃይል ማመንጫ ዘርፍ የሠለጠነ ባለሙያ ለማፍራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ
………///………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በውሃ ኃይል ማመንጫ ዘርፍ የሰለጠነ ባለሙያ ለማፍራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ቮይት ሀይድሮ ከተሰኘ የጀርመን ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና በቮይት ሀይድሮ ኩባንያ የሀይድሮ ሰርቪስ እና አውቶሜሽን ኃላፊ ሚስተር አሎይስ ታግሊበር ተፈራርመዋል፡፡
ኢንጂነር አሸብር በፊርማ ሥነስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ በአሁኑ ወቅት እያመነጨ ካለው የኤሌክትሪክ ኃይል 92 በመቶ የሚሆነው ከውሃ የሚገኝ በመሆኑ ስምምነቱ በዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት ያግዛል፡፡
ኩባንያው ያለውን የካበተ ልምድ ለተቋሙ ለማካፈል እያደረገ ያለውን ጥረት አመስግነው ስምምነቱ ከኩባንያው ጋር ያለውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረውም አስታውቀዋል፡፡
የአቅም ግንባታ ሥራው ውጤታማ እንዲሆን ኩባንያው አቅም ያላቸው ባለሙያዎች በመመድብ እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡
በቮይት ሀይድሮ ኩባንያ የሀይድሮ ሰርቪስ እና አውቶሜሽን ኃላፊ ሚስተር አሎይስ ታግሊበር በበኩላቸው ኩባንያቸው ከተቋሙ ጋር በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ሲሰራ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
በውሃ ኃይል ማመንጫዎች ላይ ለተቋሙ ባለሙያዎች የአቅም ግንባት ለመስጠት የተደረሰው ስምምነት በአቅም ግንባታ ጉዳዮች ላይ ከተቋሙ ጋር ለመስራት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ኩባንያቸውው በውሃ ኃይል ማመንጫዎች ላይ ያለውን ልምድ እና እውቀት ለተቋሙ ለማከፈል ዝግጁ መሆኑን አንስተው ለዚህም ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን በመመደብ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡
በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዱ ይማም እንደተናገሩት ስምምነቱ በውኃ ኃይል ማመንጫዎች ላይ ከዲዛይን ጀምሮ ማመንጫዎች አገልግሎት መስጠት እስከሚያቆሙበት (decommissioning) ባለው የአሰራር ሂደት ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት ያለመ ነው፡፡
በስልጠናው ላይ ከጀነሬሽን ኦፕሬሽን ዘርፍ እና ከኢንጂነሪንግ ዘርፍ የጀነሬሽን ዲዛይን የሥራ ክፍል የተውጣጡ 80 ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች እንደሚሳተፉበት ጠቁመዋል፡፡
የአቅም ግንባታ ለመስጠት የተካሄደው ስምምነት ለዘጠኝ ወራት የሚቆይ ሲሆን ለዚህም የአራት ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተደርጓል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
የተቋሙን የሥራ አፈፃፀም መለኪያ መስኮች ለማሻሻል ይሰራል
…....///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያከናውናቸውን የኃይል መሠረተ ልማቶች ግንባታና የኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲሁም አስተዳደራዊ ጉዳዮች የሥራ አፈፃፀም መለኪያዎችን ለማሻሻል እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ።
የተቋሙን የ6 ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ያቀረቡት የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ህይወት እሸቱ ተቋሙ በፕሮጀክት ግንባታ፣ በኦፕሬሽን፣ በፋይናንስ፣ በለውጥ ሥራዎች እንዲሁም በሰው ኃይል አስተዳደርና አቅም ግንባታ ሥራዎች የነበረውን አፈፃፀም አቅርበዋል።
ተቋሙ በኦፕሬሽን ዘርፍ ከ13 ሺህ ጌጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል በማምረት የዕቅዱን 115 ነጥብ 6 በመቶ ማሳካቱን የገለፁት አቶ ህይወት ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ40 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ብለዋል።
ባለፉት 6 ወራት ለሀገር ውስጥ ደንበኞች 11 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር፣ በዶላር ለሚከፍሉ ደንበኞች 70 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር እና ለጎረቤት ሀገራት 61 ሚሊዮን ዶላር ሽያጭ መከናወኑን ጠቅሰው 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በታሪፍ ለውጥ ምክንያት የተገኘ መሆኑን በሪፖርቱ አመልክተዋል።
እንደ አቶ ህይወት ገለፃ የ2016 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ንፁህ ሆኖ መገምገሙ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የስድስት ወራት የተቋም ፋይናንስ መዝጋት መቻሉ እና በውጭ ምንዛሬ የሚደረግ ግብይት መጨመሩ ባለፉት 6 ወራት ከተመዘገቡ መሻሻሎች መካከል ይጠቀሳሉ።
በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ተቋሙ 87 በመቶ የሚሆነው የፋይናንስ ገቢውን ወደፊት ሀብት ያመጣሉ ተብለው በሚታሰቡ ፕሮጀክቶች ላይ እያዋለ ይገኛል።
ባለፉት 6 ወራት የታየው የፋይናንስ ገቢ ዕድገት ከውጭ ምንዛሪ መሻሻል ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑንም ነው ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ያብራሩት።
በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ በበኩላቸው ተቋሙን በዲጂታላይዜሽን መስኮች የማዘመንና የአሰራር ሥርዓቶችን የመዘርጋት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
የተቋሙን ድረ-ገፅ ጨምሮ ሦስት የአሰራር ሥርዓቶችን የሚያዘምኑ ሶፍትዌሮች በራስ አቅም መዘጋጀታቸውንም ነው የገለፁት።
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመት ሆልዲንግስ የኢነርጂና ኮኔክቲቪቲ ዘርፍ ፖርቲፎሊዮ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድርስ ተገኘ እንደተናገሩት የኃይል ምርት ዕድገትና የአቅርቦት መሻሻሎች፣ ተቋሙን ለማዘመን እየተሠሩ ያሉ የለውጥ ሥራዎች፣ ወቅታዊ የሂሳብ መግለጫ ዝግጅት እንዲሁም ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም የማከናወን ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን የአፈፃፀም መለኪያ መስኮች ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ መለኪያዎች ጋር የማጣጣምና የማሻሻል ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው የጠቆሙት።
ተቋሙ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባው የጠቀሱት አቶ ቴዎድሮስ ከሱዳን ጋር ተያይዞ ያልተከፈሉ ውዝፍ የኃይል ሽያጭ ገቢዎችን ለመሰብሰብ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በግምገማው ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው በተቋሙ ተተኪ አመራሮችን ከማፍራት አንፃር መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል ብለዋል።
እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር በትብብር በመስራት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ተቋም ለመፍጠር በትኩረት ይሰራል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ማስተዳደር ከጀመረ ወዲህ ይህ የአፈፃፀም ግምገማ የመጀመሪያው ነው።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ለውጥ አምጥተዋል
…….///……….
የጅግጅጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ደምለው ተሾመ እንደገለፁት እየተከናወነ የሚገኘው የጂ.አይ.ኤስ ስዊችጊር ቅየራ ሥራ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማዘመን የሚያግዝ ነው።
በአሁኑ ወቅት በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩትን የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮች በሌላ ዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች የመቀየር ሥራ መሰራቱንም ነው የተናገሩት።
የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ ከዓመት በፊት ከ17 ሜጋ ዋት ያልበለጠ ኃይል የመጫን አቅም እንደነበረው የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮች ላይ በተከናወነው የአቅም ማሳደግ ሥራ ሳቢያ ኃይል የማቅረብ አቅሙ ከ24 ሜጋ ዋት በላይ ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በተደረገው የአቅም ማሳደግ ሥራ ቀደም ሲል በ15 ኪሎ ቮልት አራት የነበሩ ወጪ መስመሮችን ወደ አምስት እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት አራት የነበሩ ወጪ መስመሮችን ወደ ስድስት ማሳደግ ተችሏል።
በአየር ሲሰራ የቆየው መቆጣጠሪያ (vacume switchgear ) በዘመናዊ መቆጣጠሪያ በመቀየሩ የኃይል መቆራረጥንና በጥገና ሥራዎች ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በመቅረፍ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚረዳ ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት።
በ2016 በጀት ዓመት በጣቢያው 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ተጨማሪ ትራንስፎርመር ማስቀመጥ ቢቻልም በ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊሮች የአቅም ውስንነት የተነሳ የሚፈለገውን ኃይል ለተጠቃሚው ህብረተሰብ ማድረስ እንዳልተቻለ አስታውሰዋል።
በ1997 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው የጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ በ132 ኪሎ ቮልት ከሐረር ቁጥር ሦስት ኃይል ተቀብሎ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ለቀብሪበያህ፣ ቶጎ ውጫሌ፣ ጭናክሰን፣ ፋፈን እና በጅግጅጋ ዙሪያ ለሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች እንዲሁም በባለ 15 ኪሎ ቮልት አራት ለጅግጅጋ ከተማ ኃይል እያቀረበ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የጡረተኞች ማህበር ተመሰረተ
.....///.....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለረጅም ዓመታት አገልግለው በጡረታ የተሸኙ የቀድሞ ሠራተኞች የጋራ ማህበር ዛሬ በይፋ ተመሠረተ።
"የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የጡረተኞች ማህበር" በሚል ሥያሜ የተመሠረተው ማህበሩ በዋናነት በጡረታ የሚገኙ ጥቅሞችን ለማስከበር ታስቦ መቋሙ በምሥረታ ጉባዔው ላይ ተገልጿል።
የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ተሾመ መርዕድ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት ከወጣትነት ዕድሜ ጀምሮ በጡረታ በክብር እስከ ተሸኙበት ድረስ ዕውቀታቸውን፣ ልምዳቸውንና ጉልበታቸውን ሳይቆጥቡ በቅንነት በማገልገላቸው ለማህበረሰባዊ ለውጥ እና ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡
ይሁን እንጂ በሀዘንና ደስታ ጊዜ ከሚተጋገዙበት የመረዳጃ ዕድር በዘለለ ጡረተኞችን የሚወክል ማህበር ባለመኖሩ ከቀድሞ ተቋማቸው ማግኘት የሚገባቸውን ድጋፍ ለማግኘት እንዲሁም ለብዙ ዓመታት ያገኙትን ልምድ ለማካፈልና አብሮ ለመሥራት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ አልነበረም ብለዋል።
በመሆኑም ለረጅም ዓመት አገልግለው የተሠናበቱ ሠራተኞች በጡረታ የሚገኙ ጥቅሞችን ለማስከበር እና መብታቸውን ለመጠየቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የጡረተኞች ማህበር መመስረቱን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ሀገሪቱ የምትጠቀምባቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ "የእናንተ አሻራ ስላረፈበት ልትኮሩ ይገባል" ብለዋል።
በጡረታ የተሰናበቱ ሠራተኞች የሚያነሷቸውን ጥያቄ በህግ አግባብ ለመመለስ ተቋሙ ቁርጠኛ መሆኑን ያረጋገጡት ኃላፊው የቀድሞ አንጋፋ ሠራተኞችም የነበራቸውን እውቅትና ልምድ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የሁለቱ የኤሌክትሪክ ተቋማት መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ኃላፊዎች በበኩላቸው በጡረታ ለሚሰናበቱ ሠራተኞች ከአሁን በፊት ሲደረጉ ከነበሩ ድጋፎች በተጨማሪ የሚቀርቡ የመብት ጥያቄዎችን በጋራ እንድሚፍቱ ቃል ግብተዋል፡፡
ጉባዔው የማህበሩን ሊቀመንበር ጨምሮ አምስት አባላት ያሉት የሥራ አሥፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን በመምረጥ በይፋ ተመስርቷል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተብለው የሚጠሩት ሁለቱ ተቋማት ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ መብራትና ኃይል ባለስልጣን በኋላም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ተብለው በአንድ ሥም ይጠሩ እንደነበር ይታወሳል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
በተቋማችን የሚገኙ የኃይል ማመንጫዎች፣ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታና ኦፕሬሽን እንዲሁም ሌሎች ሥራዎችን የሚመለከቱ የተለያዩ የቪዲዮ ፕሮዳክሽኖችን በተቋማችን ስም በተከፈተ የዩቱዩብ ቻናል ላይ ሲጫኑ ቆይተዋል።
በመሆኑም ተቋማችን ሲያከናውናቸው የነበሩትንና እያከናወናቸው የሚገኙ ሥራዎችን በአግባቡ ለመረዳት እና ለብዙኃኑ ተደራሽ ለማድረግ ከዚህ በታች በተቀመጠው https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ በመግባት መረጃዎቹን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን መረጃውን ለብዙኃኑ ለማድረስ እንዲቻል ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲጋብዙ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ተቋማችን የሚያከናውናቸውን ስራዎች በምስልና ድምፅ ከሚዘጋጁት መረጃዎች በተጨማሪ የፅሁፍ መረጃዎችን ከፈለጉም በተለያዩ የዲጂታል አማራጮች መረጃዎች የሚያገኙ መሆኑን እንገልፃለን።
📡📲💡።
📖 በዲጂታል መጽሔቶቻችንን 👉 https://www.eep.com.et/?page_id=17536 ላይ ያንብቡ።
የኢ.ኤ.ኃ. ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም
15 572
ሪጅኑ አስተማማኝ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ
……..///…….
የምስራቅ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ባለፉት ስድስት ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎች ማከናወኑን አስታወቀ።
የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ወርቁ ሙሉ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በጅግጅጋ፣ ፊቅ፣ ጎዴ፣ ደገሃቡር እና ቀብሪደሃር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአስቸኳይ ጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች ተሰርተዋል።
ሪጅኑ የኃይል አቅርቦቱን ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ በጅግጅጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ማከናወኑን ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለጅግጅጋ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጠቀሱት ተወካይ ዳይሬክተሩ በጣቢያው ከተሰራው የ15 እና 33 ኪሎ ቮልት ስዊችጊር የማዘመን ሥራ ባሻገር የትራንስፎርመር አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ጥያቄዎች ለተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ መቅረቡን ተናግረዋል።
በቀጣይም በጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የዘመናዊ ስዊችጊር ቅየራ ሥራ ለማከናወን ታቅዶ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውንም ነው አቶ ወርቁ የገለፁት።
እንደ ተወካይ ዳይሬክተሩ ገለፃ ሪጅኑ በስሩ በሚያስተዳድራቸው አምስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የማስተላለፊያ መስመሮች በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ የጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች እያከናወነ ይገኛል።
በዚህም በግማሽ በጀት ዓመቱ በአምስቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 85 ቤዮችን የመጠገን እና የመፈተሽ ሥራ መስራቱን ተናግረዋል፡፡
ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ 1 ሺ 643 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች ላይ እንዲሁም 719 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የፍተሻና ጥገና ሥራዎች መከናወናቸውንም ነው አቶ ወርቁ ያብራሩት።
እንደ ተወካይ ዳይሬክተሩ ገለፃ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በተከናወኑ የጥገና እና የፍተሻ ሥራዎች በተደጋጋሚ ይከሰት የነበረውን የኃይል መቆራረጥ እንዲቀንስ አስችሏል።
በጎዴ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ደረጃውን የጠበቀ የአጥር ግንባታ ሥራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ የተናገሩት አቶ ወርቁ የአጥር ግንባታው በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ግመሎች ወደ ጣቢያው እንዳይገቡ ለመከላከል ያለመ መሆኑንም ነው የገለፁት።
ባለፉት ስድስት ወራት የጅግጅጋ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያ ቤት ዕድሳት መከናወኑን ጠቅሰው በቀጣይም የቀብሪድሃር እና ደጋሃቡር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ዕድሳት ለማከናወን የግዥ ሂደቱ መጠናቀቁን አብራርተዋል።
ሪጅኑ በጅግጅጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ በተቋሙ የራስ ኃይል የግንባታ መምሪያ በኩል ጊዜያዊ ተገጣጣሚ የቢሮ ግንባታ ለማከናወን አቅዶ በስፋት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
